tikvahethiopia | Неотсортированное

Telegram-канал tikvahethiopia - TIKVAH-ETHIOPIA

1531512

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ

Подписаться на канал

TIKVAH-ETHIOPIA

" የሚሠሩበት ቦታ የት እንደሆነ በግልጽ የማይታወቅ በመሆኑ፣ ዕርምጃ ለመውሰድ ተቸግረናል " - ባለስልጣን መ/ቤቱ

" ዘመናዊና ባህላዊ የሕክምና አገልግሎት እንሰጣለን " ብለው በተለያዩ ማኅበራዊ ድረ ገጾች ማስታወቂያ የሚያስነግሩ የተደራጁ ሕገወጥ ግለሰቦች መበራከታቸውንና ለቁጥጥር ፈታኝ እንደሆኑበት፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣን አስታውቋል።

መ/ቤቱ ፤ የዘመናዊና ባህላዊ ሕክምና አገልግሎት በተመለከተ የሚተላለፉ ማስታወቂያዎች የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣንና የምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣን ፈቃድ ሳይሰጡ ማስታወቂያ ማስተላለፍ እንደማይቻል በሕግ ተቀምጧል ብሏል።

በርካታ የተደራጁ ቡድኖች ግን ኢኮኖሚያቸውን ለማሳደግና ከሌሎች የሕክምና ተቋማት የበለጠ የተሻለ መሆናቸውን ለማሳየት በጣም የተጋነነ ማስታወቂያ እንደሚያስተላልፉ አሳውቋል።

ዘመናዊና ባህላዊ የሕክምና አገልግሎት እንሰጣለን በሚል የተሳሳተ ማስታወቂያ ምክንያት፣ ሰዎች የሕክምና አገልግሎቱን እንሞክረው ብለው የተሳሳተ ነገር ውስጥ እንደሚገቡና ችግሩን ባለሥልጣኑ መቆጣጠር እንዳልቻለ አሳውቋል።

ችግሩ ትክክለኛ የሆነ የሕክምና አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትን እንዲመረዙ የሚያደርግ መሆኑን፣ እስካሁን የባህል ሕክምና አገልግሎት ለሚሰጡ 93 ተቋማት ባለሥልጣኑ መመዝገብ መቻሉን ጠቁሟል።

በሕገወጥ መንገድ ማስታወቂያ የሚያስተላልፉ የተደራጁ ቡድኖች የሚሠሩበት ቦታ የት እንደሆነ በግልጽ የማይታወቅ በመሆኑ፣ ዕርምጃ ለመውሰድ መቸገሩን መ/ቤቱ ገልጿል።

የባህል ሕክምና አዋቂዎች ማኅበር በበኩሉ ፤ የተለያዩ የሕክምና አገልግሎቶችን እንሰጣለን ብለው የተሳሳተ ማስታወቂያ የሚያስነግሩ ሰዎች አድራሻም ቢሮም እንደሌላቸው ገልጿል።

በማኅበር ሥር ሆነው የባህል ሕክምና አገልግሎት የሚሰጡት ግን፣ የተለያዩ ሥልጠናዎችን የሚወስዱና ባለሥልጣኑም ሆነ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ያስቀመጡትን ሕግና ሥርዓት ተከትለው እንደሚሠሩ ገልጿል።

ዘመናዊና ባህላዊ የሕክምና አገልግሎት እንሰጣለን ብለው ማስታወቂያ የሚያስነግሩ ግለሰቦች ማኅበሩን እንደማይወክሉ ለማሳወቅ፣ ማኅበሩ ለአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽንና ለሚመለከታቸው አካላት ደብዳቤ ጽፎ ማስገባቱን አስታውቋል።

የባህል ሕክምና አገልግሎት አሰጣጥ ከበፊት ጀምሮ ያለና ወደፊትም የሚኖር ነው ሲል የጠቆመው ማኅበሩ ፤ ከዚህ ቀደም የተሻለ የሕክምና አገልግሎት እንሰጣለን ብለው ማስታወቂያ ባስነገሩ ሰዎች ገንዘባቸውን የተዘረፉ ሰዎች ለማኅበሩ ቅሬታ ማቅረባቸውን አስታውሷል።

አንድ የባህል ሕክምና አገልግሎት የሚሰጥ የሕክምና ባለሙያ በማኅበራዊ ድረ ገጽም ሆነ በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ማስታወቂያ እንዲያስነግር ማኅበሩ ፈቃድ እንደማይሰጥ፣ የመስጠትም ሥልጣን እንደሌለው አክሏል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Mekelle

" ህዝቡ ከገባበት የጦርነት ጦስ እንዲያንሰራራ ከመምራት ይልቅ ለስልጣናቸው ብቻ ሲሯሯጡ የህዝቡን ስቃይ እጅግ መራራ አድርገውታል " - ተገልጋይ

በትግራይ ክልል ፣ መቐለ ከተማ በሁለቱ የህወሓት ቡድኖች የተመደቡ ከንቲባዎች በስራ ገበታ የሉም ፤ የከንቲባ ፅህፈት ቤት ታሽጎ በፀጥታ ሃይሎች ጥበቃ ስር ይገኛል።

ተገልጋዮች ከከንቲባ ማግኘት ያለባቸው አገልግሎት ለማግኘት ቢመላለሱም የሚያስተናግዳቸው የለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ዛሬ ማክሰኞ ታህሳስ 8/2017 ዓ.ም ጠዋት መቐለ አስተዳደር ፅህፈት ቅጥር ግቢ ድረስ ተጉዞ አጭር ምልከታ አደርጓል።

በአስተዳደሩ ዋና በር በቁጥራቸው አነስተኛ የሆኑ ተገለግጋሎች ሲገቡ ሲወጡ ይታዩሉ ፤ ፍትሻ በሚካሄድበት ቦታ ከተለመደው በተለየ ብዛት ያላቸው የፀጥታ አካላት ይስተዋላሉ።

5ኛ ፎቅ ላይ የሚገኘው የዋና ከንቲባ ፅህፈት ቢሮ  (ከህዳር 22/2017 ዓ.ም ) እንደታሸገ ሆኖ ግራና ቀኝ የፓሊስ ደንብ ልብስ በለበሱ የፀጥታ አካላት ይጠበቃል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከከንቲባ የሚሰጥ አገልግሎት ለማግኘት ከአንድ ወር በላይ የተመላለሰ ተገልጋይ አግኝቶ አስተያየቱ ተቀብሏል።

ተልጋዩ ፀጋዛኣብ ርእሰደብሪ ይባላል የመቐለ ቀዳማይ ወያነ ክፍለ ከተማ ነዋሪ ነው።

ያለውን የመሬት ጉዳይ አስመልክቶ ከንቲባ አግኝቶ ለማነጋገር ቢመላለስም እስካሁን እንዳልተሳከለት ገልጿል።

" በሁለቱም በኩል ያሉ የህወሓት አመራሮች ማሰብ ተሰኗቸዋል ? ፤ ህዝቡ ከገባበት የጦርነት ጦስ እንዲያንሰራራ ከመምራት ይልቅ ለስልጣናቸው ብቻ ሲሯሯጡ የህዝቡን ስቃይ እጅግ መራራ አድርገውታል " ሲል በምሬት ተናግሯል።

ካለፈው ወርሀ ነሃሴ 2017 ዓ.ም ጀምሮ በይፋ ወደ ሁለት ቡድን መሰንጠቃቸው ያወጁት የደረብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) እና የአቶ ጌታቸው ረዳ ቡድን በየፊናቸው በየቦታው አመራር በመመደብና በመገለጫዎች መወራረፍ ቀጥለውበታል።

ባለፈው ወርሃ ጥቅምት 2017 ዓ.ም የቀድሞ ከንቲባ ይትባረክ ኣምሃ ተክቶ በደረብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ህወሓት እጩ አቅራቢነት በከተማው ምክር ቤት ከንቲባ ሆነው የተሾሙት ረዳአ በርሀ (ዶ/ር) በጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ወድያውኑ ተቀባይነት ማጣታቸው ተከትሎ ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም ብርሃነ ገ/የሱስ በጊዚያዊ አስተዳደሩ ተሹመዋል።

በጊዚያዊ አስተዳደሩ ከንቲባ ሆነው የተሸሙት ብርሃነ ገ/የሱስ ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም በፅህፈት ቤቱና በክፍለ ከተሞች አመራሮች በቅጥር ግቢው በሚገኘው የመሰብሰብያ አዳራሽ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጨምሮ ሚድያዎች በተገኙበት አቀባበል ቢደረግላቸውም ከነጋታው ጀምሮ ይህ ዜና አስከተጠናቀረበት ሰዓት ተመልሰው ቢሮ አልገቡም።

በወርሃ ጥቅምት 2017 ዓ.ም የተሾሙት ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) እንዲሁም ቢሮ ላይ የሉም።

በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ምክር ቤቶች በመጠቀም ፤ በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት ደግሞ በጊዚያዊ አስተዳደሩ " በተሰጠኝ ስልጣን መሰረት " በማለት መቐለ ጨምሮ በትግራይ ስድስት ዞኖች የየራሳቸው አስተዳዳሪዎች በመሾም ህዝቡን ግራ አጋብተውታል።

ይህንን መሰል ግራ የገባው የሁለቱ የህወሓት ቡድኖች አካሄድ ማብቅያው መቼ ይሆን ? የብዙዎች ጥያቄ ነው።

#TikvahEthiopiaMekelleFamily

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ለጥንቃቄ

በጥንቃቄ ጉድለት ሊደርሱ የሚችሉ የተለያዩ ድንገተኛ አደጋዎች እንዳይከሰቱ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል ሲል የአዲስ አበባ እሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን መልዕክት አስተላልፏል።

