tikvahethiopia | Неотсортированное

Telegram-канал tikvahethiopia - TIKVAH-ETHIOPIA

1531512

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ

Подписаться на канал

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

🔴 “ የአማራ ክልል ምሁራንና ሊህቃን በሰፊው እስር ቤት ነው ያሉት። አንድ ህዝብ ሊህቃን ታስሮበት ሊሳተፍ አይችልም ” - ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) 

➡️ “ ጫካ ውስጥ ያሉ ሰዎች አጀንዳ አልመጣም ብዬ አላስብም ” - ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)


የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሦስት ዓመታት ሪፓርት ለፓርላማ ማቅረቡ፣ የካቲት 14 ቀን 2017 ዓ/ም ሦስት አመቱን የሚደፍነው የኮሚሽኑ የሥራ ጊዜ በቋሚ ኮሚቴው ለአንድ አመት መራዘሙ ታውቋል።

ኮሚሽኑ በሪፓርቱ፣ በ10 ክልሎችና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች የምክክር፣ የአጀንዳ ልየታ እና ለሀገራዊ ምክክር የሚሳተፉ ተወካዮች የማስመረጥ ተግባራትን እንዳጠናቀቀ አመልክቷል።

በአማራ ክልል ያለው ሥራ መቀጠሉን፣ የትግራይ ክልል ገና መሆኑም ተመላክቷል።

ሪፓርቱ በቀረበበት ወቅት የፓርላማ አባት ያነሷቸው ጥያቄዎች ምንድን ናቸው ?

የኮሚሽኑ ሪፓርት ከቀረበ በኋላ አብዛኛዎቹ የፓርላማ አባላት በተለይ የጸጥታ ችግር ያሉባቸው አካባቢዎች ለምክክሩ የገጣማቸውን የተሳትፎ ውጥንቅጥ የሚመለከቱ ጥቄዎችን ሰንዝረዋል።

አንድ የፓርላማ አባል፣ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ማኅበረሰቡ በንቃት ነው የተሳተፈው? ለሀገር እንቅፋት የሆኑ ነገሮችን ለማስቀረት ኮሚሽኑ ምን እየሰራ ነው? የሚሉ ጥያቄዎችን አቅርበዋል።

ሌላኛው የፓርላማ አባል ደግሞ፣ ፓርቲዎች ከምክክሩ የወጡበት ምክንያት ምንድን ነው? አጀንዳቸውን አሁንስ በምን መልኩ ነው የሚሰጡት? በማለት ጠይቀዋል።

የታጠቁ ኃይሎችና አንዳንድ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በምክክሩ እንዳልተሳተፉ ሲናገሩ የተደመጡት ሌላኛው የፓርላማ አባል፣ ወደ ፊት ኮሚሽኑ በዚሁ ጉዳይ ምን ለመስራት እንዳሰበ ማብራሪያ ጠይቀዋል።

ለጥያቄዎቹ ምላሽ የሰጠው ኮሚሽኑ በበኩሉ፣ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎችም የህዝቡ ተሳትፎ ጥሩ እንደነበር፣ ፓርቲዎችም ሆኑ ታጣቂዎች አሁንም አጀንዳቸውን ካቀረቡ በሩ ክፍት መሆኑን ገልጿል።

የፓርላማ አባሉ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ምን ጠየቁ?

ጠንከር ያሉ ሀሳቦችን በማቅረብ የሚታወቁት የፓርላማ አባሉ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር)፣ “የአማራ ክልል ምሁራንና ሊህቃን በሰፊው እስር ቤት ነው ያሉት። አንድ ህዝብ ሊህቃን ታስሮበት ሊሳተፍ አይችልም” ሲሉ ተችተዋል።

በትጥቅ ትግል ላይ ያሉ አካላት አጀንዳቸውን እንዳላቀረቡ፣ የአካታትነት ችግር እንዳለ ገልጸው፣ “ይህ ባልተካሄደበት ሁኔታ ምን አይነት ምክክር ማድረግ ይቻላል?” ሲሉም ጠይቀዋል።

በአማራም ሆነ ኦሮሚያ ክልሎች ባለው ጦርነት ኮሚሽኑ የተኩስ አቁም ጥሪ ማድረግ እንደሚገባው ገልጸው፣ “ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የቁርጠኝነት ችግር እንዳለ አያለሁ” ነው ያሉት።

እንዲሁም የጸጥታ ችግር ዜጎች ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሰው የመመካከር ደኅንነታቸው ላይ ችግር መፍጠሩንም የተናገሩ ሲሆን፣ “አማራ ክልል ህዝቡ ከፍተኛ ትራውማ ውስጥ ገብቷል። ከክልሉ ውጪ ያሉትም የማንነት ጥቃት ሰለባ ሆነዋል” ብለዋል።

ሥጋት ለሚያነሱ ሰዎች የተለያዩ ፍረጃዎች እየተሰጠ የሚኬደው ነገር ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ፣ ኮሚሽኑ በትጥቅ ትግል ያሉ አካላትን እንዲያካትት አስተያየት የሰጡ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ፣ መንግስትና በልጽግና አስቻይ ሁኔታ ፈጥሯል ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል።

ለዚሁ ጥያቄ አጸፋ የሰጡት በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ እነደሳለኝና አብን ፓርቲያቸው ምን አስተዋጽኦ አድርጓል? ሲሉ ጠይቀዋል።

የታጠቁ አካላት በምክክሩ ባለመሳተፋቸው ደሳለኝ (ዶ/ር) ባቀረቡት ትችት የተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) አጸፋ፣ “የታጠቁ ቡድኖችም ሁሉም አይደሉም ያልተሳተፉት” ሲሉ ተደምጠዋል።

