ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ
🌟 በቴሌብር ሐዋላ ይቀበሉ፤ ይሸለሙ!
ከባህርማዶ በቴሌብር ሬሚት እና በአጋሮቻችን በኩል የተላከልዎን ዓለም አቀፍ ሐዋላ በቴሌብር ሲቀበሉ 10% የገንዘብ ስጦታ ያገኛሉ፡፡
💁♂️ በተጨማሪም 6ሺህ ብር እና ከዛ በላይ ሲቀበሉ አጓጊ ለሆነው ልዩ የዕድል ጨዋታ ብቁ ይሆናሉ!
🛋 የቤት ዕቃዎች - 15 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው 100,000 ብር
🐏 የበግ ስጦታዎች - 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው 15,000 ብር
🛒 የበዓል አስቤዛ - 50 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው 10,000 ብር
💰 የኪስ ገንዘብ - 300 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው 5,000 ብር
🎁 እንዲሁም በርካታ የሞባይል ዳታ ጥቅሎች
የሚቀበሉት የገንዘብ መጠን ሲጨምር የጨዋታ ዕድልዎም ይጨምራል!
🗓 እስከ ጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም ብቻ!
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSupperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
ፎቶ ፦ የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የእድሳት ሥራ ተጠናቆ በቅዱስ ፓትርያርኩ እየተመረቀ ነው።
የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የእድሳት ሥራ ተጠናቆ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ተመርቆ ታቦተ ሕጉ ጥንታዊነቱን ጠብቆ ወደ ታደሰው ካቴድራል በመግባት ላይ ይገኛል።
በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ ፤ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት መምሪያ ኃላፊዎችና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የየክፍል ኃላፊዎች ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣ ምዕመናንና ምዕመናት ተገኝተዋል።
መረጃው የቤተክርስቲያኒቱ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።
@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ
ቅዳሜ ጥር 10 ከረፋዱ 4:30 ቀጣይ ዙር የጥያቄ እና መልስ ውድድር በቴሌግራም ቻናላችን ላይ ይደረጋል። በየሳምንቱ አስር አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀልና ቀላል ጥያቄዎችን በመመለስ ይሸለሙ!
የቴሌግራም ሊንክ 👇
/channel/BoAEth
አቢሲንያ የሁሉም ምርጫ!
#Telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#FreeNaima
" ገንዘቡን ካላገኘን በቀር እንዳንደውልላቸው አስጠንቅቀውናል። በጣም ተጨንቀናል " - ቤተሰብ
በሊቢያ ታጣቂዎች በርካታ ስደተኞችን አግተው የማሰቃየት ድርጊት እየፈጸሙባቸው ይገኛል።
ከእነዚህ ታጋቾች መካከል የሀገራችን ልጅ ነሒማ ጀማል አንዷ ናት።
ነሒማ ከኦሮሚያ ክልል፤ ሻሸመኔ በመሰደድ ነው ወደ ሊቢያ ያቀናችው።
' ሬፊዩጂስ ኢን ሊቢያ ' የተሰኘው ተቋም በኤክስ ገፁ እንዳስታወቀው ነሒማ እና ሌሎች ስደተኞች ' ኩፍራ ' በምትባለው የሊቢያ ግዛት በታጣቂዎች ቁጥጥር ሥር ይገኛሉ።
ነሒማ በፎቶዎቹና በቪዲዮዎች ላይ አፏ በጨርቅ ተለጉሞ ስቃይ ሲደርስባት ትታያለች።
የነሒማ ጀማል ቤተሰቦች ቪዲዮዎች እና ፎቶዎች ተልኮላቸው የማስለቀቂያ ገንዘብ እንዲከፍሉ ማስጠንቀቂያ ደርሷቸዋል።
የነሒማ እህት ኢፍቱ ጀማል ፤ ነሒማ ከ8 ወራት በፊት ከሻሸመኔ ከተማ የ11ኛ ክፍል ትምህርቷን አቋርጣ ወደ ሊቢያ እንደተሰደደች ለቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ተናግራለች።
" ፎቶዎች እና ቪዲዮዎች ይልኩልናል። ስትሰቃይ ያሳዩናል። የድምፅ መልዕክትም ልከውልናል። እህታችን ' ገንዘብ ላኩላቸው ካልሆነ ይገድሉኛል ' ስትል ይሰማል " ስትል አስረድታችለች።
ነገር ግን ኢፍቱ እንደምትለው ቤተሰቡ አጋቾቹ የጠየቁትን ገንዘብ የመላክ አቅም የለውም።
' ሬፊዩጂስ ኢን ሊቢያ ' የተባለው ሊቢያ የሚገኙ ስደተኞችን ጉዳይ የሚከታተለው ተቋም እንዳለው የ20 ዓመቷ ነሒማ ጀማል ባለፈው ግንቦት ሊቢያ ከገባች ከቀናት በኋላ ነው በታጣቂዎቹ እጅ ውስጥ የገባችው።
በቁጥጥር ሥር ከዋለች በኋላ ስቃይ ሲደርስባት እና ስትደበደብ የሚያሳዩ ፎቶዎች እና ቪዲዮዎች ለቤተሰቦቿ ተልከዋል።
ኢፍቱ እንደምትለው ቤተሰቡ የተጠየቀውን ገንዘብ ለማሰባሰብ እርዳታ ቢጠይቅም እስካሁን ድረስ ሊሞላላቸው አልቻለም።
ቤተሰቡ የነሒማን ድምፅ ከሰማ ሁለት ሳምንት እንዳለፈው እህቷ ተናገራለች።
" ገንዘቡን ካላገኘን በቀር እንዳንደውልላቸው አስጠንቅቀውናል። በጣም ተጨንቀናል " ስትል አክላለች።
' ሬፊዩጂስ ኢን ሊቢያ ' ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስቃዩ እና ማስፈራራቱ እንደተጠናከረ እና ይህ ደግሞ ቤተሰቦች ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ እንደሆነ ገልጿል።
አጋቾቹ ለነሒማ ማስለቀቂያ የጠየቁት ገንዘብ 6 ሺህ ዶላር ነው።
የነሒማ ቤተሰብ ይህንን ሁሉ ገንዘብ ለማሰባሰብ የሚችለውን ሁሉ እያደረገ ይገኛል።
ለነሒማ ቤተሰብ የተላኩ ቪዲዮዎች በርካታ ስደተኞች በአሰቃቂ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ ያሳያሉ።
ነሒማ እጅና እግሯ ተጠፍሮ፤ አፏ በጨርቅ ታፍኖ ትታያለች። ስቃይ ሲደርስባት እና ደም በደም ሆና የሚያሳዩ ቪዲዮዎች እና ፎቶዎችም አሉ።
ድርጅቱ በለቀቃቸው ቪዲዮዎች እና ፎቶዎች ላይ ነሒማ ብቻ ሳትሆን 50 ገደማ ሌሎች የአጋቾቹ ሰለባዎች ከጀርባዋ ተደርድረው ይታያሉ።
የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በሊቢያ እየተካሄደ ያለውን የባርነት ንግድ ዓለም ረስቶታል ሲሉ ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ እየወቀሱ ናቸው።
በእርስ በርስ ጦርነት እየታመሰች ወዳለችው ሊቢያ በስደት የተጓዙት ነሒማ እና ሌሎች ስደተኞች መጨረሻቸው ምን ሊሆን እንደሚችል አይታወቅም።
በርካታ ኢትዮጵያውያንና ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ስደተኞች ሕይወታቸውን ለመቀየር በሚል ወደ አውሮፓ በሚያደርጉት ጉዞ የሜዲቴራኒያን ባሕርን ከማቋረጣቸው በፊት ሊቢያን ይረግጣሉ።
መረጃው ከሪፊውጂስ ኢን ሊቢያና ቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው የተገኘው።
#FreeNaima
@tikvahethiopia
#ብርሃን_ባንክ
መልካም ዜና ለብርሃን ቤተሰቦች በሙሉ
“በብርሃን መደጋገፍ” በሚል ፡ አዲስ የእድር አገልግሎት ጠቀም ካለ ወለድ እና የብድር አማራጮች ጋር በብርሃን ባንክ ቀርቦሎታል። በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ ቅርንጫፍ ጎራ ብለው ወይም በ8292 የደንበኞች አገልግሎት ቁጥር ደውለው ዝርዝር መረጃ ማግኘት ይችላሉ።
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ሥራችን!