ኮሚሽኑ ፤ በሰው ልጅ ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት ከሚያደርሱ ድንገተኛ አደጋዎች መካከል አብዛኞቹ በጥንቃቄ ጉድለትና በመዘናጋት የሚከሰቱ ናቸው ብሏል።

በመሆኑም ለአደጋ መንስኤ የሚሆኑ የአሰራርና የአጠቃቀም ግድፈቶችን በማስወገድ ህይወትንና ንብረትን ከጉዳት ለመታደግ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ተግባራት ማከናወን እንደሚገባ ገልጿል።

➡️ በምግብ ማብሰያ /ማዕድቤት/ አካባቢ የኤሌክትሪክ፣ የቡታ ጋዝ፣ የጧፍና የከሰል ምድጃዎችን በአግባቡና በጥንቃቄ ይጠቀሙ።

➡️ በገበያ ማእከላት የገበያተኛውን ቀልብ ለመሳብ የሚጠቀሙባቸው የኤሌክትሮኒክስ ዲኮሬሽኖች ቃጠሎ እንዳያስነሱ ይጠንቀቁ።

➡️ ሻማና ጧፍ በሚጠቀሙበት ወቅት ከተቀጣጣይ ነገር ያርቁት።

➡️ ካም ፋየር የሚያዘጋጁ ከሆነ ከአካባቢው ከመራቅዎ በፊት በደንብ መጥፋቱን ያረጋግጡ።

➡️ በኤሌክትሪክ እሳት የተነሳ እሳትን ሃይሉን ከምንጩ ሳያቋርጡ በወሃ ለማጥፋት አይሞክሩ።

➡️ ርችቶችን ሲተኩሱ በነዳጅ ማደያ ፣ በሳር ቤቶችና በሌሎች ተቀጣጣይ ነገሮች ላይ እንዳያርፍ ይጠንቀቁ።

➡️ ጠጥተው አያሽከርክሩ ለመዝናናትዎ በገደብ ይስጡ።

➡️ በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሰሩ የተለያዩ መሳሪያዎች በአንድ ሶኬት ላይ ደራርበው አይጠቀሙ።

➡️ ለአደጋ መንስኤ ሊሆኑ የሚችሉ ነገሮችን በማስወገድ/በመፍታት የሰው ህይዎትን እና ንብረትን መታደግ ያስፈልጋል።

ኮሚሽኑ ከአቅም በላይ ለሆነ ማንኛውም የእሳትና ሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች እንዲሁም የአምቡላንስ አገልግሎትን በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች ሳምንቱን ሙሉ 24 ሰዓት በመደወል ማግኘት እንደሚቻል አሳውቋል።

° ነፃ የስልክ መስመር 👉 939
° ማዕከል 0111568601/0111555300

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ሐኪሞቹ ' መግቧቸው፤ የምግብ እጥረት ነው ' ይላሉ። እኛ ደግሞ ከየት እናመጣዋለን ? ጊዜው ከፋብን " - እናት

በአማራ ክልል፣ ሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ በተከሰተ ድርቅ እና የምግብ እጥረት ከአምስት ዓመት በታች ያሉ ህፃናትን ጨምሮ 10 ሺህ የሚሆኑ ሰዎች መጎዳታቸውን ወረዳው አስታውቋል።

በክልሉ ባለው ግጭት እና ተፈጥሯዊ ተፅዕኖ ምክንያት ወረዳው ለድርቅ እና የምግብ እጥረት መጋለጡን የቡግና ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ገ/መስቀል ዓለሙ ተናግረዋል።

በአማራ ክልል የተነሳው ግጭት አንድ ዓመት ከመንፈቅ ያለፈው ሲሆን ከግጭቱ ባለፈ ወረዳው " ዝናብ አጠር እና በተፈጥሮ የተጎዳ ነው " ያሉት ኃላፊው በተደራራቢ ችግሮች ምክንያት የምግብ እጥረት መከሰቱን አስታውቀዋል።

" ማኅበረሰቡ ምርት ባለማግኘቱ እናቶች ልጆቻቸውን በአግባቡ መግበው የተሻለ የጤና እድገት እንዳይኖራቸው አድርጓል " ሲሉ ተፈጥሯዊውን ተጽዕኖ ገልጸዋል።

" ረድኤት ድርጅቶችም ለማኅበረሰቡ አልደረሱለትም " ብለዋል።

በወረዳው ብርኮ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ የካባ የአንድ ዓመት ከሦስት ወር መንታ ወንድና ሴት ልጆቻቸው በምግብ እጥረት " ስቃይ " ውስጥ እንደሆኑ ተናግረዋል።

" ምን አግኝተን እንርዳቸው ? እስካሁን ድረስ በተቻለን ይዘናቸው ነበር። ከአዲስ ዓመት ወዲህ ግን ምንም ነገር የለም። ተያይዞ ቁልጭልጭ ሆነ እኮ? " ሲሉ አስረድተዋል።

" ጡጦ የምልበት ጎን አቅም የለኝም። ጡቴን ብቻ ነው ሳጠባቸው የከረምኩት። የጡት ወተት አሁን አነሳቸው፤ እንዴት ይድረሳቸው ?. . . የተገኘው ምግብም አልሆናቸው አለ፤ አልስማማቸው አለ "ብለዋል።

ጠላ በመሸጥ ይተዳደሩ ነበሩት ወ/ሮ የካባ ልጆቻቸው ሲታመሙ ስራ እንዳቆሙ ይናገራሉ።

ከቤተሰቦቻቸው ያገኙት የነበረውን የምግብ ድጋፍ በማጣታቸው መቸገራቸውንም ያስረዳሉ።

" ሐኪሞቹ ' መግቧቸው፤ የምግብ እጥረት ነው ' ይላሉ። እኛ ደግሞ ከየት እናመጣዋለን ? ጊዜው ከፋብን። መሬቱ ደረቀ ፤ እናት አባት አንድ ሁለት ኬሻ እህል ይሰጡን ነበር። ከዛ ብሶም ዘመኑ አጠፋው " ሲሉ እርሳቸውም በቂ ምግብ ባለማግኘታቸው ሕፃናት ልጆቻቸው እየተጎዱ እንደሆነ ገልፀዋል።

አንድ የአካባቢው የጤና ባለሞያ " ጤና ጣቢያ የሚመጡት እናቶች ከሚያጠቡት ልጅ ይልቅ እነርሱ ራሱ የከሱ ናቸው " ብለዋል።

እርሻቸውን በረዶ እንደመታባቸው የሚናገሩት የወረዳው ነዋሪ አቶ ደሳለው አለባቸውም ፤ ባለቤታቸው እና የ10 ወር መንታ ልጆቻቸው በምግብ እጥረት ተጎድተው ጤና ጣቢያ መግባታቸውን ተናግረዋል።

ባቄላ፣ ገብስ እና ጤፍ ያመርቱ እንደነበር የተናገሩት አቶ ደሳለው፤ " እናት የምትበላው የላትም፤ ልጆቹም የሚጠቡት የለም " ሲሉ ዘንድሮ " የተለየ " ችግር ገጥሞናል ብለዋል።

" በጣም ሲብስብን፤ ሲጨንቀን ወደ ጤና ጣቢያ አመጣናቸው። ሁለተኛ ቀናችን ነው። . . .የምግብ እጥረት ስላለባቸው ተዳክመዋል፤ ከስተዋል" ሲሉ ልጆቻቸው ያሉበትን ሁኔታ ገልጸዋል።

አይና ጤና ጣቢያ ኃላፊ አቶ መኮንን አሻግሬ አካባቢው ካለበት ተፈጥሯዊ ችግር በተጨማሪ ከአዲሱ በጀት ዓመት በኋላ የተመጣጠነ የምግብ ላይ የሚሰሩ ረድኤት ድርጅቶች ግብዓት ማቆማቸውን አሳውቀዋል።

አንድ የጤና ባለሞያም ወረዳው የምግብ እጥረት ችግር ያለበት መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይ ካለፈው ዓመት ሐምሌ ወር ጀምሮ ችግሩ ጎልቶ መታየቱን ተናግረዋል።

በአካባቢው ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት የአልሚ ምግቦች እና መድኃኒቶች አቅርቦት በመስተጓጎሉ ነፍሰ ጡር እናቶች እና ሕፃናት " ለተወሳሰበ ምግብ እጥረት " እንደተዳረጉ ገልጸዋል።

በታኅሣሥ ወር መጀመሪያ የጤና ባለሞያዎች ለክትባት ዘመቻ ሲወጡ ነፍሰ ጡር እናቶች እና ሕፃናት ' በሥርዓተ ምግብ ልየታ ' " የከፋ " የምግብ እጥረት ላይ እንደሆኑ መታዘብ ችለዋል።

በቡግና ወረዳ ካሉ 16 ቀበሌዎች በተለይም ላይድባ፣ ብርኮ፣ ጉልሃ፣ በርኳኳ እና ፈልፈሊቅ በተባሉ ቀበሌዎች ከስድስት ወር እስከ አምስት ዓመት ያሉ ሕፃናት " አሳሳቢ " የምግብ እጥረት ላይ እንደሚገኙ የተተደረገው ጥናት አሳይቷል።

በዓለም አቀፍ 'አጣዳፊ የምግብ እጥረት' መለኪያ መሰረት 65 በመቶ የወረዳው ህፃናት በምግብ እጥረት መጎዳታቸውን የጤና ጥበቃ ፅ/ቤቱ መረጃ ያሳያል።