የተሰወሱ የፋኖ ክንፎች ሁኔታም አንስተው፣ እነ ጃል ሰኒ ደግሞ በምክክሩ እንደተሳተፉ የገለጹ ሲሆን፣ “የቀሩት የሸኔ ክፋይ የተለዬ ሀሳብ አላቸው ብለን አናምንም” ብለዋል።

ተስፋዬ ዶ/ር)፣ ጉዳዩን እያጋጋልን ነው የቆየነው ወይስ ጉዳዩ ወደ መሀል እንዲመጣ አድርገን ለመፍትሄ እየሰራን? ሲሉም ፓርቲዎችን የተመለከተ ጥያቄ አቅርበዋል።

የሀገሪዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር) በበኩላቸው፣ ኮሚሽኑ በአማራ ክልል የተሳትፎ ልየታ እንዳደረገ፣ የቀሩት 8 ወረዳዎች ብቻ እንደሆኑ ምላሽ ሰጥተዋል።

በጫካ ስላሉ አካላት አጀንዳ አለመቅረብ በተመለከተ የቀረበውን ጥያቄ ሲመልሱም፣ “ጫካ ውስጥ ያሉ ሰዎች አጀንዳ አላመጡም ብዬ አላስብም” ብለው፣ በባሕር ዳር፣ ደብረ ብርሃን፣ ጎንደር ያሉ ክላስተሮች የሕዝቡን ችግር እንዳስረዷቸው ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ኢትዮ ቴሌኮም በጅማ ከተማ የ5ጂ ኔትወርክ አገልግሎት አስጀመረ፤ የዲጂታል ኢትዮጵያን ጉዞ በማፋጠን ላይ!

በኢትዮጵያ ቀዳሚው የቴሌኮም እና ዲጂታል አገልግሎቶች አቅራቢ የሆነው ኢትዮ ቴሌኮም በሀገር አቀፍ ደረጃ የአምስተኛው ትውልድ (5ጂ) ኔትወርክ ማስፋፊያ አጠናክሮ በመቀጠል በዛሬው ዕለት በጅማ ከተማ አገልግሎቱን በይፋ አስጀምሯል፡፡

ኩባንያችን የ5ጂ አገልግሎትን በአዲስ አበባ እ.ኤ.አ በ2022 ካስጀመረበት ጊዜ አንስቶ፣ እስካሁን ድረስ፣ ጅማን ጨምሮ በ12 ከተሞች ማለትም በአዲስ አበባ፣ በአዳማ፣ በጅግጅጋ፣ በድሬዳዋ፣ በሐረር፣ በባህር ዳር፣ በሐዋሳ፣ በወላይታ ሶዶ፣ በሆሳዕና፣ በአርባ ምንጭ እና በቢሾፍቱ አገልግሎቱን ዕውን አድርጓል።

ቴክኖሎጂው የኔትወርክ አቅም ከመጨመር ባሻገር አዳዲስ የዲጂታል እና የፋይናንስ አገልግሎቶች፣ ለኦንላይን ትምህርት፣ ለጀማሪ የንግድ ተቋማት (startups)፣ የስራ እድል ፈጠራ፣ የዲጂታል ክፍተትን ለማጥበብ፣ የስማርት ስልክ አቅርቦት ለማሳደግ እና የዲጂታል ሊትሬሲን ለመጨመር አስቻይ ሁኔታ ይፈጥራል።

የ5ጂ ቴክኖሎጂ የድርጅት ደንበኞችን የዕለት ተዕለት አሰራርን ከማዘመን በተጨማሪ፣ ቁልፍ በሆኑ ዘርፎች ላይ ማለትም ጤናን፣ ግብርናን፣ ትምህርትን፣ ማኑፋክቸሪንግን እና ማዕድንን፣ ትራንስፖርትን፣ ቱሪዝምን፣ መዝናኛን በስማርት ቴኮኖሎጂ በማዘመን ረገድ ቁልፍ ሚና ይጫወታል፡፡

ክቡራን ደንበኞቻችን የ5ጂ አገልግሎት ማስተናገድ የሚያስችሉ ቀፎዎች እና ሲም እንደፍላጎት በአገልግሎት ማእከላችን በማግኘት የእጅግ ፈጣኑን ኔትወርክ ተጠቃሚ በመሆን አስደናቂ ተሞክሮ እንድታገኙ በደስታ እንጋብዛለን፡፡

ለተጨማሪ፡- https://bit.ly/42Z0ygF
አዲስ ፍጥነት፣ አዲስ ምቾት፣ አዲስ አኗኗር!

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ቪድዮ ፦ በካናዳ ቶሮንቶ ፒርሰን አየር ማረፊያ አንድ አውሮፕላን በማረፍ ላይ ሳለ ባጋጠመው አደጋ ጥቂት መንገደኞች ላይ ጉዳት ቢደርስም አብዛኛዎቹ ተሳፋሪዎች መትረፋቸውን የአየር ማረፊያው ኃላፊ አስታወቁ።

" ምንም ዓይነት የሞት አደጋ ባለመኖሩ በጣም ደስተኞች ነን። ጥቂት ሰዎች ብቻ ናቸው ጉዳት የደረሰባቸው " ሲሉ የግሬት ቶሮንቶ አየር ማረፊያ ባለሥጣን ኃላፊ ዴቦራህ ፍሊንት ተናግረዋል።

አንድ ሕፃን እና ሁለት አዋቂዎች ክፉኛ መጎዳታቸው ተነግሯል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

" በሃይማኖት አባቶች የተጀመረው የሽምግል እና የእርቅ እንዲሁም የካቲት 11 በጋራ የማክበር እንቅስቃሴ አልተሳካም አሉ " የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ።