#Beberhanmedegagef #edir #digitalfinancialservice #berhanbank #bank #Stressfreebanking #bankinethiopia #finance
➡️ Facebook
➡️ Telegram
➡️ Instagram
➡️ Twitter
➡️ LinkedIn
➡️ YouTube
" ለ1,523 ቀናት ያህል በፕላስቲክ ቤት መኖር ይብቃን " - ተፈናቃይ ወገኖች
ዛሬ ጥዋት በመቐለ ሰላማዊ ስልፍ ተካሂዷል።
ሰላማዊ ሰልፉ " በቃን ወደ ቄያችን መልሱን " ባሉ የተፈናቃይ መጠለያዎች ውስጥ በሚገኙ ወገኖች አማካኝነት ነው የተደረገው።
የመቐለ ሮማናት አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ከጥዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በከተማዋ ፓሊስ ከተሸከርካሪ እና ከእግረኞች እንቅስቃሴ ነፃ እንዲሆኑ ተደርገው ነበር።
በመቐለ እና ከመቐለ ውጪ ባሉት የተፈናቃይ መጠለያዎች የሚገኙ ወገኖች " ይበቃል !! " በሚል በሦስት አቅጣጫ ወደ ሮማናት አደባባይ ተሰባስበው ድምጻቸውን አሰምተዋል።
ሰልፈኞች በሮማናት አደባባይ እንደደረሱ ፦
- ለ1523 ቀናት በፕላስቲክ ቤት መኖር ይብቃን !
- የፕሪቶሪያ ስምምነት በሙሉነት ይተግበር !
- ወደ ቤታችን መልሱን !
- ጦርነት እንጠየፋለን ፤ ሰላም እንሻለን !
- ዓለም ድምፃችንን ስሚ !
- በመቀጠል ያለው የተፈናቃዮች ሞት ይብቃ !
- ህገ- መንግስት ይከበር ! ... የሚሉ እና ሌሎች መፈክሮች አሰምተዋል።
ተፈናቃዮቹ በተወካያቸው በኩል ባሰሙት መግለጫ ፥ በመላ ትግራይ የሚገኙ ተፈናቃዮች በረሃብ እና መድሃኒት እጦት እየሞቱ መሆናቸው ጠቅሰዋል።
ለማሳያ ከመስከረም 2017 ዓ.ም ወዲህ ብቻ በክልሉ በሚገኙ የተለያዩ የተፈናቃይ ማቆያ ጣብያዎች ይኖሩ የነበሩ ከ812 በላይ ወገኖች ህይወታቸው ማጣታቸው ገልፀዋል።
መሰል ሰለማዊ ሰልፍ የዛሬን ጨምሮ ለ3 ቀናት እንደሚኖር ተነግሯል። የዛሬው የማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት ሰላማዊ ነበር።
የተፈናቃይ ስልፈኞቹን ጥያቄ እና የሚመለከተው የመንግስት አካል ምላሽ ካለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ተከታትሎ ያቀርባል።
#TigraiTV #TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
“ በየፍርድ ቤቱ የሚሰጡ ውሰኔዎች ደካማ፣ ሕጋዊ ውሳኔ ብቻ፣ የመወሰን ስልጣን ስላላቸው ብቻ የሰጧቸው ውሳኔዎች ናቸው ” - የሕግ ባለሙያ ጥጋቡ ደሳለኝ
ጠበቃና የሕግ ባለሙያ ጥጋቡ ደሳለኝ፣ በሴቶችና ህፃናት የወሲብ ጥቃት ፈጻሚዎች ላይ “ ከ15 እስከ 25 ዓመት ጽኑ እስራት ” የሚለው ድንጋጌ ችግሩ እንዲስተካከል ስላላደረገ መሻሻል እንዳለበት ተናገሩ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጠበቃና የሕግ ባለሙያው ጋር ያደረገውን ቆይታ ያንብቡ።
Q. ህፃናትን የደፈሩ የስጋ ዝምድና ያላቸው ግለሰቦች ላይ ፍ/ቤቶች የሚጥሉት ቅጣት በማነሱ ድርጊት ፈጻሚዎችን “ አይዟችሁ በርቱ የሚል እየሆነ ነው ” የሚሉ ትችቶች ተበራክተዋል፣ ከሕጉ አንጻር በፍርድ አሰጣጥ ምን መስተካል አለበት ?
አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ ፦
“ በወንጀል ሕጉ ህፃናት ላይ የሚፈጸሙ የአስገድዶ መድፈር ወንጀሎች የቅጣት ደረጃ ‘ከ እስከ’ የሚል የግርጌና የራስጌ አይነት የቅጣት ስርዓት ነው ያለው። ሰፊ ነው ክፍተቱ።
ለምሳሌ እድሜያቸው ከ13 ዓመት በታች በሆኑ ህፃናት የአስገደድዶ መድፈር ወንጀል የፈጸመ ሰው ከ15 - 25 የሚደርስ፤ ማፈን፣ ማታለል፣ ማነቅ አይነት ተደራራቢ ወንጀል ካለው የእድሜ ልክም ሞትም ሊሆን ይችላል።
እድሜያቸው ከ14 ዓመት በላይ የሆኑ ህፃናትና አጠቃላይ በሴቶች የሚፈጸም ወሲባዊ ጥቃት ከሆነ ደግሞ እንደ ድርጊቱ አፈጻጸም ከ5 ዓመት እስከ 25 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲፈረድ የሚል ነው።
ዳኞች 10፣ 15 ዓመት ቢፈርዱ ልክ ናቸው በሕገ መንግስቱ አንቀጽ 79 መሰረት ዳኞች የሚሰጧቸው ውሳኔዎች ፍትሃዊ፣ ነጻና ገለልተኛ እንደሆነ ታሳቢ ይደረጋል።
የእኛ አገር ዳኝነት በተጻፈ ሕግ ብቻ ነው ፍርድ የሚሰጠው። ነገር ግን መሰጠት ያለበት በተጻፈ ሕግ ብቻ ሳይሆን በርትዕ (በሕሊና ፍርድ) ጭምር ነበር።
ነገር ግን ዳኞቻችን ብዙ ጊዜ የሚሰጧቸው ውሳኔዎች የጻፈውን ሕግ እንጂ ርትዕን ታሳቢ አያደርጉም።
ዳኞቻችን ደግሞ ከምልመላው እስከ ሹመቱ ድረስ ችግር ባለበት ሂደት ነው የሚመጡት። ሕግ የተማሩ ሁሉ ዳኛ አይሆኑም በመርህና በዓለም አቀፍ ደረጃ።
ኢትዮጵያ ውስጥ ግን ዳኛ ከሆነና በዐቃቢ ሕግም ይሁን በሕግ ባለሙያነት አምስት ዓመት ከሰራና ምልመላውን ካለፈ በምክር ቤት ይሾማል። የዳኞቻችን የውሳኔ አሰጣጥ ችግር አለባቸው። ደካማ ውሳኔ ነው የሚሰጡት።
ሕጋዊ ውሳኔ መስጠትና ፍትሃዊ ውሳኔ መስጠት ይለያያሉ። ሕጋዊ ውሳኔ ማንም የመወሰን ስልጣን ያለው የሚሰጠው ውሳኔ ነው። ለምሳሌ የአንድ ተቋም ጥበቃ ‘ደንበኛ ተፈትሾ ነው የሚገባው’ ቢል ያ የጥበቃው ሕጋዊ ወሳኔ ነው።
በሕግ ደግሞ ፍትሃዊ የሚባለው ከዚህ ውሰኔና አስተሳሰብ ይለያል። የወጡ ሕጎችንና ማስጃዎችን መሠረት ከማድረግ ባሻገር ርትዕን/የህሊና ፍርድን ታሳቢ ያደረገ፣ ተጎጂዎችን ሊክስ የሚችል ጥራት ያለው ውሳኔን ታሳቢ ያደረገ ነው።
ከፍርድ ቤት የሚጠበቀው ፍትሃዊ ውሳኔ እንጂ ሕጋዊ ውሳኔ አይደለም። በየፍርድ ቤቱ ያሉ ዳኞቻችን የሚሰጧቸው ውሳኔዎች ግን ፍትሃዊ ሳይሆን ሕጋዊ ውሳኔዎች ሆነዋል።
በጥያቄው መሰረት በየፍ/ቤቱ የሚሰጡ ውሰኔዎች ደካማ፣ ሕጋዊ ውሳኔ ብቻ፣ የመወሰን ስልጣን ስላላቸው ብቻ የሰጧቸው ውሳኔዎች ናቸው።
ነገር ግን ፍትህ በመርህ ደረጃ ፈውስ፣ ህክምና፣ ኢንሹራንስ በመሆኑ ያንን ታሳቢ ያደረገ ጥራትና ብቃት ያለው ውሳኔ ሊሰጡ ይገባል።
ለምሳሌ አንድ የፍርድ ውሰኔ የሰጠ ዳኛ ቢጠየቅ ‘ሕጉ ከ5 እክከ 25 ዓመት ስለሚል የተጠቀሰበትን አንቀጽ አይቼ፣ የቀረቀውን ማስረጃ መዝኜ፣ የተከሳሹን የቅጣት ማቅለያ ግምት ውስጥ አስገብቼ ተቀናንሶ 13 ዓመት ወሰንኩበት፤ ምን አጠፋሁ?’ ይላል።
ነገር ግን ኢትዮጵያ ውስጥ በፍርድ ቤቶች በኩል ዳኞች ላይ በጣም መሰራት ያለበት፦ የተጎጂዎቹን እንባ የሚያብስ፣ አጥፊዎችን የሚያርም፣ ሌላውን የሚያስጠነቅቅ ርትዕን ታሳቢ ያደረገ ውሳኔ መስጠት ላይ ነው።
በፍርድ ቤቶች እየተሰጡ የሚስተዋሉት እነዚህ አነስኛ ቅጣቶች ሕጋዊ እንጂ ፍትሃዊ ውሳኔ አይደሉም። ነገር ግን ዳኞቹ በቅጡ አይረዱትም እንጂ የዳኞች ውሳኔ ከሕጋዊ ውሳኔ የላቀ መሆን አለበት። ”
Q. ሰሞኑን የሲዳማ ክልል ፍትህ ቢሮ ያወጣው መረጃ የ9 አመት ልጁን የደፈረው አባት በ17 ዓመት እስራት እንደተቀጣና የሌሎቹንም ወንጀልና የቅጣት ውሳኔ በመጥቀስ፣ በአባቷ፣ በእህቷ ባለቤት የተደፈሩት ህፃናት መደፈር ብቻ ሳይሆን በወላጅና በቅርብ ሰው እንደተደፈሩ ጨምር ነው በአእምሯቸው የሚያቃጭልባቸው። ለመሆኑ የቅጣት ውሳኔው አላነሰም ?
የሕግ ባለሙያ ጥጋቡ ደሳለኝ ፦
“ በአስገድዶ መድፈሩ ተጨማሪ የወንጀል ድርጊት አለ። ለምሳሌ ለህብረተሰቡ ሞራል ተቃራኒ የሆኑ ድርጊቶችን መፈጸም የሚል በወንጀል በህጋችን አለ።
ለህብረተሰቡ ሞራል ተቃራኒ የሆነ ድርጊትን መፈጸም ራሱ ወንጀል ነው። እንግዲህ በተከሳሾቹ ላይ ሁለተኛ ክስ ሆኖ ቀርቦባቸው ይሁን አይሁን ባናውቅም ቢያንስ ግን ሁለት ክስ ሊቀርብ ይገባል።
የወንጀል ሕጉ መከላከል፣ ወላጅ ልጁን እንዳይደፍር የሚያስተምር፣ የሚያስጠነቅቅ ነው ዓላማው። ስለዚህ ቅጣቱ ዝቅ ሲል እድሜ ልክ ከፍ ሲል የሞት ፍርድ ቅጣት ነው የሚያሰጠው። ነገር ግን 17 ዓመት መሆኑ ተገቢነት የለውም።
የባለቤቱን እህት የደፈረውም ለህብረተሰቡ ሞራል ተቃራኒ የሆነ ድርጊት ፈጽሟል። ዝምድና በሁለት አይነት መንገድ ይፈጠራል በቤተሰብ ሕጉ አንድም በመወለድ አንድም በጋብቻ።
በዚህ የመደፈር ወንጀል ጋብቻ አለ። ጋብቻ ካለ ደግሞ ዝምድና ተፈጥሯል። ዝምድና ከተፈጠረ ደግሞ በዘመዳሞች መካከል የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ብቻ ሳይሆን በማህበረሰቡ ገደቦች አሉ።
ነገር ግን ይህን የማህበረሰቡን ወግና ባሕል ጥሶ ተላልፎ አስገድዶ መድፈር በባለቤቱ እህት ላይ ከፈጸመ 14 ዓመት የሚለው ፍርድ ያንሳል። በ23 ዓመት ዝቅ ካለ ደግሞ 20 ዓመት መቀጣት ያስፈልገዋል።
ይህም በቂ ነው እያልኩ አይደለም። እድሜ ልክ እስራት ተገቢ ነው። ግን የሚሰጡት ውሳኔ የዘፈቀደ ነው።
ዳኝነትን ዳኞቻችን እንደሚገነዘቡት ዳኝነት ስራ አይደለም። አገልግሎት ነው እንጂ። ለአገልግሎት የሚሆኑ ጥሩ ሰዎች ተመልምለው ተሹመው በፍርድ ቤት መቀመጥ አለባቸው።
ለሥራ ተብሎ ከሆነ የሚገቡት ሌላ የስራ መስክ መማር አለባቸው። ሰዎች ከስብዕናቸው፣ ከሚኖራቸው ተልዕኮና ጥሪ አንፃር ራሳቸውን መገምገም አለባቸው። ስለዚህ ከላይ የተነሱት ውኔዎች አስተማሪ አይደሉም ማለት ነው። ”
