ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ
#Update
🔴" በ104.4 የመቐለ ኤፍኤም ያጋጠመው ችግር በመግባባት እንዲፈታ አድርጊያለሁ ስልጣን መረከብ የሚፈልግ አካል እና ግለሰብ ህግ እና ስርዓት ያክብር " - የመቐለ ከተማ ፓሊስ
➡" ሬድዮ ጣቢያችን ለሁለት የተሰነጠቁ ቡድኖች መጫወቻ እንዲሆን አንፈቅድም " - የመቐለ FM አመራር
ጥሪ 21 / 2017 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ሰዓት 5 ታጣቂዎች አስከትሎ የመቐለ ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያን ለመቆጣጠረ ሙከራ ያደረገው ሬድዮ ጣብያውን እንዲመራ የመቐለ አስተዳደር " ሹሞኛል " የሚል ግለሰብ እንደሆነ የሬድዮ ጣቢያው አመራሮች ተናግረዋል።
ታጣቂዎች አስከትሎ ሬድዮ ጣብያውን ለመረከብ ሲሞክር የተፃፈለት ደብዳቤ በቦታው ለነበሩ አመራሮች ማሳየት ባለመቻሉ ምክንያት ግርግር እንዲነሳ ምክንያት መሆኑ አመራሮቹ ያብራራሉ።
ዘግይቶ በተደረገው ማጣራት የሹመት ደብዳቤ ማቅረብ ያልቻለውና ሬድዮውን ለመምራት መመደቡ የጠቀሰው ግለሰብ በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በሚመራው ህወሓት የከተማዋ ከንቲባ እንዲሆኑ በተሾሙት ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) መመደቡ በቃል እንደጠቀሰላቸው አመራሮቹ ገልጸዋል።
ጉዳዩን ወደ መቐለ ፓሊስ በመውሰድ ጊዚያዊ መፍትሄ ማግኘት መቻላቸው ከምስጋና ጭምር አስታውቀዋል።
የጣቢያው አመራሮች " በደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት በተሾመ ከንቲባ ሬድዮ ጣብያውን ለማስተዳደር መመደቡን የሚናገረው ግለሰብ የአገሪቱዋ የሚድያ ህግ በሚጥስ አካሄድ ከአንድ ክፍለ ከተማ ያሰባሰባቸው ታጣቂዎች በማስከተል የአፈና ተግባር ለመፈፀም መመኮሩ የህወሓት በሁለት መሰንጠቅ በክልሉ እያደረሰ ያለው ዘርፈ በዙ ችግር አንዱ ማሳያ ነው " ሲሉ አክለዋል።
" ከ15 ዓመት በላይ ያስቆጠረ እና ከ60 በላይ ሰራተኞች ያሉት የመንግስት የኤፍኤም ሬድዮ ለሁለት የተሰነጠቁ ቡድኖች መጫወቻ አይሆንም " ያሉት አመራሮቹ በአገሪቱ የብሮድካስት ህግ የሚተዳደር ሚድያ መሆኑ በመግለፅ ተመሳሳይ አፈና እንዳይፈፀም በግለሰቡ እና በላከው አካል ላይ ክስ እና አገዳ እንዲጣል እንቅስቃሴ መጀመራቸው አስታውቀዋል።
የመቐለ ፓሊስ በፅሁፍ ባወጣው መግለጫ የአፈና ተግባሩን አውግዞ ፤ ችግሩ በመግባባት መፍታቱን እና ወደ ሃላፊነት መምጣት የሚፈልግ አካል እና ግለሰብ ህግ እና ስርዓት አክብሮ መሆን ይገባዋል ብሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
Are you a bold innovator in Ethiopia🇪🇹,Kenya🇰🇪, Rwanda🇷🇼? The Jasiri Talent Investor program invites you to apply and build an impactful business from scratch that drives prosperity across Africa.
You bring the vision; we help you make it a reality.
Apply to join cohort 8 now: https://jasiri.org/jasiri-talent-investor/
#Jasiri4Africaw
ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባው የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅን አጽድቋል፡፡
ረቂቅ አዋጁ በሁለት ተቃውሞ፣ በአሥር ድምጸ ተዓቅቦ እና በአብላጫ ድምጽ ነው የፀደቀው።
ስለ አጠቃላይ ትምህርት አዋጅ ከዚህ ቀደም የቀረበ ፦ /channel/tikvahethiopia/92892
@tikvahethiopia
የ11 ዓመት እስር ተፈርዶባቸዋል !
ኢትዮጵያ ላይ ጫና እንዲደረግ ከግብፅ ጉቦ ሲበሉ የነበሩት ሴናተር ቦብ ሜንዴዝ የ11 ዓመታት እስር ተፈረደባቸው።
" የግብጽን ጥቅም ለማስከበር ጉቦ ተቀብለዋል " የተባሉት አሜሪካዊው ሴናተር ቦብ ሜንዴዝ የ11 ዓመት እስር ተፈርዶባቸዋል።
ባለፉት 40 ዓመታት በአሜሪካ ፖለቲካ ውስጥ ተጽዕኖ ፈጣሪ የነበሩት ቦብ ሜነንዴዝ ለዓመታት የሀገሪቱ ውጭ ግንኙነት ስራዎች ውስጥ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሰው ነበሩ፡፡
ሜኔንዴዝ ዲሞክራት ፓርቲን ወክለው የአሜሪካ ህግ አውጪ ምክር ቤት ውስጥ ሰርተዋል።
በፈረንጆቹ 2020 ላይ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሶስትዮሽ ድርድር ላይ በንቃት እንዲሳተፉ የተደረጉ ሲሆን ከፍተኛ ጫና ሲያደርጉ ነበር።
ፖለቲከኛው ይህን ያደረጉት ከግብጽ ባለስልጣናት ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ጉቦ ከተቀበሉ በኋላ ነበር፡፡
የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን መሪዎች በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የሶስትዮሽ ውይይት በማድረግ ላይ የነበሩ ሲሆን የወቅቱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይህ ውይይት ወደ ዋሸንግተን እንዲመጣ ማድረጋቸው አይዘነጋም፡፡
በዋሸንግተን በተደረጉት ተከታታይ የሶስትዮሽ ድርድር ላይ ኢትዮጵያ በጫና ወደ ስምምነት እንድትመጣ ግፊት ሲደረግ እንደነበር እና ኢትዮጵያ ስምምነቱን " አልፈርምም " በሚል አቋም መጽናቷ የሚታወቅ ነው።
በወቅቱም የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መግለጫ አውጥቶ ነበር፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ፖለቲከኛው ከግብጽ እና ኳታር ኩባንያዎች ጋር ያልተገባ ጥቅም ትስስር በመፍጠር 150 ሺህ ዶላር የሚያወጣ ወርቅ እና ከ450 ሺህ ዶላር በላይ ገንዘብ ተከፍሏቸዋል።
የሀገሪቱ ፍትህ ተቋማት ባደረጉት ምርመራ ሜኔንዴዝ በጉቦ መቀበል፣ በፍትህ ማዛባት እና ሌሎችም ወንጀሎች ክስ ተመስርቶባቸው በክርክር ላይ ቆይተዋል፡፡
የተመሰረተባቸውን ክስ አምነዋል የተባለ ሲሆን እድሜያቸውን፣ አስቀድሞ አስተዳድራዊ ቅጣቶች እንደተላለፈባቸው እና ሌሎች ምክንያቶችን ታሳቢ አድርጎ ቅጣቱን እንዲቀንስላቸው በጠበቃቸው በኩል ጠይቀዋል።
የሀገሪቱ አቃቢ ህግ በቦብ ሜኔንዴዝ ላይ የ15 ዓመት እስር እንዲተላለፍባቸው ፍርድ ቤቱን የጠየቁ ሲሆን ፍርድ ቤቱም በሴናተሩ ላይ በ11 ዓመት እስር እንዲቀጡ ወስኗል ተብሏል።
መረጃውን ሲኤንኤንን (CNN) ዋቢ በማድረግ ያስነበበው አል አይን ኒውስ ነው።
@tikvahethiopia
#USA
በአሜሪካ የመንገደኞች አውሮፕላን እና የወታደራዊ ሂሊኮፕተር በአየር ላይ ተላትመው ተከሰከሱ።
አደጋው ያጋጠመው በዋሽንግቶን ዲሲ በሀገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር ምሽት 3:00 ላይ ነው።
የፒኤስኤ ንብረት የሆነው የበረራ ቁጥሩ 5342 የሆነና 60 መንገደኞችን እና 4 የበረራ ሰራተኞችን የያዘው አውሮፕላን ሬገን ዋሽንግተን ብሔራዊ ኤርፖርት ለማረፍ በተቃረበበት ሰዓት ነው 3 የአሜሪካ ጦር አባላትን ከያዘ ወታደራዊ ሂሊኮፕተር (ብላክ ሀውክ) ጋር የተላተመው።
አውሮፕላኑ እና ሂሊኮፕተሩ ' ፖቶማክ ወንዝ ' ላይ ነው የተከሰከሱት።
አደጋውን ተከትሎ የነፍስ አንድ ስራ እየተሰራ ሲሆን የሬገን ኤርፖርት ለጊዜው የአውሮፕላን በረራ ማድተናገድ አቁሟል።
የዲሲ ፖሊስ እስካሁን ስለ ሞቱ ሰዎች የተረጋገጠ መረጃ እንደሌለና የነፍስ አድን ስራ ላይ ርብርብ እየተደረገ እንደሆነ ገልጿል።
የአይን እማኞች ግጭቱ ሲፈጠር ከፍተኛ ብርሃን በአካባቢያቸው ታይቶ እነበር ጠቁመዋል።
የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ " አሰቃቂ አደጋ " ሲሉ ገልጸው የተሰማቸውን ሀዘን አካፍለዋል።
ምክትል ፕሬዜዳንት ጄዲ ቫንስ ከአሰቃቂው አደጋ ሰዎች እንዲተርፉ ሁሉም በፀሎት እንዲተጋ ጥሪ አቅርበዋል።
የዋይት ሀውስ የፕሬስ ሴክሬታሪ ካሮሊን ሌቪት በኤክስ ገጻቸው ላይ " እግዚአብሔር ነፍሳቸውን ይማር " ብለዋል።
መረጃው ከኤስቢኤስ፣ ኒውስኤክስ፣ ቢቢሲ የተሰባሰበ ነው።
ቪድዮ ፦ avgeekjake
@tikvahethiopia
#USA
" ሥራችሁን በፈቃዳቸው ከለቀቃችሁ የ8 ወር ደመወዝ ጉርሻ እንሰጣችኋለን " - የትራምፕ አስተዳደር
አዲሱ የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትረምፕ አስተዳደር፣ ፍላጎት ያላቸው የመንግሥት ሠራተኞች በመጪው መስከረም መጨረሻ ሥራቸውን በፈቃዳቸው የሚለቁ ከሆነ የ8 ወር ደመወዝ ጉርሻ እንደሚሰጥ ትላንት ለመንግሥት ሠራተኞች በላከው ኢሜይል አስታውቋል።
ፕሮግራሙ የዶናልድ ትረምፕ አስተዳደር የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችንና ሠራተኞችን ለመቀነስ የያዘው ዕቅድ አካል መሆኑ ተመልክቷል።
ሠራተኞች ፍላጎታቸውን እስከ መጪው ሐሙስ ማለትም እአአ የካቲት 6 ቀን ድረስ ማሳወቅ እንዳለባቸው ተመልክቷል። ይህን የሚያደርጉ ሠራተኞች፣ የመንግሥት ሠራተኞች ሙሉ ለሙሉ ከቢሮ እንዲሠሩ የሚያዘው ደንብ ላይመለከታቸው እንደሚችል ታውቋል።
በስደተኞችና በብሔራዊ ፀጥታ ጉዳይ ላይ የሚሠሩ እንዲሁም የፖስታ ቤት ሠራተኞች ፕሮግራሙ እንደማይመለከታቸው ተመልክቷል።
የመንግሥት ሠራተኞችን የሚወክሉ የሠራተኛ ማኅበራት የአስተዳደሩን ሐሳብ ተቃውመዋል። ሠራተኞች እንዳይስማሙም መክረዋል።
“ የፌዴራል ሠራተኞች ታማኝ፣ አስተማማኝና በየቀኑ ለመሻሻል የሚጥሩ መሆን አለባቸው ” ብሏል ከትራምፕ አስተዳደር የተላከው መልዕክት፡፡
የአሜሪካ መንግሥት ሠራተኞች ፌዴሬሽን “ ሠራተኞች አዲሱ ፕሮግራም በፈቃደኝነት የሚያደርጉት ጉዳይ አድርገው እንዳያዩት” አሳስቧል።