ፕሬዜዳንቱ ለእርቅ እና ሽምግልና አለመሳካት " ቡድን " ሲሉ የጠሩትን አካል ተጠያቂ አድርገዋል።

ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ባወጡት መግለጫ " መንግስት የማያውቀው ርችት በመተኮስ የሚያጋጥም ችግር ካለ ተጠያቂው ቡድኑ ነው " ብለዋል።

አላስፈላጊ የአመፅ እንቅስቃሴዎች እየታዩ መሆናቸው የገለፁት ፕሬዜዳንቱ ፤ ህዝቡ አከባቢውን በልዩ ሁኔታ በመጠበቅ በዓሉ እንዲያከብር አሳስበዋል። 

ከቀናት በፊት ለእርቅና ሽምግልና ፍቃደኛ መሆናቸው በትግራይ የሃይማኖት አባቶች መግለጫ የተሰጠባቸው ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳና የህወሓት ሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በትናንቱ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እጅ ለእጅ ሲጨባበጡ የሚያሳይ ፎቶ መለቀቁ ብዙዎች አስደስቶ ነበር።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ የካቲት 11 በዓል ምን አሉ ?

" ባለፈው የከፈልነው ይብቃ ፤ ያልፈውን አልፈዋል እንዳይደገም ያለፉት ስህተቶቻችን ማረም ያስፈልጋል " - ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) 50ኛው ዓመት የካቲት 11 በዓል በማስመልከት በትግርኛ ቋንቋ ለመላው የትግራይ ህዝብ " የእንኳን አደረሳችሁ " መልእክት አስተላልፈዋል።

በአገር ውስጥና በመላው ዓለም ለሚገኙት የትግራይ ተወላጆች እና ወዳጆች " ለ50ኛው ዓመት የካቲት 11 በዓል እንኳን አደረሳችሁ " በሚል መልዕክታቸውን ያስቀደሙት ጠቅላይ ሚንስትሩ ፥ የትግራይ ህዝብ ባለፉት ዘመናት ተጋድሎ ለአገር  ሉአላውነት እና ዳር ደንበር መከበር የከፈለውን መስዋእትነት በታላቅ ክብር አስታውሰዋል። 

በአገራችን ታሪክ ፓለቲካዊ ልዩነቶች በህግ ወይ በመግባባት የመፍታት የዳበረ ልምድ እንዳልነበረ ጠቅሰዋል።

ይሁን እንጂ ማህበረሰቡ በየብሄሩ እና አከባቢው የሚፈጠሩት ልዩነቶች በእርቅ እና ሽምግልና መፍታት በሁሉም የአገሪቱ አቅጣጫዎች የተዘወተረ ነው ብለዋል። 

" ይህ ሆኖ እያለ ፓለቲካው ከባህል አፈንግጦ ሁሉም ልዩነቶች በግጭት ብቻ መፍታት ፓለቲካዊ ባህል ሆኖ ለዘመናት ቆይተዋል አሁንም ፈተና ሆኖ ቀጥለዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

" ፓለቲካዊ ልዩነት በውይይት ፣ በእርቅ እና መግባባት ብሎም በህገ -መፈታት አለበት የሚለው አቋም ከለውጡ በኋላ እንደ መንግስት የተያዘ አቋም ነው  ጠቅላአቋመያዝ በዘለለ ሕጋዊ እና ተቋማዊ አሰራር ተበጅቶለት በመተግበር ላይ እንደሚገኝ " ገልፀዋል። 

" አሰራሩ ጅምር ላይ መሆኑ ልብ ማለት ይገባል " ያሉ ሲሆን የትግራይ ህዝብ ጭቆና በምክክር እና ህጋዊ አሰራር መፈታት በማይችልበት ወቅት የነበረው ብቸኛ አማራጭ ጠብመንጃ በማንሳት ዴሞክራሲ እና እኩልነት ለማስፈን ከሌሎች ህዝቦች ጋር በማበር የየካቲት 11 ትግል ለማካሄድ መገደዱን አስታውሰዋል። 

" ጠበመንጃ በማንሳት የሚካሄድ የግጭት መንገድ በመሰረቱ የሚደገፍ ባይሆንም በወቅቱ የነበረው ፓለቲካዊ እና ህጋዊ ሁኔታ ግን ጠብመንጃ ለማንሳት የሚያስገድድ ነበር " ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ " የካቲት 11 የተቀጣጠለው በጠብመንጃ የታገዘ ፓለቲካዊ ትግል ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለማቆም ልየነቶች በውይይት ለመፍታት ያለመ በመኖሩ ከሱ በፊት ሲካሄዱ ከነበሩት ትግሎች ሲነፃፀር ይለያል " ብለዋል።  

ስለሆነም ማንኛውም ልዩነት በጠብመንጃ ሳይሆን በውይይት እና በህጋዊ መንገድ መፍታት የየካቲት 11 ፍሬዎች መሆናቸው መገንዛብ ያሻል ሲሉ አክለዋል።

" ባለፉት የቅርብ ዓመታት ያጋጠሙን መቃቃሮች ለመፍታት የተከተልነው የግጭት  መንገድ ፤ ከየካቲት 11 ዓላማዎች የወጣ መሆኑ ግልፅ ነው ፤ ይሁን እንጂ ከባድ ዋጋ ከፍለንም ቢሆን ወደ ውይይት መመለሳችን የሚደነቅ እርምጃ ነው ፤ ይሁን እንጂ አሁንም ፓለቲካዊ ልዩነት በጠንጃ ለመፍታት የመፈለግ ዝንባሌ መታየቱ አልቀረም " ብለዋል።