በዚሁ መለኪያ መሠረት 84 በመቶ የወረዳው እናቶችም " በከፋ ደረጃ " የምግብ እጥረት ጉዳት ደርሶባቸዋል።

የፅ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ገ/መስቀል ዓለሙ በቡግና ወረዳ 7 ሺህ የሚሆኑ ህፃናት በምግብ እጥረት መጎዳታቸውን እና ከ3 ሺህ በላይ ነፍሰ ጡር እናቶችም መጎታዳቸውን አስታውቀዋል።

ለ3 ቀበሌዎች አገልግሎት የሚሰጠው ብርኮ ጤና ጣቢያ ብቻ በኅዳር ወር አራት ሕፃናት በምግብ እጥረት ሕይወታቸው ማለፉን ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ የጤና ጣቢያ ባለሞያ ተናግረዋል።

በወረዳው በከፍተኛ የምግብ እጥረት የሕፃናት ሕይወት ማለፉን ማረጋገጥ እንዳልቻሉ የተናገሩት አቶ ገ/መስቀል፤ ነገር ግን ሕፃናት "የሞት አፋፍ ላይ" ናቸው ብለዋል።

" የሕክምና ሥርዓቱ ስለፈረሰ ከዚህ በላይ ልየታ ብናደርግ ተጎጂዎች እናገኛለን። . . . እያንዳንዱን ቤት አንኳኩተን አላየነውም " ሲሉ  የጤና ቀውሱ ከዚህም ከፍ ሊል እንደሚችል የአይና ጤና ጣቢያ ኃላፊ አቶ መኮንን ገልፀዋል።

የወረዳው ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ገ/መስቀል " ለጋሽ ድርጅቶች በአስቸኳይ ወደ ወረዳው ገብተው ማገዝ ካልተቻሉ የሰው ሕይወት እንደሚያልፍ ግልጽ ነው " ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

ማክሰኞ ታኅሳስ 08/2017 ዓ.ም. ሁለት ተሽከርካሪዎች አልሚ ምግብ እና መድኃኒት ጭነው ቡግና ወረዳ መደረሳቸውን ባለሞያዎች ተናግረዋል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቢቢሲ አማርኛ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ

ጊዜያዊ መቸገር ወደ ኋላ አይጎትትም! ምክንያቱም ከአፖሎ እስከ መቶ ሺህ ብር ድረስ በመበደር ስራን ማቀላጠፍ ይቻላል።
አሁኑኑ መተግበሪያውን በማውረድ ይጠቀሙ።

ለአንድሮይድ ስልኮች https://play.google.com/store/apps/details?id=com.boa.apollo&hl=en&gl=US
ለአፕል ስልኮች https://apps.apple.com/us/app/apollo-digital/id1601224628
#Apollodigitalbank #Apollodigitalproduct #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #The_Choice_For_all

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ዶክተርበየነአበራ👏

" ባለቤቴን ጨምሮ ጓደኞቼና ጓደኞቿ ለሙያው ያለኝን ፍቅርና ቁርጠኝነት ስለሚያዉቁ ሊጫኑኝ አልፈለጉም " - ዶ/ር በየነ አበራ

በሰርጉ ማግስት የሙሽሪት ቤተሰቦች ከጠሩት የመልስ ፕሮግራም ላይ ላይ ተነስቶ በመሄድና የተሳካ ቀዶ ሕክምና በማድረግ እናትና ልጅን የታደገዉ የማህፀንና ፅንስ ስፖሻሊስቱ ዶክተር በብዙዎች ምስጋና ተችሮታል።

ይህ የሚያስመሰግን ተግባር የተፈጸመው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ የንግስት እሌኒ መሐመድ መታሰቢያ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ነው።

በሆስፒታሉ የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት የሆኑት ዶክተር በየነ አበራ በትላንትናው ዕለት በሰርጋቸው ማግስት የሙሽሪት ቤተሰቦች በጠሩት የመልስ ዝግጅት ላይ ነበሩ።

በዚህ ዝግጅት ላይ እንዳሉ ነው ከሚሰሩበት ሆስፒታል የስልክ ጥሪ የደረሳቸው።

የስልክ ጥሪውም እናትና ልጅን እንዲታደጉ የቀረበ ነበር።

ዶክተር በየነ ስለሁኔታው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲናገሩ " መልስ በሀገራችን ባህልና ወግ ትልቅ ቦታ እደሚሰጠዉ አዉቃለሁ በዕለቱ አማቾቼ አክብረው ጠርተዉን ፕሮግራሙ እየተካሄደ ነበር ስልክ የተደወለልኝ " ብለዋል።

" የመጀመሪያውን ዙር አላነሳሁም ፤ በድጋሚ ሲደወልልኝ አነሳሁት አንዲትን እናት ምጥ እንዳስቸገራትና ቀዶ ሕክምና የግድ እንደሚያስፈልጋት  ተነገረኝ፤ ለመሄድ አላመነታሁም " ሲሉ የነበረውን ሁኔታ ገልጸዋል።

በኃላም ዶክተር የመልስ ዝግጅቱን አቋርጠው የእናት እና ልጅን ሕይወት ለመታደግ እየከነፉ ወደ ሆስፒታል ለመሄድ ይወስናሉ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ ጉዳዩን እንዴት ለሙሽሪት እንዳስረዱና ሙሽሪትን እንዳሳመኗት ጠይቋቸዋል።

እሳቸውም ፤ " በፍቅር ሕይወታችን ወቅት የትዳር አጋሬን በተደጋጋሚ እንደዚህ አይነት አጋጣሚዎች ሊከሰቱ እንደሚችሉ በተደጋጋሚ እነግራት ነበር፤ በሰርግ መልሳችን ቀን ግን ይሆናል ብዬ አሰቤ አላዉቅም ነበር " ብለዋክ።

" ለሙሽራዋ ባለቤቴና ለሚዜዎቼ ነገርኳቸዉና ወደ ሆስፒታሉ አመራሁ። ባለቤቴን ጨምሮ ጓደኞቼና ጓደኞቿ ለሙያው ያለኝ ፍቅርና ቁርጠኝነት ስለሚያዉቁ ሊጫኑኝ አልፈለጉም " ሲሉ ተናግረዋል።

ዶክተር በየነ " ቤተሰቦቿን ግን ተመልሼ ይቅርታ ለመጠየቅ ወስኜ ነበር ወደ ሆስፒታል የሄድኩት " ብለዋል።

" ወደ ሆስፒታሉ ስደርስ የቀዶ ሕክምና ቲሙ ዝግጁ ስለነበር አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አድርጌ ቀዶ ሕክምናውን በተሳካ ሁኔታ አጠናቀናል " ሲሉ ተናግረዋል።

ዶክተር በየነ አበራ የመጀመሪያ ዲግሪያቸዉን በሕክምና ትምህርት ከሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ያገኙ ሲሆን የስፔሻሊቲ ትምህርታቸውን ደግሞ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ተከታትለዋል።

#TikvahEthiopia

Via @TikvahethMagazine

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" የዘንድሮው ቅዝቃዜ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ጠንከር ያለ ነው " - ባለሙያዎች

አዲስ አበባን ጨምሮ በኢትዮጵያ አብዛኛው ስፍራዎች ሰሞኑን የተከሰተው ጠንከር ያለ ብርድ ከዚህ ሳምንት መጨረሻ ጀምሮ እየተዳከመ እንደሚሄድ የኢትዮጵያ ሜትሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታውቋል።

በዚህ ወቅት ከሳይቤሪያ በመነሳት ወደ ኢትዮጵያ በሚገባው ደረቅና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ ምክንያት ጠንከር ያለው ቅዝቃዜ መከሰቱን የሚያስረዱት ባለሙያዎች የዘንድሮው ቅዝቃዜ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ጠንከር ያለ መሆኑን አረገጋግጠዋል። 

" ዘንድሮ ህዳር መጨረሻ አከባቢ ከፍተኛ ቅዝቃዜ ነው ያለው፡፡ አሁን ደግሞ ያለንበት ታህሳስ ወር በጣም የባሰበት ቅዝቃዜ እያስተዋልን ነው " ብለዋል አንድ የአዲስ አበባ ነዋሪ።

አዲስ አበባ ውስጥ በተለይ ካለፈው ህዳር ወር መጨረሻ ጀምሮ አሁን እስካለንበት ታህሳስ ወር ከተለመደውም ጠንከር ያለ ከፍተኛ ብርድ ተስተውሏል፡፡

የሜትዮሮጂ ባለሞያዎች ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ዓመታዊ የአየር ጠባይ ወቅቶችን ፦
- ክረምት፣
- በጋ
- በልግ በማለት በሶስት ይከፍሉታል፡፡

የወቅቶቹን ባህሪያት የሚወስኑትም በካባቢ አየር ውስጥ፣ በየብስ እና በውሃ አካላት ላይ የሚፈጠሩ የአየር ሁኔታ ክስተቶች እንደሆኑ ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡

በኢትዮጵያ ሜትሮሎጂ ኢንስቲትዩት የትንበያና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ምርምር ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አሳምነው ተሾመ ከጥቅምት እስከ ጥር ወራት ያሉትን የሚሸፍነው አሁን የምንገኝበት በጋ ተብሎ የሚጠቀሰው ወቅት ለአብዛኛው የኢትዮጵያ ክፍሎች ደረቅና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ የሚስተዋልበት ነው ብለዋል።

" ይህ ወቅት ለአብዛኛው የአገራችን አከባቢዎች፤ ለአብነትም ለትግራይ፣ አፋር፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ አብኛው የኦሮሚያ እና ማዕከላዊና ምስራቃዊ የኢትዮጵያ አከባቢዎች በዚህ በበጋ ወቅት የበጋ ደረቃማ እና ነፋሻማ የአየር ሁኔታዎች የሚያመዝንበት ወቅት ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