የአስተዳደሩ ተግባር የሚያሳየው በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ውስጥ ጤናማ ያልሆነ አካባቢን መፍጠርና ሠራተኞች መቆየት ቢሹ እንኳ ሥራቸውን መቀጠል እንዳይችሉ ለማድረግ ነው ብሏል።
#VOA
@tikvahethiopia
#Update
“ በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ አሁን ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል ” - የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በአለባሳቸው ሳቢያ ግቢ እንዳይገቡ በመከልከላቸው፣ ከትምህርት፣ ከካፌና ከማደሪያ ውጪ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ ማቅረባቸው አይዘነጋም፡፡
ተማሪዎቹ በሰጡት ቃል፣ " 44 ሴት ተማሪዎችን ጥቁር ማስክ አድርጋችሁ 'አናስገባም' ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን " ነበር ያሉት።
ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅነው ዩኒቨርሲቲው፣ እንደ ሁሉም የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ በሴኩላሪዝምና ብዝሃ ሃይማኖትን ተረድቶና አክብሮ የሚሰራ ተቋም እንደሆነና ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ እንዳይለብሱ እንዳልተከለከለ ኒቃብ ደግሞ አስቀድሞም በዩኒቨርሲቲ እንደማይደረግ ገልጾ ነበር።
ተማሪዎቹ ግቢ እንዲገቡ ተፈቀዳላቸው ?
ወደ ግቢ ገባችሁ ወይስ አሁንም ከግቢ ውጪ ናችሁ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው ተማሪዎቹ፣ " ለጊዜው ከስምምንት ተደርሷል " ሲሉ መልሰዋል።
" በተወካዮቻችን በኩል ኒቃብ፣ ማስክና ሂጃብ ለብሰን መግባት እንደምንችል ተነገረንና ትላንት ገብተናል " ብለዋል።
በስምምነቱ መሰረት ለብሰው እንዲገቡ ከመነገራቸው ውጪ ሌላ የተባሉት ነገር እንደሌለ አስረድተው፣ " ለጊዜው ግን ግቢ ገብተናል " ነው ያሉት፡፡
በደብዳቤ ጭምር በመጠየቅ ጉዳያቸውን ሲከታተል የቆየውን የጌድኦ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትንም ግቢ እንደይገቡ ተከልክለው የነበሩ ተማሪዎች ወደ ግቢ ገብተዋል ? ስንል ጠይቀናል፡፡
የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምን አለ ?
" በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል፡፡
በዘላቂነቱ ላይ እንደ አገር የሚያዝ አቅጣጫ ይኖራል፡፡ ከዚያ ውጪ ግን ይሄ ነው ተብሎ የተገለጸ ነገር የለም፡፡ ሲጀመር ክልከለውን በተመለከተም በፅሑፍ የተገለጸ የለም፡፡ አሁን ሲፈቀድም በተመሳሳይ ነው፡፡
አገራችን የብዙ ሃይማኖቶችና ብሔሮች መገኛ ስለሆነች ስርዓቶችም ሃይማኖቶችን፣ ብሔር ብሔረሰቦችን ያማካሉ ቢሆኑ፤ ለአንዱ እድል ሰጥቶ ሌላኛውን ያላገለሉ፣ ሃይማኖት ባሉ ነገሮች ምክንያት በሌሎች ቦታዎችም ሁሉን ያማከለ ሆነው ቢወጡ የተሻለ ነው፡፡
የጥብቅ ደን/ብዙ እፅዋቶችን አንድ ላይ ነው በማልማት የሚታወቀውና እንደ አገርም ቅርስ የተያዘለት ማህበረሰብ ያለበት ዩኒቨርሲቲም ስለሆነ ነገሮች ሲከናወኑ በዚያ ቢታሰቡ እጅግ መልካም ይሆናል " ብሏል፡፡
የተደረሰውን ስምምነት በተመለከተ ማብራሪያ ለማግኘት የተደረገው ሙከራ የዩኒቨርሲቲው አካላት ስልክ ለማንሳት ፈቃደኞች ባለመሆናቸው ለጊዜው ሃሳባቸውን ማካተት አልተሳካም፡፡
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#EthiopianDefenceUniversity
የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፥ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከ2018 ዓ.ም ጀምሮ የተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ምርጫ ውስጥ እንደሚካተት አሳውቀዋል።
ሚኒስትሩ ይህንን ያሳወቁት ከከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆን በዩኒቨርሲቲው ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት ነው።
#MoE
@tikvahuniversity
" የመውጫ ምዘና ላልወሰዱ ማስረጃ እንዳትሰጡ " - ትምህርት ሚኒስቴር
የመውጫ ምዘና ላልወሰዱ መምህራን ማስረጃ እንዳይሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አሳሰበ፡፡
ሚኒስቴሩ ለዩኒቨርሲቲዎች እና ለክልል ትምህርት ቢሮዎች በጻፈው ደብዳቤ፥ የመውጫ ምዘና ላልወሰዱ መምህራን ማስረጃ እንዳይሰጥ አሳስቧል፡፡
በሚኒስቴሩ የመምህራን ትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) ከሳምንት በፊት የተጻፈው ደብዳቤ፥ " በክረምት መርሐግብር ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ ለመሸጋገር የትምህርት ማሻሻያ ስልጠና የሚከታተሉ መምህራን፣ ስልጠና ሳያጠናቅቁ መረጃ እየተሰጠ እንደሆነ ደርሼበታለሁ " ብሏል፡፡
በክረምት መርሐግብር ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ደረጃ ለማሻሻል ስልጠና እየወሰዱ ያሉ መምህራን፣ የማስተማር ሙያ (PGDT) መውሰድና የመውጫ ምዘና ማጠናቀቅ እንዳለባቸው በመስከረም 2017 ዓ.ም የትምህርት ሚኒስቴር ማሳወቁን በደብዳቤው ገልጿል፡፡
ይሁን እንጂ አንዳንድ ክልሎች ከዚህ በተለየ የማስተማር ሙያ ስልጠናም ሆነ የመውጫ ምዘና ላልወሰዱ መምህራን፣ የደረጃ ዕድገት እየሰጡ መሆኑናቸውን መረዳቱን አሳውቋል፡፡
ማንኛውም ሠልጣኝ የትምህርት ማስረጃ ማግኘት የሚችለው የትምህርት ምዘና ወስዶ ማለፍ ሲችል መሆኑ እየታወቀ፣ የዲግሪ ትምህርታቸውን እንደጨረሱ በማድረግ የትምህርት ደረጃ ማሻሻያና የደረጃ ዕድገት የሚሰጡ አንዳንድ ተቋማት መኖራቸውን ሪፖርተር ያነጋገራቸው መሪ ሥራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር ወጪያቸውን በመሸፈን የሚያስተምረው የበቁ መምህራንን ለማፍራት ነው ያሉት ኃላፊው፤ ማንኛውም ተቋም የመውጫ ምዘና ወስደው ላላለፉ ዕጩ መምህራን ምንም ዓይነት ማስረጃ እንዳይሰጥ በደብዳቤ ማሳወቁን አስረድተዋል፡፡
የመረጃው ባለቤት ሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
@tikvahuniversity
#ለጥንቃቄ
" የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለው ወንጀሎችን የሚፈፅሙ ስላሉ ተጠንቀቁ " - ፖሊስ
በተለያዩ ቦታዎች በመንቀሳቀስና የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለው በተለምዶው " ሿሿ " የተባለውን ወንጀል ፈፅመዋል የተባሉ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ።
ተጠርጣሪዎቹ ብዛታቸው 4 ሲሆን የወንጀል ድርጊቱን ፈፅመዋል ተብለው በቁጥጥር ስር የዋሉት በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 አካባቢ ነው።
የግል ተበዳይ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ቄራ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ሄደው የጤና ምርመራ ለማድረግ ዘነበወርቅ አደባባይ ትራንስፖርት እየጠበቁ ነበር።
ግለሰቦቹም በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2 B-13788 አ.አ በሆነ የቤት መኪና የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለውና የግል ተበዳይን ተሽከርካሪው ውስጥ ያገቧቸዋል።
በኃላም " ቄራ ድረስ ከምትሄጂ እዚሁ ቅርብ ቦታ የጤና ምርመራ ማድረግ ትችያለሽ እናሳይሻለን " በማለት በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ታቦት ማደሪያ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ሲደርሱ ቅያስ ውስጥ ይገባሉ።
እዛም በማስገባት በእጅ ቦርሳ ውስጥ የነበረ 7,900 ጥሬ ገንዘብ ይዘው ለመሰወር ሙከራ ሲያደርጉ በአየር ጤና አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ግለሰቦቹ ወንጀሉን ፈፅመው በተሽከርካሪ ለማምለጥ በሚሞክሩበት ሰዓትም አንድ ግለሰብ ላይ አደጋ ማድረሳቸው ተጠቁሟል።
ከተያዙት 4 ተጠርጣሪዎች ውስጥ አንዷ ሴት ስትሆን አስፈላጊው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።
ግለሰቦቹ ከዚህ በፊትም በተመሳሳይ ወንጀል በጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ፓስተር አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው እንደነበርና ደጋጋሚ ወንጀል ፈፃሚዎች መሆናቸውን ጅምር የምርመራ መዝገቡ ያመለክታል ተብሏል።
የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለውና የተለያዩ ማታለያ ዘዴዎችን በመጠቀም ወንጀሎችን የሚፈፅሙ ግለሰቦችን በህግ ለማስቀጣት ህብረተሰቡ የራሱን ጥንቃቄ እንዲያደርግና ጥቆማ በመስጠት የተለመደውን ትብብር እንዲቀጥል ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopia
#SafaricomEthiopia
🪄 ዳታው በርክቷል! ወርሃዊ የዳታ ጥቅሎችን እየገዛን እስከ 25% የበለጠ ዳታ አግኝተን በየሄድንበት በፈጣኑ ኢንተርኔት ፈታ እንበል! 🥳
M-PESA ላይ ስንገዛ ሁሉም ቅናሽ አላቸው!