" ባለፈው የከፈልነው ይብቃ ፤ ያልፈውን አልፈዋል እንዳይደገም ያለፉት ስህተቶቻችን ማረም ያስፈልጋል " ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ በትግራይ አመራሮች መካከል የተጀመረው ውይይት ተጠናክሮ እንዲቀጥልና ለውጤት እንዲበቃ ያላቸው መልካም ምኞት ገልፀዋል።

ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ፣ የተስተጓጎለው ልማት ተጠናክሮ በህዝብ ወደ ተመረጠ መንግስት ሽግግር እንዲደረግ  ከልብ እንዲሰራ ጥሪ አቅርበዋል።  

የፌደራል መንግስት እና የትግራይ ህዝብና ልሂቃን በተገለፀው የውውይት መንፈስ ማሰብ ከጀመሩ ፤ ትግራይ ወደ መደበኛ የህገ-መንግስት ስርዓት በመመለስ በሃገረ መንግስቱ ያላትን ተሳትፎ  አጠንክራ  የምትቀጥልበት ጊዜ በጣም አጭር እና ተጨባጭ እንደሚሆን አረጋግጠዋል።

መልካም የየካቲት 11 በዓል እንዲሆንም በፅሁፋቸው ተመኝተዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

🔴 “ የተሰጠው መልስ ከእውነት የራቀና በህዝቡ ስቃይ እንደመሳለቅ የሚቆጠር ነው ” - አርሶ አደሮች

➡️ “ አንድ ኩንታል እንደዬአካባቢው ስለሚለያይ ይህን ያክል ነው ብለን ለመግለጽ ያስቸግረናል ” - ግብርና ሚኒስቴር 


ሀዋሳ ዙሪያ የሚገኙ አርሶ አደሮች የማዳበሪያና በበቆሎ ምርጥ ዘር ዘንድሮ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ ከአምናው እጥፍ በላይ በመጨመሩ ማምረት እንደማይችሉ ሰሞኑን በቲክቫህ ኢትዮጵያ ድምፃቸውን ማሰማታቸው አይዘነጋም።

“ አምና 3,600 ብር ስንገዛው የነበረውን ማዳበሪያ ዘንድሮ 8,400 ብር ለመግዛት ተገደናል። አምና 1,800 ብር  የነበረው የአንድ ፕሎት ምርጥ ዘር በቆሎ ዘንድሮ 4,600 ብር ገብቷል ” ሲሉ ነበር ያማረሩት።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በወቅቱ ምላሽ የጠየቀው የሲዳማ ክልል ግብርና ቢሮ፣ “ ከኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር የማዳበሪያ ዋጋ ጨምሯል። የጨመርነው ነገር የለም። የትራንስፓርት ብቻ ነው የጨመርነው ” ብሎ፣ የምርጥ ዘር በቆሎ ዋጋም ከትራክተር፣ ከነዳጅ ዋጋ ጋር በተያያዘ መጨመሩን ቢሮው አልደበቀም።

አርሶ አደሮቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በድጋሚ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?

“ የሲዳማ ክልል ግብርና ቢሮ የሰጠው ምላሽ አጥጋቢ ካለመሆኑም አልፎ ከእውነት የራቀና በህዝቡ ስቃይ እንደመሳለቅ የሚቆጠር ነው። ምላሹ ‘ማዳበሪያ ላይ  የተደረገው ጭማሪ የትራንስፖርት ብር ብቻ ነው’ ብሏል።

የትራንስፖርቱ ብቻ ሳይሆን ለማዳበሪያ በአመት 4,000 ብር መጨመር ዝርፊያ እንጂ ጭማሪ አይባልም። የበቆሎውን በተመለከተም ቢሮው፣ የትራክተርና የነዳጅ ጭማሬን በመጥቀስ ነው ምላሽ የሰጠው።

ለህዝቡ ማሳውን የሚያርሰው መንግስት አይደለም ህዝቡ በራሱ ገንዘብ እንጂ። ስለዚህ የማይገናኝ ነገር አገናኝቶ ህዝቡን ማሰቃየት አግባብ አይደለም። 

በቆሎ የሚዘራው ከታህሳስ 15 ጀምሮ ነው። የሻመና ህዝብ ለአንድ ፕሎት እስከ 17,000 ብር በላይ አውጥቶ እንዴት ሊገዛ ይችላል ? ምንስ ሊያተርፍ ነው ? በዚህ ኑሮ ውድነት ገንዘቡንስ የት ነው የሚያመጣው ? ነው ወይስ ህዝቡን ነገ በረሃብ መቅጣት ነው የተፈለገው ? 

በአንድ በኩል ምርጥ ዘርና ማዳበሪያ የማይጠቀም አርሶ አደር እንዳይኖር ያስገድዳሉ፣ በሌላ በኩል ዋጋ በማናር እንዳይጠቀም ማድረግ አይጋጭም ? አርሶ አደሩ ዘንድሮ ምርት አያመርትም። መንግስት ችግሩን ይፍታልን ”
ሲሉ አሳስበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ማዳበሪያ ወደ አርሶ አደሩ ሲከፋፈል ዋጋው ምን ያክል ነው ? አርሶ አደሮች ዘንድሮ የተጋጋነ ዋጋ ጭማሪ እንደተደረገባቸው ገልጸዋል። ጭማሬው ከላይ ነው ከታች ? ኩንታል ማዳበሪያ (ለምሳሌ ዳፕ) ዋጋው ስንት ነው ? ሲል ለግብርና ሚኒስቴር ጥያቄ አቅርቧል።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) ምን መለሱ?