Q. መቼም ዳኞች በተቀመጠላቸው ሕግ መሠረት ነው ፍርድ የሚሰጡት። የቅጣት ውሳኔው ግን አስተማሪ አይደለም። ስለዚህ ችግሩ ያለው ከድንጋጌው አይደለም ? ሕጉ መሻሻል የለበትም?
የሕግ ባለሙያ ጥጋቡ ደሳለኝ ፦
“ የወንጀል ሕጉ ላይ መሻሻል የሚያስፈልጋቸው ነገሮች እየታዩ ነው። አንደኛ ተደራራቢ ወንጀለኞች እየተፈጸሙ ነው። ሁለተኛ ከእስከ (ከ15 ዓመት እስከ 25 ዓመት) የሚለው ስለሰፋ ወንጀለኞችን አላርም አላስተካክል እያለ ነው።
ስለዚህ ከ እስከ የተባለው ነገር ሰፊ ስለሆነ በሴቶችና ሕፃናት ላይ ያለውን ጥቃት ለመቀነስ መሻሻል አለበት ማለት ነው።
የቅጣት መጠኑ ጠንከር ማለት አለበት። ለምሳሌ በእስራት ከሆነ 25 ዓመት ወይም ዕድሜ ልክ ከዚያም ሲያልፍ ደግሞ የሞት ቅጣት ተብሎ አንደዚህ አይነት ነገሮች በወንጀል ሕጉ መሻሻል አለባቸው። ”
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#ሰርገኛ
ከአገር ውስጥም ሆኑ ከውጪ በበጀትዎ መሰረት ፕሮግራሞ የተሳካ እንዲሆን ሙሉ የማማከር አገልግሎት እንዲሁም የፕሮቶኮል ስራ እንሰራለን።
ለድግስዎ አዳራሽ ፣ ምግብ ፣ ዲኮር ፣ መኪና ፣ ዲጄ ፣ ፎቶ እና ሌሎችንም ከፈለጉ በቀላሉ ከሰርገኛ ያገኛሉ! ይደውሉልን! +251976085440 | @ChatSergegna
የማህበራዊ ሚዲያ ገፃችንን ፎሎው በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ! www.sergegna.com
Follow Sergegna 👉🏼 Telegram | Facebook | Instagram | sergegna">Tiktok
@sergegna 💍
#Ethiopia #Somalia
የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ዛሬ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
ለአንድ ቀን ይፋዊ የስራ ጉብኝት ትላንት አዲስ አበባ የገቡት የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ዛሬ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
ወደ ሀገራቸው ሲመለሱም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ቦሌ ኤርፖርት ተገኝተው ሸኝተዋቸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ " በይፋዊ ጉብኝታቸው ወቅት የሁለትዮሽ ግንኙነቶቻችንን ለማጠናከር ውጤታማ ውይይቶች አድርገናል " ብለዋል።
@tikvahethiopia
#Update
እስካሁን ድረስ መቆጣጠር ባልተቻለው የአሜሪካ፣ ሎስ አንጀለስ ሰደድ እሳት ምክንያት ቢያንስ 16 ሰዎች መሞታቸው ሲረጋገጥ ከ137 ሺህ በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል።
የበርካታ ሰዎች ቤት ወደ አመድነት ተቀይሯል።
ሰደድ እሳቱ ያደረሰው ውድመት 135 ቢሊዮን ዶላር እንደሆነ የተገመተ ሲሆን ከዚህም ከፍ እንደሚል ይጠበቃል።
እሳቱን ለመቆጣጠር የሚደረገው ጥረት ቢቀጥልም ዝነኛ ወደሆነውና የአሜሪካ ፊልሞችና የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ወደሚሰሩበት " ሆሊዉድ " እየተቃረበ ነው ተብሏል።
በቀጣይ ቀናት ምን ሊከሰት እንደሚችል በእርግጠኛነት መተንበይ ባይቻልም ነዋሪዎች ለቀው እንዲወጡ ወይም ለመውጣት እንዲዘጋጁ እንደተነገራቸው ቢቢሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት
ከተሻሻለው የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክን ለመቆጣጠር የወጣው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ፦
➡ ከፖሊስ በተሽከርካሪ ላይ የደረሰውን የጉዳት አይነት የሚገልጽ የፅሁፍ ማስረጃ ሳይቀበሉ ጥገና የሚያከናውኑ ጋራዦች / የጋራዥ ባለቤቶች / በወንጀል ህግ የሚጠየቁት እንዳለ ሆኑ የ20 ሺህ ብር ቅጣት ይጣልባቸዋል።
➡ አመታዊ የተሽከርካሪ ምርመራ ያላደረገ የተሽከርካሪ ባለንብረት 3,000 ብር ይቀጣል።
➡ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ሳይኖረው ተሽከርካሪ ያሽከረከረ ማንኛውም ሰው 5,000 ብር ይቀጣል።
➡ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ሳይኖረው ተሽከርካሪ በማሽከርከር በንብረት ላይ ጉዳት ያደረሰ ማንኛውም ሰው 7000 ብር ይቀጣል።
➡ ከባለቤትነት ወይም በይዞታው የተያዘውን ተሽከርካሪ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ለሌላው ሰው አሳልፎ የሰጠ ማንኛውም የተሸከርካሪ ባለንብረት 3,000 ብር ይቀጣል።
🚨የትራፊክ ግጭት ወይም ጉዳት አድርሶ በቦታው ላይ ያልቆመ ወይም ባደረሰው የትራፊክ ጉዳት የተጎዳውን እና ሕክምና የሚያስፈልገውን ሰው ወደ ህክምና በመውሰድ እንዲታከም ያላደረገ 👉 በወንጀል ህጉ መሰረት ይጠየቃል።
➡ ወጣት አሽከርካሪዎች፣ ጀማሪ አሽከርካሪዎች ፣ ሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎች ፣ የንግድ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች እና አደገኛ ጭነት የጫኑ አሽከርካሪዎች የአልኮል መጠን በትንፋሽ በየትኛውም መጠን ከተገኘ 2,000 ብር ቅጣት ይጠብቃቸዋል።
➡ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ታግዶበት ሳለ ያሽከረከረ 3,000 ብር ቅጣት ይጣልበታል።
➡ አልኮል መጠን በትንፋሽ ውስጥ ፦
🍻 0.24 እስከ 0.6 ሚሊግራም/ሊትር 1,500 ብር ያስቀጣል።
🍻 0.61 እስከ 0.8 ሚሊግራም /ሊትር 2,000 ብር ያስቀጣል።
🍻 0.81 እስከ 1.0 ሚሊግራም/ሊትር 2,000 ብር ያስቀጣል።
🍻 1.0 ሚሊግራም/ሊትር በላይ የተገኘበት 3,000 ብር ይቀጣል።
➡ በተሽከርካሪ ላይ ተገቢ ያልሆነ አካል የጨመረ ወይም ከተፈቀደለት ወንበር ውጭ ተጨማሪ ወንበር ወይም መቀመጫ የጨመረ የተሽከርካሪ ባለንብረት 400 ብር ይቀጣል።
➡ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ሞተር እየሰራና በተሽከርካሪው ውስጥ መንገደኞች እያሉ ነዳጅ መሙላት 1,500 ብር ያስቅጣል።
➡ ቴሌቪዥን ወይም ሌሎች ምስሎችን ተሽከርካሪ ውስጥ እየተመለከተ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።
➡ የደህንነት ቀበቶ ሳያስር ወይም ተሳፋሪዎች የደህንነት ቀበቶ ማሰራቸውን ሳያረጋግጥ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።