በልዩ ልዩ አማራጮች የቀረበልንን የሳፋሪኮም የኢንተርኔት ጥቅል የM-PESA Appን በመጠቀም አሁኑኑ እንግዛ! በአስተማማኙ ኔትወርክ ዳታ እንንበሽበሽ!
#MPESASafaricom
#1wedefit
#Furtheraheadtogether
ካናዳ ለውጭ ዜጎች ስትሰጠው በነበረው የትምህርት እድል ፍቃድ ላይ ገደብ ጥላለች።
ውሳኔው ከተለያዩ የውጭ ሀገራት ወደ ካናዳ የሚገቡ ዜጎች ቁጥር እጅግ መጨመሩን ተከትሎ የተፈጠሩ ክፍተቶችን ለማስተካከል ያለመ ነው ሲል የካናዳ የስደተኞች፣ ዜግነት ጉዳዮች ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
በካናዳ የውጭ ሀገር ዜጎች ቁጥር መጨመር በሀገሪቱ የመኖሪያ ቤት እጥረት እንድያጋጥም እና የጤና አጠባበቅ ስርዓቱ ተመጣጣኝ እንዳይሆን አድርጎታል።
በ2025 በካናዳ የትምህርት እድል የሚያገኙ የውጭ ዜጎች ባለፈው አመት እድሉን ካገኙት ጋር ሲነጻጸር 10 በመቶ ያነሰ ነው ተብሏል፡፡ #legit
Via @ThiqahEth
ብልህ ለራሱ ያውቃል ... በአቢሲንያ ሞባይል ባንኪንግ ህይወትን ቀለል አድርጎ ይመራል።#Banking #BanksinEthiopia #AddisAbaba #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
Читать полностью…" ታስረው ይቅረቡ " - ፍርድ ቤት
ከሂጃብ ክልከላ ጋር ተያይዞ የቀረበውን ክስ ፍርድ ቤት ቀርበው መልስ እንዲሰጡ የተፃፈላቸውን ትእዛዝ " አንቀበልም " ያሉ አካላት ታስረው እንዲቀርቡ የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤት አዘዘ።
ፍርድ ቤቱ ጥር 19/2017 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ ፤ ከሂጃብ ክልከላ ጋር ተያይዞ ክስ የቀረበባቸው 4 ርእሰ መምህራን የአክሱም ከተማ ፓሊስ አስሮ እንዲያቀርባቸው ፍርድ ቤቱ አዟል።
ፍርድ ቤቱ ታስረው እንዲቀርቡ ትእዛዝ ያወጣባቸው የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት፣ የአብርሃ ወ አፅብሃ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ፣ የወርዒ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ፣ የክንደያ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ርእሳነ መምህራን የካቲት 7/2017 ዓ.ም በአክሱም ከተማ ፓሊስ ተይዘው ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ይህ በእንዲህ እያለ ከሂጃብ ክልከላ ተያይዞ በአክሱም በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የተነሳው ውዝግብ ቀጥሏል።
አንዳንድ መረጃዎች አሁንም 159 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ከሂጃብ ክልከላ ጋር በተያያዘ ከሚድ ፈተና ውጪ እንዲሆኑ መደረጋቸውን እያመላከቱ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የሴት ሙስሊም ተማሪዎቹ ከፈተና መቅረት ልክ መሆኑ እና አለመሆኑ ለማጣራት ወደ ትምህርት ቤቶቹ ደውሎ ባገኘው መረጃ መሰረት " የቆየው የተማሪዎች የትምህርት ቤት የአለባበስ ደንብ በሚመለከተው አካል እስካልተቀየረ ድረስ ሂጃብ ለብሰው መግባት አይችሉም " ብለዋል።
@tikvahethiopia
🪪 የዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) በአገልግሎት ማዕከሎቻችን በነጻ ይመዝገቡ!!
የካርድ ኅትመት አገልግሎት በአዲስ አበባ፣ በሐዋሳ፣ አዳማ፣ ወላይታ ሶዶ እና ነቀምቴ ከተሞች እየተሰጠ ይገኛል፡፡
👉 በቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ‘’NID (Fayda) Printing’’ መተግበሪያ ተጠቅመው የካርድ ኅትመትዎን በቀላሉ ይዘዙ!
🔗 በአቅራቢያዎ የሚገኙ የመረከቢያ ቦታዎችን ለመመልከት፡ https://bit.ly/40efSUZ
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
የዋሪት ምርቶች በሚሊኒየም አዳራሽ !
ከጥር 22-25/2017 በሚሊኒየም አዳራሽ በሚካሄደው ፊንቴከክስ ኢክስፖ ላይ የዋሪትን ምርቶች ሲጎበኙ እሰረከ የካቲት 30/2017 ድረስ ልዩ ቅናሽ ተጠቃሚ የሚያደርግዎትን ኩፖን አዘጋጅተን እንጠብቅዎታለን ፡፡ ይምጡ ይጎብኙን !
ዋሪት ፈርኒቸር
ትክክለኛ ምርጫ!
🌟 You’re Invited! 🌟
Join Us at the Fintex Furniture Exhibition of the Year!
Dear All,
We are thrilled to invite you to an exclusive furniture and interior design exhibition Fintex,hosted by Prana Events the trusted name for the furniture industry.
CLAIM YOUR DISCOUNT from FEBRUARY 1-FEBRUARY 28
CODE: FINTEXTELEGRAM2025
📅 Date: January 30th – February 2nd, 2024
📍 Venue: Millennium Hall, Addis Ababa
#Update
አቶ ብርሃኑ አዴሎ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ሆነው ተሹመዋል።
ለሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮምሽነር በመሆን የተመረጡት አቶ ብርሃኑ በህዝብ ተወካዮሽ ምክር ቤት ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ ፈጽመዋል።
አቶ ብርሃኑ የቀድሞው የምክር ቤት አባል የነበሩ ሲሆን የአዕምሯዊ ንብረት ፅህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር፣ በኢህአዴግ ዘመን የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል።
ላለፉት 10 ዓመታት ደግሞ በጥብቅና በህግ ማማከር ስራ ላይ ቆይተዋል።
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር የነበሩት ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) የስራ ዘመናቸውን ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ ራኬብ መሰለ በተጠባባቂነት ተቋሙን ሲመሩ ነበር።
@tikvahethiopia
#NewsAlert
ቀሲስ በላይ መኮንን በ5 ዓመት ጽኑ እስራትና በ10 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ተቀጡ።
የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በእነ ቀሲስ በላይ መኮንን መዝገብ ላይ የቀረቡ የግራ ቀኝ ማስረጃዎችን መርምሮ በዛሬው የችሎት ቀጠሮ በጽኑ እስራትና በገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።
የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾች ፦
➡️ ቀሲስ በላይ መኮንን፣
በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማራው እያሱ እንዳለ፣
➡️ በኮሚሽን ስራ ላይ የተሰማራው በረከት ሙላቱ እና አለምገና ሳሙኤል
➡️ የኒሞና ንግድ ስራ ኃላ/የተ/የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አበራ መርጋ በተባሉ ተከሳሾች ላይ ክስ አቅርቦባቸው ነበር።
ተከሳሾቹ ከአፍሪካ ህብረት ምንም አይነት የክፍያ ትዕዛዝ ባልተሰጠበት ሁኔታ ላይ ተከሳሾች በተለያየ መጠን ክፍያ እንዲፈጸምላቸው የሚል አጠቃላይ የ6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ሀሰተኛ የክፍያ ሰነድ በአንደኛ ተከሳሽ አማካኝነት ለባንኩ መቅረቡ ተጠቅሶ በሁሉም ተከሳሾች ላይ ከባድ የማታለል ሙስና ወንጀል ክስ ነው አቅርቦ የነበረው።
ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ተከሳሾች ብቻ ችሎት ቀርበው የክስ ዝርዝሩ እንዲደርሳቸው የተደረገ ሲሆን 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች በአድራሻቸው ባለመገኘታቸውና በተደጋጋሚ ቀጠሮ ባለመቅረባቸው ለጊዜው ክሳቸው እንዲቋረጥ ተደርጓል።
ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱ ተከሳሾች ክሱ እንዲሻሻልላቸው ያቀረቡት የመጀመሪያ ደረጃ ክስ መቃወሚያ ነጥቦችን ፍርድ ቤቱ መርምሮ ወደፊት በማስረጃ የሚጣራ መሆኑን ገልጾ መቃወሚያቸውን አልተቀበለውም።
ከዚህም በኋላ ተከሳሾቹ በክሱ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው የዕምነት ክህደት ቃል መስጠታቸውን ተከትሎ ዐቃቤ ሕግ አጠቃላይ ሶስት ምስክሮችን አቅርቦ ምስክርነታቸውን አሰምቶ ነበር።
ፍርድ ቤቱ የምስክሮችን ቃል መርምሮ በክሱ ዝርዝር የተጠቀሰው የወንጀል ድርጊት መፈጸሙን በዐቃቤ ሕግ በማስረጃ ማረጋገጡን ጠቅሶ በአንደኛው ክስ ብቻ እንዲከላከሉ በሙሉ ድምጽ ብይን ሰጥቶ ነበር።
ሁለተኛውን ክስ በሚመለከት በሐሰተኛ ሰነድ የተፈጸመ ድርጊት መሆኑ በአንደኛውን ክስ ላይ መገለጹን ተከትሎ በሰበር ሰሚ ችሎት ትርጉም የተሰጠባቸው በተደራራቢነት የቀረቡና ተጠቃልለው ሊያስቀጡ የሚችሉ ድንጋጌዎች መኖራቸውን ፍርድ ቤቱ አብራርቶ ሁለተኛውን ክስ ውድቅ በማድረግ በአንደኛው ክስ ብቻ በከባድ አታላይነት ሙስና ወንጀል እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል።