“ አንድ ኩንታል እንደዬአካባቢው ስለሚለያይ ይህን ያክል ነው ብለን ለመግለጽ ያስቸግረናል። ምክንያቱም በርቀቱ ስለሚወሰን። በትራንስፓርት ነው የሚለያዩት። 

ከዚያ ውጪ በሁሉም የአገራቷ ክፍል የሚሰራጨውን ማዳበሪያ ሴንትራሊ ዋጋ አውጥቶ የሚልከው ግብርና ሚኒስቴር ነው። ዋጋ ስናወጣ በግብርና ሚኒስቴር በኩል የሚጨመር ምንም አይነት የፕሮፊት ማሪጅን የለም። 

ማዳበሪያው የተገዛበት፣ የትራንስፓርትና ሌሎች እንዲሁም ወጪዎች ተደርገው የአንድ ኩንታል ዋጋ ተሰልቶ ነው ወደ ታች የሚወርደው። መንግስት 84 ቢሊዮን ብር ድጎማ አድርጓል።

ማዳበሪያ ከአምናው አንጸር ሲወዳደር ዋጋ በተወሰነ መንገድ ጨምሯል። ስለዚህ ታች የጨመረ ዋጋ ሳይሆን ማዳበሪያው የተገዛበት፣ ከሪፎርሙ ጋር የተወሰነ የነዳጅ ዋጋ ጭማሬ ስላለ፣ በዚያ ምክንያት የማዳበሪያ ዋጋ ጨምሯል። 

ማዳበሪያ በዶላር ከውጪ ነው የሚገዛው። ታች ሊጨመር የሚችለው ትንሽዬ ወይ 100 ብር ወይ 50 ብር የዩኒየን ማሪጅን፣ ወደ ታች ደግሞ ሲወርድ እኛ እስከ ማዕከላዊ መጋዘን ነው የምናቀርበው። 

ከማዕከላዊ መጋዘን ወደ መሠረታዊ ህብረት ሥራ ማኀበር ሲያወርዱ ሁሉም ክልሎች እንደየርቀቱ የትራንስፓርት ዋጋ ልዩነት ይኖራል። 

ስለዚህ አንድ ኩንታል ዋጋ ይሄን ያክል ብር ነው ብልህ ሀገራዊ ዋጋን ሪፕረሰንት ስለማያደርግ እንደዬ አካባቢው የተለያዬ ነው የሚሆነው። ግን ሴንትራሊ ለሁሉም የተገዛበትም ድጎማውም እኩል ነው የሚሰራው ”
ብለዋል።

በአጠቃላይ ያለውን አቅርቦት ሲያስረዱም፣ “ 24 ሚሊዮን ኩንታል ነው የምናቀርበው። እስካሁን የ13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል ግዥ ፈጸመናል ” ነው ያሉት።

(ማዳበሪያን በተመለከተ ተጨማሪ መረጃ የምናቀርብ ይሆናል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#AU #ADDISABABA

38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ እና 46ኛው የሥራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ በስኬት መጠናቀቁን የፀጥታና ደኅንነት ጥምር ኃይል አስታውቋል።

የፀጥታና ደኅንነት ጥምር-ኃይሉ "  የአዲስ አበባ ከተማን ሰላምና ደህንነት የበለጠ በማጠናከር የኅብረተሰቡ እንቅስቃሴ ሳይገታ ከመቼውም ጊዜ በተሻለ የትራፊክ ፍሰቱን የተሳለጠ በማድረግ በቅንጅት በመሥራቱ ጉባኤው በስኬት ተጠናቋል " ሲል ገልጿል።

በሌላ በኩል የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ " የህብረቱ ጉባኤ ለከተማችን ድምቀትና የኢኮኖሚ መነቃቃት ከመፍጠሩ ባሻገር የቱሪዝም መስህቦችን እና የከተማችንን መልካም ገጽታዎችን እንዲሁም የህዝባችንን ጨዋነትና እንግዳ ተቀባይነት በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና ተጫውቷል " ብለዋል።

" ጉባኤው እጅግ ደማቅ እና ከወትሮው የተለየ ሁኔታ የተካሄደ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

እንግዶች ወደየሀገራቸው በመመለስ ላይ ናቸው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#AU

38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ተጠናቋል።

በጉባዔው ላይ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎችና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም የሕብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች አመራሮች ተሳትፈዋል።

በጉባኤው ፦
➡️ የአፍሪካ ሕብረት ተቋማዊ ማሻሻያዎች፣
➡️ የማካካሻ ፍትህ፣
➡️ አፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ለማግኘት እየተደረጉ ያሉ እንቅስቃሴዎች፣
➡️ አህጉራዊ ሰላምና ደህንነት፣
➡️ የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና አፈጻጸምና አህጉራዊ የንግድና ኢኮኖሚ ትስስር፣
➡️ ግብርናና የአየር ንብረት ለውጥ፣
➡️ ሰብዓዊ መብቶች፣
➡️ ስርዓተ ጾታና ወጣቶችን ማብቃት እንዲሁም የተቋማትና አደረጃጀቶች ምርጫ ውይይት ከተደረገባቸው ዋንኛ አጀንዳዎች መካከል ይገኙበታል ተብሏል።

የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ ከጉባኤው ጎን ለጎን ከተለያዩ ሀገራት መሪዎች እና ተቋማት አመራሮች ጋር መክረዋል።

ባለፉት ቀናት እጅግ በርካታ አህጉር አቀፍ መሪዎች እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ኃላፊዎችን ፣ እንግዶችን ስታስተናግድ የቆየችው የአፍሪካና የኢትዮጵያ መዲና አዲስ አበባ እንግዶቿን እየሸኘች ትገኛለች።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ሌሎች ምን እንማር ? "

በትግራይ ክልል የነበረውን ግጭት ያስቆመው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ሂደትን በተመለከተና ከስምምነቱ " ሌሎች ምን እንማር ? " በሚል ርዕስ ዛሬ በአፍሪካ ህብረት ሪፓርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