በተለይ ከሳይበሪያ የሚነሳው ደረቅና ነፋሻማ የአየር ጠባይ በነዚህ አከባቢዎች ለሚስተዋለው የአየር ጠባይ ወሳኙን ሚና እንደሚጫወቱ የሚያነሱት ባለሙያው በተጠቀሱት አንዳንድ አከባቢዎች በሚከሰት ከፍተኛ ቅዝቃዜ የሙቀት መጠኑ ከአንድ ድግሪ ሴልሽየስ በታች እንደሚወርድ ጠቁመዋል።

ዘንድሮ አዲስ አበባን ጨምሮ በበርካታ አከባቢዎች ከባለፈው ዓመት እንኳ ሲነጻጸር ጠንከር ያለ የማለዳ ቅዝቃዜ አሁን መስተዋሉን አንስተዋል፡፡

" በተለይም አዲስ አበባን ከባለፈው በጋ 2016 ዓ/ም ተመሳሳይ ወቅት ጋር አነጻጽረን ስንመለከተው የቀኑ ዝቅተኛ የሙቀት መጠን ከ10 ወደ 6.6 ድግሪ ሴንትግሬድ ዝቅ ብሎ ተመልክተናል " ብለዋል።

" በአዲስ አበባም ሆነ በሌሎች አከባቢዎች ላይ የማለዳው ቅዝቃዜ ማለዳ ላይ መጠናከሩን ተመልክተናል " ሲሉ አስረድተዋል። 

ይህ ከሳይበሪያ ላይ በመነሳት ወደ አገሪቱ ስገባ የነበረው ደረቅና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ በመጠናከሩ ነው ብለዋል፡፡

ይህ ቅዝቃዜ እስከ ታህሳስ ወር አጋማሽ ድረስ እንደሚቀጥልና ከታህሳስ 13 በኋላ ግን የቅዝቃዜ መጠኑ እየተዳከመ እንደሚሄድ አስረድተዋል፡፡
 
ከዚህ ቀደም ብርዱ በጥቅምት ላይ እንደሚጠነክር፤ ዘንድሮ ግን ከህዳር መጨረሻ ጀምሮ አሁን እስከ ምንገኝበበት ታህሳስ ወር የተጠናከረበትን ምክንያት የተጠየቁት ባለሙያው፤ ባለፈው ግንቦት ወር የተሰጠውን የአየር ሁኔታ ትንቢያ ማስታወስ እንደሚያስፈልግ አንስተዋል፡፡

" የክረምቱ ዝናብ አወጣጥ ሊዘገይ እንደሚችል ባለፈው ግንቦት 2016 ኣ.ም. አንስተን ነበር " ያሉት ዶ/ር አሳምነው፤ እስከ ህዳር አጋማሽ ከበርካታ አገሪቱ አከባቢዎች ያልጠፋው ዝናብና ደመና ወበቅ በመፍጠሩ የቅዝቃዜውን ወቅት ወዲህ መግፋቱን አስረድተዋል፡፡

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

“ የልብ ክፍተት ህመም ያለበት ልጄን አድኑልኝ ” - አባት

በሞጆ ከተማ የሚገኙ አቶ አማረ አለማየሁ የተባሉ አባት የአንድ አመት ጨቅላ ህፃን ልጃቸው በልብ ክፍተት ህመም እየተሰቃዬ በመሆኑ ድጋፍ እንዲደረግላቸው ተማጸኑ።

የህፃኑ አባት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?

“ ህፃኑን ይዤ ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ተመላለስኩ። ‘የሚሆን ነገር አይደለም’ ብለው ወደ ህፃናት ልብ ህሙማን መርጃ ማዕከል መርተውኝ ነበር።

በማዕከሉ ያለው ወረፋም የሚቻል አይደለም። ‘በአስቸኳይ መሰራት አለበት ክፍተቱ ከ7 ሚሊ ሜትር የበለጠ ነው’ አሉኝና ወደ ግል ሆስፒል መሩኝ።

ቦሌ አካባቢ በሚገኘው ኢሉዜር ሆስፒታል ሄጄ ስጠይቅ ለማሳከሚያ 685 ሺሕ ብር ጠየቁኝ። በአካባቢዬ እርዳታ ብጠይቅም እስካሁን ምንም ገንዘብ አላገኘሁም።

የልጄ ህመም የተፈጥሮ የልብ ክፍተት ነው። ክፍተቱ በተፈጥሮ መዝጋት ነበረበት ሳይዘጋ ቀረ። ‘መደፈን ያለበት ደግሞ ግዴታ በህክምና ነው’ ተባለ።

ህመሙን ያወቅነው በ6 ወሩ ነው። አዳማ ኃይለማርያም ሆስፒታል ወሰድነወሰና የልብ ኬዝ እንዳለብ ነገሩን። ከዛም ወደ ጥቁር አንበሳ ሪፈር ፃፉልኝ። በሽታው እንዳይባባስበት በመድኃኒት እየተከታተለ ነው ያለው።

የኢትዮጵያ ህዝብ ልበ ቀና ነው። በመረዳዳት የታወቅን ነን። ወገኖቼ አነሰ በዛ ሳትሉ በመተባበር ልጄን አድኑልኝ ”
ሲሉ ተማጽነዋል።

ለመርዳት 1000045518586 የአቶ አማረ አለማዬሁ ደስታ የኮፕራትቭ ባንክ ሒሳብ ቁጥር ነው።

ለመደወል እና ዝርዝር ማስረጃዎችንም ለመጠየቅ 0915846447 የእጅ ስልካቸው ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#SafaricomEthiopia

በምንፈልገው ሰዓት እና ቦታ ያለመቆራረጥ የሚሰራልን ኢንተርኔት ያስፈልገናል ፤ አሁኑኑ የM-PESA ሳፋሪኮምን የ4G ዋይ ፋይ ጥቅል ከM-PESA mini app በመግዛት የማይቆራረጠውን ኢንተርኔት እናጣጥም !

🔗የM-PESAን ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

#MPESASafaricom
#1Wedefit
#FurtherAheadTogether

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

“ የግል ትምህርት ቤቶችን መፈናፈኛ የሚያሳጣ፣ አለመፈለጋችንን በግልጽ ያስረዳ ረቂቅ ዐዋጅ ነው ” - የኢትዮጵያ የግል ትምህርት ቤቶች ማኀበር

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወደ ቋሚ ኮሚቴ መራው የተባለው የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ ዐዋጅ ላይ ብርቱ ተቃውሞ እንዳለው የኢትዮጵያ የግል ትምህርት ቤቶች ማኀበር በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ገለጸ።

የማኀበሩ ፕሬዜዳንት አቶ አበራ ጣሰው፣ “ የግል ትምህርት ቤቶችን መፈናፈኛ የሚያሳጣ፣ አለመፈለጋችንን በግልጽ ያስረዳ ረቂቅ ዐዋጅ ነው ” ሲሉ ተችተውታል።

ፕሬዜዳንቱ በዝርዝም ምን አሉ ?

በረቂቁ ብዙ ነገሮች መሻሻል አለባቸው። አንኳር አንኮር የሆኑትን ለማንሳት፦ 

አንዱ ‘አንድ የግል ትምህርት ቤት ት/ቤት ሆኖ ለመቀጠል ‘የ6 ወራት የሰራተኞችን ደመወዝ በዝግ ሂሳብ ቁጥር ማስቀመጥ አለበት’ የሚለው ነው።

ይሄ ገንዘብ ከተቀመጠ በኋላ መቼ እንደሚወጣ አይታወቅም፣ Forever እንዲቀመጥ ነው እንድምታው። ምክንያቱም ገንዘቡ ከወጣ ፈቃድ ይነጠቃል።

አንደኛ የትምህርት ሥራ እንደንኛውም ድርጅት ንግድ ነው። በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በላሎች የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ነጋዴዎች ያለምንም ዋስትና ስራቸውን እያከናወኑ ነው ያሉት።

ዋስትና መሠረቱ ጥርጣሬ ነው። ስለዚህ እነዚህ ሁሉ ድርጅቶች ሳይጠረጠሩ የትምህርት ሥራ ተጠርጣሪ ሆኖ ‘ዋስትና ካልያዝክ አትሰራም’ መባሉ አሳዛኝ ነው።

የገል ትምህርት ቤቶች ተርፏቸው የ6 ወራት ደመወዝ በአካውንት ማስቀመጥ አይችሉም። ስለዚህ ይሄ ረቂቅ ሕግ ሆኖ ከቀጠለ ትምህርት ቤቶች ሥራቸውን አይቀጥሉም።

ምናልባት ሌላ ንብረት ያላቸው ከባንክ ተበድረው በአካውንት ቢያስቀምጡ እንኳ 19% ወለድ ይከፍላሉ፣ ገንዘቡን በቶሎ መመለስ ስለሚያዳግት አመታት ይወስዳል። ወለዱም ዋናው ገንዘብም ተንገዳግደው ከፍለው እንኳ መቀጠል አይችሁም። ስለዚህ ይሄ ፈጽሞ የሚተገበር አይሆንም።

ሁለተኛ ማንም ሰራተኛ የትም ይስራ ዬት በአሰሪና ሠራተኛ ህግ ነው የሚዳኘው። ስለዚህ ረቂቅ ዐዋጁ ያለ ቦታው ነው የተቀመጠው። 

ሌላው የበላይ አካል ማነው? ከትምህርት ቤት ውጪ ያለ የመንግስት አካል ነው? ወይስ ትምህርት ቤት ውስጥ ያሉ የትምህርት አመራሮች ናቸው? የሚለው በረቂቁ ግልጽ አይደለም። 