ሆኖም ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ በሰጠው ብይን የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው ማስተባበል አለመቻላቸው ተጠቅሷል።
በዚህም 1ኛ ተከሳሽ ቀሲስ በላይ መኮንን በሙሉ ድምጽ የጥፋተኝነት ፍርድ የተሰጠባቸው ሲሆን ፤ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች በአንድ ዳኛ የሀሳብ ልዩነት በአብላጫ ድምጽ ጥፋተኛ ተብለዋል።
የሀሳብ ልዩነት ያቀረቡት አንደኛው ዳኛ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት የባንክ ሂሳባቸው በመገለጹ ብቻ የወንጀል ተግባሩ በስምምነት ተፈጽሟል ለማለት አያስችልም የሚል የሀሳብ ልዩነት እንዳላቸው ጠቅሰው ልዩነታቸውን አሳይተዋል።
ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት መርምሮ ዐቃቤ ሕግ ወንጀሉ የተፈጸመው በትብብር መሆኑን ጠቅሶ ያቀረበውን የቅጣት ማክበጃ ይዟል።
በዚህም1ኛ ተከሳሽ ቀሲስ በላይ መኮንን ያቀረቡትን አራት የቅጣት ማቅለያ በመያዝ በዕርከን 21 መሰረት በ5 ዓመት ጽኑ እስራትና በ10 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።
2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት ደግሞ እያንዳንዳቸው አራት፣ አራት የቅጣት ማቅለያ አስተያየት በመያዝ በዕርከን 17 መሰረት በ3 ዓመት ከ3 ወር ጽኑ እስራትና በ3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።
በፍርድ ቤቱ በተከሳሾች ላይ የተወሰነውን የጽኑ እስራት ውሳኔን የአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት እጃቸው ከተያዘ ጀምሮ ታሳቢ በማድረግ እንዲያስፈጽም ታዟል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ነው።
@tikvahethiopia
አቶ ብርሃኑ አዴሎ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነርነት ዕጩ ሆነው ቀረቡ።
በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ዘመነ መንግስት የሚኒስትሮች ካቢኔ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ ገብረማርያም ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኮሚሽነርነት ለመሰየም ዛሬ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ/ም ፓርላማ ቀርበዋል።
ሌሎች አራት ዕጩዎችም መቅረባቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።
አቶ ብርሃኑ ከዚህ ቀደም በተለያዩ መንግሥታዊ ኃላፊነቶች ላይ የሠሩት ሲሆን የመጨረሻ መንግሥታዊ ኃላፊነታቸው የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተርነት ነበር።
ከኃላፊነታቸው የተነሱት " በቀረበባቸው ቅሬታ " መሆኑን ሪፖርተር ጋዜጣ ከ10 ዓመታት በፊት ዘግቧል።
" ከሠራተኞች እና ከተቋሙ ደንበኞች ቅሬታዎች ይቀርቡባቸው እንደነበር " ጋዜጣው በወቅቱ ዘግቧል።
የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ አቶ ብርሃኑን ከዚህ ኃላፊነት ማንሳታቸውም የሪፖርተር ዘገባ ያሳያል።
አቶ ብርሃኑ የአዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬከተር ሆነው ከመሾማቸው በፊት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ሆነው ከ1996 እስከ 2002 ዓ.ም. ለ6 ዓመታት አገልግለዋል።
በሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባ መሠረት አቶ ብርሃኑ ከዚህ ኃላፊነታቸው የተነሱትም በቀረበባቸው ቅሬታ ምክንያት ነው።
ከተወለዱበት ካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች አዲስ አበባ ድረስ በመምጣት በአቶ ብርሃኑ ላይ የተፈራረሙትን ቅሬታ በጊዜው ጠቅላይ ሚኒስትር ለነበሩት አቶ መለስ ዜናዊ ማቅረባቸውን የሪፖርተር ዘገባ ያስታውሳል።
ይህን ተከትሎ " በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር የተቋቋመ አጣሪ ኮሚቴ ባቀረበባቸው ሪፖርት ከካቢኔ ጉዳይ ሚኒስትርነታቸው እና ከኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው እንዲነሱ " መደረጉን ሪፖርተር ከ10 ዓመታት በፊት በሠራው ዘገባ ጠቅሷል።
አቶ ብርሃኑ በመንግሥታዊ ተቋማት ከነበራቸው ኃላፊነት በተጨማሪ አወዛጋውን የ1997 ምርጫ ተከትሎ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ነበሩ።
የትምህርት ሁኔታቸው ምን ይመስላል ?
ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የመጀመሪያ ዲግሪ አላቸው። በዓለም አቀፍ ሰብዓዊ መብቶች ከሕንድ አገር የማስተርስ ዲግሪያቸውን ተቀብለዋል።
የስራ ህይወታቸው ምን ይመስላል ?
- ከመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት እስከ ዩኒቨርሲቲ አስተምረዋል።
- በዞን ፋይናንስ መምሪያ የህግ አማካሪ ሆነው አገልግለዋል።
- የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ባገኙበት የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የህግ ፋካልቲ ለ3 ዓመታት አስተምረዋል።
- በቀድሞው ደቡብ ክልል የፍትህ ቢሮ ኃላፊነት ላይ ሰርተዋል። ከዛ በመቀጠልም በቀረበባቸው ቅሬታዎች ከስልጣን ወደተነሱባቸው የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት አቅንተዋል።
- ከመንግስታዊ የሥራ ኃላፊ ከተነሱ በኋላ ላለፉት 10 ዓመታት በጥብቅና እና በህግ ማማከር ስራ ላይ መሰማራታቸውን ለፓርላማ አባላት የቀረበው የስራ ልምድ ያሳያል።
@tikvahethiopia
ትላንት በጎረቤት ሀገር ደቡብ ሱዳን ዩኒቲ ግዛት አነስተኛ አውሮፕላን ከግዛቷ ተነስቶ ወደ ዋና ከተማ ጁባ በማቅናት ላይ ተከስክሶ የ20 ሰዎች ህይወት አልፏል።
በአደጋው ህይወታቸውን ያጡት የቻይናው ብሔራዊ ፔትሮሊየም ኮርፖሬሽን እና የደቡብ ሱዳን መንግስት ተቋም የሆነው ናይል ፔትሮሊየም በጋራ የመሰረቱት ግሬተር ፐዮኔር ኦፕሬቲንግ ካምፓኒ ሰራተኞች ናቸው ተብሏል።
ከሞቱት መካከል ሁለት ቻይናውያን እና አንድ ህንዳዊ ዜጋ እንደሚገኙበት ተነግሯል።
ስለ አደጋው ምክንያት በዝርዝር የተባለ ነገር የለም።
@tikvahethiopia
“ ‘እስካሁን የተፋጠነ ምላሽ አላገኘንም' እያሉ ያሉ በችሎት ሁሌ ነው የሚያነሱት፤ በኛ እምነትም የተፋጠነ ፍትህ እያገኙ አይደለም ” - የእነ አቶ ክርስቲያን ጠበቃ
እነ አቶ ክርስቲያን ታደለ እና አቶ ዮሐንስ ቧያለድ ትላንት የችሎት ቀጠሮ ነበራቸው።
ጉዳዩን የሚከታተሉ የቅርብ ሰዎች፣ “የእምነት ክህደት ቃል ለመስጠት ነበር ትላንት ተዘጋጅተው የሄዱት ግን ያ ሳይሆን ቀርቷል” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በዝርዝር ምን አሉ ?
“ ትላንት ፍርድ ቤት የቀረቡት ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ ክሱን አሻሽሎ ይቀርባል ተብሎ ስለተጠበቀ የእምነት ክህደት ቃላቸውን ይሰጣሉ ተብሎ ተጠብቆ ነበር።
ሐምሌ 29/2016 ዓ/ም ላይ ክሱን አሻሽሎ እንዲያቀርብ የስር ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር። ከዛ ‘አሻሽዬ አላቀርብም ብሎ ይግባኝ’ ብሎ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቀረበ።
ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ፣ የስር ፍርድ ቤቱ የወሰነው ትክክል ነው ብሎ ባለፈው ሐሙስ በድጋሚ ክሱን እንዲያሻሸል ትዕዛዝ ሰጥቶት ነበር። በዚያ መሠረት ትላንት አሻሽሎ መጥቶ የእምነት ክህደት ቃላተቸውን ይሰጣሉ፤ ክሱም ይሻሻላል ተብሎ ተጠብቆ ነበር።
ግን ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ አሻሽሎ አልመጣምና አሻሽሎ እንዲመጣ ብሎ ረዘም ያለ ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር ፍርድ ቤቱ። ነገር ግን አቶ ዮሐንስና አቶ ክርስቲያን ባቀረቡት ጠንካራ ክርክር ምክንያት ክሱ ተሻሽሎ መጥቶ ለጥር 29 የእምነት ክህደት ቃላቸውን እንዲሰጡ ትዕዛዝ ሰጥቷል። " ብለዋል።
ስለትላንቱን የችሎት ውሎ ማብራሪያ የጠየቃቸው የእነ አቶ ክርስቲያን ጠበቃ አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ፣ “ ከአራት ወራት በኋላ የጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ ቤቱን ውሳኔ በማጽናት ነው ትላንት የቀረቡት ” ብለዋል።
“ ትላንትም ታግዶ የነበረው የከፍተኛ ፍርድ ቤት መዝገብ ተንቀሳቅሷል። ከዚህ በኋላ የእምነት ክህደት ቃላቸውን ነው የሚሰጡት እርሱም ለጥር 29 ተቀጥሯል ” ነው ያሉት።
እየ ክርስቲያን ትላንት የእምነት ክህደት ቃል አልሰጡም መባሉንና የጤንነታቸውን ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ የጠየቅናቸው ጠበቃቸው ምላሽ ሰጥተዋል።
ምን አሉ ?
