tikvahethiopia | Неотсортированное

Telegram-канал tikvahethiopia - TIKVAH-ETHIOPIA

1531512

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ

Подписаться на канал

TIKVAH-ETHIOPIA

ስኬት ባንክ አ.ማ የባለአክስዮኖች 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ህዳር 28 ቀን 2017 ዓ.ም በሃያት ሬጀንሲ ሆቴል አካሂዷል፡፡

በጉባኤው ላይ የስኬት ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ጥላሁን ወርቁ የ2023/2024 የሒሳብ ዓመት ዓመታዊ ሪፖርት ለባለ አክሲዮኖች ያቀረቡ ሲሆን ባንኩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ያገኘው የተጣራ ትርፍ 1.54 ቢሊዮን ብር መሆኑን ገልፀዋል፤ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ50 በመቶ ብልጫ አለው፡፡

ባንኩ ያገኘው አጠቃላይ ገቢ 2.3 ቢሊዮን ብር ሲሆን ይህም ከባለፈው ተመሣሣይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ42 በመቶ እድገት አሳይቷል፡፡ በ2023/24 በጀት ዓመት አጠቃላይ ካፒታሉ 7.9 ቢሊዮን ብር የደረሰ ሲሆን ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ31 በመቶ እድገት አሳይቷል፡፡ የባንኩ አጠቃላይ ሀብት 15.9 ቢሊዮን ብር የደረሰ ሲሆን ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ30 በመቶ እድገት አሳይቷል፡፡ ስኬት ባንክ አጠቃላይ የደንበኞቹን ቁጥር ወደ 537,428 ማድረስ የቻለ ሲሆን ይህም ከባለፈው አመት ጋር ሲነፃፀር የ17 በመቶ ዕድገት አሳይቷል፡፡

በበጀት አመቱ የባንኩ ዋና መ/ቤትን ጨምሮ ሁሉንም ቅርንጫፎች በTemenos T24 core banking ሲስተም ማስተሳሰር ተችሏል፡፡ በሌላ በኩል ለደንበኞቹ አስተማማኝና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት Tier Three የተባለ ዘመናዊ የሆነ የመረጃ ማዕከል በመገንባት ወደ አገልግሎት አስገብቷል፡፡ በተጨማሪም የማህበራዊ ኃላፊቱንት ለመወጣት ከባንኩ እና ከሰራተኞች በማስተባበር በበጀት ዓመቱ በአጠቃላይ 10 ሚሊዮን ብር በማውጣት ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እና ማህበራዊ ግልጋሎቶች እንዲውል ተደርጓል፡፡

ስኬት ባንክ
የስኬትዎ መሰረት!

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" የፈረሙት ሁለቱ አገራት ናቸው፣ እኛ ሶማሊላንድ ነን ! " - ሞሐመድ ፋራህ አብዲ

ሶማሌላንድ ስለ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ስምምነት ምን አለች ?

በአንካራው ስምምነት ዙሪያ የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አብዲራህማን ሞሐመድ አብዱላሂ (ኢሮ) ዋዳኒ ፓርቲ ቃል አቀባይ ሞሐመድ ፋራህ አብዲ የሶማሌላንድ መንግሥትን አቋም ለቢቢሲ ሶማሊኛ ተናግረዋል።

ቃል አቀባዩ ፤ " የፈረሙት ሁለቱ አገራት ናቸው፣ እኛ ሶማሊላንድ ነን። ሁለቱ ወንድማማች አገራት የራሳቸውን ስምምነት ነው የተፈራረሙት። እነሱ ተነጋግረው ከስምምነት ላይ መድረሳቸው የተለመደ ነገር ነው። እኛን የሚመለከት አይደለም " ብለዋል።

በተጨማሪ ቀደም ሲል በሶማሊላንድ ሥልጣን ላይ የነበረው መንግሥት ከኢትዮጵያ ጋር የተፈራረመው የመግባቢያ ሰነድ (MoU) ያለበትን ሁኔታን በተመለከተ ተናግራዋል።

ሞሐመድ ፋራህ ፥ " ገና ሥልጣን መረከባችን ነው፤ ከኢትዮጵያ ጋር የተደረገውን ስምምነት አልተመለከትነውም። ነገር ግን የምናየው ይሆናል፤ አይተነው የሶማሊላንድን ጥቅም የሚያስጠብቅ ከሆነ እንሠራበታለን፤ ካልሆነ ግን የሚቀር ይሆናል። ስለዚህ ምን እንሚሆን ለማወቅ መጠበቅ አለብን፣ ከዚያ በኋላ ውሳኔ ይሰጥበታል " ብለዋል። #BBCSOMALI

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ፎቶ ፦ የሶሪያ ፕሬዜዳንት በሽር አላሳድ ከተገረሰሱ በኃላ ዛሬ የመጀመሪያው የጁምአ ሶላት እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ምእመናን በተገኙበት ተካሂዷል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ሕብር ብሩህ የቁጠባ ሒሳብ

ለልጆችዎ የህፃናት ተቀማጭ ሒሳብ  ይክፈቱላቸው፡፡ የሕብር ብሩህ የህፃናት ተቀማጭ ሒሳብ ተጠቃሚ በመሆን ለነጋቸው ጥሪት ያስቀምጡላቸው፡፡

ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!

📞  For more information call our free call center - 995. 
🤳 To receive new information join our Telegram page. /channel/HibretBanket
🌐 Visit our other social media pages and wesite on   linktr.ee/Hibret.Bank

#childrenssavings  #teachkidstosave #HibretBank

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Tigray

" ከፌደራል መንግስት ስልጣን እንዲቸረው የሚለምን አማፂ እና ቂመኛ ቡድን ሌሎችን በባንዳነትና እና በክህደት ለመፈረጅ መድፈሩ አስደማሚ ነው " - በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት

ለሁለት በተከፈሉት የህወሓት አመራሮች መካከል ያለው የመግለጫ ምልልስ አሁንም ቀጥሏል።

በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ፤ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ታህሳስ 2/2017 ዓ.ም ላወጣው መግለጫ መልስ ሰጥቷል።

በዚህም በአቶ ጌታቸው የሚመራው ህወሓት በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራውን ህወሓት " አማፂ እና ቂመኛ " ሲል ፈርጆታል። 

" በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ጊዚያዊ አስተዳደር ቃሉን አጥፈዋል በአጭር ጊዜ ልኩ ለማስገባት በማካሂደው ትግል ህዝቡ ከጎኔ ይቁም የሚል የሚያስደምም መግለጫ ታህሳስ 2/2017 ዓ.ም በመገናኛ ብዙሃን አሰራጭቷል " ሲል የአቶ ጌታቸው ቡድን ከሷል።

" አማፂ እና ቂመኛ ቡድን " በመባል የተገለፀው በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " የፌደራል መንግስት የጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት በሁለት ሳምንት እንዲነሳ ቀጠሮ ተሰጥቶኛል " ሲል እንዳልቆየ " ጊዚያዊ አስተዳደሩን በአጭር ጊዜ መልክ ለማስያዝ ወሰኜ ቃል ገብቻለሁ ተከተሉኝ " የሚል የክተት ጥሪ አቅርቧል ሲል በአቶ ጌታቸው የሚመራው ህወሓት ገልጿል።

" የዚህ አማፂ እና ቂመኛ ቡድኑ አካሄድ ለህዝብ አዲስ አይፈለም " ያለው መግለጫው  " ቡድኑ ከፌደራል መንግስት የሚነጋገረው እና የሚስማማው ሌላ ለትግራይ ህዝብ የሚለው ደግሞ ሌላ " ሲል ገልፆታል።

" ከፌደራል መንግስት ስልጣን  እንዲቸረው የሚለምን አማፂ እና ቂመኛ ቡድን ሌሎችን በባንዳነትና እና በክህደት ለመፈረጅ መድፈሩ አስደማሚ ነው " ሲል  በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት ገልጿል።

" አማፂ እና ቂመኛ ቡድኑ የትግራይን ህዝብ ከፌደራል መንግስት የሚያጋጭ አቅጣጫ እየተከተለ መሆኑ ያወጣው መግለጫ አመላካች ነው " ሲል አክሏል።

የደብረጽዮን (ዶ/ር) ቡድን ህዝቡ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ላይ እንዲያምፅ የሚቻለውን ሁሉ እያደረገ ነው በሚል ተከሷል።

ከፌደራል መንግስት በድብቅ " የውጭ ሽምጋይ ሳያስፈልገን ጉዳያችን ብቻችን መጨረስ እንችላለን " በማለት ስልጣን ይለምናልም ተብሏል።

" ቡድኑ ከስልጣን ውጪ የትግራይ ህዝብ ጉዳይ እንደ ጉዳዩ የማይቆጥር ራስ ወዳድ " ሲል አቶ ጌታቸው የሚመሩት ህወሓት አብጠልጥሎታል።

ከዚህ በተጨማሪ ፤ " ለስልጣን ሲል ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዳይመለሱ የመከልከል እና የማደናቀፍ ስራውን ቀጥሎበታል ፣ ዴሞብላይዜሽን (DDR) እንዲደናቀፍ ሴራዎች እየሸረበ ነው " ሲል ከሷል።