➡ የተንቀሳቃሽ ስልክ በእጁ ይዞ እያነጋገረ፣ ወይም መልዕክት እየጻፈ እየላከ ወይም እያነበበ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።
➡ ጫት ቅሞ ወይም እየቃመ ወይም አደንዛዥ ዕፅ ወስዶ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።
➡ የተሽከርካሪ የፊት ወይም የኃላ ሰሌዳ ሳይኖረው ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።
➡ ለአውቶብስ ብቻ ተብሎ በተለየ መንገድ ላይ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።
➡ ቀይ መብራት የጣሰ 1,500 ብር ይቀጣል።
➡ የትራፊክ ተቆጣጣሪ ትዕዛዝ ያልፈጸመ፣ ወይም የተሳሳተ መረጃ የሰጠ ወይም እንዲቆም ሲታዘዝ በእንቢተኝነት ሳይቆም የሄደ 1,000 ብር ይቀጣል።
➡ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ኖሮት ሳይዝ ያሽከረከረ ወይም የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃዱን ሳያሳድስ ያሽከረከረ 1,000 ብር ይቀጣል።
➡ ከተፈቀደው ፍጥናት በታች ያሽከረከረ ወይም የቀኙን ጠርዝ ሳይዝ በዝግታ ያሽከረከረ 1,000 ብር ይቀጣል።
➡ ከመጠን በላይ ድምጽ እያሰማ ወይም የጆሮ ማዳመጫ እያዳመጠ ያሽከረከረ 1,000 ብር ይቀጣል።
➡ መንገድ ላይ ያለን ውሃ በተሽከርካሪው አማካኝነት እግረኛ ላይ እንዲረጭ ያደረገ 1,000 ብር ይቀጣል።
(ተጨማሪ የጥፋት ዝርዝር እና ቅጣቶቹን ከላይ ያንብቡ)
@tikvahethiopia
#ያንብቡ
የተሻሻለው የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክን ለመቆጣጠር የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ከላይ ተያይዛል።
(ዝቅ ያለ የፋይል ጥራት 7.4 ሜጋባይት)
ምንጭ ፦ የትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን
@tikvahethiopia
#Earthquake
" ቅልጥ አለቱ ባለፈው መስከረም ሲጀመር እስከ 10 ኪሎ ሜትር ነበር፤ በመሀል ቆም ብሎ ነበር፤ አሁን ግን እስከ 50 ኪሎ ሜትር አዳርሷል " - ኤሊያስ ሌዊ (ዶ/ር)
በፈንታሌ እና በዶፈን ተራራዎች መካከል መሬት ውስጥ ያለው ቅልጥ አለት ወደ ሰሜን ምስራቅ 50 ኪሎ ሜትር ማዳረሱ ተነግሯል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂዮ ፊዝክስ፣ ስፔስ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ኤሊያስ ሌዊ (ዶ/ር) ምን አሉ ?
(ለብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ የሰጡት ቃል)
" በተራራዎቹ መካከል መሬት ውስጥ ያለው ቅልጥ አለት ወደ ሰሜን ምስራቅ 50 ኪሎ ሜትር አዳርሷል።
የርዕደ መሬቱ መነሻ በሁለቱ ተራራዎች መካከል ያለ ነው።
የንዝረቱ መጠን ቢለያየም አዲስ አበባ፣ አዳማ፣ አዋሽ፣ መተሀራ እና ደብረ ብርሃን ድረስ ተሰምቷል።
በአዋሻ አርባ፣ በሳቡሬ፣ በመተሀራ ከተሞችና አካባቢዎቻቸው የንዝረት መጠኑ ከፍተኛ ነው።
ከፈንታሌ ወደ ዶፈን ባለው አቅጣጫ የውስጥ ለውስጥ ቅልጥ አለቱ ባለፈው መስከረም ሲጀመር እስከ 10 ኪሎ ሜትር ነበር፤ በመሀል ቆም ብሎ ነበር፤ አሁን ግን እስከ 50 ኪሎ ሜትር አዳርሷል።
አዲስ አበባን ጨምሮ እየተከሰተ ያለው የንዝረት መጠን መነሻው በተራራዎቹ አካባቢ ነው በተለይም እዛው አካባቢ ቤቶችን እና ህንፃዎችን ሊያፈርስ ይችላል።
ቅልጥ አለቱ መሬት ውስጥ ሊቀር ይችላል በተቃራኒው ደግሞ እሳተ ገሞራ በማንኛውም ሰዓት ወደ ገፀ መሬት ሊወጣ የሚችልበት ዕድልም ስላለ ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል።
በአካባቢው የፈላ ውሃ ፈንድቶ ፍል ውሃው ስብርባሪ ድንጋይ ይዞ ወደ ላይ እየወጣ ነው ወደ ላይ የሚፈነዳው ውሃ ከፍተኛ ሙቀት ያለው፣ ሰልፈር ዳይኦክሳይድና ሌሎች መርዛማ ጋዞችን የያዘ በመሆኑ ለሰው ልጆች ጤና አደገኛ ነው።
የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የስነ ምድር ክፍል ቡድን ሰሞኑን እየወጣ ባለው ፍል ውሃ ባደረገው የናሙና ምርመራ፤ ውሃው ለእንስሳትም፣ ለሰው ልጅም አገልግሎት የማይሆን በመሆኑ ህብረተሰቡ ሊጠቀመው አይገባም።
የሰዎች ወደ ፍንዳታው ሥፍራ መጠጋት ችግር ሊያስከትል ስለሚችል ማህበረሰቡ በተቻለ መጠን ከአካባቢው ራቅ ማለት አለበት። "
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ኢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ኢትዮጵያ መጥተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድን ተቀብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት " የሶማሊያ ፌዴራል ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድ ይፋዊ ጉብኝት ለማድረግ እንኳን ወደ ኢትዮጵያ መጡ እላለሁ " ብለዋል።
ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በቱርክ አንካራ ስምምነት ከተፈራረሙ በኃላ በመካከላቸው ተፈጥሮ የነበረው መቃቃር እየለዘበ መምጣቱ ይታወቃል።
ከዚህ ቀደም ከፍተኛ የሀገሪቱ ባለስልጣናት ኢትዮጵያ መጥተው እንደነበር ይታወሳል።
ዛሬ ደግሞ ፕሬዝዳንቱ ኢትዮጵያ መጥተዋል።
@tikvahethiopia
" በትግራይ ክልል የምትገኙ የሃይማኖት አባቶች መበደላችሁን እናውቃለን ፣ በኀዘናችሁ ሰዓት አብረን መቆም ባለመቻላችን ማዘናችሁም እርግጥና ተገቢ ነው። ነገር ግን ሁሉም ነገር የሚካሰው በእርቅ ሲሆን እኛ የገፋነውን እርቅ ዓለም ሊቀበለው ስለማይችል፤ በእጃችንም የያዝነው መስቀለ ክርስቶስ የሰላም ዓርማ ነውና ልባችሁን ለሰላም፣ ለአንድነት እንድታዘጋጁ እንጠይቃለን " - ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
@tikvahethiopia
ወጋገን ባንክ ደንበኞች የሞባይል ዋሌት አገልግሎት ከኢ-ብር ሞባይል ፋይናንሻል ሰርቪስስ ጋር በመተባበር መስጠት ጀምሯል። አገልግሎቱ የባንክ ሂሳብ የሌላቸው ግለሰቦችንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው።
ባንኩ አገልግሎቱን ያስተዋወቀው በሽረ ከተማ በርካታ ደንበኞች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ነው።