“ በስነ ስርዓት ህጉ መሠረት አንድ ለጊዜው የተዘጋ ፋይል መንቀሰቀስ አለበት፡፡ ከተንቀሳቀሰ በኋላ ነው ሌላው ሂደት የሚቀጥለው። በእለቱ መሆን ያለበት ፋይል ተንቀሳቅሶ ቀጠሮ መስጠት ነው እንጅ ሁለቱም አንድ ጊዜ አይታይም።
ስለዚህ እኛም ግልባጭ አምጥተን ከእግድም የተነሳ ነው በማለት ተዘግቶ የነበረው መዝገበ ተንቃሳቅሷል፡፡ ለእምነት ክህደት ቀጠሮ በማለት እንጅ በሌላ ምክንያት አይደለም።
ስለጤንነታቸውን በ6 እና በ3 ወራት የሚታወቅ ውጤት ስላለ ሙሉ ለሙሉ ተሸሏቸዋል ማለት አይቻለም፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ ወደነበሩበት ሙሉ ጤና ተመልሰዋል ማለት አይቻልም ግን የህመም ስሜታቸው ቀንሷል” ብለዋል።
የፍርድ ሂደቱ በየወቅቱ እየተራዘመ ነው ያለው ፤ ታራሚዎቹም በህመም እየተሰቃዩ እንደሆነ በቤተሰቦቻቸው በተደጋጋሚ ተነግሯል ፤ የፍርድ ሂደቱ ምን መሆን ነበረበት ? በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ተከታዩን አስተያየት ሰጥተዋል፡፡
“ ተከሳሾቹም በችሎቱ የሚያነሱት ጉዳይ ነው፡፡ የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብት አላቸው፡፡ ህገ መንግስታዊ መብት ነው ይሄ፡፡ ሕገ መንግስታዊ ብቻም ሳይሆን ዓለም ዓቀፋዊም መብት ነው፡።
‘እስካሁን የተፋጠነ ምላሽ አላገኘንም' እያሉ ያሉ በችሎት ሁሌ ነው የሚያነሱት፤ በኛ እምነትም የተፋጠነ ፍትህ እያገኙ አይደለም፡፡
ምንያቱም የሽብር ችሎት አንድ ችሎት ነው፡፡ ይሄ ችሎት ነው ከ10 ዓመታት በላይ መዝገብ ይዞ እያየ ያለው፡፡ በዳኞችም ሆነ በችሎቱ መፍረድ አይቻልም፡፡ የፍርድ ቤቱ የተለያዩ ችሎቶችን አለመመደብ ችግር ነው እንጂ የዳኞች ስራ አለመስራት ችግር አይደለም፡፡
ስለዚህ ትልቁ ችግር የችሎት ማነስ ነው፡፡ አንድ ችሎት ብቻ ነው ያለው፡፡ የችሎት መታጠፍ አለ፡፡ ሦስት ችሎት ነበር ከዚህ በፊት። አሁን አንድ ችሎት ብቻ ነው ያለው፡፡ በአንድ ችሎት ደግሞ ሊታይ አይችልም፡፡
ከዚያ ውጪ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ላይም ደግሞ 4፣ 5 ወራት ቆይቷል፡፡ የተጓደለ ፍትህ ፍትህ እንዳለማግኘት የሚቆጠር ነውና የፍትህ መዘግየት የፍትህን መጓደል የሚያሳይ ነው፡፡
ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ 4፣ 5 ወራት ማቆየት አልነበረበትም፡፡ በተመሳሳይ ደግሞ በተመሳሳይ ጉዳይ፣ በተመሳሳይ መዝገብ የተወሰነ ውሳኔ አለ፡፡ ያ ውሳኔ በአጭር ጊዜ ውስጥ ነው የተወሰነው ይኼኛው ግን 4፣ 5 ወራት ነው የቆየው፡፡ አሁንም የፍትህ መዘግየት አለ።”
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" እግዚአብሔር ያለዉ ይሆናል ብዬ አይዞ ! አይዞ ! እያልኩ ነበር ወደ ወንዝ ዉስጥ የገባነዉ፤ በፈጣሪ እርዳታ ነው እንጂ በህይወት መትረፍ የማይታሰብ ነበር " - ከአደገኛ የመኪና አደጋ በህይወት የተረፈው ረዳት
በቅርቡ በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ቦና ዙሪያ ወረዳ ገላና ድልድይ ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ ከባድ የትራፊክ አደጋ ተከስቶ የ71 ሰዎችን ሕይወት ቀጥፎ እንደነበር አይዘነጋም።
በትናንትናው ዕለት ምሽት ይኸው ቦታ ሌላ የትራፊክ አደጋ አስተናግዷል።
የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ- 3 - 85774 ኢት የሆነ ሲኖትራክ መኪና በትናንትናው ዕለት ምሽት 5:30 ገደማ ዶንጎራ ተብሎ ከሚጠራው አከባቢ የግንባታ አሸዋ ጭኖ ወደ በንሳ ወረዳ እየሄደ በነበረበት ወቅት ቦና ዙሪያ ወረዳ ገላና ወንዝ ሲደርስ ከሳምንታት በፊት የ71 ሰዎችን ሕይወት በቀጠፈዉ ቦታ አደጋ ደርሶበታል።
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የመንገድ ደህንነትና የትራፊክ አደጋዎች መከላከል ዳይሬክቶረት ዳይሬክተር ዋና ኢ/ር ዳንኤል ሹንኩራ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ በመኪናዉ ዉስጥ ሹፌሩ እና ረዳቱ ብቻ ነበሩ።
" ከቦታዉ አደገኝነትና ከጫነዉ ሙሉ አሸዋ ክብደት አንፃር በሕይወት ይተርፋሉ ተብሎ ባይታሰብም በፈጣሪ እርዳታ መኪናዉ ተገልብጦ በአራቱም ጎማ ዉሃ ዉስጥ ማረፉን ተከትሎ በሕይወት መትረፋቸዉን " ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሲኖትራክ ሹፌሩን አቶ ቴዎድሮስ ተስፋዬን እና ረዳቱን ወጣት ሲሳይ አንዴቦ በስልክ አግኝቶ አነጋግሯቸዋል።
" ምሽት 5:30 ገላና ወንዘ አከባቢ ስንደርስ ፍሬን እምቢ አለኝ " ያለው ሹፌሩ " አሸዋ ጭነን ስለነበር በድንጋጤ ዘለህ ዉረድ...እያልኩ ረዳቱን ብማፀንም ግራ በተጋባንበት ሁኔታ እያየኝ መኪናዉ ከቁጥጥሬ ዉጪ ሆኖ ወደ ገደል ገባ " ሲል ስለሁኔታው አስረድቷል።
ረዳቱ ወጣት ሲሳይ አንዴቦ በበኩሉ " ከቦታዉ ቁልቁለታማነት እና መኪናዉ ከነበረበት ፍጥነት አንፃር እሱ ' ዝለል ' እያለኝ የነበረ ቢሆንም መዝለሉ የባሰ አደጋ ስለነበረዉ እግዚአብሔር ያለዉ ይሆናል ብዬ አይዞ ! አይዞ ! እያልኩ ነበር ወደ ወንዝ ዉስጥ የገባነዉ " ሲል ስለሁኔታው አክሏል።
" በፈጣሪ እርዳታ እንጂ ከቦታዉ አደገኝነት አንፃር በሕይወት መትረፍ የማይታሰብ ነዉ " የሚሉት ሹፌርና ረዳቱ " ሰዎች እየደወሉ ' ሞልታችኋል ተብሎ በየፌስቡኩ እየተሰራጬ አይደል!? ' እያሉ ይጠይቁናል " ብለዋል።
" በወቅቱ መኪናዉ ወደታች ሲወድቅ በጎማ ዉሃ ዉስጥ በማረፉ በኛ ላይ የከፋ አደጋ አልደረሰም " ያሉን ሲሆን " በአካባቢዉ ሰዎች እርዳታ ወዲያዉኑ ወደ ቦና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተወስደን መጠነኛ ሕክምና ከተደረገልን በኋላ በትራንስፖርት መኪና ተሳፍረን ወደ ሀዋሳ መጥተናል " ብለዋል።
በሌላ በኩል ይህ ቦታ ካስከተለዉና እያስከተለ ካለዉ አደጋ አንፃር ምን ታስቦበታል ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለሲዳማ ክልል መንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የመንገድ ደህንነት ዘርፍ ኃላፊ ኮለኔል ሮዳሞ ኪአ ጥያቄ አቅርቧል እሳቸውም ጉዳዩን ለፌደራል መንገዶች ባለስልጣን ማቅረባቸውንና ዘላቂ መፍትሔ እንዲበጅለት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
በመቐለ ኤፍ ኤም 104.4 ምንድነው የተፈጠረው ?
" በመቐለ ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያ ላይ የአፈና እና የስራ አመራር የማባረር ሙከራ " መደረጉን ጣቢያው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።
ሙከራው በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የመቐለ ከንቲባ እንዲሆኑ በተሾመቱ ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) ያስተባበሩት ነው ተብሏል።
ዛሬ ጥር 21/2017 ዓ.ም የተካሄደው የአፈናና አመራር የመቀየር ሙከራ ለጊዜው ከሽፏል።
የ104.4 ኤፍኤም መቐለ ስራ አስኪያጅ በመሆን በማገለገል ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ሹመይ ረብሶ ስለሁኔታው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ መረጃ አካፍሏል።
መሩከራው እንዴት እና መቼ ተፈፀመ ?