ሕግ ይከበር እንላለን እዚህ አገር የሚያሳዝነው ነገር ግን በዬአካባቢው ራሳችን ሕግ አውጪ ሆነን ቁጭ እንላለን።

ሕግ ይከበር ስንል እኮ ሕግ የማውጣት ስልጣን ያለው አካል የሚያወጣውን ሕግ ለማክበር እንጂ እያንዳንዳችን እየፈበረክን የምንወጣባቸውን ሕጎች ለማክበር አይደለም።

ስለዚህ በሕግ አውጪው አካል የወጣው ህግ ‘ትምህርት ቤቶች እንደማንኛውም አይነት ንግድ ነጋዴዎች ናቸው’ ብሏል። ድርጅቶችምሕጋዊ ሰውነት ያላቸው ናቸውና መጀመሪያ ይህንን ሲመሰርቱ እኮ በአገሪቱ የሚሰራ ሥራ አለ ብለውናል። 

የኢንቨስትመንት ፓሊሲው፣ ሕገ መንግስቱ የሚያሰራ ሆኖ ሳለ በመሃል እየመጡ እንደዚህ አይነት ችግር የሚፈጥሩ ከሆነ ያሉ ትምህርት ቤቶች አይቀጥሉም፤ ሌሎች ትምህርት ሊከፈቱ አይችሉም። ምክንያቱም በዬቦታው ያለው እንቅፋት ነው ”
ብለዋል።

ጉዳዩን በሚመለከት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት እንደተደረገ ይሻሻል የሚል ተስፋ እንዳለውም ማኀበሩ ገልጿል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" በአሁኑ ወቅት በኦሮሚያ ክልል በሚደረገው ምክክር ላይ ኦፌኮ እንዲሳተፍ ጥሪ አቀርባለሁ " - ኮሚሽኑ

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በኢትዮጵያ የሚስተዋሉ አለመግባባቶች በሰላማዊ መንገድ ይፈቱ ዘንድ አጀንዳዎች እያሰባሰበ መሆኑ ይታወቃል። 

ኮሚሽኑ እስካሁን በ10 ክልሎች አጀንዳ እንዳሰባሰበ፣ አንዳንድ የፓለቲካ ፓርቲዎች ግን አጀንዳቸውን በማስረብ ፋንታ ከኮሚሽኑ እንዳገለሉ መግለጻቸው ይታወሳል።

የኦሮሞ ፈደራሊስት ኮንግረንስ (ኦፌኮ) ፓርቲ ከሳምንታት በፊት በሰጠን ቃል፣ " አሁንም ቢሆን ሀገራዊ ምክክሩ በሚሄድበት አቅጣጫ እርካታ የለንም " ብሎ ነበር።

ፓርቲው ይህን ያለው ኮሚሽኑ ተጠሪነቱ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቢሆንም “ምክር ቤቱም በገዢው ፓርቲ የተሞላ ስለሆነ ገልተኛነቱ ያን ያክል አስተማማኝ አይደለም” በማለት ጭምርም ነው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በበኩሉ ኮሚሽኑን ፓርቲዎችን ለማካተት ምን እየተሰራ እንደሆነ በወቅቱ ጠይቆ ምላሽ ማግኘት ሳይቻል የቆዬ ሲሆን፣ ኮሚሽኑ አሁን ምላሽ ሰጥቷል።

ምን አለ ?

" ኮሚሽኑ ገለልተኛ ተቋም ነው። ተቃዋሚ የፓለቲካ ፓርቲዎች በሂደቱ ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርቧል።

ኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚሰሩ ሌሎች ፓርቲዎችም በኦሮሚያ ክልል በሚደረገው ምክክር ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ አድርጓል። በምክክሩ አብዛኛዎቹ የፓለቲካ ፓርቲዎች ፈቃደኛ ሆነው በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

ኦፌኮ እንደተባለው ሂደቱን ለመቀበል ፈቃኛ አይደለም። ኮሚሽኑ ፓርቲው ፈቃደኛ ያልሆነበትን ምክንያት በተደጋጋሚ ከኦፌኮ ጋር  በአካልም እንደገና በደብዳቤም እንነጋገር በሚል ጥረት አድርጓል።

 ፓርቲው ግን ፈፈቃደኛ መሆን አልቻለም። በዚህ ሂደት የኮሚሽኑ እይታ ፓርቲው በማንኛውም ሰዓት ሀሳቡን ለውጦ ለመመካከር ከመጣ ኮሚሽኑ በሩ ክፍት ነው።

ግን ኮሚሽኑ በራሱ መንገድ ለመሳተፍ ፈቃደኛ ያልሆነውን አካል አስገድዶ ማሳተፍ አይችልም። ስለሆነሞ ኦፌኮ እንደ ኦሮሚያ በምክክሩ ባለመሳተፉ ኮሚሽኑ ያዝናል።

በአሁኑ ወቅት በኦሮሚያ ክልል በሚደረገው ምክክር ላይ ኦፌኮ እንዲሳተፍ ጥሪ እናቀርባለን። ምክክሩ ላይ ልዩነትን ይዞ እስከመጨረሻው መሄድ ይቻላል። 

የሀሳብ የበላይነት እንጂ የኃይል የበላይነት በምክክሩ ላይ  አይንጸባረቅም። በሀገራዊ ምክክሩ የፓለቲካ ፓርቲዎች አጀንዳዎቻቸውን ለማህበረሰቡ ግልጽ ማድረግ ይችላሉ።

በሚስማሙባቸው ጉዳዮች ላይ ይስማማሉ በማይስማሙባቸው ጉዳዮች ላይ ደግሞ በልዩነት መሄድ ይችላሉ። ሀገራዊ ምክክሩ በባህሪው በትውልድ መካከል ከረጅም ጊዜ በኋላ የሚመጣ በመሆኑ ሂደቱን ከማበላሸት ይልቅ አሁንም ቢሳተፉ ይመረጣል።

ኮሚሽኑ አካታች ነው። ፈቃደኛ የሆኑትን አካቶ እየሰራ ነው። ፈቃደኛ ያልሆኑት እስከመጨረሻው እንዲመጡ በሩ ክፍት ነው፣ ይጠብቃል። ምንም አይነት አሉታዊ ተፅዕኖም እንደማይደርስባቸው ኮሚሽኑ ዋስትና ይሰጣል። ”

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ዮናታን_ቢቲ_ፈርኒቸር

በዓሉን ልዩ ቅናሽ በተደረገባቸው የቤት እቃዎቻችን ቤትዎን ያድምቁ 🎁
የውበት ፣የጥራት እና የምቾት ዳር ድንበር
ዮናታን ቢቲ ፈርኒቸር !

📍አድራሻችን
1. ፒያሳ እሪ በከንቱ ቢቲ ታወር (ከኢቲዮ ሴራሚክ ዝቅ ብሎ)
2. ከዊንጌት አደባባይ አለፍ ብሎ ከአቢሲኒያ ባንክ ፊትለፊት
3. ከሲኤምሲ አደባባይ ወደ አያት መንገድ መሪ ሳይደርስ (ዘመን ባንክ አጠገብ)

☎️ ይደውሉልን
+251957868686
+251995272727
+251993828282

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ለጥንቃቄ ሲባል መንገደኞች እና የበረራ ሠራተኞች በአስቸኳይ ከአውሮፕላኑ እንዲወርዱ ተደርጓል " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ

የበረራ ቁጥሩ ET 612 የሆነ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ታህሳስ 05 ቀን 2017 ዓ.ም. ከአዲስ አበባ ወደ ዱባይ በሚያደርገው በረራ ከተነሳ ከ30 ደቂቃ በኋላ የቴክኒክ ችግር አጋጥሞታል።

በዚህም አውሮፕላኑ ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በሰላም አርፏል።

ለጥንቃቄ ሲባል መንገደኞች እና የበረራ ሠራተኞች በአስቸኳይ ከአውሮፕላኑ እንዲወርዱ መደረጉን አየር መንገዱ አሳውዋል።

" ሁልጊዜም ለመንገደኞቼ ደህንነት ቅድሚያ እሰጣለሁ " ያለው አየር መንገዱ መንገደኞች ለደረሰባቸው መጉላላት አየር ይቅርታ ጠይቋል።

የቴክኒክ ችግሩ በመጣራት ላይ መሆኑንም ገልጿል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Tigray : በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት የራሱን ምክር ቤት አቋቁሟል።

" የሃላቀርነት እና ወንጀል ቡድን " ሲል የገለፀውን በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራውን የህወሓት ቡድን በፅኑ ለመታገል ቆርጦ እንደተነሳ ገልጿል።

በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት እስከ ቀጣዩ 14ኛው የደርጅቱ መደበኛ ጉባኤ የሚቆዩ ሊቀመንበር እና ምክትል ያቀፈ 7 አባላት ባሉት አስተባባሪ ኮሚቴ የሚመራ ም/ቤት አቋቁሟል።

የደርጅቱን ምክትል ሊቀመንበር ማን አድርጎ እንደሰየመ ያልገለፀው መግለጫው  ፤ አስተባባሪ ኮሚቴው የቀጣይ 3 ወራት እቅድ ማዘጋጀቱ አስታውቋል።

ደርጅቱ 14 ኛ ጉባኤውን መቼ እንደሚያካሂድ ያልገለፀ ሲሆን የተመሰረተው ምክር ቤት አባላት ሁሉም በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ከሚመራው ህወሓት " አንሰለፍም " ብለው የተቆራረጡ ናቸው።

በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት በከተማና ገጠር ከክልል ፣ ዞን ፣ ወረዳ እና እስከ ቀበሌ ድረስ አደራጃጀቶች በመዘርጋት " የኃላቀርነት እና ወንጀል ቡድን " ሲል የገለፀውን በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራውን ህወሓት በፅኑ ለመታገል ቆርጦ መነሳቱ ገልጿል።

መላው የትግራይ ህዝብ ፣ የህወሓት አባላት ፣ የፀጥታ ሃይሎች ፣ የአገር ሽማግሌዎች ፣ በተለይ ወጣቶች ፣ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች እና የዳያስፓራ ማህበረሰብ ከጎኑ እንዲሰለፉ ጥሪ ያቀረበው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት " በሰላማዊ ትግል የትግራይን ህዝብ ጥቅም ለማስክበር እታገላለሁ " ብሏል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#MPESASafaricom

ከM-PESA ወደ የትኛውም የነጋዴ የባንክ አካውንት መክፈል ተችሏል ፤ በM-PESA ሁሌም ሽልማት ሁሌም ቅናሽ አለ!

የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details... የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉/channel/Safaricom_Ethiopia_PLC

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን /channel/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#FurtherAheadTogether

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#AAiT

Call for Applications in MSc and PhD Programs 2024/25 Second Semester

1. Computer Engineering - MSc and PhD
2. Communication Engineering - MSc and PhD
3. Control Engineering - MSc and PhD
4. Electrical Power Engineering - MSc and PhD

School of Electrical & Computer Engineering, Addis Ababa University,

Application Deadline for GAT: Friday December 20, 2024

More information, see our channel /channel/TrainingAAiT or check application procedure here.

Email: dean.sece@aait.edu.et

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

🔈#የጤናባለሙያዎችድምጽ

🔵 " ቸግሮናልጠምቶናል፣ ርቦናል፣ ሰልችቶናል፣ ከኑሮ ውድነቱ ጋር ተያይዞ የዱቲ ሳይከፈለን ለ17 ወራት ስንሰራ ከመንግስት አካል ማንም ያሰበን የለም " - ጤና ባለሞያዎች

🔴 " ምንም ምላሽ የለንም። ቢሮ መጥተው ይጠይቁን " - ወናጎ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት

በጌዴኦ ዞን ወናጎ ወረዳ ያሉ ጤና ባለሙያዎች የወራት ያልተከፈለ የዱቲ ክፍያ እንዲፈጸምላቸው በመጠየቃቸው ከደመወዛቸው እንዲቆረጥባቸው መወሰኑን በመግለጽ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

" ዱቲ ስላልከፈሉን የሰራነውን ገንዘብ ስለጠየቅን ብቻ ከሦስት ወራት በላይ ደሞዛችን ከ960 ብር ጀምሮ በስኬል  እየተቆረጠ ይገኛል " ብለው፣ ደመወዛቸው እንዲቆረጥ የተወሰነው የዱቲ ሥራ በማቆማቸው መሆኑን ገልጸዋል።

የዱቲ ሥራ በመቆሙ ህዝቡም ችግር ላይ ስለሆነ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀው፣ " ካልሆነ ለሚፈጠር ችግር ተጠያቂ አንሆንም " ሲሉ አስጠይቅቀዋል።

በዞኑ ዲላ ዙሪያ ወረዳ ጪጩ ጤና ጣቢያ ያሉ ባለሙያዎቹ በበኩላቸው፣ የ17 ወራት የዱቲ ክፍያ እንዳልተፈጸመላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ያማረራቸውን ቅሬታ በተመለከተ በዝርዝር ምን አሉ ?

" በጌዴኦ ዞን በዲላ ዙሪያ ወረዳ የ17 ወራት የዱቲ ክፍያ ባለመከፈሉ የጪጩ ጤና ጣቢያ ከመስከረም 1 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ የዱቲ ሥራ በማቆም ሕዝቡ ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቋል።

በተደጋጋሚ ለዞኑና ለወረዳው ቅሬታ ብናቀርብም ምላሽ በመስጠት ፈንታ ባለሞያዎችን ለእስር ሲዳርግ ቆይቷል። ለሦስት ዓመት ያክል በዱቲ ክፍያ እየተከራተተ የሚገኝ የዲላ ዙሪያ ወረዳ ጤና ባለሞያ እስከ ዛሬ ተገቢ ምላሽ አላገኘም።

በጌዴኦ ዞን በወናጎ ወረዳ የሚገኙ ጤና ባለሞያዎች የዱቲ ጥያቄ አቅርበው ተገቢ ምላሽ ባለማግኘታቸው መብታቸው ለማስከበር የዱቲ ሥራ በማቆማቸው በየወሩ ከደሞዛዝ እንዲቆረጥ ተወስኗል።

ዱቲ ስላልከፈሉን የሰራነውን ገንዘብ ስለጠየቅን ብቻ ከሦስት ወር በላይ ደሞዛችን ከ960 ብር ጀምሮ በየወሩ እየተቆረጠ ይገኛል። መንግስት አፋጣኝ ምላሽ ይስጠን።

ቸግሮናል፣ ጠምቶናል፣ ርቦናል ሰልችቶናል ሞራላችን ተነክቷል መውጫ ቀዳዳ አሳጥቶናል ከኑሮ ውድነት ጋር የዱቲ ሳይከፈለን ለ17 ወራት ስንሰራ ከመንግስት አካል ማንም ያሰበን የለም " ብለዋል።


ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ የጠየቀው የወናጎ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ቀጥተኛ ማብራሪያ በመስጠት ፋንታ፣ " ምንም ምላሽ የለንም። ቢሮ መጥተው ይጠይቁን " ብሏል።

ሰሞኑን በተደጋጋሚ ስልክ ለማሳት ፈቃደኛ ባይሆኑም የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አንዱዓለም ማሞ ከዚህ ቀደም ጉዳዩን በተመለከተ በሰጡትን ምላሽ ችግሩን ለመቅረፍ እየተሰራ መሆኑን ገልጸውልን ነበር።

"ጉዳዩ በእርግጥ ያለ ነው። መሠረታዊ ችግሩ የበጀት ችግር ነው፤ የካሽ እጥረት ነው ያለው። ያን ለመፍታት በጋራ እየሰራን ነው" የሚል ቃል ነበር የሰጡን።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ቴሌብር ሱፐርአፕን ይጠቀሙ፤ ተጨማሪ ስጦታዎችን ያግኙ!

🎁 በቴሌብር 100 ብር እና ከዚያ በላይ የሞባይል አየር ሰዓት ሲሞሉ 25%፣ ከ100 ብር በታች ሲሞሉ 15% እንዲሁም ጥቅል ሲገዙ 10% ተጨማሪ ስጦታ ያገኛሉ፡፡

➡️ አዲስ ደንበኛ ከሆኑ መተግበሪያውን https://onelink.to/uecbbr ሲጭኑ በ100ሜ.ባ ስጦታ እንቀበልዎታለን፣ የመጀመሪያውን ግብይት ሲፈጽሙ ደግሞ የ15 ብር ስጦታ ያገኛሉ!

ለተጨማሪ፡ https://youtu.be/l7sSDPhPig4 ይመልከቱ!


ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ወደ ኢትዮጵያ የውጭ ባንኮች መግባት እንዲችሉ የሚፈቅደው አዋጅ ፀድቋል።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በኢትዮጵያ የውጭ ባንኮች እንዲሳተፉ የሚፈቅደውን የባንክ ስራ ረቂቅ አዋጅ ዛሬ አጽድቋል፡፡

ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅን በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#AAiT

Call for Applications in MSc and PhD Programs 2024/25 Second Semester

1. Computer Engineering - MSc and PhD
2. Communication Engineering - MSc and PhD
3. Control Engineering - MSc and PhD
4. Electrical Power Engineering - MSc and PhD

School of Electrical & Computer Engineering, Addis Ababa University,

Application Deadline for GAT: Friday December 20, 2024

More information, see our channel /channel/TrainingAAiT or check application procedure here.

Email: dean.sece@aait.edu.et

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ጥንቃቄ

ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ በተለይም ኮድ 3 እና ኮድ 2 መኪና ይዘው እየተነቀሳቀሱ ሰዎችን የሚዘርፉ የዘነጡ ሌባዎች በከተማይቱ እንዳሉ በተለያዩ ቦታዎችም ዜጎች እየተዘረፉ መሆኑን ጥቆማ ሰጥተናችሁ ነበር።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዛሬ የአዲስ አበባ ፖሊስ አንድ መረጃ አጋርቷል።

መረጃው ምን ይላል ?