በዚህ ውይይት ላይም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እና የህወሓት ሊቀመንበር ደብረ ጽዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ደግሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ፣ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ መሐመድ እድሪስ እና ሌሎች ተገኝተዋል።

የፕሪቶሪያውን ስምምነትና አፈፃፀም የተመለከተውን ሪፓርት ደግሞ ተሰናባቹ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፉኪ ማህማት፣ የቀድሞ የናይጀሪያ ፕሬዚዳንትና የአፍሪካ ህብረት አደራዳሪ ቡድን ሰብሳቢ ኡሊሲንጎን ኦባሳንጆ እና ከፍተኛ ኮሚሽነሮች አቅርበዋል።

ከአንድ ሰአት በላይ የዘለቀ ውይይት ከተካሄደ በኋላ አቶ ጌታቸው ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።

የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት " የዛሬው መድረክ እስካሁን የሄድንበት ርቀት መገምገም ነው። ከጀመርነው ፍጥነት አንፃር ገና ያላለቁ ነገሮች አሉ። ግን በተሻለ ፍጥነት መጨረስ የምንችልበት እድል ለማግኘት ነው የመጣነው " ብለዋል።

አክለውም ሰላምን ከመስበክ ፣ ሰላምን ከመተግበርም ሆነ ከምንም ነገር በላይ ግን ተፈናቃዮች ወደወትሮ ህይወታቸው የሚመለሱበትና ህገመንግስቱ በሚያስቀምጠው መሰረት የፕሪቶሪያ ውል ሙሉ ለሙሉ ተፈፃሚ የሚሆንበት ጉዳይ ላይ ነው ሀሳብ የተለዋወጥነው። በቀጣይም በዚህ መሰረት የምንቀጥል ይመስለኛል" ብለዋል።

መረጃው የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።

ፎቶ ፦ ሪፖርተር ጋዜጣ (መስፍን ሰለሞን)

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

“ እግዱ እንዲሰጥ መደረጉ ተገቢነት ስለሌለው እግዱ ሊነሳ ይገባል ”- እናት ፓርቲ

ይግባኝ ባይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ ያሰራጨው የቤት ግብር ግምት ማሻሻያ የጥናት ሰነድን በተመለከተ ያቀረበው የእግድ ማመልከቻ እንዲነሳለት እናት ፓርቲ ጠየቀ።

ቢሮው፣ “ከሕግ ውጪ አዘጋጅቶ ተግባራዊ እንዲያደርጉት ለከተማው የግብር ሰብሳቢ አካላት የበተነው” ሰነድ ከፍተኛ ግብር የሚጥል፣ የቤት ግብር ክፍያን የሚለውጥ በመሆኑ ‘ተፈጻሚነት ሊኖረው አይገባም’ ተብሎ በመመሪያ እንዲሻር በሙሉ ድምፅ” የተሰጠውን ውሳኔ እግድ እንዲሰጠው ማመልከቱን እንደተገነዘበም ፓርቲው ገልጿል።

ፓርቲው ይህን ያለው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከውና ጉዳዩን በተመለከተ የተቃውሞ ባወጣው መግለጫ ነው።

ፓርቲው በመግለጫው፣ ይግባኝ ባይ የፌራሉ ፍርድ ቤት የሰጠው ውሳኔ እና አፈጻጸሙ እንዲታገድለት ለእግዱ የተለያዩ ምክንያቶች ማቅረቡን በበደረሰው የእግድ ትዕዛዝ እንዳወቀና ምክንያቶቹን እንደማይቀበላቸው ገልጿል።

በዚህም ፓርቲው፣ ፍርድ ቤት ጥር 9/2017 ዓ/ም በዋለው ችሎት፣ “የይግባኝ አቤቱታው ተመርምሮ የዚህ ችሎት ውሳኔ ውጤት ከመታወቁ በፊት እንደስር ፍርድ ቤት ውሳኔ ቢፈጸም ሊካስ የማይችል ጉዳት እንደሚደርስባቸው ስለገመትን” በሚል የስር ፍርድ ቤት የሰጠው ውሳኔ ታግዶ እንዲቆይ አዟል” ብሏል።

አክሎ፣ “ይሁን እንጂ ይግባኝ ባይ የስር ፍርድ ቤት ውሳኔ ሊታገድለት እንደሚገባ በምክንያትነት ያቀረባቸው ነጥቦች በሙሉ መሠረተ ቢስ” መሆናቸውን በመጥቀስ የእግድ ትዕዛዙ እንዲነሳ ተቃውሞ አቆርቧል።

ፓርቲው፣ ይግባኝ ባይ፣ የፍርድ ቤት ውሳኔ እንዲታገድለት፣ “ውሳኔው ቢፈጸም የከተማ አስተዳደሩን መብትና ጥቅም በከፍተኛ ደረጃ የሚጎዳ በመሆኑ” ሲል ምክንያት ማቅረቡን ጠቅሶ፣ የነበረው ክርክር ለከተማ አስተዳደር ተብሎ በተጠበቀለት መብትና ጥቅም ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ድሮም በነበረ የግብር ክፍያ መሰረት መሆኑን ገልጿል።

“ይግባኝ ባይ የሥር ፍርድ ቤት ውሳኔ ከከተማው ነዋሪዎች ላይ በስራ ላይ ባለው አዋጅና ደንብ በተደነገገው መሠረት ግብሩን ለመተመንንና ለመወሰን የፈጠረበት ደንቃራና የአፈጻጸም ችግር በሕግ የተደገፈ ምንም አይነት ምክንያት ዘርዝር” አለማቅረቡን ፓርቲው አስረድቷል።

የእግዱ መነሳት የሚያስገኘውን ጥቅም በገለጸበት አውድ ፓርቲው፣ “የሕግ መሰረት የሌለውንና ከአገራችን ህግ ሥርዓት ውጪ በጥናት ሰነድ ላይ በመመስረት የሚጣል የግብር አተማመንና አሰባሰብ የአገሪቱን የግብር ሥርዓት የሚያናጋ የዘፈቀደ እርምጃ በመሆኑ በፍትህ ስርዓቱ በመጠቀም ወደ ትክክለኛው መንገድ እንዲገባ ያደርጋል” ብሏል።

(የፓርቲው ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

ከፍተኛ ፉክክር በታየበት የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበርነት ቦታ የጅቡቲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ 6 ዙር ከፈጀው የድምጽ አሰጣጥ በኋላ አዲሱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሆነው መመረጥ ችለዋል።

የምርጫ ሂደቱ ምን ይመስላል?