" አማፂ እና ቂመኛ ቡድኑ ቃሉ እና ተግባሩ ለየቅል ናቸው ፤ የህዝብ ችግር እና መከራ እንዳይፈታ በማወሳሰብ እንደ ምክንያት ተጠቅሞ ህዝብን እና መንግስት በማቃቃር በአመፅ ስልጣን ላይ ለመቆየት  ሙጥኝ ያለ ፀረ ህዝብ ነው " ሲል  ፈርጆታል።

የትግራይ ህዝብ ጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሰጡት አስተዳደራዊ ፣ ፓለቲካዊ ተልእኮዎች በተሰጠው ጊዜ አጠናቅቆ በህዝብ የተመረጠ መደበኛ መንግስት እንዲኖር የሚደረገው ትግል በመደገፍ  " አማፂ እና ቂመኛ " ሲል የጠራውን የነ ደብረጽዮን (ዶ/ር) ቢድን " የሚያካሂደውን አፍራሽ ተግባር በፅኑ እንዲቃወመውና እንዲያመክነው ጥሪውን አቅርቧል።

ከትላትና በስቲያ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ፤ በምክትል ሊቀመንበር ጌታቸው ረዳ የሚመራውን ህወሓት " በትግራይ ህዝብ ብሄራዊ ክህደት የፈፀመ ቡድን " ሲል መፈረጁ ይታወሳል።

አቶ ጌታቸው ረዳ እንዲሁም ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በተገኙበት ከቀናት በፊት በአዲስ አበባ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የመሩት ውይይት ቢደረግም ወደ መቐለ ከተመለሱ በኃላ ጠንከር ባሉ መግለጫዎች አንድ ሁለት እየተባባሉ ነው።

የመግለጫዎቹ ይዘት ጠንካራ ከመሆናቸው አልፎ እየተወረወሩ ያሉት ቃላት ነገሩ ከመርገብ ይልቅ እየተካረረ እየሄደ እንዳለ ማሳያ ናቸው።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#MoE

ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ዕድገት እንዳይሰጡ በድጋሜ እገዳ ተጣለባቸው፡፡

ከታህሳስ 1 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በየትኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የተሰጠ እና የሚሰጥ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ዕድገት ተቀባይነት እንደማይኖረው ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

ከጥቅምት 4/2013 ዓ.ም ጀምሮ በሥራ ላይ የነበረውንና በትግበራ ወቅት ክፍተት የታየበት "የአካዳሚክ ሠራተኞች የደረጃ ዕድገት መመሪያ" በመሻሻል ላይ እንደሚገኝ ሚኒስቴሩ አስታውሷል፡፡

በዚህም ማሻሻያው ተጠናቆ ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እስከሚላክ ድረስ በሁሉም ተቋማት የፕሮፌሰርነት ዕድገት አሰጣጥ ለጊዜው መታገዱን ሚኒስቴሩ ሐምሌ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ለተቋማቱ በጻፈው ደብዳቤ ገልጾ ነበር፡፡

ይሁን እንጂ " አንዳንድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ክልከላውን በመጣስ፣ መመሪያውን ባልተከተለ፣ ግልጽነት በጎደለው፣ ወጥነት በሌለው እና ከትምህርት ጥራት ማስጠበቂያ ሪፎርሞች ጋር በሚጣረስ መልኩ የፕሮፌሰርነት ዕድገት መስጠት መቀጠላቸውን ለመረዳት ችለናል " ብሏል በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በቀን ታህሳስ 1/2017 ዓ.ም ተፈርሞ ለተቋማቱ የተላከ ደብዳቤ።

ከታህሳስ 1 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በየትኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የተሰጠ እና የሚሰጥ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ዕድገት ተቀባይነት እንደማይኖረው የገለፀው ትምህርት ሚኒስቴር፤ የተቋማቱ ከፍተኛ አመራር አካላት እና የሥራ አመራር ቦርድ የተሻሻለው መመሪያ ተጠናቅቆ እስኪደርሳቸው ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁ ጠይቋል፡፡

Via @tikvahuniversity

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#DStvEthiopia

በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የማንቼስተር ደርቢ በጎጆ ፓኬጅ💥
63ተኛውን ጨዋታዎቸውን የሚያደርጉት ሁለቱ ቡድኖች ማን ሲቲ 25 ጊዜ ሲያሸንፍ ማን ዩናይትድ 28 ጊዜ ድል አድርጓል! ሁለቱ ብድኖች 9 ጊዜ በአቻ ተለያይተዋል

🏆 ማን ሲቲ ከማን ዩናይትድ ጋር የሚያደርጉትን ጨዋታ ጨምሮ 10 የፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎችን በጎጆ ፓኬጅ በ400 ብር ብቻ በቀጥታ ይከታተሉ!

ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh

ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇
www.dstv.com/en-et

#PremierLeagueallonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Somaliland

የአዲሱ የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አብዱረህማን መሀመድ አብዱላሂ (ኢሮ) በዓለ ሲመት በሀርጌሳ እየተከናወነ ይገኛል።

በበዓለ ሲመቱ ላይ የቀድሞ ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ፣ የቀድሞ ፕሬዜዳንት ዳሂር ሪያሌ ካሂን፣ የአሜሪካው አምባሳደር ሪቻርድ ሪሌይን ጨምሮ የሀገራት ዲፕሎማቶች ተወካዮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ የሶማሌ ክልል ፕሬዜዳንት ሙስጠፋ ሙሁመድ በዚሁ የበዓለ ሲመት ስነ ስርዓት ላይ ለመገኘት ትላንት ልዑካቸውን ይዘው ሀርጌሳ መግባታቸው ይታወሳል።

ከሶማሊያ ተነጥላ ላለፉት በርካታ አመታት ራሷን የምታስተዳድረው ሶማሊላንድ በሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እንዲሁም ደግሞ በዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ምርጫ በግንባር ቀደምነት ትታወቃለች።

ቪድዮ፦ አዲሱ የሶማሊላንድ ፕሮዜዳንት እና የቀድሞው ፕሬዜዳንት በፈገግታ ተሞልተው ወደ አዳራሽ ሲገቡ።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ሶማሊያውያኑ ምን እያሉ ነው ?

በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ሶማሊያውያን በተለይም አክቲቪስቶች " ሀሰን ሼክ ሀገራችንን ሸጠብን ፤ በዲፕሎማሲ ተበልጦ አስበላን " ማለት ጀምረዋል።

ኢትዮጵያ የሶማሊያን ሉላዓዊነት፣ አንድነት እና የግዛት አንድነት ባከበረ ሁኔታ ዘላቂነት ያለው አስተማማኝና ደህንነቱ የተጠበቀ የባህር በር ታገኛለች መባሉ የሶማሊያ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን አበሳጭቷቸዋል።

በማህበራዊ ሚዲያ በተለይ በX ቪላ ሶማሊያ ገጽ ስር ፤ ከወራት በፊት ሲያሞጋግሷቸው የነበሩትን ፕሬዜዳንታቸውን ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ላይ ውግዘት ማዝነብ ጀምረዋል።

እኚህ አስተያየት ሰጪዎች ምን እያሉ ነው ?

➡️ " ሀሰን ሼክ ባህራችንን ሸጠብን። ካደን ፤ ከሀዲ ነው "

➡️ " እንዴት በድርድሩ ላይ ሆነ በስምምነቱ ላይ ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ጋር ያደረገችው የባህር በር ለማግኘት የፈረመችው የመግባቢያ ስምምነት / MoU አልተነሳም ፤ በግልጽ ቀርቷል ለምን አልተባለም "

➡️ " አዋረደን ! ለሶማሊያ ጨለማ ቀን ነው "

➡️ " ስለ ኢትዮጵያ የቀጣይ የሰላም ማስከበር ተሳትፎ (ሶማሊያ ውስጥ) ለምን አለተነሳም "

➡️ " ዘላቂነት እና አስተማማኝ የባህር በር ኢትዮጵያ ስታገኝ ሶማሊያ በምላሹ ምን ታገኛለች ? "

➡️ " ሁሉንም ኢትዮጵያ የፈለገችውን ነው የተቀበልነው፤ ኢትዮጵያ በመረጠችው መንገድ ሄዳ ፤ በዚህም በዚያ ብላ ባህር በር ስታገኝ እኛ ምን አገኘን ? " 

➡️ " ኢትዮጵያ ዲፕሎማሲው እና ድርድሩ በልጣ ባህር በር አሳካች " ... የሚሉ አስተያየቶችን በመስጠት ፕሬዜዳንታቸው ላይ ውግዘት እና የስድብ ናዳ እያወረዱ ነው።

አንዳንዶቹ ከቦታው ይነሳልን ወደማለትም ገብተዋል።

120 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ " በፍጹም የማልተወው የህልውዬ ጉዳይ ነው " ብላ በይፋና በድፍረት አደባባይ ከወጣች በኃላ ጉዳዩ ከፍተኛ አጀንዳ ሆኖ ዓለም አቀፍ መወያያ መሆን ችሏል።

ከሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ከተፈራረመች በኃላ ሶማሊያ አኩርፋ ብዙ ስትል ከርማለች ፤ ከኢትዮጵያ ጋርም ተጎረባብጣለች።

ፕሬዜዳንቷ እና አስተዳደራቸው በየጊዜው ወደ ሚዲያ እየወጡ ፦
- ከኢትዮጵያ ጋር በፍጹም አንነጋገርም፤
- የኢትዮጵያ ወታደሮች በሰላም ማስከበር ላይ አይሳተፉም፤
- እንድንነጋገር ከፈለገች MoU ቀዳ ጥላ በይፋ ይቅርታ ትጠይቅ ይህ ካልሆነ ኢትዮጵያን አንሰማትም፤
- በኢትዮጵያ ያሉ ታጣቂዎችን እንደግፋቸዋለን / እናስታጥቃለን፤
- ኢትዮጵያ ለሶማሊያ ደሟን እንዳልገበረችላት የኢትዮጵያ እድገት እንቅልፍ ከሚነሳቸው አካላት ጋር እየሄደ ጥምረት ሲፈጥር
- ከኢትዮጵያ ለመነጋገር ቅድመ ሁኔታዎችን ሲደረድር ... ሲዝት ፣ ሲፎክር ከርሟል።

በመጨረሻ በቱርክ አሸማጋይነት አንካር ሄደው ከኢትዮጵያ ጋር ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

በስምምነቱ ይፋዊ ሰነድ ላይ ሆነ በመሪዎች መግለጫ ምንም ቦታ ላይ ስለ ሶማሊለንዱ MoU አለመነሳቱ ፤ ማብራሪያ አለመሰጠቱ እንዲሁም በግልጽ ተሰርዟል አለመባሉን በማንሳት " ኢትዮጵያ የምትፈልገውን አገኘች " በማለት ሶማሊያውያን በፕሬዜዳንታቸው ላይ ተነስተዋል።

#TikvahEthiopia
#Ethiopia🇪🇹
#Seaaccess

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#TecnoAI

ዘምኖ የሚያዘምኖ፣ ህይወቶን የሚያቀል፣ ከበርካታ አርቴፊሻል ቴክኖሎጂ ካመጣቸው ከፍ ያሉ ቴክኖሎጂዎች ጋር የሚያስተዋውቆት በኪስዎት ውስጥ ይዘውት የሚዞሩት ፕሮፌሽናል አጋዥ ቴክኖ ኤ አይ ወደ እርሶ እየመጣ ነው፡፡

ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመከተል የቴክኖ ቲክቶክ ገጽ ፎሎው በማድረግ እና Bio ላይ ያለውን ሊንክ ተጭነው በመመዝገብ ታህሳስ 10 በስካይላይት ሆቴል በሚካሄደው የሀገራችን ትልቁ የኤ አይ ሁነት ላይ ይሳተፉ፡፡

tecnoet" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@tecnoet

@tecno_et @tecno_et

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Ethiopia #Somalia

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ስምምነት ላይ ደረሱ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በቱርክ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን አሸማጋይነት በቱርክ አንካራ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

(ዝርዝር መረጃዎችን ይጠብቁ)

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Tigray

በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ፤ በምክትል ሊቀመንበር ጌታቸው ረዳ የሚመራውን ህወሓት " በትግራይ ህዝብ ብሄራዊ ክህደት የፈፀመ ቡድን " ሲል ፈረጀ።

በምክትል ሊቀ-መንበር ጌታቸው ረዳ የሚመራውን ህወሓት " ብሄራዊ ክህደት ፈፅሟል " ሲል የፈረጀው ማእከላዊ ኮሚቴ " ቡድኑ ከአፍራሽ ተግባሩ እንዲቆጠብ " መላው የትግራይ ህዝብ እና አባላት እንዲታገሉት ሲል ጥሪ አቅርቧል።

ማእከላዊ ኮሚቴ ፤ በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት " የትግራይ ህዝብ መብት እና ራስን በራስ የማስተዳደር መገለጫ የሆኑት ምክር ቤቶች እንዲፈርሱ ለፌደራል መንግስት ጠይቀዋል " ሲል ገልፀዋል።

በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ በአዲስ አበባ ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስተር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ካካሄደው ውይይት መልስ ባወጣው መግለጫው ነው ይህን ጠንከር ያለ ፍረጃ ያቀረበው።

በተጨማሪ በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት የትግራይ ሉአላዊ ግዛት ሳይረጋገጥ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ሳይመለሱ የትግራይ ሰራዊት በዲሞብላይዜሽን (DDR) ምክንያት በችኮላ እንዲሰናበቱ እያደረገ ነው ብሏል።

በትግራይ በኩል የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ፈራሚን ጥያቄ ውስጥ በሚከት መልኩ ፤ " የፕሪቶሪያ ውል ፈራሚ ባለቤት ማን እንደሆነ የኢትዮጵያ መንግስት እንዲወስን " በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት ጠይቀዋል ሲልም አክሏል።

በክልሉ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን እየተካሄደ ነው ከሚባለው ህገ ወጥ የወርቅ ማእድን ማውጣት እና ማዘዋወር ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያን በትግራይ ክልል ከኤርትራ በሚያዋስኑዋት አከባቢዎች የአገር መከላከያ ሰራዊት እንዲሰፍር በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት ለፌደራል መንግስት ጥያቄ እንዳቀረበም በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ገልጿል።

እስካሁን በእነ አቶ ጌታቸው ረዳ በኩል የተሰጠ ምላሽ የለም።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Jubaland #Somlaia

ከሶማሊያ ፌዴራል መንግስት ጋር ሁሉንም ግኑኝነቴን አቋርጫለሁ ፤ ተቆራርጫለሁ ያለው የጁባላንድ አስተዳደር እና የሶማሊያ ፌዴራል መንግሥት ዛሬ ወደ ግጭት ገብተዋል።

ዛሬ ከቀትር ጀምሮ ራስኮምቦኒ ላይ ከፍተኛ ውጊያ መደረጉ ተነግሯል።

ሁለቱም ወገኖች ግጭት መነሳቱን ገልጸው ግጭቱን ማን አስጀመረ በሚለው ላይ እርስ በእርስ እየተወነጃጀሉ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#SafaricomEthiopia

🎉ለወራት የፈለግናቸውን ኳስ ጨዋታዎች ሁሉ ከዳር እስከ ዳር በሚገኘው በሳፋሪኮም ኔትወርክ ላይ በDSTV በቀጥታ እንከታተል! ⚽️

በM-PESA ላይ ስንገዛ የ6ወር 90ጊባ በ6,000 ብር ብቻ! 

🔗የM-PESAን ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቦታችንን /channel/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይንም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!

የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉/channel/Safaricom_Ethiopia_PLC

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም ቻናላችን /channel/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom #1Wedefit
#Furtheraheadtogether

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Berbera

የሶማሌላንድ የገንዘብ እና ልማት ሚኒስቴር ዛሬ በሶማሌላንድ በርበራ ወደብ የኢትዮጵያ ትራንዚት ማሳለጫ ቢሮ ስራ መጀመሩን ገልጿል።

የሶማሌላንድ የንግድና ቱሪዝም ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አብዲረሺድ ኢብራሂም ደግሞ " የሶማሌላንድ መንግሥት በበርበራ ወደብ የኢትዮጵያ ትራንዚት ማሳለጫ ቢሮ ስራ አስጀምሯል " ሲሉ ይፋ አድርገዋል።

" ይህ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድና ኢንቨስትመንት ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ ምዕራፍ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ይህ ውጥን ቀጠናዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስርን ለማጠናከር ሶማሌላንድ ያላትን ቁርጠኝንተ ያሳያል ሲሉ አክለዋል።

ቢሮው በወደቡ የሚራገፉ ጭነቶችን ወደ ኢትዮጵያ የተለያዩ መዳረሻዎች እንዲጓጓዙ የሚያሳልጥ ነው ተብሏል።

በሌላ በኩል ፥ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴሌቪዥን በይፋዊ ማስጀመሪያ ስርዓቱ ላይ ወደቡን የሚያስተዳድረው የተባበሩት አረብ ኤሜሬትሱ DP World በርበራ ዋና ስራ አስፈፃሚ ስፓቺ ዋታንቫራቺ ተገኝተው እንደነበር ገልጿል።

ዋና ስራ አስፈጻሚው ፤ " ይህ ቢሮ ወደቡ ላይ የሚራገፉ የተለያዩ ጭነቶችን ወደ ኢትዮጵያ እንዲጓጓዙ የሚያሳልጥ ነው " ብለዋል።

የሶማሌላንድ የገንዘብ እና ልማት ሚኒስትሩ ሳድ (ዶ/ር) " ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ ግንኙነታቸው የተጠናከረ ነው ፤ 120 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ አማራጭ ወደቦችን መጠቀም ትችላለች " ማለታቸውን ብሔራዊ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