በተሽከርካሪዎች ላይ ሀሰተኛ ሰሌዳ ቁጥር በመለጠፍ ቅሚያ ሲፈጽሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎች እንደተያዙ ይገልጻል።

ተጠርጣሪዎቹ ተሽከርካሪ
#በመከራየት በቂርቆስ፣ በቦሌ እና በጉለሌ ክፍለ ከተሞች እየተንቀሳቀሱ  ሞባይል ስልክ  እየቀሙ እንደሚሰወሩ ፖሊስ ባሰባሰበው መረጃ አረጋግጧል፡፡

ህዳር 29 ቀን 2017 ዓ/ም በቂርቆስ ክ/ ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ቦታው በተለምዶ " ወሎ ሰፈር " እየተባለ ከሚጠራው አካባቢ ከምሽቱ 1 ሰዓት ላይ ተጠርጣሪዎቹ በኮድ 2 A-28629 አአ በሆነ ተሽከርካሪ ላይ ኮድ 3 B-35824 አአ የሚል ሀሰተኛ ሰሌዳ ቁጥር ለጥፈው ግምቱ 12 ሺህ ብር የሚያወጣ አይነቱ ሳምሰግ ሞባይል ቀምተው ይሰወራሉ።

ወንጀሉን በፈፀሙ በአንድ ሰዓት ልዩነት  በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 8 ጉለሌ ሸገር አካባቢ  ከአንድ ግለሰብ ላይ 8 ሺህ ብር የሚገመት ቴክኖ ሞባይል ይቀማሉ፡፡

የቂርቆስ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ወንጀል ፈፃሚዎችን ለመያዝ በክትትል ላይ እያለ ወንጀሉን በፈጸሙበት እለት በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ሁለት ተጠርጣሪዎች ተይዘዋል።

በተመሳሳይ  ሌሎች ወንጀል ፈፃሚዎች በኮድ 2C -28629 አዲስ አበባ በሆነ ተሽከርካሪ ላይ ኮድ 3A-21634 አዲስ አበባ የሚል ሀሰተኛ ሰሌዳ ቁጥር  በመለጠፍ  በተመሳሳይ የቅሚያ ወንጀል ለመፈፀም በመንቀሳቀስ ላይ እንዳሉ ህዳር 29 ቀን 2017 ዓ/ም በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 " ሸዋ ዳቦ " አካባቢ ተይዘዋል።

በተሽከርካሪ ውስጥ ከተለያዩ ግለሰቦች የተቀሙ ሶስት ሞባይሎች የተገኙ ሲሆን ከሶስቱ ተጠርጣሪዎች መካከል አንደኛው በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራበት ሲሆን ሁለቱን ተጠርጣሪዎች ለመያዝ ክትትል እየተደረገ ነው።

ተጠርጣሪዎቹ በቀን ገቢ ተሽከርካሪዎችን በመከራየት እና ሀሰተኛ የሰሌዳ ቁጥር አዘጋጅተው በመለጠፍ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች እየተንቀሳቀሱ  ወንጀል ሲፈፅሙ መቆየታቸውን ፖሊስ በምርመራው አረጋግጧል።

የሞባይል ቅሚያ የተፈፀመባቸው ግለሰቦች ቂርቆስ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ቀርበው ንብረታቸውን መረከብ እንደሚችሉ ተጠቁሟል።

ተሽከርካሪን ማከራየት የሚቻለው የህግ አግባብን ተከትሎ መሆን ስላለበት መኪና የሚያከራዩ ባለንብረቶች ተገቢውን ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገበ ፖሊስ አሳስቧል።

ህብረተሰቡ ተመሣሣይ የወንጀል ድርጊት እንዳይፈፀም ተገቢውን ጥንቃቄ ከማድረግ ባሻገር አጠራጣሪ የተሽከርካሪ ሠሌዳ ቁጥር ካጋጠመው ለፖሊስ መረጃ በመስጠት ተባባሪ እንዲሆን ጥሪ ቀርቧል።


መኪኖቻችሁን ለማን እንደምታከራዩ ለማንስ እንደምታውሱ እወቁ ፤ ተጠንቀቁ !

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ኦሮሞ ሕዝብ የዘመናት ጥያቄ የሆኑት የቋንቋ፣
የወሰን ጥያቄዎች ይፈታሉ ብለን እናምናለ ፤ አዲስ አበባ ጉዳይ የኦሮሞ ህዝብ የዘመናት ጥያቄ ነው "  - አባገዳዎቹ

የኦሮሚያ ክልል የምክክር ተሳታፊዎች የኦሮሞ ህዝብ ለ150 ዓመታት ሲጠይቅ የነበረው ጥያቄ መልስ እንዲያገኝለት አጀንዳ ሆኖ እንዲቀርብ አባገዳዎች ጠየቁ፡፡

አባ ገዳዎች ይህን የጠየቁት ዛሬ በአዳማ ከተማ የ ሀገራዊ ምክክር ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት የመክፈቻ መርሀ ግብር ላይ ነው፡፡፡

አባ ገዳዎቹ " የኦሮሞ ህዝብ ለ150 ዓመታት ሲጠይቃቸው የነበሩ ጥያቄዎች አንድም እንዳይዘነጉ " ሲሉ ለምክክሩ ተሳታፊዎች አሳስበዋል፡፡

" በምክክሩ የኦሮሞ ሕዝብ የዘመናት ጥያቄ ናቸው የተባሉት ፦
➡️ የቋንቋ፣
➡️ የወሰን ጥያቄዎች ይፈታሉ ብለን እናምናለን " ብለዋል፡፡

‘" የአዲስ አበባ ጉዳይ የኦሮሞ ህዝብ የዘመናት ጥያቄ ነው "  ያሉት አባገዳዎቹ ይህም በምክክሩ እንዲፈታ ጠይቀዋል፡፡

የምክክሩ ተሳታፊዎች የወከሉት የኦሮሞ ህዝብ ተቆራርጠው የቀሩት ፦
- የመሬት ጥያቄዎች፣
; የወሰን ጥያቄዎች እንዲፈቱ አጀንዳ ሆነው እንዲያቀርቡ አሳስበዋል፡፡

አፋን ኦሮሞ ቋንቋም የፌዴራል የስራ ቋንቋ እንዲሆን አባ ገዳዎቹ ለተሳታፊዎቹ " አጀንዳ " አድርጋችሁ አቅርቡ ብለዋቸዋል፡፡

አባ ገዳዎቹ የኦሮሞ ህዝብ መልስ እንዲያገኝ ጠይቁ ባሉበት ወቅት፤ በምክክር ሂደት ላይ ለመሳተፍ በስታዲየም የተገኙት ሰዎች በጭብጨባና በፉጨት ድጋፋቸውን አሳይተዋቸዋል፡፡

በዛሬ በኦሮሚያ ክልል በአዳማ ከተማ በተጀመረው የምክክር ምዕራፍ ከ356 ከክልሉ ወረዳዎች የተወከሉ ከ7,000  በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ተወክለዋል፡፡

መረጃው ከሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ የተወሰደ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#TecnoAI

ታህሳስ 10 በስካይ ላይት ሆቴል የሚካሄደው በሀገራችን ትልቁ የቴክኖ ኤ አይ ኢቬንት ጥቂት ቀናት ቀርተውቷል፡፡ ታዋቂው የቴክኖሎጂ ባለሙያ ሰለሞን ካሳ የዝግጅቱ አካል ሲሆን ስለ ቴክኖ ኤ አይ እና ስለ አዲሶቹ የቴክኖ የቴክኖሎጂ ምርት ውጤቶች ሙያዊ ማብራሪያ የሚሰጥ ይሆናል፡፡

ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመከተል የቴክኖ ቲክቶክ ገጽ ፎሎው በማድረግ እና Bio ላይ ያለውን ሊንክ ተጭነው በመመዝገብ ታህሳስ 10 በስካይላይት ሆቴል በሚካሄደው የሀገራችን ትልቁ የኤ አይ ሁነት ላይ ይሳተፉ፡፡

tecnoet" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@tecnoet

@tecno_et @tecno_et

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ብርሃን_ባንክ
በቀላሉ በስልክዎት!

#ባርኮት_ፔይ ለቤተ እምነቶች አሥራት፣ መባ፣ ልዩ ሥጦታ እና ቃል የተገቡ የቤተእምነት ገቢዎችን በተለያየ አማራጭ መሰብሰብ የሚያስችል ልዩ የብርሃን ባንክ አገልግሎት ነው!

#barkotpay #berhanbarkotpay #pay #berhanbank #bank #finance
#Stressfreebanking #bankinethiopia

ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ!
➡️ Facebook
➡️ Telegram
➡️ Instagram
➡️ Twitter
➡️ LinkedIn
➡️ YouTube

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ፋይል: አጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅ።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተመዝግበዋል? እንግዲያውስ ይህን ያስተውሉ።

#ፋይዳ #ፋይዳለኢትዮጵያ #Fayda #DigitalID

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#DStvEthiopia

በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የማንቼስተር ደርቢ በጎጆ ፓኬጅ💥
63ተኛውን ጨዋታዎቸውን የሚያደርጉት ሁለቱ ቡድኖች ማን ሲቲ 25 ጊዜ ሲያሸንፍ ማን ዩናይትድ 28 ጊዜ ድል አድርጓል! ሁለቱ ብድኖች 9 ጊዜ በአቻ ተለያይተዋል

🏆 ማን ሲቲ ከማን ዩናይትድ ጋር የሚያደርጉትን ጨዋታ ጨምሮ 10 የፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎችን በጎጆ ፓኬጅ በ400 ብር ብቻ በቀጥታ ይከታተሉ!

ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh

ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇
www.dstv.com/en-et
#PremierLeagueallonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" እነ ድብረፅዮን በአዲስ አበባው ውይይት ' ጌታቸውን ከፕሬዜዳንት እንሱልን ብቻ እንጂ ጊዚያዊ አስተዳደሩ መልሰን በማደራጀት አብረናችሁ ለመስራት ዝግጁ ነን ' ብለዋል " - ሌ/ጄነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዜዳንት ሌተናል ጀነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ ከድምጺ ወያነ ጋር በነበራቸው ቆይታ ምን አሉ ?