የባንኩ የኢንተርፕራይዝ ሰርቪስስ ም/ሥራ አስፈፃሚ አቶ የኋላሸት ዘውዱ የወጋገን ኢ-ብር የሞባይል ዋሌት አገልግሎት ደንበኞች ካሉበት ሆነው በማንኛውም ጊዜ ገንዘብ ማስተላለፍ እና ክፍያ መፈፀም እንደሚያስችላቸው ገልፀዋል፡፡
የኢ-ብር ሞባይል ፋይናንሻል ሰርቪስስ ቦርድ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ በዕውቀት ታፈረ በበኩላቸው ባንኮች ከቴክኖሎጂ አቅራቢ ባለድርሻ አካላት ጋር የሚያደርጉት ትብብር የባንክ ኢንዱስትሪውን ለማዘመን የሚያግዝ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የወጋገን ኢ-ብር የሞባይል ዋሌት አገልግሎት ከፕሌይ ስቶር ወይም አፕ ስቶር የኢ-ብር መተግበሪያውን በማውረድ ወይም ወደ *602# በመደወል ደንበኞች በቅድሚያ ወጋገን ባንክን በመምረጥ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡
https://linktr.ee/WegagenBank
#ሹመት : ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር) የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሀን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሹመትን አስመልክቶ የቀረበለትን የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ በአንድ ድምፀ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል።
በዚሁ መሠረት ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር) የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሹመዋል።
ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር) ማናቸው ?
➡️ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የስትራቴጂክ ኮሚዩኒኬሽን እና አለምአቀፋዊነት ጽህፈት ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ሲሰሩ ቆይተዋል።
➡️ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በጋዜጠኝነት እና ተግባቦት የትምህርት ዘርፍ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ አግኝተዋል።
➡️ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተማሩበት የትምህርት ክፍል በአስተማሪነት አገልግለዋል።
➡️ በውጭ ቋንቋዎች የማስተርስ ዲግሪ ባገኙበት አምቦ ዩኒቨርስቲ እና በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ አስተምረዋል።
➡️ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የ12 ዓመታት የማስተማር እና የአመራርነት ልምድ አለቸው።
➡️ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ከደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርስቲ (UNISA) በኮሚዩኒኬሽን አግኝተዋል።
➡️ በተለያዩ የምርምር ህትመቶች ላይ የወጡ ጽሁፎችን በግላቸው እና በጋራ አሳትመዋል።
➡️ በብሉምበርግ የአፍሪካ ሚዲያ ኢኒሼቴቭ ስር የሚሰጠውን የፋይናንስ ጋዜጠኝነት ስልጠናን በስራ አስኪያጅነት መርተዋል በሌሎች ተቋማትም በማማከር ስራዎች ተሳትፈዋል።
#HoPR #EthiopiaInsider
@tikvahethiopia
#Earthquake : ዛሬ ሰኞ ምሽት 5:24 ሲል በሬክተር ስኬል 4.8 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ከአዋሽ 17 ኪ/ሜ ርቀት ላይ መከሰቱን የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ አሳውቋል።
የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ አዲስ አበባና ሌሎችም ከተሞች ተሰምቷል።
" አሁን ላይ ቀንሷል ቆሟል ፣ ከአሁን በኃላ ምንም ነገር አይፈጠርም " በሚል መዘናጋት ጥንቃቄ እና ትኩረት ማጣት እንዳይመጣ መጠንቀቅ ይገባል።
የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተት ቅፅበታዊ ፣ ተገማች ያልሆነና መተንበይ የማይቻል ነገር በመሆኑ ዘውትር ነቅቶ መጠበቁ የተሻለ ነው።
@tikvahethiopia
#Update
የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ዛሬ ጥር 5/2017 ዓ.ም ተፈናቃዮች " ይበቃል ወደ ቄያችን መልሱን ! " በሚል የጀመሩትን ሰላማዊ ሰልፍ የሚደግፍ መግለጫ አውጥተዋል።
" ይበቃል ወደ ቄያችን መልሱን በሚል መሪ ቃል በተፈናቃዮች የተጠራው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ቀናና የሚደገፍ " ብሎታል ጊዚያዊ አስተዳደሩ በመግለጫው።
" የተፈናቃዮች መከራ ተገቢ ምላሽ አልተሰጠውም " ያለው መግለጫው " የፌደራል መንግስት የገባው ውል እና ቃል በመተግበር ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው መመለስ አለበት " ሲል በአፅንኦት ገልጿል።
" አሁንም በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት ከአገር መከላከያ ውጪ ያሉ ታጣቂዎች ይውጡ " ሲልም አክሏል።
" በህገ-መንግስቱ ማእቀፍ የትግራይ ግዛታዊ አንድነት ተከብሮ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው መመለስ አለባቸው "ም ብሏል።
" የአፍሪካ ህብረት ፣ የአሜሪካ መንግስት ፣ የአውሮፓ ህብረት እና የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ የህዝቡ ድምፅ በማዳመጥ የፕሪቶሪያ ውል በአግባቡ ተግባራዊ እንዲሆን ጫናቸው እንዲያሳድሩ " ሲልም ጥሪ አቅርቧል።
" ፅላል ስቪክ ማሕበር ማሕበረሰብ ምዕራብ ትግራይ " የተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ማህበር ያስተባበረውና " ይበቃል ! " በሚል መሪ ቃል ዛሬ በመቐለ ሮማናት አደባባይ መንገድ በመዝጋት የተጀመረው የተፈናቀዮች ሰላማዊ ሰልፍ እስከ ጥር 7/2017 ዓ.ም እንደሚቀጥል ታውቋል።