Photo Credit : #SomalilandFinanceDevelopment

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ደመወዝ

🚨 " የሚከፈለው ክፍያና እንከፍላለን ብለው የሚያሳውቁት በጣም የሚያስቅ ልዩነት ያለው ነው " - ገቢዎች ቢሮ

🔴 " ቢሮው የፈጸመው ህገወጥ ድርጊት ነው " - የህግ ምሁር


የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ሆቴሎች እና መጠጥ ቤቶችን ጨምሮ በተመረጡ የንግድ መስኮች የሚሰሩ ሰራተኞችን ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እና የሰራተኞቻቸውን ብዛት የሚተምን ተመን አውጥቶ ስራ ላይ አውሏል።

ሆቴሎች፣ ስጋ ቤቶች፣ መጠጥ ቤቶች ፣ ምግብ ቤቶች፣ ካፍቴሪያዎችን ጨምሮ ሌሎች የንግድ ዘርፎች ላይ የሰራተኞች ደመወዝን በተመለከተ አሰሪዎች ትክክለኛ መረጃ ስለማይሰጡ ግብር እያጭበረበሩ ነው ብሏል።

ይህንን ተከትሎም ነው ይህን አሰራር መዘርጋቱን ገልጻል።

ስራ ላይ በዋለው ተመን መሰረት ፦
👉 የሆቴሎች ከ32 እስከ 50 ሰራተኞች
👉 ባርና ሬስቶራን ከ20 እስከ 24 ሰራተኞች
👉 ካፍቴሪካ ከ17 እስከ 25 ሰራተኞች
👉 ምግብ ቤት ከ17 እስከ 22 ሰራተኞች
👉 ምግብ፣ መጠጥ እና ስጋ ቤት ከ28 እስከ 48
👉 ስጋ ቤት እና መጠጥ ንግድ ከ20 እስከ 28 ሰራተኞች ይኖራቸዋል ተብሎ ተተምኗል።

በዚህ መሰረት የደመወዝ ግብር በተጠቀሰው የሰራተኛ ቁጥር ልክ ይጠየቃሉ።

ከአስተናጋጅ፣ ጥበቃና የፅዳት ሙያ ውጭ ላሉ ሰራተኞች ትንሹ የሚከፍሉት ደመወዝ 5,000 ብር ሆኖ ተተምኗል።

የወር ደመወዝ ተመኑ ምን ይመስላል ?

➡ ስጋ ቤት እና መጠጥ ንግድ
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ5,000 እስከ 9,500
° ካሸር 5,000 እስከ 6,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,000 እስከ 18,000
° አስተናጋጅ ከ3,000 እስከ 3,500
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ2,500 እስከ 3,000
° ዋና ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 7,000
° ረዳት ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 5,500
° ስጋ ጠባሽ ከ6,000 እስከ 9,000

➡ ምግብ፣ መጠጥ እና ስጋ ቤት
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ8,000 እስከ 13,500
° ካሸር 5,000 እስከ 7,000
° ዋናው ሼፍ ከ6,000 እስከ 18,000
° አስተናጋጅ ከ2,500 እስከ 4,000
° ፅዳት ከ3,000 እስከ 3,500
° ጥበቃ ከ3,500 እስከ 4,000
° ዋና ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 6,000
° ረዳት ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 5,500
° ስጋ ጠባሽ ከ6,000 እስከ 9,000

➡ ምግብ ቤት
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ / ከ6,000 እስከ 10,000
° ካሸር 5,000 እስከ 6,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,000 እስከ 7,000
° አስተናጋጅ ከ2,000 እስከ 3,000
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ2,500 እስከ 3,000

➡ ካፍቴሪያ
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ6,000 እስከ 7,000
° ካሸር 5,000 እስከ 7,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,500 እስከ 7,000
° አስተናጋጅ ከ2,500 እስከ 3,000
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ2,500 እስከ 3,000
° ሻይ ቡና / ጁስ አስተናጋጅ ከ5,000 እስከ 8,000

➡ ባርና ሬስቶራንት
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ7,000 እስከ 10,000
° ካሸር 5,000 እስከ 6,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,000 እስከ 7,000
° አስተናጋጅ ከ2,000 እስከ 2,500
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ3,000 እስከ 3,500

➡ ሆቴል
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ8,000 እስከ 13,500
° ካሸር 5,000 እስከ 7,000
° ዋናው ሼፍ ከ6,000 እስከ 18,000
° አስተናጋጅ ከ2,500 እስከ 4,000
° ፅዳት ከ3,000 እስከ 3,500
° ጥበቃ ከ3,500 እስከ 4,000
° ዋና ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 6,000
° ረዳት ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 5,500

ወርሃዊ ደመወዝ ተተምኗል።


ይህ ለአንድ ሰራተኛ ይከፈላል ተብሎ የተተመነ ነው።

በዚህ ተመን ባለቤቶቹ የደመወዝ ግብር ሲከፍሉ ለተጠቀሱት የስራ መደቦች " ከዚህ ያነሰ ነው የምከፍለው " ማለት አይችሉም።

የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ምን አሉ ?

ቢሮው ተመን ማውጣቱን አረጋግጠዋል።

ዳይሬክተሩ " በጥናት ላይ ተመስርቶ ነው ውሳኔው የተቀመጠው።

ከደመወዝ ግብር ጋር በተያያዘ የሚከፈለው ክፍያና እንከፍላለን ብለው የሚያሳውቁት በጣም የሚያስቅ ልዩነት ያለው ነው። በጣም ትልቅ ክፍተት ነው ያለው እኛ በከተማችን ያሉ የስራ መደቦችን በዝርዝር ጥናት አድርገን አብዛኛው በትንሹ የሚከፈላቸው ከ5000 ብር በላይ መሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም።

ለፅዳት እና የቤት ሰራተኛ እንኳን ስንት እንደሚከፈል ይታወቃል።

እነሱ እንከፍላለን ብለው የሚያቀርቡት ዋጋ በጣም በጣም ዝቅተኛ ነው። ያንን ምንቀበልበት ሁኔታ የለም አሰራሩም አይፈቅድም። ጥናት ላይ ተመስርተን ዝቅተኛውን ተመን አስቀምጠናል " ብለዋል።

ገቢዎች ቢሮ ከተማውን የምታመነጨውን ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ ኃላፊነት እንደተጣለበትና በዚህም ምክንያት ዝቅተኛ የደመወዝ ተመን ስራ ላይ እንዳዋለ አሳውቋል።

ጉዳዩ በሚመለከተው አካል ህግ ሆኖ ሳይወጣ ገቢዎች ቢሮ ዝቅተኛ የደመወዝ መጠን አስቀምጦ ግብር መሰብሰብ ይቻላል ወይ ? የሚለው የህግ ጥያቄ ተነስቶበታል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ንግድና የኢኮኖሚ ህጎች መምህር አቶ ጌዲዮን ወ/ዮሐንስ ምን ይላሉ ?

" ድርጊቱ ህገወጥ ነው።

እስካሁን ባለው ነባራዊ  ሁኔታ በገቢዎች በኩል አነስተኛ ደመወዝን መወሰን ያንን ተከትሎ ግብር መሰስበብ እስካሁን ባለው የህግ ማዕቀፍ ይህንን የሚፈቅድ ነገር ስለሌለ ህጋዊ አይደለም።

በተለይ ከግብር ጋር ተያይዞ ህገመንግስቱ ግብር የሚጣለው በህግ ነው ይላል። በአንድ አስፈጻሚ / በአንድ የስራ ክፍል ኃላፊ ወይም እንደ ገቢዎች ቢሮ አይነት ደብዳቤን መሰረት አድርጎ ደመወዝን መወሰን አይቻልም።

ደመወዝ ግብር የሚከፈልበት አንድ ገቢ ነው። ይሄም ታክስ ቤዝ / ግብር የሚጣልበት አንድ ገቢ እንለዋለን። እሱ በህግ ተወስኗል። ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ከዚህ እስከዚህ ሲሆን ይሄን ያህል ... ከዚህ እስከዚህ ይሄን ያህል ... ብር እየተባለ በግብር አዋጃችን ላይ ተቀምጧል።

በዚህ በገቢ ግብር አዋጅ ላይ በተለያዩ የስራ ክፍሎችና አይነቶች የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ዝቅተኛውን የደመወዝ መጠን ለመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል የሚል ህግ የለም ኢትዮጵያ ላይ።

በህግ ባልተከለከለበት / አይቻልም ባልተባለበት ሁኔታ አንድ ሰው 10,000 ብር ነው ዝቅተኛ መቅጠር የምትችለው ፣ በ8,000 ነው በ18,000 እያሉ ሰንጠረዥ ማውጣት የሰዎችን የመዋዋል ነጻነት ይጎዳል።

ድርጊቱ፦
- የመዋዋል ነጻነትን የሚገድብ
- ህገመንግስታዊ ድንጋጌን የሚጥስ ተግባር ነው።

ቢሮው ' ግብር እየተጭበረበርኩ ነው ' ብሎ ካሰበ የተለያዩ የምርመራ ስራዎችን በመስራት ፣ የስራ ውሉን ከአሰሪዎቹ በመቀበል ይሄም ደግሞ በህግ አነስተኛ ደወመዝን በማውጣትና በመደንገግ ነው። እንጂ የግብር ማጭበርበር ለመከላከል ተብሎ የገቢ ግብርን በዚህ መንገድ ለማስተዳደር መሞከር የታክስ ህግን፣ መርሆችን የሚጥስ ነው። "

NB. በኢትዮጵያ እስካሁን ድረስ መንግሥት ለግሉ ዘርፍ ለተቀጣሪዎች ዝቅተኛ ደመወዝ ወለል አላስቀመጠም። ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲያስቀምጥ ጥረቶች እየተደረጉ እነደሆነ ይታወቃል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው። #ሸገርኤፍኤም

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ምንድነው ያስተላለፈው ውሳኔ ?

