tikvahethiopia | Неотсортированное

Telegram-канал tikvahethiopia - TIKVAH-ETHIOPIA

1531512

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ

Подписаться на канал

TIKVAH-ETHIOPIA

" ትምህርት ሚኒስቴር ' ቴክኒካል የሆኑ ነገሮችን ጨርሰን እንልካለን ' ብሎናል " - ማህበሩ

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የ2017 ዓ.ም አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና ውጤት #እንዳልደረሳቸው የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት እና ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት ማህበር ገለፀ፡፡

የመውጫ ፈተና ውጤት ለኮሌጆችም እንደተላከ ትናንት የተገለፀ ቢሆንም ፤ የተፈታኞች ውጤት እስካሁን ለግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አለመድረሱን የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት እና ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት ማህበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የተማሪዎች ውጤት ለግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አለመላኩን ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ ከተለያዩ የግል ትምህርት ተቋማቱ ማረጋገጣቸውን የማህበሩ ሥራ አስኪያጅ ተፈራ ገበየሁ ገልፀዋል፡፡

በጉዳዩ ዙሪያ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር መነጋገራቸውን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ፤ " ቴክኒካል የሆኑ ነገሮችን ጨርሰን እንልካለን " መባላቸውን ጠቁመዋል፡፡

በመሆኑም ውጤቱ ተጠናቅሮ ለግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ እስከሚላክ ድረስ የግል ተፈታኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ ሥራ አስኪያጁ ጠይቀዋል፡፡

#TikvahEthiopiaUniversity

Via
@tikvahuniversity

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ፋይዳን ከሕብረት ባንክ!

ሕብረት ባንክ ከኢትዮ ፖስት ጋር በመተባበር የፉይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ካርድ ምቹ እና ቀልጣፋ በሆነ መንገድ ታትሞ እንዲደርስዎ ለማድረግ በሁሉም የባንኩ ቅርንጫፎች ምዝገባ ጀምሯል፡፡ ከእርስዎ የሚጠበቀው የተላከልዎትን የፉይዳ ልዩ ቁጥርዎን በመያዝ በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ የሕብረት ባንክ ቅርንጫፍ ጎራ ብለው የተዘጋጀውን ፎርም መሙላት ብቻ ነው፡፡
በተጨማሪም የፋይዳ ቁጥር የሌላችሁ በዋና መስሪያ ቤት በሚገኘው ሕብር ታወር፣ ቃሊቲ ሳሎ እና አያት ቅርንጫፎቻችን በመመዝገብ ወዲያው የፋይዳ ልዩ ቁጥር ያግኙ ።

ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ExitExamResult

" የፈተናው ውጤት ተለቆ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ተልኳል " - የትምህርት ሚኒስቴር አመራር

🔴" የፈተና ውጤት ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ጋር መጥቷል " -  የኢትዮጵያ ተማሪዎች ኅብረት

የሀገር አቀፍ መውጫ ፈተና ውጤት ለዩኒቨርሲቲዎች መላኩን የትምህርት ሚኒስቴር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት አጭር ቃል ፥ " ፈተናው ተለቆ ለዩኒቨርሲቲዎች ተልኳል " ብለዋል።

" በነገራችን ላይ ለዩኒቨርሲቲዎች ነው የሚላከው ሊንኩም ይላክላቸዋል። ውጤት ሁሉም ዩኒቨርሲቲ ጋር ደርሷል " ሲሉ ገልጸዋል።

ምን ያክል ተማሪ አለፈ ? ለሚለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ " ውጤቱ አሁን ስለተለቀቀና ለተቋማት ስለተላከ አጠቃላይ ዳታውን የምናየው ነገ ነው " ብለዋል።

የኢትዮጵያ ተማሪዎች ኅብረት ቡኩሉ፣  " ውጤቱ ተለቋል። የሁሉም ዩኒቨርሲቲ መጥቷል " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

ውጤት መመልከቻ ሊንኩ ደርሷችኋል ? ስንል ላቀረብንለት ጥያቄ በሰጠን ምላሽ ደግሞ፣ " ዝም ብሎ ውጤቱ ነው የመጣው " የሚል አጭር ምላሽ ሰጥቷል።

ውጤቱ ለየዩኒቨርሲቲዎች ሬጅስትራር መላኩን የገለጸው ኅብረቱ ተፈታኞች ውጤታቸውን በየዩኒቨርሲቲያቸው / ካምፓሳቸው
#ከነገ ጀምሮ ማየት እንደሚችሉ ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የፈተናው ውጤት በኦንላይ የሚታይበት መንገድ ካላ ጠይቆ ያቀርባል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#NewsAlert

ህወሓት ለሦስት ወር ከፖለቲካ እንቅስቃሴ ታገደ።

ሦስት ወራት የዕግድ ጊዜ የዕርምት ዕርምጃ ሳይወስድ ቢቀር የፖርቲው ምዝገባ እንዲሠረዝ ተወስኗል።

የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ ( ህ.ወ.ሓ.ት) ከፖለቲካዊ እንቅስቃሴ መታገዱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳወቀ።

ፓርቲው በልዩ ሁኔታ ከተመዘገበ ጊዜ አንሥቶ ባሉት  6 ወራት ውስጥ የቦርዱ ታዛቢዎች በተገኙበት ጠቅላላ ጉባዔ ማድረግ ይጠበቅበት ነበር።

ቦርዱ ፥ ታኅሣሥ 17 ቀን 2017 ዓ.ም. በፃፈው ደብዳቤ ፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔ የማድረጊያ ጊዜ ገደቡ ሊጠናቀቅ ከሁለት ወር ያነሰ ጊዜ አንደቀረው በመግለጽ በሕግ የተጣለበትን ግዴታ አንዲፈጽም ማሳሰቡን አስታውሷል።

ይህንን የሕግ ግዴታ በወቅቱ ሳይፈጽም ቢቀር ቦርዱ ሕጉን መሠረት በማድረግ ተገቢ ነው የሚለውን ውሣኔ የሚሰጥ መሆኑን መግለጹንም አክሏል።

ይሁንና ፓርቲው የዐዋጁንና የመመሪያውን ደንጋጌዎችና የቦርዱን ውሣኔዎች በማክበር የጠቅላላ ጉባዔ ሳያካሄድ፣ መተዳደሪያ ደንቡን ሳያፀድቅና አመራሮቹን ሳይመርጥ በሕግ የተሰጠው የ6 ወር ጊዜ ተጠናቅቋል።

በዚህ መሠረት ቦርዱ የካቲት 4 ቀን 2017 ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ ጉዳዩን መርምሮ ፦

1ኛ. ፓርቲው ከፍ ዐዋጅና መመሪያ ላይ የተመለከቱ ድንጋጌዎችን ባለማክበር ጉልህ ጥሠት በመፈጸሙ ይህ ውሣኔ ከደረሰው ቀን ጀምሮ ለሦስት ወራት በምንም ዓይነት የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ አንዳይሣተፍ እንዲታገድ ወሥኗል።

2ኛ. ፓርቲው ለእግዱ ምክንያት የሆነውን ጥሠት በማረም፤ ዐዋጁን፣ ዐዋጁን ተከትሎ የወጣውን መመሪያ፣ የቦርዱን ውሣኔዎችና ትዕዛዞች በማክበር ፖርቲው ሊያደርግ የሚገባውን ጠቅላለ ጉባዔ ለማድረግ የሚያስችለውን የጉባዔ ቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ለመሥራት ለቦርዱ በጽሑፍ ሲያሳውቅና ቦርዱ ይህንኑ ሲያረጋግጥ በመመሪያው መሠረት ቦርዱ ዕግዱን የሚያነሣ መሆኑን ወሥኗል።

3ኛ. ፖርቲው በተሰጠው የሦስት ወራት የዕግድ ጊዜ የዕርምት ዕርምጃ ሳይወስድ ቢቀር የተለየ አካሄድ ሳይከተል የፖርቲው ምዝገባ እንዲሠረዝ ወሥኗል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

የ2017 ዓ/ም የመውጫ ፈተና ውጤት እካሁን ይፋ አልተደረገም።

ትምህርት ሚኒስቴር የፈተናውን ውጤት ይፋ ማድረጉን ሲያሳውቅ እና የውጤት መመልከቻው አገልግሎት ሲሰጥ ተከታትለን የምናሳውቃችሁ ይሆናል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#DStvEthiopia

ያልተጠበቁ ውጤቶች ያስተናገደው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች የውጤቱን ግምቶቻችሁን ከስር አጋሩን፦
👉እነዚህን ድንቅ ፍልሚያዎች ጨምሮ ሌሎች የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን በቀጥታ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ይመልከቱ።

🎊 ከጥር 5 እስከ መጋቢት 22 ባሉት ቀናት አሁን ካሉበት የዲኤስቲቪ ፓኬጅ የቀጣዩን ፓኬጅ፣ የአንድ ወር ሙሉ ክፍያ ሲከፍሉ፣ ዲኤስቲቪ ደግሞ ከዛም ወደ ሚበልጠው ፓኬጅ በነፃ ከፍ ያደርጎታል

ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!https://bit.ly/3RFtEvh

ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ : www.dstv.com/en-et

#PremierLeagueallonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ፋይዳ #NationalID

" ከፍርድ ቤት እና ከብሔራዊ ደኅንነት ጥያቄው ከዛ እስካልመጣ [የግል መረጃ] ለመንግስት የሥራ አስፈጻሚ አይሰጥም " - አቶ ዮዳሄ አርአያሥላሴ

ኢትዮጵያ የዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራምን በይፋ ካስተዋወቀችበት ጀምሮ እስከ አሁን 12 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች ተመዝግበዋል፤ እስካሁንም ይህንን አገልግሎት ከ50 በላይ ከሆኑ አገልግሎቶች ጋር የማስተሳሰር ሥራም ተሰርቷል።

ይህ ፕሮጀክት የኢትዮጵያ መንግስት ከሚበጅተው በጀት በተጨማሪ ለተግባራዊነቱ ኢትዮጵያ ከዓለም ባንክ 300 ሚሊዮን ዶላር ብድር እንዲሁም 50 ሚሊዮን የሚሆን ድጋፍ አግኝታለች።

የፋይዳ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮዳሄ አርአያሥላሴ ኢትዮጵያ የዲጂታል መታወቂያ ትግበራን ዘግይታ መጀመሯ ላይ ቢስማሙም በአንጻሩ ግን የተሻለ ቴክኖሎጂ እና ልዩ ልዩ እሳቤዎችን እንድታካትት ረድቷቷል ይላሉ።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በወሳኝ አገልግሎቶች ላይ በአስገዳጅነት ጭምር መቅረቡ የተመዝጋቢዎችን ቁጥር ከፍ እንዳደረገው ይታመናል። አሁን ላይ በቀን ከ60ሺ ሰዎች በላይ የመመዝገብ አቅም መፈጠሩን ከፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ያገኘነው መረጃም ያመለክታል።

አሁን ካሉት የመመዝገቢያ ሳጥኖች ተጨማሪ በቅርቡ 3000 የሚያህል እንደሚጨመር ዋና ዳይሬክተሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። ይህም የተመዝጋቢዎችን ቁጥር በዚህ ዓመት መጨረሻ ወደ 30 ሚሊዮን ለማሳደግ የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል።

በኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም የጣት አሻራ የሰጡ ዜጎች ብዛት 33 ሚሊዮን፤ እንዲሁም የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN Number) ያገኙ ዜጎች 5.6  ሚሊዮን በላይ እንደዮኑ መረጃዎች ያመለክታሉ።

በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የባዮሜትሪክ ዳታን መሰረት ያደረገ የዲጂታል መታወቂያ ተግባራዊ  ያደረጉ ሲሆን ለአብነትም ናይጄሪያ በዓለም ባንክ ድጋፍ ከ10 ዓመታት በላይ በፈጀው ጉዞዋ ከ107 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን መዝግባለች።

ሀገራት የባዮሜትሪክ መረጃዎችን ያካተተ ምዝገባ በሚያከናውኑበት ወቅት በመሰረታዊነት ሦስት ተግዳሮቶች ይገጥሟቸዋል። እነዚህም ከዜጎች ጋር ያለ የተግባቦት ክፍተት፤ የዲጂታል ክህሎት ማነስ እና የደኅንነት ጥያቄዎች ናቸው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከቤተሰቦቹ የተነሱ ጥያቄዎችን ሰብስቦ ምላሽ እንዲሰጥባቸው ለጽ/ቤቱ አቅርቧል።

በተለይም ከመሰረታዊ ዓላማ እና ከግል መረጃ ደኅንነት ጋር የተያያዙ፤ ከቤተሰቡ የተሰበሰቡ ጥያቄዎችን ለፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮዳሄ አርአያሥላሴ ምላሽ እንዲሰጥባቸው አድርጓል።

የፋይዳ ዋና ዓላማው ምንድን ነው?

"ፋይዳ" ከሌሎች መታወቂያዎች ጋር ለንጽጽር የሚቀርብ እንዳልሆነ ዋና ሥራ አስኪያጁ ያስረዳሉ። ይህም ፋይዳ የተናበበ የዜጎች መረጃ በብሔራዊ ደረጃ እንዲኖር የሚያስችል መሰረተ ልማት እንደሆነ ነው የሚገልጹት።

አቶ ዮዳሄ፥ "ፋይዳ እንደ Social Security ቁጥር ነው" በማለትም አሁን ላይ ከሌሎች መታወቂያዎች ጋር የሚደረጉ ንጽጽሮች ይህን ካለመረዳት እንደሆነ ይጠቅሳሉ።

ሌሎች መታወቂያዎችንስ ይተካል ?

ፋይዳ፤ የነዋሪነት መታወቂያ ላይ ያለው መረጃ ከፖስፖርት መረጃ ጋር እንዲሁም ከጤና፤ ከፋይናንስ መሰል አገልገሎቶች ጋር ትስስር እንዲፈጠር የሚያስችል እንጂ ሌሎቹን የመተካት ዓላማ እንደሌለው ገልጸዋል። "ሲስተሞቹ እየተናበቡ ሲሄዱ ነው ብዙ ጥቅም ማግኘት የሚቻለው" ሲሉ ዋና ሥራ አስኪያጁ አስረድተዋል።

ለምን የደም አይነት አልተካተተም ?

የደም አይነትም ሆነ የእናት ስም በፋይዳ የዲጂታል መታወቂያ የማይሰበሰቡት ለሚሰጠው መረጃ ማረጋገጫ ማቅረብ አስቸጋሪ በመሆኑና ለሲስተሙ የተመጠነ መረጃ መውሰድ (Data Minimization) እንደ ስትራቴጂ በመያዙ መሆኑን ዋና ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል።

የሚሰበሰበው መረጃ የት ይቀመጣል ?

የዜጎች የግል መረጃ ከተሰበሰበ በኋላ ደኅንነቱ በተጠበቀ በብሔራዊ መረጃ ቋት እንደሚቀመጥ የገለጹት አቶ ዮዳሄ፥ የተቋማቸው ዋና ተልዕኮም ይሄንን ብዙ ሀብት የወጣበት መረጃ በአስተማማኝ ሁኔታ መጠበቅ እንዲሁም ከተጠቃሚ አካላት ጋር ማስተሳሰር እንደሆነ አስረድተዋል።

የዜጎች የግል መረጃ ለሦስተኛ ወገን ተላልፎ ይሰጣል ?

በርካቶች በስጋት የሚጠቅሱት አንዱ ዋነኛ ጉዳይ መረጃቸው ለሦስተኛ ወገን ተላልፎ ስለመሰጠቱ ነው። ለዚህ ጥያቄ አቶ ዮዳሄ ሲመልሱ "ከፍርድ ቤት እና ከብሔራዊ ደኅንነት ጥያቄው ከዛ እስካልመጣ [የግል መረጃ] ለመንግስት የሥራ አስፈጻሚ አይሰጥም" ብለዋል።

ከዚህ በላይ በአግባቡ ዲዛይን ካልተደረገ የግል መረጃን አደጋ ላይ የሚጥለው ብለው ያነሱት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ከባለቤቱ ፈቃድ ውጪ እርስ በእርስ የሚያወሩ ከሆነ እንደሆነ አስረድተዋል።

ለዚህም በቅርቡ ላይ "Verify Fayda 2" የተሰኘ ሲስተም ማበልጸጋቸውን በመጥቀስ ለሁሉም የተለየ Token እንዲኖራቸውና የሚያስፈልጋቸውንና የተፈቀደላቸውን መረጃ ብቻ እንዲወስዱ የሚያስችልና ያለ መረጃ ባለቤቱ ፈቃድ ሁለት ተቋማት እርስ በእርስ መረጃ እንዳይቀያየሩ የሚያስችል እንደሆነ ጠቅሰዋል።

ፋይዳ ለምን አስገዳጅ ሆነ ?

አንዳንድ ተቋማት ፋይዳን ግዳጅ ሲያደርጉት አንዳንድ ተቋማት ደግሞ ሳይቀበሉ ሲቀሩ ይስተዋላል። ይህንን አስመልክቶ ጥያቄ የቀረበላቸው ዋና ሥራ አስኪያጁ "ፋይዳ ስላለኝ መኪና ልንዳ ማለት አትችልም፤ እንዲሁ ፖስፖርት ለማውጣት ሌሎች የሚያስፈልጉ ነገሮች አሉ" ሲሉ ፋይዳን አስገዳጅ የማድረግ እና ያለማድረግ ጉዳይ በአገልግሎት ሰጪ ተቋማቱ እንደሚወሰን ገልጸዋል።

ከሁሉም ነገር ጋር እንዲተሳሰር እንደማይጠበቅ የገለጹት አቶ ዮዳሄ ለዲጂታል ኢኮኖሚው ከሚጠቅሙ አገልግሎት ጋር በዋነኛነት እንደሚያያዝ አንስተዋል።

ለአብነትም በቅርቡ ሲም ካርድ ለማውጣት ፋይዳ በግዳጅነት እንደሚቀመጥ እንዲሁም በፖስፖርት እና በአዲስ አበባ ነዋሪነት መታወቂዎች ላይ የፋይዳ ቁጥር እንደሚካተት አንስተዋል።

ፋይዳ በቀጣዩ ምርጫ ላይ አገልግሎት ላይ ይውላል ?