በምርጫው የሚያሸንፈው ተመራጭ ድምጽ መስጠት ከሚችሉት 48 አባል ሀገራት ሁለት ሶስተኛውን ድምጽ (33 ድምፅ) ማግኘት ይጠበቅበታል።

በሚደረገው ምርጫ ለማሸነፍ የሚያስፈልገውን 33 ነጥብ ማግኘት ካልተቻለ ተከታታይ ምርጫዎች የሚካሄዱ ሲሆን ዝቅተኛ ድምጽ ያገኘው ከውድድሩ ተሰናብቶ ቀሪ ተወዳዳሪዎች ለማሸነፍ የሚያስችላቸውን ነጥብ እስኪያገኙ ይወዳደራሉ።

በዚህም ለ7ኛ ጊዜ በተደረገው በዚህ ውድድር አሸናፊውን ለመለየት 6 ዙሮች ፈጅቷል።

በመጀመሪያዎቹ ተከታታይ ዙሮች የኬንያው የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ መምራት ቢችሉም የማሸነፊያ ነጥብ ሳያገኙ ቀርተዋል።

በስድስተኛው ዙር ድምጽ የጅቡቲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ ለማሸነፍ የሚያስፈልጋቸውን 33 ነጥብ በማግኘታቸው ምርጫውን አሸንፈዋል።

በዚህም ለቀጣይ 4 ዓመታት የቀድሞውን የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋቂን በመተካት 7ኛው የኅብረቱ ሊቀመንበር በመሆን መመረጥ ችለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ኢትዮጵያ በጉባኤው የምታቀርበው አጀንዳ ምንድን ነው?

በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው 38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ የአፍሪካ ሀገራት የውይይት አጀንዳዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን ኢትዮጵያም ከአረንጓዴ ልማት የግብርና ምርት ማሳደግ እና የአካባቢ ጥበቃ ጋር የተያያዘ አጀንዳ እንደምታቀርብ ይጠበቃል።

በዘንድሮ የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድቡን በሚመለከት የያዘችው አጀንዳ እንደሌለም ታውቋል።

"የህዳሴ ግድቡ ጉዳይ ለአረንጓዴ ልማት ጋር በተያያዘ በጨረፍታ የሚመጣ ጉዳይ ካልሆነ በቀር በአጀንዳነት አልተያዘም" ሲሉ የኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት ቋሚ መልእክተኛ የሆኑት ወ/ሮ ሂሩት ዘመነ ከጉባኤው ቀደም ብለው ማሳወቃቸው ይታወሳል።

በሶማሊያ የሚገኘው ሰላም የማስከበር ተልእኮ ላይ ኢትዮጵያ የሚኖራት ሚናን በተመለከተም በሂደት ላይ ያለ በመሆኑ አጀንዳው በጉባኤው ላይ እንደማይነሳ ታውቋል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ውጤት እስከ ነገ ይለቀቃል " - ትምህርት ሚኒስቴር

በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የ2017 ዓ.ም አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና የወሰዱ ተፈታኞች ውጤት እስካሁን አልተለቀቀም።

ከዚህ ጋር በተያያዘ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ (
@tikvahuniversity) አቅርበዋል።

ውጤቱ ለምን ከመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እኩል አልተለቀቀም ? ስንል የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራርን ጠይቀናል።

ለመጀመሪያ ጊዜ የመውጫ ፈተና የሚወስዱ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተፈታኞችን ክፍያ የሚፈፅሙት ተቋማቱ መሆናቸውን አመራሩ ገልፀዋል።

ይሁን እንጂ ተቋማቱ ክፍያውን ባለመፈፀማቸው ውጤት መለቀቅ ላይ መዘግየት እንዳጋጠመ ኃላፊው ተናግረዋል።

አሁን ላይ ብዙዎቹ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ክፍያውን እየፈፀሙ በመሆናቸው የተፈታኞቹ ውጤት እስከ ነገ ቅዳሜ የካቲት 8/2017 ዓ.ም እንደሚለቀቅ ኃላፊው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።

የመውጫ ፈተናውን በግል የወሰዱ ድጋሜ ተፈታኞች ውጤትም ወደየተፈተኑበት ተቋማት ይላካል ብለዋል።

Via
@tikvahuniversity

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Tigray

" ችግሮቻቸውን በውይይት ለመፍታት መስማማታቸው ለህዝቡ እፎይታ ይሰጣል " - የሃይማኖት አባቶች

የትግራይ ክልል አመራሮች በመካከላቸው የተፈጠረው የፓለቲካ ልዩነት በሰላም እና በውይይት ለመፍታት መስማማታቸው የትግራይ የሃይማኖት መሪዎች አስታወቁ።

ችግሮቻቸው ለመፍታት እና ወደፊት ሊያራምዳቸው የሚችል የስነ-ምግባር ደንብ ወጥቶ መፈራረማቸውም ሰላማዊ ውይይቱን የመሩ የሃይማኖት አባቶች ዛሬ የካቲት 7/ 2017 ዓ.ም በመቐለ በሰጡት መግለጫቸው አስታውቀዋል።