💡" ምሽት መብራት ማጥፋት እንዲከለከል እና ሙሉ የመብራት አገልግሎት እንዲኖር  ውሳኔ ተላልፏል ! "

🌃 " ዋና እና መጋቢ መንገድ ላይ የሚገኙ የንግድ እና የአገልግሎት መስጫ ተቋማት እስከ ምሽቱ 3፡30 አገልግሎት እንዲሰጡ ተወስኗል ! "

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ዛሬ 4ኛ ዓመት 4ኛ መደበኛ ስብሰባ አካሂዶ ነበር።

የተለያዩ አጀንዳዎች ላይም ተወያይቶ አፅድቋል፡፡

ከነዚህም አንዱ ፥ በሁሉም የከተማዋ ዋና ዋና መንገዶች ያሉ የንግድ እና የአገልግሎት መስጫ ተቋማት እስከ ምሽቱ 3፡30 ለህብረተሰቡ የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚል ነው።

ሌላኛው የምሽት ትራንስፖርትን ይመለከታል።

በዚህም ከተማ አስተዳደሩ የኤሌክትሪክ አውቶቡሶች ማቅረብ በመጀመሩ የኤሌክትሪክ አውቶቡሶች አገልግሎት አስተዳደር ረቂቅ መነሻ ሀሳብ መርምሮ በመወያየት በመንግስት እና  የግል አጋርነት (PPP) እንዲተዳደሩ ብሎም በከተማዋ የመንግስት እና የግል ትራንስፖርት አገልግሎት እስከ ምሽቱ 4፡00 ድረስ ግልጋሎት እንዲሰጡ ተብሏል።

በሁሉም የኮሪደር ልማት በሚተገበርባቸው ቦታዎች የትራንስፖርት አገልግሎት እለታዊ የጊዜ ሰሌዳ እንዲጠቀሙ እንዲደረግ ተወስኗል።

ከዚህ በተጨማሪ ካቢኔው ሁሉም ዋና መንገድ እና መጋቢ መንገድ ላይ ያሉ ተቋማት፣ ህንፃዎች እንዲሁም የግልና የመንግስት ቢሮዎች ምሽት መብራት ማጥፋት እንዲከለከል እና ሙሉ የመብራት አገልግሎት እንዲኖር  ውሳኔ ተላልፏል።

በተጨማሪ ካቢኔው ፦

- የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ብክለት መከላከል ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ለከተማዋ ነዋሪዎች ጤና፣ ፅዳት እና ውበት ወሳኝ እና ጠቃሚ ስለሆነ ደንቡን በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

- በከተማ ፕላን ልማት ቢሮ የተዘጋጁና የሚዘጋጁ የአካባቢ ልማት ፕላን ዝግጀት፣ አፈፃፀም ቁጥጥር እና ደንብ ማሻሽያን መርምሮ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል፡፡

#AddisAbaba

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#EthioTelecom

✨🤩 ታላቅ ቅናሽ!! እንዳያመልጥዎ!

💁‍♂️ እስከ 50% በሚደርስ ቅናሽ ያቀረብናቸውን የስልክ ቀፎዎች፣ ስማርት ሰዓቶች፣ ቻርጀሮችና ኬብሎች እንዲሁም የኢንተርኔት ሞደሞችና ራውተሮች የራስዎ ያድርጓቸው!!

🗓 እስከ ጥር 19/2017 ዓ.ም ብቻ!

📍 በሁሉም የአገልግሎት ማዕከሎቻችን ያገኟቸዋል።

በተጨማሪ የአዲስ አበባ ደንበኞቻችን በቴሌገበያ https://telegebeya.ethiotelecom.et ማግኘት ይችላሉ፡፡

#Sale #Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #SmartAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#MoE

በወጥነት ይተገበራል የተባለው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሜኑ ምን ይመስላል ?

የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዕለታዊ የምግብ ወጪ ከታህሳስ 01/2017 ዓ.ም ጀምሮ 100 (መቶ ብር) እንዲሆን መወሰኑ ይታወቃል።

የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የምግብ ሜኑም ሁሉም ጋር ወጥ እንዲሆንብ እየተሰራ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር መግለጹ አይዘነጋም።

ይህንን ተከትሎ ፤ የተማሪዎች የምግብ አቅርቦት በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በወጥነት እንዲከናወን ትምህርት ሚኒስቴር ከምግብ ተመን ማሻሻው ጋር የተጣጣመ ስታንዳርድ የምግብ ሜኑ በማዘጋጀት ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ልኳል።

የምግብ ሜኑው ዝቅተኛውን መስፈርት መሠረት በማድረግ መዘጋጀቱን የገለጸው ሚኒስቴሩ ተቋማት ከባቢያዊ ነባራዊ ሁኔታን ከግምት ውስጥ በማስገባት በአንድ ተማሪ ሳምንታዊ ወጪው ከ700 (ሰባት መቶ) ብር ባልበለጠ መልኩ ስራ ላይ መዋል እንዳለባቸው ማሳሰቢያ አስተላልፏል።

ለዩኒቨርሲቲዎች በተላከው የምግብ ሜኑ ከላይ የተያያዘ ሲሆን ፦

👉 ቁርስ ላይ ፦ እንጀራ ፍርፍር / ሩዝ + ዳቦ + በሻይ ፣ ቅንጬ ፣ ስልስ ፣ ማካሮኒ ተካተለዋል።

👉 ምሳ ላይ ፦ ምስር/አተር ክክ/ሽሮ / አተር / ባቄላ / ድንች / አትክልት ማለትም ጎመን ፣ድንች፣ ካሮት የመሳሰሉ / ፓስታ /  + እንጀራ / ዳቦ ፣ ከዚህ በተጨማሪም በሳምንት 1 ቀን ስጋ በምስር/በድንች/ በክክ (በዳቦ ወይም በእንጀራ) ተካተዋል።

👉 እራት ላይ ፦ ምስር/ክክ/ፓስታ / ሽሮ + በእንጀራ/ዳቦ ፣ ከዚህ በተጨማሪ በሳምንት 1 ቀን ስጋ በምስር/በድንች/ በክክ (በዳቦ ወይም በእንጀራ) ተካተዋል።


🔵 ለበለጠ መረዳት ከሰኞ እስከ እሁድ የተከፋፈለውን የምግብ ሜኑ ከላይ መመልከት ይቻላል።

አጠቃላይ ትምህርት ሚኒስቴር ለዩኒቨርሲቲዎች በላከው የምግብ ሜኑ መሰረት ለቁርስ ፣ ለምሳ፣ ለእራት ለአንድ ተማሪ የተመደበው 100 ብር ነው።

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት / ለመንግሥት ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎች የተመደበው ዕለታዊ የምግብ በጀት በየጊዜው እየጨመረ ያለውን የምግብ ዋጋ ንረት ሊሽፍን ባለመቻሉ መንግሥት በፊት የነበረውን ዕለታዊ የተማሪ ምግብ ወጪ 22 ብር ወደ 100 ብር ከፍ አድርጎታል።

(በትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ ኮራ ጡሸኔ ተፈርሞ ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የተላከው ሰርኩላር ከላይ ተያይዟል)

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" የመኖሪያ ቤት ችግር ባለበት ከተማ ውስጥ ክፍት ቤት ማስቀመጥም ፍትሐዊ አይደለም " - የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን

የአዲስ አበባ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በጨረታና በዕጣ የተላለፉ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እስከ ኅዳር 30 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ ባልገቡት ባለንብረቶች ላይ ውሳኔ እንደሚያስተላልፍ አስታውቋቃ።

የኮርፖሬሽንኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሽመልስ ታምራት ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?