አቶ ዮዳሄ ምርጫ ቦርድ ሲስተም ቢኖራቸውና ትስስር መፍጠር ከተቻለ ተቋማቸው ዝግጁ መሆኑን ገልጸው " ለዩኒክነስ ያስፈልገናል ካሉ ቢያስተሳስሩት ደስ ይለናል . . . እንኳን እንደ ምርጫ ቦርድ አይነት ትልቅ የዲሞክራሲ ተቋም ጋር ቀርቶ ከፊንቴኮች ጋርም ትስስር ፈጥረናል" ሲሉ ምላሻቸውን አስቀምጠዋል።

📱 አቶ ዮዳሄ አርአያሥላሴ ለቀረቡት ጥያቄዎች የተሰጡትን ምላሾች ይመልከቱ https://youtu.be/b_X_LnM4cTA?feature=shared

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ከታክስ በፊት 34.4 ቢሊዮን ብር አትርፊያለሁ " - ኢትዮ ቴሌኮም

ኢትዮ ቴሌኮም 3.24 ሚሊዮን አዳዲስ ደንበኞች በማፍራት አጠቃላይ የቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞቹን ብዛት 80.5 ሚሊዮን ማድረሱን አስታወቀ።

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ መንፈቅ ሪፖርት ያቀረቡት የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ምን አሉ ?

➡️ 3.24 ሚሊዮን አዳዲስ ደንበኞች አፍርተናል።

➡️ 9.3 ሚሊዮን የአዳዲስ ሲም ካርድ ሽያጭ የተከናወነ ሲሆን ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ8% ጭማሪ እንዲሁም ከእቅድ ጋር ሲነጻጸር የ113% አፈጻጸም አለው።

➡️ የሞባይል ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ቁጥር 7.5 % እድገት በማሳየት የተጠቃሚዎች ቁጥር 43.5 ሚሊዮን ደርሷል።

➡️ የሞባይል ኢንተርኔት ትራፊክ ማለትም (በሞባይል ኔትወርክ የተላከ እና የተቀበለው የዲጂታል መረጃ መጠን) በተመለከተ በበጀት አመቱ እስከ ህዳር ወር ድረስ 642.2 ቢሊዮን ሜጋ ባይት ትራፊክ ተመዝግቧል። ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ48.8 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።

➡️ የብሮድባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት 5% ጭማሪ በማሳየት የተጠቃሚዎቹ ቁጥር 784.1 ሺ ደርሷል።

➡️ በአጠቃላይ ከባለፈው የበጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የደንበኞች እድገቱ በ7.9 በመቶ አድጓል።

ኩባንያው ምን ያህል አተረፈ ?

➡️ በመጀመሪያው መንፈቅ ዓመት 61.9 ቢሊዮን ገቢ አግኝተናል። ይህም የዕቅዳችን 90.7 በመቶ ያሳካ ነው።

➡️ ከታክስ መሰል ወጪዎች በፊት ያለው ምጣኔ (EBITDA) 55.5 በመቶ ነው። ከታክስ በፊት 34.4 ቢሊዮን ትርፍ ተመዝግቧል።

➡️ ከአጠቃላይ ከገቢ ውስጥ 72.61 ሚሊዮን ዶላር የሚሆነውን በውጭ ምንዛሬ የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ከጦርነቱ በፊት ነጋዴዎች ተበድረውት የነበረው 32 ቢሊዮን ብር አሁን ከነወለዱ ወደ 80 ቢሊዮን ብር  አድጓል " - ከትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ም/ቤት

የትግራይ ክልል ነጋዴዎች ከጦርነቱ በፊት ተበድረውት የነበረው 32 ቢሊዮን ብር አሁን ከነወለዱ ወደ 80 ቢሊዮን ብር ማደጉን የትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አሳውቋል።

ም/ቤቱ ይህን ያሳወቀው ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ በሰጠው ቃል ነው።

የትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዘዳንት አቶ በሪሁን ሃፍቱ ምን አሉ ?

➡️ ነጋዴዎች ከጦርነቱ በፊት ከባንክ ወስደውት ነበረው የባንክ እዳ በ5 አመት ወስጥ ከ32 ቢሊዮን ብር አሁን ከነወለዱ ወደ 80 ቢሊዮን ብር ደርሷል።

➡️ ተከስቶ የነበረው ጦርነት ብዙ ሀብት አውድሟል የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን አጥፍቷል፣ ቀሪዎችንም ከንግድ እንቅስቃሴ ውጭ አድርጎ የገበያ ትስስራቸውን እንዲያጡ አድርጓል።

➡️ የወደሙ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የጠፉት የባንክ ብድር ይዘው ነው።

➡️ የባንክ እዳ ይዘው የወደሙ የንግድ ተቋማትን ወደ መደበኛ ሥርዓት ለመመለስ ከባድ ነው ፤ ምክንያቱም ባለሀብቱ ፈልጎ ባላመጣው ጦርነት ተዳክሟል።

➡️ በክልሉ ያሉ ባለሀብቶች ንብረታቸው መውደሙ እና ሀብታቸው መጥፋቱ ሳያንስ እዳቸውን ከነወለዱ እና ከነቅጣቱ እንዲከፍሉ እየተገደዱ ነው። ይህም አግባባብ አደለም። ምክኒያቱም ባለሃብቶች ጦርነቱን ፈልገውት አይደለም ያመጡት።

➡️ የወደሙ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ተቋማት ተመልስው ወደስራ የሚገቡበት ሁኔታ ሳይፈጠር ባለሃብቶች ባልሰሩበት የተበደሩትን እዳ ከነወለዱ እንዲከፍሉ መደረጉ ተገቢ አይደለም። መከፈል ግዴታም ከሆነም ደግሞ ቢያንስ እየሰሩ እንዲከፍሉ ልዩ ማበረታቻ ያሰፈልጋቸዋል።

➡️ የወደሙትን በአዲስ ለመተካት የተዳከሙትን ደግሞ ለማነቃቃት ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል። ያን ማድረግ የሚቻል ከሆነ ነጋዴው ነግዶ አትርፎ አዲስ ግብር ከፋይ ብቻ ሳይሆን ከዚህ በፊት የነበረበትን እዳም የመክፈል አቅም ይኖረዋል።

➡️ አሁን ያለብን ትልቁ ችግር ተጨማሪ ድጋፍ አለማግኘት ነው። ባንኮች ተጨማሪ ብድር ለመስጠትም እየተቸገሩ ነው።

➡️ ባለሃብቶች ከጦርነቱ በፊት የተበደሩት እዳ ወለዱም ከዛሬ ነገ እየጨመረ ነው ያለው ፤ አይደለም ሰርቶ ማትረፍ ይቅርና ስራ በቆመበት እና ንብረት በወደመበት ወቅትም ወለዱ እየታሰበ ነው ያ ወለድ ደግሞ የወለድ ወለድ ቅጣት እየታሰበበት ነው።

➡️ ያለው ችግር የተለየ የብደር ጥቅል ካልተዘየደለት አሁን ባለው አሰራር የሚፈታ አይደለም።

➡️ የወደመው ንብረት በቢሊዮን የሚገመት ነው በዚህ ላይ ደግሞ የኢኮኖሚው ማሻሽያ ሲጨመር ችግሩን የከፋ አድርጎታል።

➡️ ጦርነቱ ከቆመ ወዲህ ባለፉት ሁለት አመታት ለክልሉ ባለሃብቶች የቀረበው ብድር 2 ቢሊዮን ብር የማይሞላ ነው ይህም ከችግሩ ስፋት ጋር አብሮ የሚሄድ አይደለም።

➡️ በቅረቡ ከብሄራዊ ባንክ ጋር ውይይት ተደርጎ ነበር በዚህም ነጋዴዎች በሐራጅ ለመሸጥ ጊዜውን ለአንድ አመት እንዲራዝም ተደርጓል ግን ይህ በቂ አይደለም።

የመረጃው ባለቤት ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

" እያጠፋን በነበርንበት ወቅት የኤሊና እባብ ዝርያዎች ተቃጥለው አግኝተናል። ከ350 እስከ 400 ሄክታር ሳራማ ቦታ ተቃጥሏል ብለን እንገምታለን " - ፓርኩ

በሃላይደጌ አሰቦት እጩ ብሔራዊ ፓርክ ተከስቶ የቆየውና ለቀናት ከቁጥጥር ውጪ ለማድረግ አስቸግሮ የነበረው ቃጠሎ በቁጥጥር ስር መዋሉን ፓርኩና የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ባለስልጣን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።

ይህን ተከትሎም ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ በአደጋው የደረሰው የጉዳት መጠን ምን ያክል እንደሆነ የጠየቀ ሲሆን፣ እንስሳት መቃጠላቸውንና ከ350 እስከ 400 ሄክታር የሚገመት ሳራማ ቦታ መቃጠሉን ሰምቷል። 

የፓርኩ ኃላፊ አቶ አሕመድ እንድሪስ ምን አሉ ? 