ሌ/ጄነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ ፤ የትግራይ አመራሮች በአዲስ አበባ ከጠቅላይ ሚንስትር ዐበይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር በወቅታዊ ጉዳይ በነበራቸው ቆይታ በክልሉ ጉዳይ የሃሳብ ልዩነት አልነበራቸውም ብለዋል፡፡

ነገር ግን " የትግራይ ፓለቲካ ከድጡ ወደ ማጡ እያመራ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

" የፀጥታ ሃይሎች ከማንኛውም ጫና ነፃ ሆነው የህዝቡ ብሄራዊ ጥቅም ማረጋገጥ ይገባቸዋል " ሲሉ አክለዋል፡፡

በአዲስ አበባው ውይይት በደብረፅዮን (ዶ/ር) ይሁን በአቶ ጌታቸው የሚመሩት የህወሓት ልኡካን እንዲሁም የጊዚያዊ አስተዳደሩ ተወካዮች መካከል በትግራይ ወቅታዊ ሁኔታና ችግሮች ዙሪካ ያለልዩነት መስማማታቸውን ገልጸዋል።

በወቅቱ " የፌደራል መንግሰት የትግራይ ችግሮች እንዲፈቱ አላገዝክም " በማለት ወቀሳ ማቅረባቸውን ጠቁመዋል።

" የፌደራል መንግስት ' ጉባኤ እንድናካሂድ ፤ የትግራይ ፓለቲካ እንድናስተካክል ጊዜ ስጠን በማለት ዕድል እና ጊዚያችሁን አባክናቹሃል ' በማለት መልሶልናል " ሲሉ አብራርተዋል።

ሌተናል ጄነራሉ ፥ " በመሃከላችን እየታየ ያለው ክፉኛ መሳሳብ የትግራይ ሉአላዊ ግዛት እንዳይረጋገጥ ፣ ተፈናቃዮች ወደ ቁያቸው እንዳይመለሱ አደገኛ መሰናክል ሆኗል " ብለዋል።

የፕሪቶሪያ ውል በይፋ የተቃወመ የለም ፤ በተግባር ግን ውሉን የሚያደናቅፍ አሉታዊ ተግባር የሚፈፀሙ አካላት አሉ ብለዋል።

" የፕሪቶሪያ ውል በተሟላ መልኩ በመተግበር ብቻ ነው አቃፊ መንግስት ማቋቋም የሚቻለው " በማለትም አስረግጠዋል።

" እነ ድብረፅዮን በአዲስ አበባው ውይይት ' ጌታቸውን ከፕሬዜዳንት እንሱልን ብቻ እንጂ ጊዚያዊ አስተዳደሩ መልሰን በማደራጀት አብረናችሁ ለመስራት ዝግጁ ነን ' ብለዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

" እኛም በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት የፌደራል መንግስት ዓለምአቀፋዊ ወሰኖች የመጠበቅ እና የማስከበር ስልጣን አለው፤ ይህንኑ ስልጣኑ ተጠቅሞ በቦታው የሚገኙ የውጭ ሃይሎች አውጥቶ የግዛት አንድነት እንዲያረጋግጥ በአፅንኦት ጠይቀናል " ብለዋል።

በዚህ ምክንያት " ' ከሃዲዎች ' በሚል ስማችንን ማጠልሸት ተገቢ አይደለም " ሲሉ በምሬት ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ፤ በፌደራል መ/ቤቶች የትግራይ ውክልና ባለመኖሩ ምክንያት የህዝቡ ድምፅ በተገቢው መንገድ ሊሰማ ባለመቻሉ ምክንያት ከጦርነቱ በፊት የነበረው የክልሉ ውክልና እንዲመለስ ለፌደራል መንግስት ጥያቄ መቅረቡን  ሌተናል ጀነራሉ አሳውቀዋል።

በተጨማሪ ፤ " የፕሪቶሪያ ውል አንቀፅ 8 ዓለምቀፍ ወሰኖች በፌደራል መንግስት እንዲጠበቁ ስለሚያዝ ኢትዮጵያ በትግራይ በኩል ከኤርትራ እና ከሱዳን የሚያገናኙ ወሰኖች ጠባቂ ስለሌላቸው የውጭ ሃይሎች እየገቡ ግፎች እየፈፀሙ ፣ ወርቅ ዝውውርን ጨምሮ ሌሎች ህገ-ወጥ ወንጀሎች እየተፈፀመባቸው በመሆኑ ወሰኖቹ በፌደራል መንግስት እንዲጠበቁ መጠየቃቸውን አሳውቀዋል።

#Tigray #TPLF

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

“ ገንዘቡ ይመለስ አይመለስ የሚለው ገና ውሳኔ ላይ አልደረስንም ” - የኮሬ ዞን ትምህርት መምሪያ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ሳርማሌ ወረዳ የሚገኙ መምህራን ከደመወዛቸው ያለፈቃዳቸው የተቆረባቸው ገንዘብ እንዲመለስላቸው በመጠየቃቸው መታሰራቸውን የዞኑና የክልሉ መምህራን ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው ይታወሳል።

ከታሰሩት መምህራን መካከል የተደበደቡ እንደነበሩና የሚመለከታቸው አካላት በጉዳዩ ዙሪያ ተወያይተው ታሳሪዎቹ መፈታታቸውን የዞኑ መምህራን ማኅበር ገልጾልን ነበር።

እስራቱ ለምን እንደተፈጸመ በወቅቱ የጠየቅነው የዞኑ ትምህርት መምሪያ፣ የመምህራኑ ደመወዝ የተቆረጠው የተማሪዎች መፅሐፍ ለማሳተም በተገባው በስምምነት እንደሆነ ነበር ምላሽ የሰጠው።

“ መምህራኑ የታሰሩት ድንጋይ በመወርወር ሌሎችን ረብሸዋል ” በሚል መሆኑን፣ መታሰራቸው ልክ ስላልሆነ በኋላም ውይይት ተደርጎ እንደተፈቱ ነበር የነገረን።

ጉዳዩ ከምን ደረሰ ?

የመምህራኑ ጉዳይ ከምን ደረሰ ? ስንል የጠየቅነው የዞኑ መምህራን ማኅበር፣ ገንዘቡን የመመለስና አለመመለስ በተመለከተ ጉዳይ ገና በሂደት ላይ መሆኑን ገልጿል።

የመምህራኑ ጥያቄ  ያለፈቃዳቸው የተቆረጠው ገንዘብ እንዲመስላቸው መሻት ነበር፤ ገንዘቡ ተመለሰላቸው ? ሙሉ ለሙሉ ስምምነት ተፈጠረ ? ስንል ለዞኑ ትምህርት መምሪያ ጥያቄ አቅርበናል።

ትምህርት መምሪያው ምን ምላሽ ሰጠ ?

ገንዘቡ ተቆርጦ መፅሐፍ ታቶሞበታል። ግን ይሄንን ወደ ታች ወርደን ከመምህራኑ ጋር መወያዬት አለብን። ገንዘቡን ሰጡ መፅሐፉ ታትሞ መጥቷል። 

ስለገንዘቡ ገና አልተስማማንም። ወደ ታች ወርዳችሁ በጋራ እንወያይ የሚል አቅጣጫ ነው ያለው። ግርግሩ፣ እስሩ ተገቢነት እንደሌለው የማረጋጋት ሥራ ቢሰራ ይህን ያህል የተጋነነ አይሆንም ነበር ብለን ነው የተነጋገርነው።

ገንዘቡ ይመለስ አይመለስ በሚለው ገና ውሳኔ ላይ አልደረስንም።

የክልሉ መምህራን ማኀበር፣ የክልሉ ትምህርት ቢሮ፣ የዞኑ ትምህርት መምሪያ፣ የዞኑ መምህራን ማኀበር፣ ችግሩ ተከስቶበት የነበረው የወረዳ መምህራንና አመራር ባለፈው ሳምንት ችግሩ ተከስቶበት የነበረ ቦታ ላይ ቁጭ ብለን ተነጋግረናል።

በመምህራን ማኀበርም፣ በወረዳ ጽ/ቤት በኩልም ችግር ነበር፤ በመምህራን በኩል ቀርቦ አመራር ጋር ተነጋግሮ ችግሩን ከመፍታት ጋር ችግሮች እንደነበሩ ገምግመናል።

መምህራኑ ‘ሳንንስማማ ነው ገንዘቡ የተቆረጠው’ የሚል ነበር የገለጹት። በኛ በኩል ደግሞ ሌሎች ሁለት መዋቅሮች በተመሳሳይ ተስማምተው ስላልቆረጡ ነው የሚለውን ነበር ስንገልጽ የነበረው።

በኋላ መተማመን ላይ ደርሰናል። ጉራማይሌ ነው የሆነው። የተስማማ አካባቢ አለ ያልተስማማ አካባቢ አለ። ችግሩ ይሄው ነበር። የተስማሙም፣ ተስማምተው ሲያበቁ አልተስማማንም ብለው ግርግር ውስጥ የተሳተፉም ነበሩ።

መምህራኑ ወደ መማር ማስተማር ገብተዋል። ችግሩ ምንድን ነው? የሚለውን ከማኀበሩ ጋራ ወደ ታች ወርደን የቀጣይ አቅጣጫ ልናስቀምጥ ተስማምተን፣ ክልሉም አቅጣጫ አስቀምጦ ነው የተለያየነው። ”


#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ንጉስማልት

የንጉስ ማልት ጠርሙስን በስክሪን ሾት ይይዙት ይሆን? በመጀመሪያ ሙከራ ያገኛችሁትን በፌስቡክ ወይም በቴሌግራም ቻናሎቻችን ያጋሩን!

https://fb.watch/wiDa1wrfDa/ /channel/Negus_Malt


#nonalcoholic #ንጉስማልት #DesDesWithNegus #ደስደስበንጉስ #የጣዕምልኬት_የደስታስሜት

Читать полностью…
Подписаться на канал