- ከታኅሳስ 1 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ መሠረት ወደ ቤታቸው የገቡና ያልገቡትን የመለየት ሥራ ተጀምሯል።

- ከመስከረም 20 ቀን እስከ በጥቅምት 30 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ የቤት ባለንብረቶች እንዲገቡ ማሳሰቢያ ተሰጥቶ ነበር በድጋሚ ቀነ ገደቡን በማራዘም እስከ ኅዳር 30 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ ባለንብረቶች እንዲገቡ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶ ነበር። 

- ባደረገው ምልከታ ወደ ቤታቸው የገቡ፣ ያከራዩና በዕድሳት ላይ የሚገኙ አሉ።

- የተቀመጠው ቀነ ገደብ በመጠናቀቁ በሁሉም ሳይቶች የመለየት ሥራ ይጀመራል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በዕጣ ተላልፎባቸው ቤታቸው ያልገቡትን ባለንብረቶች፣ ቤቶቹን ምን ለማድረግ ታስቧል ? ለሚለው ጥያቄ " ቀነ ገደቡ በቅርቡ በመጠናቀቁና ወደ ቤታቸው ያልገቡበትን ማለትም ፦
° በሕይወት አለመኖር፣
° መግባት አለመፈለግ፣
° በአገር ውስጥ አለመኖር፣
° በሕግ በተያዙ ጉዳዮችና በሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች መሆኑን ማጣራት ይደረጋል " ብለዋል፡፡

በዕጣና በጨረታ ተላልፈው ባለቤቶቻቸው ያልገቡባቸው ቤቶች ምን ያህል ናቸው ? ለሚለው ጥያቄ " መጠናቸው ይለያይ እንጂ በሁሉም ሳይቶች እንደሚገኙ፣ ቁጥራቸውን ግን ይህን ያህል ነው ለማለት ያስቸግራል " ሲሉ መልሰዋል።

" ዋናው ነገር የቁጥር ጉዳይ አይደለም፤ ክፍት በመሆናቸው ምክንያት ነዋሪዎች ለተለያዩ ችግሮች መዳረጋቸውንና ከተለያዩ ሳይቶች በርካታ አቤቱታዎች ለኮርፖሬሽኑ እየደረሱ በመሆኑ ነው  " ሲሉ ገልጸዋል።

" የመኖሪያ ቤት ችግር ባለበት ከተማ ውስጥ ክፍት ቤት ማስቀመጥም ፍትሐዊ አይደለም " ያሉ ሲሆን " ባለቤቶቹ ያልገቡባቸው ቤቶች ከተለዩ በኋላ በቅርቡ ውሳኔ ይሰጣል " ብለዋል።

ኮርፖሬሽኑ በሰጠው የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ የቤት ባለቤቶቹ ወደ ቤታቸው የማይገቡ ከሆነ፣ በሕግ አግባብ ውል የሚቋረጥ መሆኑን ከዚህ ቀደም መግለጹ ይታወሳል።

በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ የማይገቡ ነዋሪዎች የሽያጭ ውላቸው ከማቋረጥ ባለፈ በቤታቸው ውስጥ ለሚፈጸም ማንኛውም ሕገወጥ ድርጊት ተጠያቂ እንደሚሆኑ መግለጹ አይዘነጋም፡፡

መረጃውን ከሪፖርተር ጋዜጣ ነው የተገኘው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" የጦር ሰፈሩን መልሰን ተቆጣጥረናል " - የጁባላንድ ባለስልጣናት

የሶማሊያ የፌዴራሉ ሰራዊት የጁባላንድ ከፊል ራስ ገዝ ክልልን ለቆ መውጣቱት ተነግሯል።

በሶማሊያ መከላከያ ሰራዊት እና በጁባላንድ ከፊል ራስ ገዝ ኃይሎች መካከል ትናንት ረቡዕ ከተቀሰቀሰ ዉጊያ በኋላ የሶማሊያ መከላከያ ግዛቲቱን ለቆ መውጣቱን የፌዴራሉ መንግስት ዛሬ አስታውቋል።

የመንግስት እና ወታደራዊ ባለስልጣናት በራስ ካምቦኒ ከተማ እና አካባቢው ለበርካታ ሰዓታት ለቆየው ዉጊያ  የጁባላንድ ፕሬዜዳንት አህመድ ማዶቤን በግጭት ቀስቃሽነት ከሰዋል።

የጁባላንድ ባለስልጣናት ትናንት ግጭቱ ሲቀሰቀስ ባወጡት መግለጫ የፌዴራል ኃይሎች በድሮን የታገዘ ጥቃት ፈጽመውብናል ሲሉ ለግጭቱ መቀስቀስ የፌዴራል መንግስቱን ተጠያቂ አድርገዋል።

ከጁባላንድ ዛሬ የተሰማው ዜና ግን ከዉግያው በኋላ የፌዴራል ኃይሎች ጁባ ላንድን ለቀው መውጣታቸውን ነው የሚያመለክተው።

የጁባላንድ ባለስልጣናት ይህንኑ በሚያረጋግጠው መግለጫቸው " የጦር ሰፈሩን መልሰን ተቆጣጥረናል "  ብለዋል።

የአካባቢው የፀጥታ ጥበቃ ምክትል ሚኒስትር አዳነ አህመድ " በመጨረሻም የጁባላንድ ወታደሮች ከቀትር በኋላ የራስ ካምቦኒ ከተማ ተቆጣጥረውታል " ሲሉ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።

በአንድ ቀን ዉግያው ከሁለቱም ወገኖች የተገደሉ ወታደሮች መኖራቸውን ያመለከተው የሮይተርስ ዘገባ ነገር ግን አኃዙን በተመለከተ መረጃ አለማግኘቱን ጠቅሷል።

በራስ ገዟ አስተዳደር የግንኙነት ችግር መፈጠሩንም ዘገባው አመልክቷል።

በጁባ ላንድ የተቀሰቀሰው ግጭት ከሶማሊያ ባሻገር ሶማሊያ ውስጥ አልሸባብን የሚዋጉት ኢትዮጵያ እና ኬንያን ያሳስባቸዋል።

መረጃው የዶቼ ቨለ ሬድዮ / ሮይተርስ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት 11ኛውን ዙር አገር አቀፍ የጥራት ሽልማት ሥነ ሥርዓት የኤፌዲሪ ፕሬዚዳንት እና የድርጅታችን የበላይ ጠባቂ ክቡር ታዬ አጽቅ ሥላሴ፣ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የኩባንያ ባለቤቶችና ሥራ አስፈጻሚዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በታላቅ ሥነሥርዓት ያከናውናል::

🗓 ቀን፡ ታኅሣሥ 5፣ 2017
🕒 ሰዓት፡ ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ
📍 ቦታ፡ ታላቁ ቤተ መንግሥት
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#JawarMohammed

" አልፀፀትም " / " HIN GAABBU "

በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የገዘፈ ስም ካላቸው ፖለቲከኞች አንዱ የሆኑት የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጃዋር መሀመድ መፅሀፍ ይዘው እየመጡ እንደሆነ ገለጹ።

የኢህአዴግን ስርዓት በሰላማዊ መንገድ በመታገል ስርዓቱ ሳይወድ በግዱ እንዲቀየር በማድረጉ ረገድ ግንባር ቀደሙን ድርሻ እንደሚይዙ የሚነገርላቸው አቶ ጃዋር መሀመድ ከዚህ ቀደም ሰፋ ያለ መፅሀፍ እየጻፉ እንደነበር መግለፃቸው ይታወሳል።

በመጨረሻም መፅሀፋቸው መጠናቀቁን እና ለአንባቢያ ሊደርስ መሆኑን አሳውቀዋል።

በቀጣይ ሳምንት ኬንያ፣ ናይሮቢ ውስጥ በሚዘጋጅ ዝግጅት መፅሀፉ ለአንባቢያን ይቀርባል ተብሏል።

" አልፀፀትም " / " HIN GAABBU " በሚል ርዕስ የተዘጋጀው መፅሀፋቸው በርካታ እና ከዚህ ቀደም ይፋ ያላደረጓቸው ጉዳዮች የተዳሰሰበት እንደሆነ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመረዳት ችሏል።

አቶ ጃዋር መሀመድ ፦
° በኢትዮጵያ ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል የገዘፈ ስም ያላቸው ፤
° አሜሪካ ሆነው የኢህአዴግን ስርዓት በሰላማዊ ትግል በመጣሉ በኩል ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፤
° ' ለውጥ መጣ ' ተብሎ ወደ ሀገር ከገቡ በኃላ የሀጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ ከቀብር ጋር በተያያዘ በተፈጠረው ሁኔታ ታስረው ለበርካታ ወራት በእስር ቆየተው መፈታታቸው ይታወሳል።

ፖለቲከኛው ከእስር ቤት ቆይታ በኃላ ቀድሞ የሚታወቁባቸውን ኃይለኛ ንግግሮችን እና ፅሁፎችን በመተው ዝምታን መርጠው ብዙ ጊዜያቸውን በመፅሀፍ ዝግጅት ላይ እንዲሁም በሀገሪቱ ያሉ ግጭቶች እንዲቆሙ የድርሻቸውን የተለያዩ ጥረቶችን ሲያደርጉ መቆየታቸው ይነገራል።

ከእስር በኃላ ኢትዮጵያ እንዲሁም ኬንያ ናይሮቢ እየተመላለሱ የሚኖሩ ሲሆን አብዛኛውን ጊዜያቸውን ግን ናይሮቢ ናቸው።

በኬንያ ፣ ናይሮቢ ገቢ የሚያገኙባቸውን ስራዎች ከመስራት ባለፈ እንደ ኢትዮጵያ ብዙ ሰዎች ሊያገኟቸው / ሊጠይቋቸው ስለማይመጡ በጥሞና ለማሰብ፣ ለማንበብ እና መፅሀፋቸውን ለማዘጋጀት ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው ለመረዳት ተችሏል።

" አልፀፀትም / HIN GAABBU " የተሰኘው መፅሀፋቸው ቀጣይ ሳምንት ሀሙስ ናይሮቢ ውስጥ ላውንች ይደረጋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Ethiopia🇪🇹

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በቱርክ አንካራ ፤ ከሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ጋር ያደረጉትን የፊት ለፊት ውይይትና ድርድር አጠናቀው ጥዋት አዲስ አበባ መግባታቸውን ከጠ/ሚ ፅ/ቤት የተገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ምን ተስማሙ ?

በቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን አደራዳሪነት የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

ስምምነቱ " የአንካራ ስምምነት " ተብሏል።

ይህ ተከትሎ በወጣው የስምምነት ሰነድ የተስማሙባቸው ጉዳዮች በዝርዝር ተቀምጠዋል።

ምንድናቸው ?

➡️ የሶማሊያ እና የኢትዮጵያ መሪዎች አንዳቸው ለሌላኛቸውን ሉዓላዊነት ፣ አንድነት ፣ነፃነት እና የግዛት አንድነት ለማክበር ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል።

➡️ በወዳጅነት እና በመከባበር መንፈስ ልዩነቶችን እና አከራካሪ ጉዳዮችን በመተው ፤ በመተጋገዝ ለጋራ ብልጽግና ለመስራት ተስማምተዋል።

➡️  ሶማሊያ በአፍሪካ ህብረት ተልዕኮ ውስጥ የኢትዮጵያ ወታደሮች ለከፈሉት መስዋዕትነት እውቅና ሰጥታለች።

➡️ ኢትዮጵያ የሶማሊያን የግዛት አንድነት ባከበረ ሁኔታ የባህር በር ተጠቃሚ መሆኗ / ወደ ባህር እና ' ከ ' ባህር / ሊያስገኝ የሚችለው ልዩ ልዩ ጥቅም ላይ ተማምነውበታል።

➡️ ሁለቱንም ተጠቃሚ ባደረገ ሁኔታ የንግድ ውል ይታሰራል።

➡️ ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና እና ቀጣይነት ያለው / ዘላቂ የባህር በር መዳረሻ / አክሰስ እንዲኖራት ስምምነት ላይ ተደርሷል
ይህም በሶማሊያ መንግሥት ስልጣን ስር የሚተገበር ነው።

ለዚህም የሚሆን ፦
- የኮንትራንት
- የሊዝ ውልን ጨምሮ ሌሎች ሞዳሊቲዎች ላይ በቀጣይ በቅርበት አብሮ ለመስራትና ለማጠናቀቅ ተስማምተዋል።

ለነዚህ ዓላማዎች መሳካት በጥሩ እምነት ከየካቲት 2025 መጨረሻ በፊት የቴክኒካል ድርድር ለመጀመር ወስነዋል። ይህም በቱርክ አመቻችነት የሚሳለጥ ሲሆን በ4 ወራት ውስጥ ተጠናቆ ስምምነት ይፈረማል።

ለዚህም ቁርጠኝነትና ለቃል ኪዳኑ ተግባራዊ መደረግ የቱርክን እገዛ በደስታ ተቀብለዋል።

➡️ በአተገባበር ሆነ በሌሎች ጉዳዮች ላይ ያሉ ልዩነቶችን በውይይት እና በሰላማዊ መንገድ ' እንደአስፈላጊነቱ ' በቱርክ ድጋፍ ለመፍታት ቃል ገብተዋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Somaliland

አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ ሶማሊለንድ ፤ ሀርጌሳ ገብተዋል።

አዲሱ የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት በሶማሊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ ለተመራ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ልዑክ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አቶ አብዱረህማን መሀመድ አብዱላሂ በአቶ ሙስጠፋ የተመራውን ልዑክ በጽ/ቤታቸው ተቀብለዋቸዋል።

ልዑኩ በሀርጌሳ ቆይታው ተመራጩ አዲሱ የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አቶ አብዱረህማን መሀመድ አብዱላሂ በዓለ ሲመት ላይ ይሳተፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ የሶማሊ ክልል ቴሌቪዥን ዘግቧል።

#Ethiopia #Somaliland

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" በመርሕ ደረጃ መጥፎ ሰላም ጥሩ ጦርነት ባይኖርም የስምምነቶች ግልጽነት ማጣት ውጤቱን የተገላቢጦሽ ሊያደርገው ይችላል ! " - የትብብሩ ፓርቲዎች

መኢአድ፣ ኢሕአፓ፣ ዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄና እናት ፓርቲ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግለጫ ልከዋል።

ፓርቲዎቹ ፤ " አገራችን በሰላም እጦት፣ ሕዝባችን ለዓመታት በዘለቀ ጦርነት ቁምስቅሉን እያየ እንዳለ ምሥክር መቁጠር አይሻም። " ብለዋል።

" በተለይ በብዙ ተስፋና ጉጉት ተጠብቆ የነበረው ' ለውጥ ' የኋልዮሽ መሄድ ከጀመረ ወዲህ ሰላም ማደር ብርቅ፣ ፍጅትና ትርምስ ጌጣችን ከኾነ ሰነበተ " ሲሉ ገልጸዋል።

" ከዚህ ቀደም ኤርትራ በረሃ ከኦነግ ጋር በክልል አመራሮች ደረጃ ግልጽነት የጎደለው ስምምነት ከተደረገ በኋላ ሕዝብ ደስታውን ሳያጣጥም የሰላም ተፈራራሚው ኃይል " ቃል የተገባልኝ አልተፈጸመም " በሚል ሰበብ ተመልሶ ጫካ ከገባ ወዲኽ እንደ አገር ባጠቃላይ በተለይም ደግሞ የኦሮሚያ ክልል ያየው ቁምስቅል ተነግሮ የሚያልቅ አይደለም " ሲሉ ገልጸዋል።

ከሰሞኑ መንግሥት ' ኦነግ ሸኔ ' እያለ የሚጠራው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የተወሰነ ቡድን ሰላም መፈረሙ በመንግሥት የመገናኛ ብዙሃን በስፋት መዘገቡን የገለጹት ፓርቲዎቹ " መጥፎ ሰላም የለም በሚል ጥቂቶች እንኳን የሰላም አካል መኾናቸውን በበጎ የምንመለከተው ነው " ብለውታል።

ከዚኹ ጋር ተያይዞ " የታጣቂ ቡድኑ መሪ ናቸው የተባሉ ግለሰብና የተወሰኑ ወጣቶች ከክልል አመራሮች ጋር ስምምነት ሲፈራረሙ ታይተዋል " ብለዋል።

" ከስምምነቱ ማግስትም አዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች ለሦስት ቀናት በዘለቀ ተኩስ ስትናጥ ከርማለች " ያሉት ፓርቲዎቹ " በተኩሱ እስከ አኹን አንዲት እናት በጥይት ተመትተው ሕይወታቸው ማለፉን አረጋግጠናል " ብለዋል።

ይኸው ድርጊት በተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች እንደተከሰተ ገልጸዋል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ ሂደቱ ጥርጣሬን እንዳጫረባቸው ጥርጣሬያቸው የሚነሳውም ከስምምነቱ ግልጸኝነት ማጣት ብቻ ሳይሆን ከእንዲህ ዓይነት ክስተቶች ጭምር መሆኑን ገልጸዋል።

" ስምምነቱ መሣሪያ ማውረድን አይጨምርም ወይ ? " ያሉት ፓርቲዎቹ " የከተማ አስተዳደሩ ርችት እንኳን እንዳይተኮስ ሲከለክል እንዳልከረመ እንዴት ሙሉ ትጥቅ ተይዞ መግባትንና ለቀናት ጭምር የድልነሺነት ብሥራት በሚመስያመስል መልኩ ተኩስን ሊፈቅድ ቻለ ? " ሲሉ ጠይቀዋል።

በተጨማሪ ፦

° ' ከተማ ውስጥ ኹከት ለመፍጠር የመጡ ' በሚል በመታወቂያ ማንነት በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን ተጉዘው የመጡ ነብሰ ጡሮችና አረጋውያን ጭምር ከአዲስ አበባ መግቢያ ክብረ ነክ በኾነ መንገድ ሲመልስ የነበረ ኃይል አኹን የት ሄዴ ?

° ከዚኹ መሐል ሲገድል ሲቀማ የነበረ በውል ተጣርቶ ተጠያቂነት አይኖርም ወይ ?

° መንግሥት የሰላም ስምምነት ፈጸመ ከተባለው ግለሰብና ቡድን ጋር ከዚኽ ቀደም የነበረው ግንኙነት ምን ነበር ?

° ታንዛኒያ ድረስ ኹለት ጊዜ አድካሚ ሙከራዎች ተደርገው ጫፍ እየደረሱ የተናፈቀው ሰላም ሲጨነግፍ በአቋራጭ አዲስ አበባ እውን የኾነበት ተዓምር ምን ቢኾን ነው ?