" የካቲት 1/2017 ዓ/ም መንስኤው ባልታወቀ ምክንያት የእሳት ቃጠሎ ተነስቶ ነበር። ትላንት 10 ሰዓት በቁጥጥር ስር ተደርጓል። ዛሬም ከጠዋቱ 11 ሰዓት ጀምረን ጫካ ነበርን ሙሉ በመሉ መጥፋቱን አረጋግጠናል።

ተራማጅ የሆኑና መሮጥ የሚችሉ የዱር እንስሳት ብዙዎቹ አምልጠዋል። ግን መራመድ የማይችሉ፣ አዲስ የተወለዱ የዱር እንስሳት ጉዳት ሊያደርስ ችሏል።

እያጠፋን በነበርንበት ወቅት የኤሊና እባብ ዝርያዎች ተቃጥለው አግኝተናል። ግን የጉዳቱን መጠን ሰርቨይ መሰራት አለበት "  ብለዋል።

የፓርኩ ምን ያክል ክፍል እንደተቃጠለ ታውቋል? ለሚለው ጥያቄ በሰጡን ምላሽ፣ " መለካት ያስፈልጋል። ከ350 እስከ 400 ሄክታር ሳራማ ቦታ ተቃጥሏል ብለን እንገምታለን "  የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

" ደረቃማ ሳር ስላለ በትንሹ ነው የሚቀጣጠለውና በሰው ኃይል ለመቆጣጠር አስቸጋሪ አድርጎት፣ በሰው ኃይል ከመቆጣጠር በላይ ሆኖ ነው በግሬደርና፣ ከእሳቱ ርቆ በሎደር የማስራብ ሥራ የተሰራው” ሲሉ አስታውሰዋል።

ፖርኩ ወደ 244 የአእዋፍ ዝርያዎች፣ 42 አጥቢዎችና ሌሎች እንስሳት እንዳሉበት አስረድተው፣ “የተመሰረተው በኬንያና በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘውን ትልቁ የሜዳ አህያ ለመጠበቅ ነው” ብለዋል።

ኮቪድ ከመከሰቱ በፊት እስከ 200 ሺሕ፣ ኮቪድ ተከስቶ ከቆዬ በኋላ የቱሪስት ቁጥር በመቀነሱ ከ50 ሺሕ እስከ 100 ሺሕ ገቢ የሚገኝበት እጩ ፓርክ መሆኑ ተነግሯል።

ፓርኩ ከአዲስ አበባ በ27ዐ ርቀት ላይ ያለ፣ ኤሪያው 1099 ስኩየር ኪሎሜትር የሆነ፣ ወይራ፣ የሀበሻ ጽድ፣ ዝንባ የመሳሰሉ እፅዋቶች ያሉበት፣ 40 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሜዳ ላይ ያረፈ ሳር ያለበት ነውም ተብሏል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

" እሳቱ በቁጥጥር ስር ውሏል " - የኢትዮጵያ የዱር እንሰሳት ጥበቃ ባለስልጣን 

በሃላይደጌ አሰቦት ዕጩ ብሔራዊ ፓርክ ተከስቶ የነበረው የእሳት ቃጠሎ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ስር እንደዋ ለየኢትዮጵያ የዱር እንሰሳት ጥበቃ ባለስልጣን አሳውቋል።

ላለፉት ሶስት ቀናት በብሔራዊ ፓርኩ ውስጥ ተከስቶ ነበረው የእሳት ቃጠሎ ለመቆጣጠር የኢትዮጵያ የዱር እንሰሳት ጥበቃ ባለስልጣን መ/ ቤቱ  የሃላይደጌ እና የአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ሠራተኞች፣ የገቢ ራሱ ዞን እና አሚባራ ወረዳ ነዋሪዎችና አመራሮች እንዲሁም የሃላይደጌና አንዲዶ ቀበሌ ነዋሪዎች ርብርብ ማድረጋቸው ተገልጿል።

" እሳቱን ለማጥፋት በተደረገው ርብርብ ትናንት ከሰዓት ጀምሮ በፓርኩ ላይ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር ተችሏል " ሲል ባለስልጣን መ/ቤቱ አሳውቋል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#እንድታውቁት

አዲስ አበባ በሚከናወነው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና ሌሎች ተያያዥ ስብሰባዎች ምክንያት ከነገ ማለትም ረቡዕ የካቲት 5/ 2017 ዓ.ም ረፋዱ 4፡00 ጀምሮ እስከ መጪው ሰኞ ማለትም የካቲት 10/2017 ዓ.ም ድረስ :-

1. አረቄ ፋብሪካ አጠገብ የነበረው ተርሚናል ወደ ዲያፍሪክ ሆቴል አካባቢ ፤

2. ዋቢ ሸበሌ ሆቴል አጠገብ የነበረው ተርሚናል ወደ ለገሐር ተርሚናል፤

3. በተለምዶ ጠማማ ፎቅ የሚባለው አካባቢ የነበረው ተርሚናል ወደ ሳር ቤት ድልድይ ስር መዘዋወራቸውን እና ስብሰባዎቹ እንደተጠናቀቁ ወደ ቀድሞ ቦታዎቻቸው እንደሚመለሰ የአዲስ አባባ ከተማ አስታዳደር አሳውቋል።

#AU #ADDISABABA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" 4 ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል " - ፖሊስ

በቦንብ ፍንዳታ የተጠረጠሩ 4 ሰዎች በቁጥጥር ስር ማዋሉ ፓሊስ አስታውቋል።

ትናንት የካቲት 3/2017 ዓ.ም በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን እንዳስላሰ-ሽረ ከተማ በአንድ የህዝብ መዝናኛ ስፍራ በተጣለ ቦምብ በ13 ሰዎች ላይ ከባድ እና ቀላል ጉዳት ደርሷል።

ሞት አላጋጠመም።

አደጋው ከተከሰተበት ጀምሮ ከክልል እስከ ወረዳ የተቀናጀ የወንጀል አጣሪ ቡድን አቋቋሞ መንቀሳቀስ መጀመሩ የጠቀሰው ፓሊስ ፤ ከፍነዳታው ጋር በተያያየ 4 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ማዋሉ አስታውቀዋል። 

የቢንጎ ማጫወቻ መሆኑ በተጠቀሰው የህዝብ መዝናኛ ማእከሉ ሰዎች በብዛት እንደሚሰባሰቡበት የጠቀሰው ፓሊስ ባለፈው ጥር ወር በተመሳሳይ ቦንብ ተጥሎ ሳይፈነዳ በመቅረቱ አደጋ አላደረሰም ብሏል።

ፓሊስ " ጥቃቱን አድርሰዋል " በማለት በጠረጠራቸው ሰዎች ላይ ውጤታማ የሆነ የማጣራት በማካሄድ ጉዳዩ ለህዝብ እንደሚያሳውቅ ገልፆ የህዝቡ ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#COC

ጤና ሚኒስቴር የሙያ ብቃት ምዘና ለመውሰድ እየጠበቁ ለሚገኙ የጤና ተመራቂዎች ምዘናው ለመስጠት ዝግጅት ማጠናቀቁን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።

በትምህርት ሚኒስቴር ባለፈው ሳምንት የተሰጠውን የመውጫ ፈተና ወስደው ያለፉ ተማሪዎችን ዝርዝር እየጠበቀ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የመውጫ ፈተና ውጤት መገለፅን ተከትሎ፥ COC የሚወስዱ አመልካቾች (በድጋሜ ተፈታኞችን ጨምሮ) ምዝገባ እንደሚደረግ ሚኒስቴሩ አረጋግጧል።

የCOC ምዘና አመልካቾች ምዝገባ በጊዚያዊነት ከየካቲት 10/2017 ዓ.ም በኋላ ለመጀመር መታቀዱን ሚኒስቴሩ ጠቁሟል።

በዚህም ምዘናውን በየካቲት ወር መጨረሻ ወይም በመጋቢት ወር የመጀመሪያ ሳምንት ለመስጠት በጊዚያዊነት መታቀዱን ከሚኒስቴሩ ሰምተናል።

Via
@tikvahuniversity

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

✨🌍 Make the most of your stay with our ultimate visitors' plan!!

📶 Effortlessly connected.
🎁 Access exclusive deals and offers tailored just for you.
🛫🏡 Enjoy benefits both locally and around the world.
💳 Choose your preferred currency and simplify your transactions.

Get your Visitor Plan today and elevate your experience!

📍 Available at Bole International airport and all service centers.