ዛሬ በርካታ የመቐለ ጎዳናዎች ተዘግተው በርካታ የፖሊስ አባላትም ተሰማርተው ነው የዋሉት።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" መላው የሎስ አንጀለስ ግዛት በእሳት ስጋት ውስጥ ይገኛል " - ባለስልጣናት
በአሜሪካ ፤ ሎስ አንጀለስ የተነሳው ሰደድ እሳት አሁንም መቆጣጠር ያልተቻለ ሲሆን የሟቾች ቁጥርም ወደ 24 ከፍ ብሏል። 16 ሰዎች ደግሞ የገቡበት አይታወቅም።
በሎስ አንጀለስ ዙሪያ 3 አካባቢዎች መቃጠላቸውን ቀጥለዋል።
በአሁኑ ላይ ትልቁ እሣት ሚገኘው በፓሊሳድስ ሲሆን 9307 ሔክታር መሬትን ሲያቃጥል 11 በመቶውን መቆጣጠር ተችሏል።
የኢቶን እሳት በትልቅነቱ 2ኛ ደረጃ ሲይዝ ከ5665 ሔክታር በላይ አቃጥሏል። 27 በመቶው በቁጥጥር ስር ውሏል።
ከሞላ ጎደል በቁጥጥር ስር በዋለው በሃረስት እሳት 323 ሄክታር መሬት መቃጠሉ ታውቋል።
የእሳት አደጋ ሠራተኞች ትልቁን እሳት መቆጣጠር ቢጀምሩም ባለስልጣናት ግን ቀጣዮቹ ንፋሶች " አደጋ ሊያስከትሉ የሚችሉ የንፋስ ሁኔታዎች ሊሆኑ ይችላሉ መላው የሎስ አንጀለስ ግዛት በእሳት ስጋት ውስጥ ይገኛል " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
እሳቱ በአሜሪካ ታሪክ አውዳሚው ለመሆን መቃረቡ ተገልጿል።
የግል ትንበያ ተቋም የሆነው " አኩዌዘር " በእሳት ቃጠሎ የተነሳ የደረሰው ኪሳራ ግምት ከ250 እስከ 275 ቢሊዮን ዶላር ሊደርስ ይችላል ብሏል።
ለሌላ በኩል ፥ የአደጋ ቀጠና ከሆኑ ቦታዎች ሰዎች እንዲወጡ የታዘዘ ሲሆን የወጡም አሉ።
ነዋሪዎች እንዲወጡ በታዘዙባቸው አካባቢዎች ዝርፊያ ሲፈፅሙ የነበሩ 29 ሰዎች መታሰራቸው ተነግሯል።
ሰዎች ቤታቸው ለቀው ሲወጡ ሲዘርፉ የነበሩ በርካቶች ነበሩ።
ከዚህ ባለፈ ፥ በሰደድ እሳቱን ምክንያት አከራዮች በህገወጥ መንገድ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ላይ ከፍተኛ የሆነ ጭማሬ ማድረጋቸው ተነግሯል።
እሳቱን ተከትሎ ከዚህ ቀደም ይጠየቅበት ከነበረው የቤት ኪራይ በሺዎች በመጨመር እንደተጠየቁ አንዳንዶች ገልጸዋል።
በሰደድ እሳቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ቤታቸው አመድ ሆኗል። በርካታ የተፈናቀሉ ተጎጂዎች " የማይቀምስ የቤት ኪራይ እና የሆቴል ክፍያ እየተጠየቅን ነው " ማለታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የኢትዮ ቴሌኮም የቀጥታ ድርሻ ባለቤትነት ዕድል የካቲት 7 ያበቃል!
💁♂️ የአክሲዮን ሽያጩ በቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ይከናወናል፤ እርስዎም የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተጋብዘዋል፡፡
🗓 እስከ የካቲት 07/2017 ዓ.ም ብቻ!
📖 የደንበኛ ሳቢ መግለጫውን https://teleshares.ethiotelecom.et/ ያንብቡ፡፡
ለተጨማሪ መረጃ ወደ 128 ይደውሉ!
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
" ያልተመዘገበ ተማሪ አይፈተንም " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
የ2ዐ17 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ / የ12ኛ ክፍል ፈተና ምዝገባ መጪ ማክሰኞ ጥር 6 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ላይ እንደሚጠናቀቅ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
በተለያየ ምክንያት ያልተመዘገቡ ካሉ በእነዚህ ቀሪ ሁለት ቀናት ላይ ብቻ እንዲመዘገቡ ያሳሰበ ሲሆን " ያልተመዘገበ አይፈተንም " ብሏል።
@tikvahethiopia
ዮናታን ቢቲ ፈርኒቸር !
በዓሉን አስመልክቶ የተደርገው ልዩ ቅናሽ ሳያመልጥዎ እነዚህን ውብ እቃዎች የግልዎ ያድርጉ።
🌐 የማህበራዊ ገጾቻችንን ይቀላለቀሉ
Telegram 👉 Telegram/yonatanbtfurniture
Facebook 👉 Facebook/yonatanbtfurniture
Instagram 👉 Instagram/yonatanbtfurniture
TikTok 👉 yonatanbtfurniture?is_from_webapp=1&sender_device=pc">TikTok/yonatanbtfurniture
📍አድራሻችን
1. ፒያሳ እሪ በከንቱ ቢቲ ታወር (ከኢቲዮ ሴራሚክ ዝቅ ብሎ)
2. ከዊንጌት አደባባይ አለፍ ብሎ ከአቢሲኒያ ባንክ ፊትለፊት
3. ከሲኤምሲ አደባባይ ወደ አያት መንገድ መሪ ሳይደርስ (ዘመን ባንክ አጠገብ)
ስልክ ፦ +251957868686/ +251995272727/ +251993828282
#ተፈጸመ : የጉምቱው ፖለቲከኛና የምጣኔ ሃብት (የኢኮኖሚ) ሊቅ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ስርዓተ ቀብር ተፈጸሟል።
ከስርዓተ ቀብራቸው ቀደም ብሎ በአድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ የአስክሬን ሽኝት ተደርጓል።
@tikvahethiopia
#Update
የጉምቱው ፖለቲከኛ እና የምጣኔ ሃብት (የኢኮኖሚ) ሊቅ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ስርዓተ ቀብር ዛሬ ይፈጸማል።
ከስርዓተ ቀብራቸው ቀደም ብሎ በአድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ የአስክሬን ሽኝት ይደረጋል።
ከሽኝቱ በኋላ ከቀኑ 7:00 ሰዓት ዊንጌት አካባቢ በሚገኘው በጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር ስርዓተ ቀብራቸው ይፈጸማል።
አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ከኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) መስራቾች አንዱ እንደነበሩ የሚታወቅ ሲሆን ፓርቲው መላው ህዝብ በነቂስ ወጥቶ ከቤታቸው ለገጣፎ አንስቶ በሚደረገው ሽኝት እና በስርዓተ ቀብራቸው ላይ እንዲገኝ ጥሪ አቅርቧል።
ኦፌኮ አቶ ብልቻ ደመቅሳን " የሀገር ዋርካ " ሲል ገልጿቸው በህልፈታቸው ሀዘን ላይ መሆኑን ገልጿል።
@tikvahethiopia
#ያንብቡ
የተሻሻለው የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክን ለመቆጣጠር የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ከላይ ተያይዛል።
(ከፍ ያለ የፋይል ጥራት 64.5 ሜጋባይት)
ምንጭ ፦ የትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ መሪዎች በምን ጉዳዮች ላይ መከሩ ፤ ምንስ ተስማሙ ?
የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ዛሬ በአዲስ አበባ የሁለትዮሽ ምክክር አድርገዋል።
ከውይይቱ በኃላ የጋራ መግለጫ ወጥቷል።
ምን ተባለ ?
- በሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።
- በሁለቱ ሀገራት ህዝቦች መካከል ያለውን ወንድማማችነትና ግንኙነት በማጠናከር ላይ ገንቢ ውይይት አድርገዋል።
- የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ወደነበረበት ለመመለስ እና በየመዲኖቻቸው ሙሉ ዲፕሎማሲያዊ ውክል እንዲኖር ለማድረግ ተስማምተዋል።
- መሪዎቹ ለቀጣናው መረጋጋት የሁለቱ ሀገራት የጋራ የእርስ በርስ እምነት ፣ መተማመን እና መከባበር ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ትብብር እንደሚያስፈልግ አረጋግጠዋል።
- ቀጠናዊ ግንኙነቶችን ለማሻሻል፣ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር እና የጋራ እድገትን ለማስቀጠል በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል።
- መሪዎቹ የጸጥታ ትብብር ማስቀጠልና ማጠናከር በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ያተኮረ ውይይት አድርገዋል። በቀጠናው ፅንፈኛ ታጣቂ ሃይሎች እየፈጠሩ ያሉትን አሳሳቢና እየጨመሩ ያሉ ስጋቶችን በመገምገም መሪዎቹ በቀጠናው ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን የሚደረገውን ትብብር ለማጠናከር ለጸጥታ ተቋሞቻቸው መመሪያ ለመስጠት ተስማምተዋል።
- በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ማጠናከር ያለውን ጠቀሜታ ላይ ተወያይተዋል ፤ አጽንኦትም ሰጥተዋል። የበለጠ ጠንካራ ኢኮኖሚያዊ ትብብር በማድረግ የንግድ ልውውጥን ለማሳለጥ እና የጋራ ብልጽግናን ለመፍጠር የመሰረተ ልማት ትስስሮችን ለማስፋት ተስማምተዋል።
- ለአንካራው ስምምነት በጓደኝነት እና በአብሮነት መንፈስ ቁርጠኝነታቸውን ዳግም ያረጋገጡ ሲሆን በስምምነቱ ላይ የታቀዱትን የቴክኒክ ድርድሮችን ለማፋጠንም ተስማምተዋል።
#Ethiopia #Somalia #Peace
@tikvahethiopia
#Earthquake
ከትላንት ለሊት ጀምሮ እስከ ዛሬ ምሽት 12:20 ድረስ አዋሽና አካባቢው ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶች ተመዝግበዋል።
የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶቹ አዲስ አበባ ድረስ ንዝረታቸው ተሰምቷል።
ከትላንት ለሊት ጀምሮ እስከ ዛሬ ምሽት 12:20 ድረስ በተለያየ ጊዜ በሬክተር ስኬል ፦
👉 4.6
👉 4.5
👉 5.2
👉 4.3
👉 5.2 የሆኑ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶች ተመዝግበዋል።
በተለይ 5.2 የተመዘገቡት ሁለቱ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶች ባለፉት ሰዓታት ከተመዘገቡት ከፍተኛው ሲሆኑ በተለይ አንዱና ለሊት ላይ የተከሰተው ሰዎችን ከእንቅልፍ ያባነነ ጭምር ነበር።
አሁንም አዋሽ እና አካባቢው የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቱ ተደጋግሞ እንደቀጠለ ነው።
@tikvahethiopia
ንጉስ ማልት ከምግብ ጋር አቤት ደስስስስስስስስስስስስስስ ማለቱ!
ለተጨማሪ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ /channel/Negus_Malt
#nonalcoholic #ንጉስ #DesDesWithNegus #ደስደስበንጉስ #የጣዕምልኬት_የደስታስሜት#ንጉስማልት
የኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ምን አለ ?
" በትናንቱ እንግዳ የሕዋ ክስተት ዙሪያ ከተለያዩ የሕዋ አካላት መከታተያ እና የመረጃ ቋቶች ያገኘናቸውን መረጃዎች በማጠናቀር ባደረግነው ጥልቅ የሆነ ትንተና መሰረት የሚከተለው ሳይንሳዊ መላምት ላይ ደርሰናል።
በመረጃው መሰረት የሕዋ አካሉ ባለቤትነቱ የቻይና የሆነ ሺ ጂያን-19 (ShiJian-19) የተባለ ሳተላይት ቀሪ አካል ሊሆን እንደሚችል ያመላክታል።
ከዚህም በተጨማሪ የሳተላይቱን ቀሪ አካል የምህዋር እና የይዘት መረጃ ጠቅላላ ትንታኔውን ከላይ አጋርተናል።
ሳተላይቱ በመስከረም 17 ቀን 2017 ዓ.ም ወደ ምህዋር የተወነጨፈ ሲሆን ተልዕኮውን ጨርሶ በጥቅምት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ወደ መሬት ተመልሷል።
ነገር ግን ሳተላይቱ በተልዕኮው ላይ ሲገለገልባቸው የነበሩ የተለያዩ ክፍሎቹ ከዋናው ሳተላይት ተነጥለው በምህዋር ላይ ሲዞሩ ቆይተዋል።
ለትንተናው የተጠቀምናቸው መረጃዎች ከሶስተኛ ወገን የመረጃ ቋቶች የተገኙ በመሆኑ የተረጋገጠ መረጃውን የሳተላይቱ ባለቤት ሃገር ቻይና እስክታረጋግጥ መጠበቅ ይኖርብናል።
ዋቢ ምንጮች ፦ https://www.satcat.com/sats/61506 / http://www.satflare.com/track.asp?q=61506&sid=2#TOP ናቸው "
@tikvahethiopia