° የአዲስ አበባ ከተማ ሕዝብ ሥነልቡናዊ ጫና እንዲደርስበት ታስቦ ተሠርቷል ወይ ? የሚሉ ጥያቄዎችን ፓርቲዎቹ አንስተዋል።

ፓርቲዎቹ ፤ የለአንድም ቀን እንኳን ሰላም መስፈን እጅጉን እንሻለን ብለዋል።

" የአንድም ሰው የሰላምን መንገድ መምረጥ ያስደስተናል " ሲሉ አክበላለዋል።

" በአንጻሩ ደግሞ በሂደቱ ዙሪያ የግልጽነት አለመኖርና የሰላሙ ዘላቂነት እጅግ ስለሚያሳስበን አጠራጣሪ ጉዳዮች ሲኖሩ ማንሳት በጎ ይመስለናል " ብለዋል።

ፓርቲዎቹ፦

➡️ የሰላም መጥፎ የለውምና የተደረሰውን ስምምነት ከነገዘፉ ችግሮቹ በበጎ እናየዋለን ብለዋል።

➡️ መንግሥት የስምምነቱን ሂደትና ዝርዝር ነጥቦች የመከራው ግንባር ቀደም ገፈት ቀማሽ ለሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ ይፋ እንዲያደርግ በአጽንኦት አሳስበዋል።

➡️ በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች ለቀናት የዘለቀው ተኩስ፣ በሰላም ስምምነት የመጣ ሳይኾን ኾን ተብሎ የሕዝብን ሥነ ልቡና ለመስለብና ለማስፈራራት የተደረገ መኾኑን ሕዝባችን እንዲያውቀው እንሻለን ብለዋል።

➡️ በዚኹ የተኩስ እሩምታ ሰበብ መገናኛ አካባቢ ለተገደሉት እናት መንግሥት ሓላፊነት የሚወስድ ኾኖ ቢያንስ ቤተሰባቸውን ይፋዊ ይቅርታ እንዲጠይቅና ተገቢውን ካሳ እንዲከፍል እንጠይቃለን ብለዋል።

➡️ መንግሥት ከሽርፍራፊ ደስታና ማስመሰል ወጥቶ ዘላቂ ሰላምን በሰጥቶ መቀበል መርኅ በገለልተኛ ታዛቢዎች አማካይነት ድርድር ለማድረግ ፈቃደኝነቱን በመግለጽና ለዚህም ተግባራዊ እርምጃ በመውሰድ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ያሉ ደም አፋሳሽ ጦርነቶች ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እልባት እንዲያገኙ፣ በአፋጣኝም ተኩስ አቁም እንዲታወጅ በአጽንዖት አሳስበዋል።

#እናትፓርቲ
#መኢአድ
#ኢሕአፓ
#ዐማራግዮናዊንቅናቄ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Ethiopia #Somalia #Turkey

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ልዑካቸው አንካራ ቱርክ ይገኛሉ።

የቱርክ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በጽሕፈት ቤታቸው አቀባበል ያደረጉላቸው ሲሆን ሁለቱ መሪዎች ከልዑካን ቡድናቸው ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።

በሌላ በኩል ፤ የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሼክ መሐመድ አንካራ ይገኛሉ።

እሳቸውም ከኤርዶጋን ጋር ተነጋግረዋል።

መሪዎቹ አንካራ የሄዱበት ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ የገቡበትን ውጥረት ለማርገብ እንዲቻል ኤርዶጋን የንግግር መድረክ አመቻችተውላቸእ ነው።

መሪዎቹ ፊት ለፊት ይነጋገራሉ እየተባለ ይገኛል።

ሮይተርስ የሶማሊያ ዜና አገልግሎት ሶናን ጠቅሶ እንደዘገበው የሁለቱ መሪዎች የፊት ለፊት ንግግር እየተካረረ የሄደውን የሁለቱን ሃገራት ዲፕሎማሲያዊ ቀውስ ለማርገብ ያስችላል ብሏል።

እንደ ተባለው ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ከሀሰን ሼክ መሀመድ ጋር ፊት ለፊት የሚገናኙ ከሆነ ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሌ ላንድ ጋር የወደብ ባለቤት የሚያደርጋትን ስምምነት ከተፈራረሙ ወዲህ ይህ የመጀመሪያዉ ይሆናል።

መረጃው ከጠ/ሚ ፅ/ቤት ፣ ዶቼ ቨለ ፣ ሮይተርስ የተሰባሰበ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#TecnoAI

በተለምዶ ረጅም ሰዓታትን አንድ ስራ ላይ ማባከን ታሪክ ሆነ ፤ ቀናት የሚወሰዱ ስራዎችን በሰዓታት ብቻ መፈፅም የአዲሱ ቴክኖ ኤ አይ ዋነኛ መገለጫ ነው፡፡

ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመከተል የቴክኖ ቲክቶክ ገጽ ፎሎው በማድረግ እና Bio ላይ ያለውን ሊንክ ተጭነው በመመዝገብ ታህሳስ 10 በስካይላይት ሆቴል በሚካሄደው የሀገራችን ትልቁ የኤ አይ ሁነት ላይ ይሳተፉ፡፡

tecnoet" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@tecnoet

@tecno_et @tecno_et

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ArbaMinch

🔴 የእሳት አደጋ መድረሱን ተከትሎ የድረሱልን ጥሪ ሲያሰሙ የነበሩ እናት ህይወት አለፈ።

በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ ረፋድ 4 ሠዓት አከባቢ በተለምዶ ' ቡቡ ሜዳ ' ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ በሚገኘዉ አዲሱ ገበያ የእሳት አደጋ ተከስቶ በንብረት ላይ ዉድመት ማድረሱን የከተማው አስተዳደር ፖሊስ አስታውቋል።

በእሳት አደጋዉም የሰዉ ሕይወት መጥፋቱን የሚገልፁ መረጃዎች መውጣታቸውን ተከትሎ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ፖሊስን ማብራሪያ ጠይቋል።

የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ም/ኢንስፔክተር ጋፋሮ ቶማስ ፤ በአከባቢው በሚገኝ አንድ የኤሌክትሮንክስ ሱቅ ዉስጥ በኤሌክትሪክ ኮንታክት ምክንያት በተነሳ የእሳት አደጋ 12 ሱቆች መዉደማቸዉን ገልጸዋል።

በአደጋው ወቅት በገበያው ዉስጥ በተለምዶ መንገድ በጩኸት ይድረሱልን ጥሪ ሲያደርጉ ከነበሩ ሴቶች መካከል አንዲት እናት ባለባቸው የጤና እክል ምክንያት ህይወታቸው ማለፉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

እኚህ እናት የልብ ሕመም እንደነበራቸው የገለጹት ም/ኢንስፔክተር ጋፋሮ ፤ በጩኸት የድረሱልን ጥሪ ሲያሰሙ ሳለ በመድከማቸው ወደ ነጭ ሳር ሆስፒታል ቢወሰዱም ሕይወታቸው ማርተፍ አልተቻለም ነው ያሉት።

ሆኖም በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ሕይወቷ ያለፈዉ በእሳት አደጋዉ በደረሰ ጉዳት ተደርጎ የሚሰራጨው መረጃ የተሳሳተ ነዉ ብለዋል።

በገበያዉ ዉስጥ ያለዉ የሱቆች አሰራር እና አጠቃቀም ለእሳት አደጋ አጋላጭ ነዉ ያሉት አዛዡ ፤ ሕይወቷ ያለፈዉ ግለሰብ በገበያው ዉስጥ ሱቅ እንደነበራቸውና ሱቃቸዉም እሳት አደጋዉ እንዳልደረሰበት ገልፀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የእሳት አደጋዉ በተገለፀው አኳሃን መፈጠሩን በገበያው ውስጥ ካሉ ነጋዴዎች የሰማ ሲሆን ሕይወታቸዉ ያለፈዉ ግለሰብም በቀጥታ በእሳት አደጋው በደረሰ ጉዳት አለመሆኑን ነጋዴዎች ተናግረዋል።

" ሞች ወ/ሮ አበባየሁ መንገሻ እንደ እናት ያሳደጉኝ እናቴ ናቸዉ፤ የሞቱት በእሳት አደጋዉ አይደለም " ያሉት አቶ አማኑኤል ሰይፉ የተባሉ ነጋዴ አስቀድመው የልብ ሕመምና የሕክምና ክትትል እንደነበራቸው አስረድተዋል።

አክለው በእሳት አደጋዉ ወቅት መደንገጣቸዉና ከሌሎችም ሴቶች ጋር ሆነዉ ለይድረሱልን ብዙ መጮኻቸዉን ተከትሎ መዳከማቸዉንና ወደ ነጭ ሳር ሆስፒታል ቢወሰዱም ሕይወታቸው ማለፉን ነው የገለጹት።

#TikvahEthiopiaFamilyArbaMinch

@tikvahethiopia

Читать полностью…
Подписаться на канал