Read more: https://bit.ly/4cXi8Uv


#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

በመኖሪያ ቤት ዉስጥ በተነሳ የእሳት አደጋ የ3 ታዳጊ ልጆች ሕይወት አለፈ።

በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፤ ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ፤ በንሳ ወረዳ ' ሞኮንሳ ' ተብሎ በሚጠራዉ ቀበሌ በአንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ዉስጥ የተነሳ እሳት የ3 ታዳጊ ሕፃናትን ሕይወት ቀጥፏል።

ትላንት ሐሙስ ቀትር 8 ሰዓት አከባቢ እንደተነሳ በተነገረዉ በዚህ የእሳት አደጋ በቤቱ ዉስጥ ይጫወቱ የነበሩ 3 ሕፃናትና 3 የቤት እንስሳት መሞታቸዉን የወረዳዉ አስተዳዳሪ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።

የእሳቱን ትክክለኛ መንስኤ እና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ የአካባቢውን ፖሊስ አነጋግረን ተጨማሪ መረጃ የምናደርስ ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#UPDATE #ExitExamResult

“ ከዲሲፒሊን ጋር በተገናኘ 540 ተማሪዎች ተለይተዋል። ከዚህኛው ውጤት እስከ መሰረዝ፣ የሚቀጥለውንም ድጋሚ ያለመፈተንና እንቅፋታቸው ትልልቅ የሆኑም እስከነጨረሻውም የሚይፈተኑበት ጊዜ ሊኖር ይችላል ” - ትምህርት ሚኒስቴር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ

ሃገር አቀፉን የመውጫ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤት ከሰዓታት በፊት መለቀቁን ትምትርት ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ተማሪዎች ኅብረት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸውን ነግረናችኋል።

በወቅቱም የፈተናው ውጤት የሚታይበት ሊንክ ስንጠይቅ “ ለዩኒቨርሲቲዎች ተልኳል ” በመባሉ የተለዬ መመልከቻ ካለ እንደምናጋራችሁ ቃል ገብተንላችሁ ነበር።

በዚህም፣ የውጤት መመልከቻው ሊንክ የትኛው ነው ? ስንል የጠየቅናቸው አንድ የትምህርት ሚኒስቴር አመራር በሰጡን ቃል፣ “ ውጤት የሚታይበት ሊንክ ኖርማሊ ለዩኒቨርሲቲዎች ተልኳል። ከተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች ውጪ ሁሉም ማዬት እንዲችሉ ተነግሯቸዋል ” የሚል ምላሽ ሰጥተውናል።

“ ሊንኩ፦ ባለፈው ኦንላይን ሳፓርቲንግ የምንጠቀምበት ፔጅ ነበረ፤ እዛ ፔጅ ላይ ተለቋል። ያውቁታል እነሱ ፤ ከዚህ በፊት የተለቀቀ ሊንክ ነው ለኤግዚት ኤግዛም የተመዘገቡበት ሊንክ ላይ ውጤት ማየት ይችላሉ ” ሲሉ አስረድተዋል።

ስንት ተማሪዎች እንዳለፉና እንደወደቁ ጠይቀናቸው ገና እንዳልታወቀ በገለጹበት አውድ፣ “ አናላይስሱ አልተሰራም። አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ቅዳሜ እለት ስለሚያስመርቁ ለእነሱ ተብሎ ነው በችኮላ የተለቀቀው ” ብለዋል።

በሌላ በኩል፣ የዲሲፒሊን ጉድለት የታየባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ላይ የፈተና ውጤት አለመለቀቁንም እኝሁ አካል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

“ የዲሲፒሊን ግድፈት ጎልቶ የታየባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ላይ ውጤት አልተለቀቀም፤ ወደ 6 በሚሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች። ከዛ ውጪ ተለቋል። ስለዚህ አናላይሲሱ የ6ቱም ተጨምሮ ሲያልቅ ይሰራል ” ሲሉ ነግረውናል።

ስለዚህ የፈተናው ውጤት በተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች ነው የተላከው ማለት ነው ? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ ፣ “ የፈተና ኮራፕሽኑ፤ ስርቆቱ የጎላባቸው 6 ዩኒቨርሲቲዎች ብቻ ላይ ነው እንጂ ያልተለቀቀው ሁሉም ላይ ተለቋል ” የሚል ምላሽ ነው የሰጡን።

በፈተናው ወቅት የተፈጠረ ችግር ነበር ወይስ በሰላም ተጠናቋል ? ለሚለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የአመራሩ ምላሽ፣ “ በዚህኛው ፈተናችን በሰላም ነው የተጠናቀቀው። የጎላ ቸግር አልነበረም ” የሚል ነው።

አክለው ደግሞ፣ “ የተለመዱ የዲሲፒሊን ችግሮች ናቸው የነበሩት፣ የተማሪዎች ከስርቆት ጋር በተገናኘ ያልተፈቀዱ እንደ ሞባይል ያሉ ኤሌክትሮኒክ ዲቫይሶችን ለመጠቀም ሙከራ ማድረግ፣ ወጣ ያለ ደግሞ ከዚህ በፊት የተፈተኑ ተማሪዎች ገብተው ለመፈተን ሙከራ ማድረግ፣ ናቸው እንጂ በጣም የጎላ ችግር አልታዬም ” ነው ያሉት።

ከዲሲፒሊን ግድፈት ጋር በተያያዘ ስንት ተማሪዎች ተገኝተዋል ? ለሚለው ጥያቄ በሰጡን ምላሽ፣ “ ከዲሲፒሊን ጋር በተገናኘ እስካሁን ድረስ ወደ 540 ተማሪዎች ተለይተዋል። የዚህኛው ራውንድ ውጤት እስከ መሰረዝ፣ የሚቀጥለውንም ድጋሚ ያለመፈተንና እንቅፋታቸው ትልልቅ የሆኑ እስከነጨረሻውም የማይፈተኑበት ጊዜ ሊኖር ይችላል ” ብለዋል።

“ እስካሁን ግን አልተወሰነም። ለጊዜው ግን የዚህኛው ውጤት ዲስኳሊፋይድ እንደሚደረግ ነው 54ዐ ተማሪዎች የተለዩት። ቁጥሩ ሊበልጥ ይችላል፤ ለጊዜው ግን ወደ 540 ተማሪዎች ተለይተዋል ” ሲሉም አክለዋል።

(ስንት ተፈታኞች እንዳለፉና እንዳላለፉ ውጤቱን ተከታትለን በቀጣይ የምናሳውቃችሁ ይሆናል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

" ከ3,000 ወጣቶች ወደ 130 የሚሆኑት ወጡ ተብሎ ዝም የሚባል ከሆነ ለቀሪዎቹ አደጋ ነው " - የወላጆች ኮሚቴ

ሰርተው ለመለወጥ በሚል ከኢትዮጵያ የተሰደዱ ዜጎች በማይናማር በአጋቾች የከፋ ስቃይ እያሳለፉ በመሆኑ መንግስት ከስቃይ እንዲታደጋቸው በተደጋጋሚ መጠየቁ አይዘነጋም። 

የወላጆች ኮሚቴ፣ ኢትዮጵያዊያኑ በታገቱበት የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው፣ አጋቾች ልጆቹን ዶላር ማጭበርበር ላይ እንደሚያሰሯቸው በመግለጽ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ደጋግሞ መፍትሄ መጠየቁ ይታወቃል። 

አሁንስ ኢትዮጵያዊያኑ ተለቀቁ
?

ለመፍትሄው ቅርብ የሆኑ አካላት ሁሉ መረጃ በመጠየቅ የታጋቾቹን ጉዳይ በጥልቀት የሚከታተሉ አንድ የታጋች ቤተሰብ በሰጡን ቃል፣ " ከሌሎች ዜጎች ጋር ተደምሮ 261 ልጆች ተለቀዋል። ከ261 ውስጥ ከ126 እስከ 138 ይደርሳል የወጡት የኢትዮጵያዊያኑ ቁጥር " ሲሉ ገልጸዋል።

የታጋቾቹ ወላጆች ኮሚቴ በበኩሉ፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን እንዳልተለቀቁ፣ ነገር ግን  የታይላንድ የጸጥታ ኃይሎችና ኤንጂኦዎች ጥረት በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ከእገታው እንደወጡ ገልጾልናል።

ኮሚቴው በሰጠን ቃል፣ " ከቀናት በፊት 6ዐ ኢትዮጵያዊያን አጥር ዘለው ጠፍተው ከሌሎች አገር ዜጎች ጋር ወጥተው ፓሊስ በቁጥጥር ስር አውሏቸው ነበር " ብሏል።

" ትላንት ደግሞ ወደ 70 ኢትዮጵያዊያን ከተለያዩ ቦታዎች፣ ከ60ዎቹ ጋር በአጠቃላይ 130 ኢትዮጵያዊያን ወጥተው ወደ ባንኮክ እየተጓዙ ነው " ያለው ኮሚቴው፣ ቀሪዎቹም ልዩ ትኩረት እንደሚሹ ገልጿል።

" እንዲወጡልን ብለን ካመለክትንላቸው ልጆቻችን አንድ ሦስተኛ የሚሆኑት እንኳ ገና አልወጡም " ብሎ፣ " የኢትዮጵያ መንግስት ልጆቻችንን ችላ ብሎብናል " ሲል ወቅሷል።

" ቶኪዮ ያለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በአሁኑ ወቅት ትንሽ ቢንቀሳቀስ በጣም ጥሩ ነው " ሲልም በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አስገንዝቧል።

ወጡ የተባሉ ልጆችን ያወጣቸው የኢትዮጵያ መንግስት ነው ወይስ ሌላ ? ስንል ጠይቀነው በሰጠን ምላሽ ኮሚቴው፣ " የኢትዮጵያ መንግስት ምንም እጁ የለበትም። ካሁን በኋላ እጁን ካስገባልን ግን አናውቅም " ሲል መልሷል።

ማነው ያወጣቸው ታዲያ ? ስንል በድጋሚ ላቀረብነው ጥያቄ በምላሹ ፣ " ያወጧቸው ኤንጂኦዎችና የታይላንድ መንግስት ማይናማር ያሉ የጸጥታ አካላት ናቸው " ብሏል።

" ለሚዲያ ከቨሬጅ ብለው እንደሆነም አናውቅም። ከተለያዩ አገራት ያሉ ልጆችን ‘አንተን፣ አንተን’ እያሉ ነው አሉ ያወጡት " ሲልም ስጋቱን ተናግሯል።

ኮሚቴው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል በዝርዝር ምን አለ ?