አቶ ዘመንፈስ ቅዱስ ፍስሃ የሚባሉ የመቐለ ከተማ አመራር አባል ዛሬ ጥር 21 /2017 ዓ.ም ጠዋት ሦስት ታጠቂዎች ይዘው በመመጣት የስራ አስኪያጅ ፀሃፊዋ የሬድዮ ጣብያው ማህተም እንድታስረክባቸው ይጠይቃሉ።
አስረክቡ አናስረክብም በሚል ሰጣ ገባ መሃል የሬድዮ ጣብያው አመራሮች ወደ ከተማው ፓሊስ ደውለው ሃይል እንዲመጣላቸው ሆነ።
ፓሊሶቹ ከመቐለ አስተዳደር የመጣው ግለሰብ እና ታጣቂዋቹ ከሬድዮ ጣብያው እንዲወጡ እና ተግባራቸው እንዲያቆሙ በማድረግ ወደ ህግ ቦታ ወስደዋቸዋል።
በአሁኑ ወቅት 104.4 የመቐለ ኤፍኤም የተለመደ ስራው በመቀጠል ላይ እንደሆነ ስራ አስኪያጁ ገልፀው የአፈና እና የስራ አመራር መቀየር ሙከራ ባደረጉት ላይ ክስ መጀመሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።
104.4 የመቐለ ኤፍ ኤም ሬድዮ በከተማው አስተዳደር ስር የሚተዳደር በትግራይ የመጀመሪያው የኤፍኤም ሬድዮ ጣብያ ነው።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ከክፍያ ለመሸሽ የተቋሙን ገጽታ ማበላሸት አይቻልም በህግ እንጠይቃለን ፣ ከፖሊስ እና ጸረ ሙስና ጋር በመሆን አጣርተን እርምጃ እንወስዳለን " -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በቦሌ አራብሳ ሳይት 3 ብሎክ 734 እና 735 የጋራ መኖሪያ መንደር የሚኖሩ ነዋሪዎች ከቆጣሪ እዳ ጋር በተገናኘ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማቅረባቸው ይታወሳል።
ከጉዳዩ ጋር በተገናኘ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ዝርዝር ምላሽ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።
አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?
" ነዋሪዎቹ ሃይል የተቋረጠባቸው በየብሎኩ የገባላቸውን ቆጣሪዎች ትተው በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ለኮንስትራክሽን ሥራ የገባውን ቆጣሪ እንዳይቆጥር አድርገው ሲጠቀሙ በእኛ ኢንስፔክሽን ቲም (የምልከታ ቡድን) በ15/04/17 ዓ/ም በተረገ ምልከታ ተደርሶባቸው ነው።
በእኛ አሰራር መሰረት ደግሞ ቆጣሪን እንዳይቆጥር አድርጎ ሲጠቀም የተገኘ ካለ አገልግሎቱን በማቋረጥ ሂሳቡ ይሰላል በድጋሚ ሃይል ለማግኘት ያንን ሂሳብ መክፈል አለበት።
በዚህ ምክንያት ሃይል ተቋርጧል ከተቋረጠ በኋላ ሲጠቀሙ የነበሩትን ሂሳብ አስልተን በደብዳቤ ክፈሉ ብለን አሳውቀናቸዋል።
በእነሱ ስም ቆጣሪው ስለሌለ በቤቶች ልማት ጽ/ቤት ስም አሳውቀናቸዋል በተደጋጋሚ ለመክፈል ፈቃደኛ አልነበሩም ኤሌክትሪኩ ተቋርጦ ነው ያለው።
ቆጣሪው ቢሉ የወጣው በኮንትራክተሩ ሳይሆን በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ነው እኛ የምናውቀው በኮንትራክተር የገባ ቆጣሪ የለም ውላችንም ከቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር ነው ኮንትራክተሩን አናውቀውም።
አንድን ኮንትራክተር ሊቀጥረው የሚችለው የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ነው እኛም ውል የሚኖረን ከኮንትራክተሩ ጋር ሳይሆን ኮንትራክተሩን ቀጥሮ ከሚያሰራው ተቋም ጋር ነው ሃላፊነቱን ወስዶ ደብዳቤ ጽፎ ቆጣሪ ይግባ የሚለው የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ነው።
በስርቆት ቆጣሪ በማሰናከል ኤሌክትሪክ ሲጠቀሙ ሲገኝ የመጀመሪያው እርምጃ አገልግሎት ተቋርጦ መንግስት ያጣውን ገንዘብ ታስቦ ክፈሉ ብሎ ማሳወቅ ነው ነዋሪዎች እኛን አይመለከትንም እያሉ ነው ነገር ግን እየተጠቀሙ ነው አይ ቤቶች ልማት እኔን አይመለከተኝም ኮንትራክተሩን ነው ካለም ሃላፊነት መውሰድ አለበት " ብለዋል።
አቶ ብርሃኑ ነዋሪዎቹ ቆጣሪው እንዳይቆጥር በማሰናከል ካርድ መሙላት ካቆሙ ጀምሮ በሦስት ቆጣሪዎች የተጠራቀመው እዳ ቅጣትን ጨምሮ 480,538 ብር መሆኑን ተናግረዋል።
ይህንን ያህል መጠን ኤሌክትሪክ ሃይል የተጠቀሙት ተብለው ለቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በተላከ ደብዳቤ የተገለጹት የጋራ መኖሪያ መንደሩ ነዋሪዎች ብሎክ 734 ፣ 735 ፣ 750 እና 751 ነዋሪዎች ሲሆኑ ነገር ግን ቆጣሪዎቹ የተመዘገቡት በኮርፖሬሽኑ በኩል በመሆኑ የተጠቀሰውን ክፍያ እንዲፈጽም አገልግሎቱ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽንን በተደጋጋሚ መጠየቁን ነገር ግን እስካሁን ክፍያው አለመፈጸሙን አቶ ብርሃኑ ተናግረዋል።
ነዋሪዎች ሃይል ከቆጣሪው ጠልፈው አለመጠቀማቸውን እና ቆጣሪዎቹ መንገድ ላይ የሚገኙ በመሆናቸው ምክንያት ነዋሪ ያልሆኑ አካላት መስመሩን እንደሚጠቀሙ ይገልጻሉ ታውቁታላቹ ወይ ? ስንል ላነሳንላቸው ጥያቄ ዳይሬክተሩ ምላሽ ሰጥተዋል።
" በእኛ በኩል እንደዚህ አይነት ጥቆማ አልደረሰንም ይህንን ቆጣሪ ካስገባን በኋላ በየወሩ ለንባብ ስንመጣ እንዲሁም በእቅድ ምልከታ እናደርጋለን የተጠቀስነውን ችግር ያገኘነው ለምልከታ ስንመጣ ነው። ይሄንን ጥቆማ እንመለከተዋለን በቦታው ስንሄድ ግን የተባለውን ጉዳይ አልተመለከትንም " ብለዋል።
ቆጣሪዎቹ በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በኩል ለግንባታ አላማ ነበር የተቀመጡት ግንባታው ከተጠናቀቀ ቆይቷል ለምን አልተነሱም ስንል ላነሳነው ጥያቄም።
" ቤቶች ልማት አገልግሎቱን ጨርሰናል ቆጣሪው ይነሳልን አገልግሎቱን አንጠቀመውም ብለው ደብዳቤ መጻፍ አለባቸው ውል አለን ዝም ብለን ቆጣሪ ማንሳት አይቻልም ይግባልን ተብሎ በደብዳቤ እንደተጠየቀው ሁሉ ይነሳልን ብለው ሲጠይቁ ብቻ ነው የሚነሳው " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ዳይሬክተሩ ነዋሪዎች የተቋረጠው ሃይል ተመልሶ እንዲቀጠል ጉቦ ክፈሉ ያለን ባለሞያ አለ ሲሉ ላነሱት ቅሬታም " ከክፍያ ለመሸሽ የተቋሙን ገጽታ ማበላሸት አይቻልም በህግ እንጠይቃለን ፣ ከፖሊስ እና ጸረ ሙስና ጋር በመሆን አጣርተን እርምጃ እንወስዳለን " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽንን ምላሽ የሚያካትት ይሆናል።
በተጨማሪም ነዋሪዎች ከተጠቀሱት ቆጣሪዎች ላይ ሃይል መቀጠላቸውን እና አለመቀጠላቸውን እንዲሁም ሌሎችም ነዋሪዎች ያቀረቧቸውን ቅሬታዎች በሚመለከት በቦታው ተገኝቶ ምልከታ ማድረግ እንደሚቻል የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቦታው በመገኘት ቅሬታውን በማጣራት የሚያሳውቅ መሆኑን ይገልጻል።
@tikvahethiopia
ዋሪት !
እስከ ጥር 23 ቀን 2017 የሚቆየው የዋሪት ፈርኒቸር ቅናሽ ሊጠናቀቅ 3ቀናት ብቻ ቀርተውታል።
እንዳያመልጥዎ ! አሁኑኑ ይጎብኙን!
*ወሎ ሰፈር- ከጋራ ሙለታ ህንጻ ጎን
* 22 - ዋሪት ህንፃ
* ጉርድ ሾላ - ሴንቸሪ ሞል
* ለቡ - ቫርኔሮ ፊት ለፊት
* አዳማ - ሶረቲ ሞል
* ቡልቡላ- ልዑል ህንፃ ፊት ለፊት
* ፒያሳ- ፍርዱ ኮሜርሻል
ለተጨማሪ መረጃ: ☎️ 0911210706 / 07
ዋሪት ፈርኒቸር
ትክክለኛ ምርጫ !
#ለጥንቃቄ
(በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቀረበ)
ፋርማ ፕላስ (Pharma+) ምንድነው ?
ፋርማ ፕላስ (Pharma+) ስልካችን ላይ ከማህበራዊ ትስስር ድረ-ገፆች በምንጭናቸው መተግበሪያዎች አማካኝነት ወደ ስልካችን ሰርጎ የሚገባ ሲሆን እንደ ቴሌግራም፣ ዋትስአፕ፣ የመሳሰሉ ማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ በስፋት እየተሰራጨ ጥቃትን የሚሰነዝር #መተግበሪያ ነው፡፡
ጉዳቱ ምንድነው ?