" ከ3,000 ወጣቶች ወደ 130 የሚሆኑት ወጡ ተብሎ ዝም የሚባል ከሆነ ለቀሪዎቹ አደጋ ነው። ቀሪዎቹም ብዙ ናቸው። ማንም ካሁን በኋላ ዘወር ብሎ የሚያቸውም አይኖርም።

ያልወጡት ልጆቻችን ላይ አሁንም እዛው ያሉ አጋቾች የከፋ እርምጃ ሊወስዱባቸው የሚችሁሉበት አጋጣሚ ሰፊ ነው እንደወጡት ሁሉ ቶሎ የማውጣት ስራ ካልተቀላጠፈ።
 
እስቲ እንዲያው መንግስት ይድረስላቸው። የኢትዮጵያ መንግስት እዛው ቆሞ አለሁ ይበላቸው ልጆቻችንን። ታይላንድ ላይም ሰው ይመደብልን።

በእርግጥም የማይናማር አካባቢ የጸጥታ አካላት የእገታውን አካባቢ ተቆጣጥሯል ተብሏል። ስለዚህ ቶኪዮ ያለው የኢትዮጵያ ኢምባሲ ከማይናማር መንግስት በአስቸኳይ ቀርቦ ልጆቹ የሚወጡበትን መንገድ ይነጋገርልን።

አሁንም ቢሆን የኢትዮጵያ መንግስት ይድረስልን እያልን ነው። የታይላንድ መንግስትና በማይናማር ያሉ አካላት ተባብረው የቻይና መንግስትም እየረዳቸው ነው እየተንቀሳቀሱ ያሉት። 

ቶኪዮ ያለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በከስቸኳይ ሰዎች መድቦ እንዲየጋገርና ሁሉም ልጆቻችን እንዲወጡልን አሁንም በድጋሚ መልዕክቴ ነው " ሲል አሳስቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#AddisAbaba

የኢትዮጵያ እና አፍሪካ መዲና የሆነችው አዲስ አበባ እንግዶቿን እየተቀበለች ትገኛለች።

በርካታ እንግዶች ለ38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ አዲስ አበባ እየገቡ ናቸው።

ዛሬ የተመድ ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ እንዲሁም የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ አዲስ አበባ ገብተዋል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ጊዚያዊ መንግስት ይሁን ጊዚያዊ አስተዳደር ተቀባይነት የለውም ! ... ፃድቃን  ከ93 ዓ.ም ጀምሮ  የCIA አባል በመሆን ህወሓት ለማጥፋት ተንቀሳቅሰዋል  ተው ብለው እምቢ ብሎኛል"  - የህወሓት ታጋይ እና ከፍተኛ አመራር የነበሩት አቶ ስብሃት ነጋ

በኢትዮጵያ ፓለቲካ በአነጋጋሪነታቸው የሚታወቁት ከቀንደኞቹ የህወሓት ነባር ታጋዮች አንዱ የሆኑት ከ80 ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩት ስብሓት ነጋ የካቲት 11/2017 ዓ.ም የህወሓት 50 ዓመት የትግል ምስረታ ምክንያት በማድረግ የደርጅቱ ልሳን ለሆነው ወይን ጋዜጣ ቃለ-መጠይቅ ሰጥተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ 90 ደቂቃ ያህል ርዝማኔ ያለው የህወሓት ነባር ታጋይ ስብሓት ነጋ በትግርኛ የሰጡት ቃለ-መጠይቅ ተከታትሎታል።

ህወሓት ከተመሰረተ ጀምሮ ውስጣዊ የአመራር መከፋፈል ፈተና እንዳልተለየው የገለፁት አቦይ ስብሓት ነጋ ፥ " በ1969 ዓ.ም  እንደ አንድ የፓለቲካ ድርጅት በተመሰረተ ማግስት ያጋጠመው የአመራር መከፋፈል በመጋዳደል ሳይሆን በፓለቲካዊ ክርክር ነው የፈታው " ብለዋል። 

" ህወሓት ከመመስረትዋ በፊት ሁሉም ይንቁን ነበር " በማለት ይንቁዋቸው የነበሩት በስም ያልጠቀሱት ስብሓት " እንደ ሰው የሚቆጥረን አልነበረም ፤ ' ትግራይ ከበላ ከጠጣ ፓለቲካዊ ስልጣን ምን ይፈይድለታል ? ' የሚለውን ስላቅ የቀየረው ህወሓት ነው " ብለዋል።  

" ህወሓት ሁሌ ተማሪ ህዝባዊ እና ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በመሆኑ ይታወቃል ያሉት የቀድሞ ታጋይ " ባለፉት 50 ዓመታት በህወሓት ላይ ያልተሞከረ ክፋት አልነበረም፤ ድርጅቱ ግን ህዝብ መሰረት ያደረገ ትግል በማካሄድ ችግሮቹ ተሻግሮዋቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

ከ1969 ዓ.ም እስከ 1971 ዓ.ም ባሉት ዓመታት ኢድዩ (የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ህብረት ) የተባለ ፓርቲ ህወሓትን ከገፀ ምድር ለማጣፋት ያለመ ያልተሳካ ዘመቻ ማወጁ ፣ 1977 ዓ.ም ከባድ የአመራር መከፋፈል አጋጥሟት እንደነበረ ያወሱት ስብሓት " ፈተናዎቹ በፅናት እና በዴሞክራሲያዊ ክርክር መታለፍ ችለዋል " ሲሉ አብራርተዋል።    

" ቀደም ሲልም አሁንም ከህወሓት ያፈነገጡት አመራሮች ከጠላት በላይ ጠላት ናቸው " ሲሉ የፈረጁት ስብሃት " ፃድቃን ከ93 ዓ.ም ጀምሮ  የCIA አባል በመሆን ህወሓት ለማጥፋት ተንቀሳቅሰዋል  ፤ ተው ብለው እምቢ ብሎኛል " ሲሉ ከሰዋል። 

ጊዚያዊ አስተዳደሩ እንደ ከሃዲ ፣ ቂመኛ የህወሓት እና የትግራይ መንግስት መዋቅር አፍራሽ መሆኑን በመግለፅ እንደማይቀበሉት እና በፅኑ እንደሚቃወሙት አሳውቀዋል።

ስብሃት " የፌደራሊዝም የፓለቲካዊ አስተዳደር ስርዓት በማሞካሸት ፤ ህወሓት የፌደራል ስርዓት ለማጠናከር ከመሰል የፓለቲካ ፓርቲዎች በማበር እንዲታገል እና ችግሮቹ እንዲፈታ " ብለዋል።

የኢፌዴሪ ህገ-መንግስት ሳይሸራረፍ እንዲተገበር እና እንዲከበር ህወሓት መታገለ እንዳለበተ የተናገሩት ስብሓት " መሪዎች ከህዝብ መነጠል የለባቸውም ፤ ህዝባቸው እንዳይከፋፈል መታገል መምራት አለባቸው የህወሓት ድምፅ ይሰማ " ሲሉ ለወይን ጋዜጣ ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ጥቅምት 24/ 2013 ዓ.ም በተካሄደው የትግራይ ጦርነት በፌደራል መንግስት ተማርከው በእስር ከቆዩ በኋላ ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ በምህረት የተለቀቁት የቀድሞ የህወሓት ታጋይ እና ከፍተኛ አመራር ስብሓት ነጋ አሁን ለህክምና በአሜሪካ ይገኛሉ።

ስብሓት ነጋ ከ ቀድሞው የደርግ ስርዓት መውደቅ በኋላ የኢፈርት ኢንደውመንት የባለ አደራ ቦርድ  ሰብሳቢ ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ የሰላም እና ምርምር ተቋም ዋና ዳይሬክተርነት ጨምሮ በበርካታ የስልጣን እርከኖች የቦርድ አባል በመሆን ሰርተዋል።

ህወሓትን በሊቀ-መንበርነት የመሩት ስብሓት ነጋ በትጥቅ ትግሉ ወቅት ለቀድሞው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ በራሳቸው ፍቃድ የሊቀመንበር ስልጣናቸው አሳልፈው መስጠታቸው በፓርቲያቸው ይነግርላቸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

Join us for an in-person info session in Addis Ababa to explore how the Jasiri Talent Investor Program supports aspiring entrepreneurs with the resources and support needed to launch impactful businesses.
📢 What to Expect:
✅ Learn about program benefits
✅ Get insights on the application process
Don't miss this opportunity to take the first step toward your entrepreneurial journey! 🚀

Addis Ababa: February 20, 2025 - RSVP: https://bit.ly/3Qbs5nu

#Jasiri4Africa

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

🔊 #የሠራተኞችድምፅ

“ ያለፈቃዳችን ከአመት ደመወዛችን 100% እየተቆረጠብን ነው። ወዴት እንጩህ ? ” - ሠራተኞች

በምዕራብ አርሲ ዞን ዝዋይ ዱግዳ ወረዳ ያሉ ጤና ባለሙያዎችና ሠራተኞች “አመራሮች ደመወዛችንን እንደፈለጉ ነው የሚቆርጡት። ለምን? ብሎ መጠየቅም አይቻልም” ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ምሬታቸውን አሰምተዋል።

“‘የቀበሌ ቤት መስሪያ’ በሚል ያለፈቃዳችን ከአመት ደመወዛችን 100% እየተቆረጠብን ነው" ያሉት ስሞታ አቅራቢዎቹ፣ "ወዴት እንጩህ?” ሲሉ ጠይቀዋል።

“ለቀበሌ ቤት መስሪያ" እንዲሁም "ለቡሳ ጎኖፋ” በሚል ደመወዛቸው ያለፈቃዳቸው እንደሚቆረጥ፣ የዲቲ ክፍያ በወቅቱ እንደማይከፈላቸው፣ አዲሱ የደመወዝ ጭማሪ ክፍያም እንዳልተፈጸመላቸው አስረድተዋል።

“ዝም ብለው ነው የሚቆርጡብን ፈቃዳችንንም እንኳ አይጠይቁንም” ያሉ ሲሆን፣ የኑሮ ውድነቱን ተቋቁመው ቤተሰብ ማስዳደር ስላልቻሉ መፍትሄ እንዲሰጣቸው አሳስበዋል።

ሠራተኞች ስላማረራቸው ጉዳይ ምን አሉ?

“ ከደመወዛችን እንደፈለጉ ነው የሚቆርጡት። ያለ ማንም ፍላጎት ሰሞኑን 100% ከደመወዛችን ቆርጠዋል። ደመወዙ የሚቆረጠው ለፈረሙትም ላልፈረሙትም ነው።

በአመት 100% በደመወዝ ስኬል ነው የሚቆረጠው። ይህ በወር ከ500 እስከ 800 ሊሆን ይችላል። እንደዬ ስኬሉ መጠኑ ይለያያል። በዚህ ወር ደመወዛችን ተቆርጧል። 

የዱዩቲ ክፍያም የአሁኑ ዘግይቷል። ሌላው የሦስት ወራት የዱቲ ክፍያ አልተፈጸመልንም ገና እየጠበቅን ነው። ፋይናንስ ነው ያልከፈለን። ፎርሙ ፋይናንስ ጋ ደርሷል።

የሁለት ወራት አዲሱ የደመወዝ ጭማሪ አልተከፈለንም። ደመወዛችንን አናውቅም የማይቆረጥ የለም። ዝም ብለው ነው የሚቆርጡት ያለምንም ፈቃድ። እኛን አይጠይቁንም። እንደፈለጉ ነው የሚያደርጉን። ሠራተኛም አይጠይቅም።

ገንዘባችን በብዛት እየተቆረጠ ያለው ‘የቀበሌ ቤት መስሪያ’ ተብሎ ነው። ከዚህም በፊት ያለፍላጎታችን ይቆርጡ ነበር። የትም አቤት ቢባል መልስ አይገኝም።

ይህ ድርጊት የሚፈጸመው እኛ ወረዳ ብቻ እንጂ ሌላ ወረዳ ላይ አልሰማንም ደመወዝ እየቆረጡ ያሉት ” ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለቅሬታው ምላሽ ለማካተት ከክልል፣ ዞን እንዲሁም ወረዳ ባለስልጣናት ለቀናት ሙከራ ቢያደርግም ለጊዜው ምላሽ አልተገኘም። ሆኖም ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኞች ከሆኑ በድጋሚ ጥረት ያደርጋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#AU #Ethiopia

46ኛው የአፍሪካ ሕብረት መደበኛ የአስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ ዛሬ ተጀምሯል።

በዚህም ዛሬ በተካሄደው ምርጫ #ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና ጸጥታ ምክር ቤት አባል ሆና ተመርጣለች።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#SafaricomEthiopia

የየእለቱን ዜናዎችን በSMS እናግኝ! 🗞📲
ከሳፋሪኮም ቁጥራችን 'A’ ብለን ወደ 30000 SMS አሁኑኑ በመላክ ወይም ወደ *779# በመደወል የቲክቫህ ትኩስ መረጃዎችን እናግኝ! በቀን 1ብር ብቻ! ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት ⚡️

🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ:
https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

#MPESASafaricom
#1Wedefit
#Furtheraheadtogether

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#እንድታውቁት

የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና ተያያዥ ስብሰባዎች እስከሚጠናቀቁ ድረስ በአዲስ አበባ ከተማ ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር ክልክል መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

የመሪዎች ጉባኤ እስከሚጠናቅ ድረስ ባሉ ቀናቶች ውስጥ በየትኛውም የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር ፍፁም ክልክል መሆኑን ነው ፖሊስ አሳስቧል።

ትእዛዝ በመተላለፍ ሲንቀሳቀሱ በሚገኙ የሞተር አሽከርካሪዎች ላይ ሆነ ባለ ንብረቶች ላይ እርምጃ እንዳሚወሰድ አስገንዝቧል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

በአፖሎ ዲጂታል ባንክ ከአካውንትዎ ገንዘብ ሲልኩ ደቂቃ አይፈጅም።
አሁኑኑ መተግበሪያውን በማውረድ ይጠቀሙ።
ለአንድሮይድ ስልኮች: https://play.google.com/store/apps/details?id=com.boa.apollo&hl=en&gl=US
ለአፕል ስልኮች: https://apps.apple.com/eg/app/apollo-digital/id1601224628
ለህዋዌ ስልኮች ፡https://appgallery.huawei.com/app/C108966741

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

“ አደጋው በጣም አሰቃቂ ነው። 28 ሰዎች ሞተዋል። 45ቱ ሰዎች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል ” - የኦሮሚያ ክልል ፓሊስ ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ

በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን ጉደያ ቢላ ወረዳ ደረሰ በተባለው የትራፊክ አደጋ፣ እስካሁን የሟቾች ቁጥር 28 መድረሱን የኦሮሚያ ክልል ፓሊስ ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

ኮሚሽኑ ስለአደጋው መንስኤ በሰጠን ቃል፣ “የፊት ጎማው በሮ ወጥቶ ነው። በፍጥነት ላይም ነበር። የፍሬን ቴክኒክ ችግር እንዳለም መረጃ አለ” ብሏል።

የሟቾች ቁጥር ከ26 ጨመረ እንዴ? ስንል የጠየቅናቸው የክልሉ ፓሊስ ኮሚሽን የትራፊክ አደጋና መረጃ ክፍል ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር መሰለ አበራ፣ “እስካሁን ባለው መረጃ የሟቾች ቁጥር 28 ነው” ብለዋል።

“ ከባድ አደጋ የደረሰባቸው 45 ሰዎች ናቸው። እነርሱም በባኮ ሆስፒታል ህክምና ላይ ናቸው ” ነው ያሉት።

የደረሰባቸው ጉዳት ቀላል ጭምር ነው ወይስ ከባድ ብቻ ነው ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ ዋና ኢንስፔክተሩ፣ “ 45ቱም ከባድ አደጋ ነው የደረሰባቸው ” ሲሉ መልሰዋል።

“ ከሻምቡ ወደ አዲስ አበባ ተሳፋሪዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ማርሴዲስ ኮድ 3A 12661 መኪና ጉደያ ቢላ ወረዳ ጎንካ ኢጃ ቀበሌ ጅማ ወንዝ የሚባል ልዩ ቦታ ነው የፊት ጎማው በሮ ገደል የገባው ” ሲሉም የአደጋውን መንስኤ ጨምር አስረድተዋል።

አክለው፣ “ የፊት ለፊት ጎማው በሮ ወጥቶ ነው። በፍጥነት ላይም ነበር። የፍሬን ቴክኒክ ችግር እንዳለም መረጃ አለ። ፓሊስ በማጣራት ላይ ይገኛል ” ነው ያሉት።

የተሳፈሩ ሰዎች ስንት ነበሩ ? ጉዳት ሳይደርስባቸው የተረፉ ይኖሩ ይሆን? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም፣ “ አሁን ባለው መረጃ 28 ሟች፣ 45 ከባድ ጉዳት አጠቃላይ ሹፌርና ረዳት፣ ተሳፋሪን ጨምሮ ነው። መኪያው ውስጥ የነበሩት እነዚሁ ናቸው ” ብለዋል ዋና ኢንስፔክተሩ።

“ አደጋው የደረሰበት ማርሴዲስ ተሽከርካሪ ስሪቱ በጣም የቆዬ በመሆኑ ለረጅም ርቀት መመደብ አልነበረበትም ” የሚል አስተያዬት ሲሰጥ ተስተውሏል፤ የፓሊስ አስተያዬት ምንድን ነው ? የሚል ተጨማሪ ጥያቄም አቅርበናል። 