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመረጃ ሥርዓት ደህንነት ክፍል ፋርማ ፕላስ (Pharma+) የተሰኘውን መተግበሪያ ጉዳት አምጪ እንደሆነ ገልጿል።
ፋርማ ፕላስ (Pharma+) ከማህበራዊ ትስስር ገጾች አውርደን በምንጭናቸው ሌሎች መተግበሪያዎች ጋር በመለጠፍ ወደ ስልካችን ሰርጎ በመግባት ፦
- የስልካችንን ስክሪን ማየት፤
- አጭር የጽሑፍ መልዕክቶችን ማንበብ፣
- ሀሰተኛ የመግቢያ ገጾቸን በማዘጋጀት
- የይለፍ ቃሎችን መመንተፍ እና የመሳሰሉ የግል መረጃዎችን የሚሰርቅ መተግበሪያ ነው፡፡
የፋይናንሻል ግብይቶችን ከተጠቂው እውቅና ውጪ መፈፅሙ እና ስልካችን ላይ ተጭነው ካሉት መተግበሪያዎች ውስጥ መደበቁ ማየት ስለማንችል ለመከላከል በጣም አዳጋች ነው።
እንዴት ራሳችንን ከፋርማ ፕላስ (Pharma+) እንጠብቅ ?
➡️ ካልታመኑ ምጮቾች ማንኛውንም መተግበሪያ ስልኮት ላይ አይጫኑ፤
➡️ በማህበራው ገጽ አማካኝነት የሚላክሎትን ማንኛውንም ማስፈንጠሪያ ወይም መተግበሪያ ምንነቱን ሳያረጋግጡ አይክፈቱ፤
➡️ ብቅ ባይ (Pop up) ማስታወቂያዎችን ወይም አጠራጣሪ ገጾችን በፍጹም አይክፈቱ፤
➡️ እንደ ጎግል ፕሌይ፣ አማዞን፣ አፕስቶር ወይም ሳምሰንግጋላክሲ ስቶር ጥብቅ የደህንነት ፍተሻዎችን የሚያደርጉ ይፋዊ የመተግበሪያ ማከማቻዎችን ብቻ ይጠቀሙ።
ትክክለኛ የስልክ መተግበሪያዎችን በመጠቀም እራስዎትን ይጠብቁ።
(የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)
@tikvahethiopia
“ 763 ሠራተኞች ከ2013 ዓ/ም እስካሁን ደመወዝ አልተከፈላቸውም። ሌላ ቦታ እንዳይቀጠሩም የስንብት ደብዳቤ የለም ” - ጽሕፈቱ ቤቱ ስለቀድሞ ሰሜን ዕዝ ሲቪል ሰርቫንቶች
ከ760 በላይ የቀድሞ ሰሜን ዕዝ ሠራተኞች ከ4 ዓመት በላይ ደመወዝ ስላልተከፈላቸው ከነቤተሰቦቻቸው በከፋ ችግር መሆናቸውን በኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የትግራይ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
የምን ያህል ጊዜ ደመወዝ ነው ያልተፈጸመላቸው? ስንል የጠየቅናቸው የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ፀሐዬ እምባዬ፣ “763 ሠራተኞች ከ2013 ዓ/ም ጀምሮ እስካሁን ደመወዝ አልተከፈላቸውም። ሌላ ቦታ እንዳይቀጠሩም የስንብት ደብዳቤ የለም” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
“በሌላ መስሪያ ለመቀጠርምኮ የአገልግሎት ድጋፍ ያስጋል። ይህን የፃፈላቸው አካልም የለም። ዝም ብለው በባዶ እናንተ ‘ስላላመለከታችሁ ተሰናብታችኋል’ የሚል ነው” ነው ያሉት።
“ ይህ እንደ ዜጋ አግባብነት የለውም። ከ20 ዓመት በላይ የሰሩ ናቸው የመከላከያ ሰሜን ዕዝ ሲቪል ሰርቫንት ሆነው ” በማለት ሁነቱን አስረድተዋል።
“ ከሠራተኞቹ ወጣት የሚበል የለም ማለት ይቻላል” ብለው፣ “ ከነቤተሰቦቻቸው ችግር ላይ ናቸው የሚመለከተው አካል መፍትሄ ይስጥ ” ሲሉም አሳስበዋል።
ኃላፊው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል በዝርዝር ምን አሉ ?
“ ከጦርነቱ በኋላ ሰሜን ዕዝ ከፈረሰ በኋላ ሰሜን ዕዝ ሲቪል ሰርቫንት በሥራ ላይ አልነበሩም እንደማንኛውም ሲቪል ሰርቫንት ሰራተኛ። ከፕሪቶራያው በኋላም ስምምነት ማንም ሰው ሊመለከታቸው አልቻለም።
ወደ ዋና መስሪያም ቤት ደብዳቤ ልከናል። መከላከያ ሚኒስቴርም ተጠይቋል። እነርሱ ግን ‘ነገሩ ከተስተካከለ በኋላ ተመለሱና ረፖርት አድርጉ ብለን አሳውቀናል’ይላሉ።
ግን በዚህ ጉዳይ የተፃፈ ደብዳቤም፣ የደረሳቸው ነገርም የለም። 2016 ዓ/ም እንደደረሳቸው ወዲያውኑ መጥተው ወደኛ አመለከቱ። ግን ሪፓርት ያደረጉትን ተቀብለናቸዋል፤ ያላደረጉ እንደሰናበቱ ይቆጠራል’ ብለው ነው የፃፉላቸው።
የሚከታተል ሰው ካለ መጥቶ ያለና የሌለ፣ የሚገባውና የማይገባውን መለየት እንጂ የዓመታት ደመወዝ የሌላቸውን ሠራተኞች ‘ወደ አዲስ አበባ ተጉዛችሁ ሪፓርት አድርጉ’ ማለት አግባብ አይደለም።
ሊሄዱ የፈጉም ነበሩ ግን የሦስትና አራት ዓመታት የቤት ኪራይ እዳ አለባቸው። እዳቸውን ሳይከፍሉ የሚለቃቸው የለም። ይህን ለማድረግ ንብረታቸውን ለአከራይ ማስረከብ አለባቸው።
እንዳይሄዱ መሳፈሪያ ገንዘብ የላቸውም። መካላከያም ‘ካልመጣችሁ አይሆንም ነው ያለውያና መንግስት እያሰራቸው በነበረው ቦታ ሰው ልኮ ቁጥጥር አድርጎ የሚገባውና የማይገባው ማጣራት አለበት ” ብለዋል።
“ ሲቪል ሰርቫንቱ መፍትሄ እየጠበቀ ነው ያለው። መፍትሄ ሊልጣቸው ይገባል። በወረቀት መወራወር ከሆነ ግን ጥሩ አይደለም ለቀጣይም ዜጋ ” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
(የሚመለከታቸው አካላት ለዚህ ቅሬታ ምላሽ እንደሰጡ የምናቀርብ ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ' ብር (ጉቦ) ክፈሉና እንቀጥልላቹ ' ያለን የቴክኒክ ክፍል ሰራተኛ አለ " - ቅሬታ አቅራቢዎች
በአዲስ አበባ ከተማ በለሚኩራ ክፍለ ከተማ በቦሌ አራብሳ ኮንዶሚኒየም ሳይት 3 የብሎክ 734 እና 735 ነዋሪዎች ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በገቡት የቆጣሪ እዳ ውዝግብ ምክንያት ሃይል ከተቋረጠባቸው 1 ወር ከ 5 ቀን መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በተጠቀሱት ብሎኮች ሃይል ያቋረጠው " በሦስት ቆጣሪዎች ያልተከፈለኝ ከ160 ሺ ብር በላይ እዳ አለ " በማለቱ ምክንያት ነው።
ቆጣሪዎቹ የተተከሉት ሳይቶቹ በግንባታ ላይ በነበሩበት ወቅት የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በገባው ውል ሲሆን ቆጣሪዎቹ የተመዘገቡት ደግሞ ከቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር ውል በገባው እና ግንባታዎቹን ባከናወነው የስራ ተቋራጭ (ኮንትራክተር) ስም ነው።
" ይህ በሆነበት ሁኔታ ቆጣሪዎቹን ባልተረከብንበት እና ከእነዚህም ቆጣሪዎች ሃይል ቀጥለን ባልተጠቀምንበት ሁኔታ እዳውን ክፈሉ ተብለናል " ሲሉ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሰምተዋል።
" የመኖሪያ መንደሩ በግንባታ ላይ በነበረበት ወቅት የስራ ተቋራጩ (ኮንትራክተሩ) የተጠቀማቸው እና ግንባታቸው ተጠናቆ ከገባን በኋላም እንዲነሱ ባልተደረጉ ቆጣሪዎች ምክንያት የቆጣሪዎቹን የተጠራቀመ የክፍያ እዳ ክፈሉ ተብለናል ለመክፈል ፈቃደኛ ባለመሆናችንም ምክንያት ላለፈው አንድ ወር በላይ ለሚሆን ጊዜ ሃይል ታቋርጦብናል" ነው ያሉት።
በሁለቱ ብሎኮች ከ60 በላይ ነዋሪዎች የሚገኙ ሲሆን አብዛኛዎቹ በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወነ በሚገኙ የልማት ሥራዎች ምክንያት የተነሱ እና ከሁለት ዓመት እስከ ሁለት ወር ለሚሆን ጊዜ ገብተው መኖር የጀመሩ ናቸው።
ነዋሪዎቹ ቅሬታቸውን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የሰሜን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት እና ለለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ያሳወቁ ሲሆን ጽ/ቤቶቹም ሃይል እንዲመለስላቸው የሚጠይቅ ደብዳቤ በተናጠል ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጽፈዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው እና በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የሰሜን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ ኢ/ር በላይ ሞቱማ ተፈርሞ በ07/05/17 ዓም የወጣው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው ብሎኮቹን የገነባው ኮንትራክተር ቆጣሪዎቹን ከኮርፖሬሽኑ መረከቡን ከግንባታው በኋላም እነዚህን ቆጣሪዎች ከኮንትራክተሩ በመረከብ ለነዋሪዎች አለመተላለፉን እና አሁንም በኮንትራክተሩ የተመዘገበ መሆኑን ይገልጻል።
በዚህም ምክንያት ከቆጣሪው ጋር ተያይዞ የሚመጣ እዳ ሁሉ ኮንትራክተሩን እንጂ ነዋሪዎችን እንደማይመለከት በማስረዳት አስፈላጊውን ህጋዊ ድጋፍ ይደረግላቸው ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትን ጠይቋል።
የለሚኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በበኩሉ በ 09/05/17 ዓም በጻፈው ደብዳቤ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የጻፈውን ደብዳቤ በመጥቀስ ለነዋሪዎች የመብራት አገልግሎት እንዲያገኙ እንዲደርግ እንገልጻለን ብሏል።
ሁለቱም ጽ/ቤቶች በተናጠል በጻፉት ደብዳቤ ሃይል የተቋረጠባቸው ነዋሪዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲያገኙ ቢጠይቁም አገልግሎቱ ሃይሉን ለመመለስ ፈቃደኛ ሳይሆን በመቅረቱ ላለፉት አንድ ወር በላይ በጨለማ ለመቀመጥ መገደዳቸውን ነዋሪዎች ገልጸዋል።
ነዋሪዎች በዝርዝር ባቀረቡት ቅሬታ ምን አሉ ?
" የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተጠራቀመውን እዳ ኮንትራክተሩን ፈልጋቹ አስከፍሉ ወይም የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን እዳውን እንዲከፍል አድርጉ እያለን ነው እነሱ በተዋዋሉት እኛ የምንጠየቀው ለምንድነው ?
መንገድ ላይ ያሉ ቆጣሪዎች እንዲነሱ ማህበረሰቡ ከአመት በፊት ጀምሮ አቤቱታ እያቀረበ ነው ያለው አልተሰማንም ቆጣሪዎቹ ሃይል አልተቋረጠባቸውም፣ አላነሳቸውም እኛ ከእነዚህ ቆጣሪዎች ሃይል አልቀጠልንም።
በዚህም ምክንያት ተዋውለን ለብሎካችን ያስገባነውን ስሪ ፌዝ ቆጣሪ ሃይል አቋረጡብን ለምን ? ስንል የዛኛውን ቆጣሪ እዳ ካልከፈላቹ ተባልን ባልገባነው ውል ባልተጠቀምንበት ሃይል ክፈሉ ተብለን ለምን እንገደዳለን ? እዳው የተመዘገበው በኮንትራክተሩ ነው እኛ ለምንድነው የምንከፍለው።
ምግብ ለማብሰል እንጨት እና ከሰል ነው እየተጠቀምን ያለነው ተማሪዎች አሉ የሚመገቡትን ትተን ፈተና የሚፈተኑበት ጊዜ እንደመሆኑ ያጥኑ እንኳን ቢባል በምን ? ለተጨማሪ እና አላስፈላጊ ለሆነ ወጪ ነው የተዳረግነው።
ፊዩዝ በተደጋጋሚ እያመጡ እየነቀሉ እያዋጣን መክፈል ሥራ ሆነብን ሲበዛብን ከወር በፊት ሊነቅል የመጣውን ሰራተኛ ለማስቆም ሞከርን ለምን ታስቆሙታላቹ በሚል አጠፉብን በዚህ ምክንያት እየተበቀሉን ነው እስካሁን መብራት የለንም።
እያዋጣን ጉቦ መክፈል ሰልችቶናል ' ብር ክፈሉና እንቀጥልላቹ ' ያለን የቴክኒክ ክፍል ሰራተኛ አለ ይሄንን እና ሌሎች ነገሮች ስላሳወቅንባቸው ሌሎች ተመሳሳይ የሆኑ ቆጣሪ ያለባቸው ሳይቶች ላይ እንደዚህ አይነት እርምጃ ሳይወሰድ እኛ ላይ የተደረገው ለብቀላ ነው " ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፣የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን እና የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በጉዳዩ ላይ የሰጡት ምላሽ በቀጣይ ይቀርባል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ተመዝግበንና ክፍያም ከፍለናቸው ትምህርት በመጀመር ሂደት ላይ ባለንበት ዩኒቨርሲቲዉ አላስተምራችሁም ብሎናል " - የሪሚዲያል ተማሪዎች
➡️ " ዉሳኔዉ የትምህርት ሚንስቴ እንጂ የዩኒቨርሲቲው አይደለም " - የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
" የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከሁለት ወራት ፊት በሣምንቱ የዕረፍት ቀናት የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ከፍለዉ መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች ባወጣዉ ማስታወቂያ መሰረት የምዝገባ እና የመማሪያ ክፍያ አጠናቀን ትምህርት በመጀመር ሂደት ላይ እያለን ዩኒቨርሲቲው ሌሎች አማራጮችን መጠቀሚያ ጊዜ ባለፈብን በዚህ ወቅት አላስተምራችሁም ብሎናል " ሲሉ ተማሪዎሽ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድርሰዋል።
ቅሬታቸዉን ካደረሱን ተማሪዎች መካከል በመደበኛው የትምህርት ሚንስቴር ምደባ ጅግጅጋ ፣ሰላሌ እና ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲዎች ተመደብዉ እያለ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) በእረፍት ቀናት በክፍያ ለማስተማር ማስታወቂያ ማዉጣቱን ተከትሎ ከቤተሰብ ላለመራቅና በአንዳንድ አከባቢዎች ካለዉ የፀጥታ ችግር የተነሳ ከፍለዉ ለመማር በመወሰን የምዝገባና የትምህርት ክፍያ አጠናቀው የትምህርት መጀመርን ሲጠባበቁ እንደነበር ገልፀዉ ዩኒቨርሲቲዉ " ኃላፊነት በጎደለው መልኩ 'ትምህርት ሚንስቴር በግል ከፍሎ መማርን ስላልፈቀደ ማስተማር የማንችል በመሆኑ ክፍያችሁን መዉሰድ ትችላላችሁ ' ብሎ የለጠፈዉ ማስታወቂያ እጅግ አሳዝኖናል " ብለዋል።
በተመደብንባቸዉ ዩኒቨርሲቲዎች መሄድ በማንችልበትና ሌሎችም በግል ኮሌጆች ከፍለን የመማሪያ ጊዜዉ ካለፈብን በኋላ የተወሰነዉ ይህ ዉሳኔ ከጊዜ እና ገንዘብ ጉልበት ብክነት ባሻገር በስነልቦናም ጉዳት አድርሶብናል ብለዋል።
ተማሪዎቹ ቅሬታቸዉን ለዩኒቨርሲቲዉና በግልባጭ ለትምህርት ሚንስቴርም ማቅረባቸውን ገልፀዉ የሚመለከተዉ አካል አስፈላጊውን መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጉቼ ጉሌን አግኝቶ በጉዳዩ ዙሪያ አነጋግሯል።
ዶክተር ቅሬታዉ እንደደረሳቸዉና ዩኒቨርሲቲዉ ከዚህ ቀደም እንደሚያደርገዉ ሁሉ " በሣምንቱ መጨረሻ ቀናት የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ለመስጠት ማስታወቂያ ማዉጣቱንና 400 የሚሆኑ ተማሪዎች ተመዝግበው ክፍያ ላጠናቀቁ ተማሪዎች ትምህርት የመጀመር ሂደት ላይ እያለን ትምህርት ሚንስቴር በሰጠዉ ትዕዛዝ መሰረት ማስተማር ስለማንችል ማስታወቂያ ለጥፈናል " ሲሉ ተናግረዋል።
ዩኒቨርቲዉ ለማስተማር ካለዉ ፍላጎት የተነሳ ተማሪዎችን መዝግቦ ወደ መማር ማስተማር ሂደት በመግባት ሂደት ላይ እንደነበር ያስታወሱት ፕሬዘረዳንቱ የተማሪዎችንና የወላጆችን ቅሬታ ተከትሎ ጉዳዩን ወደ ትምህርት ሚንስቴር በማቅረብ ሂደት ላይ መሆናቸዉን ገልጸዋል።
" በሚንስትር መስሪያ ቤቱ ምላሽ ላይ ተመስርተን ' አስተምሩ ' የሚባል ተስፋ ሰጪ ጉዳዮች የሚገኙ ከሆነ ለተማሪዎቹ ጥሪ እናቀርባለን " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።
ጉዳዩን ተከታትለን ተጨማሪ መረጃ የምናደርስ ይሆናል።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
" እስር እና ሰዎችን ወደ መጡበት አገር የመመለስ ሥራ በቁጥር ይጨምራል " - የትራምፕ የስደተኞች ጉዳይ ኃላፊ
በአሜሪካ ሕገወጥ ከተባሉ ስደተኞች ጋር በተያያዘ ከእሑድ ጀምሮ በተጀመረ የአሰሳ ዘመቻ እስካሁን 956 ሰዎች መታሰራቸው ተገለጸ።
ይህም ዶናልድ ትራምፕ ወደ ሥልጣን ከተመለሱ በኋላ ከፍተኛ ቁጥር መሆኑን የአገሪቱ የስደተኞች እና የጉምሩክ ተቋም የሆነው ኢሚግሬሽን ኤንድ ከስተምስ ኢንፎርስምነት (አይሲኢ) አስታውቋል።
የፌደራል ተቋማት በቁጥጥር ሥር የማዋል ሥልጣናቸው እንዲሰፋ መደረጉን ተከትሎ በቺካጎ፣ ኔዋርክ፣ ኒው ጀርዚ እና ማያሚ ሰነድ የሌላቸውን ስደተኞችን የማደኑ ዘመቻ ተካሂዷል።
ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳቸው ወደንጀለኞች ያሏቸውን ያልተመዘገቡ ስደተኞችን በጅምላ ወደመጡባቸው አገራት እንደሚመልሱ ቃል ሲገቡ ነበር።
የትራምፕ የስደተኞች ጉዳይ ኃላፊ " ሰነድ አልባ ሰዎች በአሰሳ ወቅት ከተያዙ ወደመጡበት አገር ይመለሳሉ " ብለዋል።
" እስር እና ሰዎችን ወደ መጡበት አገር የመመለስ ሥራ በቁጥር ይጨምራል " ሲሉ ተናግረዋል።
" አሁን ትኩረታችን የሕዝብ ደኅንነት እና የብሔራዊ ደኅንነት ስጋትን ማስወገድ ነው " ብለዋል።
ያለፈው ሳምንት አርብ 538፣ ቅዳሜ 593 እና እሑድ 286 ሰዎች ተይዘዋል። በጆ ባይደን የአራት ዓመታት አስተዳደር ዘመን ከአሜሪካ ተባረው ወደ አገራቸው የተመለሱ 1.5 ሚሊዮን ስደተኞች ናቸው።
መረጃው የቢቢሲ እና ኤቢሲ ኒውስ ነው።
@tikvahethiopia