ኢንስፔክተሩ፣ “እኛ ይሄ መረጃ አልደረሰንም። መንገድ ትራንስፓርት መረጃውን አይቶ ከመናኸሪያ የሚመድበው ስለሆነ ከትልቁ መናኸሪያ ነው ይሄ ስምሪት የሚሰጠው” ብለዋል።

“የሚመለከተው አካል፣ ፌደራል መንገድ ትራንስፓርት አይቶ ስሞሪት የሚሰጥ ስለሆነ እንደኛ እንዲህ አይነት ችግር ካለ እነርሱም ፍተሻ እንዲያደርጉና እንዲህ አይነት ርቀት ቦታም ባይመደብ ጥሩ ነው” ሲሉም አክለዋል።

የፍጥነትም ሆነ የቴክኒክ ችግር እንዲህ አይነት አደጋዎች እንዳይደገሙ ባስላለፉት መልዕክት፣ “ይሄ አሰቃቂ አደጋ ነው። እንደ ኦሮሚያ የደረሰው ከባድ አደጋ ነው። በድጋሚ እንዳይከሰት ባለ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች ሳይሰማሩ በፊት የቲክኒክ ችግር ቢመረምሩ” ሲሉ አሳስበዋል።

ዋና ኢንስፔክሩ በምላሻቸው፣ “የቲክኒክ ችግር በጣም ለአደጋ ስለሚያጋልጥ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ነው መልዕክት የማስተላልፈው” ሲሉም አስገንዝበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" በአደጋው ሁለት ሰዎች ወዲያዉኑ ሲሞቱ ስራ ላይ የነበረ አንድ ተረኛ የፖሊስ አባልን ጨምሮ በሶሰት ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል" - የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ

ትላንት ምሽት 4 ሰዓት ገደማ መነሻዉን ሻሸመኔ ያደረገ ኮድ (3)  - B311533 AA የሆነ አይሱዙ የጭነት መኪና ሶዶ ከተማ ሲደርስ ባደረሰዉ የትራፊክ አደጋ  በሰዉ ሕይወትና በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ም/ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

እንደ ፖሊስ አዛዡ ገለፃ ከኦሮሚያ ክልል አርሲ አከባቢ የግብርና ምርት / ሙሉ ቲማቲም / ጭኖ የነበረዉ ተሽከርካሪ ሶዶ ከተማ ' ሲዳር ቄራ ' በሚባለዉ አከባቢ በከተማዉ በሞተር ሳይክል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሁለት ሰዎችን ገጭቶ ወዲያዉ ሕይወታቸዉ አልፏል።

በተመሳሳይ መልኩ የምሽት ተረኛ የነበረ አንድ የፖሊስ መርማሪም ጥሪ ተደርጎለት በሞተር ሳይክል ጥሪ ወደተደረገለት ስፍራ ሲንቀሳቀስ ይሄዉ ተሽከርካሪ ገጭቶት ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት የፖሊስ አዛዡ ገልጸዋል።

አደጋ አድራሹ ተሽከሪካሪ አራት የመብራት ፖሎችን ከገጨ በኋላ ዲች ዉስጥ ገብቶ የቆመ ሲሆን በአሽከርካሪዉና ረዳቱ ላይ ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰበት የፖሊስ መርማሪ በሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሲሆን ቀላል ጉዳት የደረሰባቸዉ ሹፌሩና ረዳቱም በኦቶና አጠቃላይ ሆስፒታል በሕክምና ላይ መሆናቸዉን የከተማው ፖሊስ አዛዥ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

አጠቃላይ በአደጋዉ 2 የሞት፣ 1 ከባድና 2 ቀላል የአካል ጉዳት እንዲሁም 7 የንብረት ጉዳት መድረሱን አሳውቀዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ExitExam

🔴" የተፈተነው ፈተና ኮንተንቱ(ይዘቱ) ህክምና ያልሆነ ነው በትምህርት ሊገኝ የማይችል ነው " - ተፈታኝ ተማሪዎች

🔵" የተማሩት ነው የሚወጣው የተፈተኑትም ይህን መሰረት አድርጎ ነው " - ትምህርት ሚኒስቴር

ሃገር አቀፍ የመውጫ ፈተና (Exit Exam)  ከጥር 26-30/2017 ዓም በ 87 የፈተና ማዕከላት መሰጠቱ ይታወሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ፈተናው ከተጠናቀቀ በኋላ " ፈተናው ለፈተና ዝግጅት ከሚያግዘው ' ብሉፕሪንት ' ውጪ ነው ይዘቱም ከተማርነው ትምህርት ጋር የማይገናኝ ነው " የሚሉ ቅሬታዎችን ከተፈታኞች ተቀብሏል።

ከተለያየ የትምህርት ክፍል ፈተናውን የወሰዱ ተፈታኞች ፈተናውን ከብሉ ፕሪንት ውጪ የመጣ መሆኑን በመግለጽ ትምህርት ሚኒስቴር ምላሽ ይስጠን ብለዋል።

ቅሬታውን ካቀረቡ ተፈኞች መካከል የሆኑ የህክምና ተማሪዎች " የመጣው ፈተና በጣም ከስታንዳርዱ የወጣ የህክምና ተማሪዎችን የማይመጥን ነበር " ብለዋል።

አክለውም " የተፈተነው ፈተና ኮንተንቱ (ይዘቱ) ህክምና ያልሆነ ነው በትምህርትም ሊገኝ የማይችል ነው " ያሉ ሲሆን " የሚመለከተውን አካል ለማናገር ብንሞክርም ከውጤት በፊት ንግግር እንደማይኖር ተነግሮናል " ሲሉ ገልጸዋል።

" ከእኛ በፊት አምና የተመረቁ ተማሪዎች የተፈተኑትን ፈተና ተመልክተናል ሰርተንም ስለገባን እናውቀዋለን ትክክለኛ ፈተና ነበር የተፈተኑት ይዘቶቹም ጥሩ ነበሩ  ዘንድሮ ምን እንደተፈጠረ አናውቅም የወጣው ፈተና ከህክምና ጋር የማይገናኝ ጥያቄ ይበዛው ነበር " ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

በተጨማሪ ከጤና ተማሪዎች ውጭ የፊዚክስ ተማሪዎች ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

የትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር ) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ከብሉ ፕሪንት ውጪ ተፈትነናል የሚለው ቅሬታ " ውሸት ነው " ብለዋል።

" ከስልጠና ፕሮግራም ብቃት (Competency) ውጪ የሚዘጋጅ አንድም ጥያቄ የለም " ያሉት ስራ አስፈጻሚው የተባለው ቅሬታ " ውሸት ነው ሪፖርትም አልቀረበልንም እንደዚህ ብሎ የጠየቀንም የለም ከኮምፒተንሲ ውጭ የሚወጣ ፈተና የለም " ነው ያሉት።

አክለውም "ፈተናው ከብቃት ጋር የተገናኘ ከሁለተኛ ዓመት እስከ መጨረሻ ዓመት የተማሩት ነው የሚወጣው የተፈተኑትም ይህን መሰረት አድርጎ ነው " ብለዋል።

" ጥያቄው ከዚህ ውጪ ወጣ የሚል ቅሬታ ከሱፐር ቫይዘር፣ ፈታኝ ፣ተማሪ እንዲሁም ዩኒቨርሲቲዎች የቀረበልን አንድም ሪፖርት የለም መረጃው የለንም ሪፖርቱም አልቀረበልንም " ሲሉ ገልጸዋል።

በሌላ በኩል ሃገር አቀፉ የመውጫ ፈተና ውጤት ነገ አልያም ከነገ በስቲያ ይፋ እንደሚደረግ ከትምህርት ሚኒስቴር መስማቱን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎች ህብረት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል፡፡

ህብረቱ ፥ ሚኒስቴሩ ከComprehensive Nursing የመውጫ ፈተና ጋር ተያይዞ የቀረበ ቅሬታን እያጣራ እንደሚገኝ አስረድቷል።

ረቡዕ ወይም ሐሙስ አጠቃላይ የመውጫ ፈተና ውጤት ይፋ እንደሚደረግ ሚኒስቴሩ እንደገለጸለት ህብረቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" 26 ሰዎች ወዲያ ነው ህይወታቸው ያለፈው። ቁጥሩ ሊጨምር ይችላል " - ፖሊስ

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ፤ ጉዳያ ቢላ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ26 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ።

አደጋው ከሻምቡ ከተማ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በመገልበጡ ነው የተከሰተው፡፡

በደረሰው አደጋ የ26 ወገኖቻችን ሕይወት ወዲያው ሲያልፍ 42 ወገኖቻችን ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት መድረሱን የዞኑ የትራፊክ ደህንነት ሃላፊ ኢንስፔክተር አስናቀ መስፍን ተናግረዋል፡፡

በአደጋው ሕይወታቸው ያለፉ ወገኖች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችልም ሃላፊው ገልጸዋል፡፡

መረጃው የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…
Подписаться на канал