የሃይማኖት አባቶቹ በመግለጫቸው " አመራሮቹን ለማቀራረብ ሲካሄድ የነበረው ሰላማዊ ውይይት ስምምነት ላይ አድርሷቸዋል " ብለዋል።

በአመራሮቹ መካከል የተፈጠረው ችግር ለመፍታት ከሁለት ወር በላይ ጥረት መደረጉ ያብራሩት የሃይማኖት አባቶቹ መሪዎቹ ችግሮቻቸውን በውይይት እንዲፈቱ መስማማታቸው ለህዝቡ እፎይታ ይሰጣል ሲሉ ገልጸዋል።

አመራሮቹ በመካከላቸው የተፈጠረ የፓለቲካ ልዩነት በውይይት እንዲፈቱ መስማማታቸው አስመልክቶ በሃይማኖት አባቶች የተሰጠው መግለጫ ብዙ የማህበራዊ የትስስር ገፅ ተጠቃሚዎች ያላቸው ደስታ እና ድጋፍ በመግለፅ ላይ ይገኛሉ።

በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ የሚመሩ የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ከወራት በፊት ችግሮቻቸው ለመፍታት በሃይማኖት አባቶች ፊት ቢጨባበጡም ጠብ የሚል ለውጥ ማምጣት ባለመቻላቸው ምክንያት ህዝቡን ወደ ከፍተኛ ጭንቀት እና ወጥረት መክተታቸው የሚታወስ ነው።

አሁንስ ቃላቸው ጠብቀው ልዩነቶቻቸው ጠረጴዛ ዙሪያ በመፍታት ለህዝብ አገር እፎይታ ይሰጡ ይሆን ? የብዙዎች ጥያቄ ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

ፎቶ 2 ፦ ፋይል

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ፎቶ ፦ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ነገ ለሚጀምረው 38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ አዲስ አበባ ይገኛሉ።

ጎን ለጎንም የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የተለያዩ ሀገራት መሪዎች ተቀብለው እያነጋገሩ ናቸው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

በአዲስ አበባ የምናዘጋጀውን የመረጃ ሴሚናር በመታደም ጃሲሪ ታለንት ኢንቨስተር ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች ተጸዕኖ ፈጣሪ ይሆኑ ቢዝነሶችን እንዲፈጥሩ በሚያረገው ድጋፍ ዙሪያ መረጃ ያግኙ።

📢 ከሴሚናሩ ምን ያገኛሉ?
✅ ስለ ጃሲሪ ታለንት ኢንቨስተር ፕሮግራም ጥቅም ማወቅ
✅ ለጃሲሪ ታለንት ኢንቨስተር እንዴት ማመልከት እንደምትችሉ ማወቅ

የሥራ ፈጣራ ጉዞዎን የመጀመሪያውን እርምጃ ለመውሰድ ይህንን እድል እንዳያመልጥዎት!

ቀን፡ የካቲት 13, 2017
ቦታ፡ አዲስ አበባ | ከቤት እስከ ከተማ የከተማ ማዕከል
ለመመዝገብ፡ bit.ly/4jVdqdI

@jasiri4africa

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሥራ ዘመን ለአንድ አመት ተራዘመ።

ኮሚሽኑ ዛሬ የሦስት አመታት ሪፓርቱን ለፓርላማ ያቀረበ ሲሆን፣ የፓርላማ አባላት በሪፓርቱ ላይ የተለዩዩ ጥያቄዎችንና አስተየቶችን ሰጥተዋል።

በመጨረሻም ሦስት አመቱን የካቲት 14 ቀን በመድፈን የሥራ ዘመኑ ይጠናቀቅ የነበረው ኮሚሽኑ፣ በፓርላማው ቋሚ ኮሚቴ የአንድ አመት ተጨማሪ ጊዜ ተሰጥቶታል።

በቋሚ ኮሚቴው የተሰጠው የአንድ አመት ተጨማሪ ጊዜ ውሳኔው የቀረበበት ሦስት የተቃውሞ ድምፅ ብቻ ነው።

በተለይ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ስላለው ሁኔታ የፓርላማ አባላት ያነሷቸውን ነጥቦችና የተሰጡ ምላሾችን በተመለከተ ተጨማሪ ይኖረናል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/ፕሮፈሰር ፀጋዬ ቱኬ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከቀረበባቸው ሁለት ክሶች በነፃ ተሰናበቱ።

የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፈሰር ፀጋዬ ቱኬ የሕግ ጠበቃቸው አቶ ገብረመድህን ተክሌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሀዋሳ ማዕከል ከቀረበባቸው ከባድ የሙስና ወንጀል እና በሕገወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ መጠቀም በሚል የቀረበባቸዉን ሁለት ክሶች ላለፉት አንድ ዓመት ሲከታተሉ ቆይዋል።

በዛሬዉ ዕለት በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሐዋሳና አከባቢዋ ማዕከል በነፃ መሰናበታቸውን ጠበቃቸው ተናግረዋል።

ከቀድሞ የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/ፕሮፈሰር ፀጋዬ ቱኬ በተጨማሪ ተመሳሳይ ክስ ተመሰርቶባቸዉ የነበሩት የቀድሞ የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበራ አሬራም በነፃ መሰናበታቸውን ጠበቃ ገብረመድህን ተክሌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" የሞት ፍርድ ተፈርዶበታል ! "

የ17 አመት ታዳጊ በሆነችው አዶናይት ይሄይስ ላይ የአስገድዶ መድፈርና የግድያ ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ የሞት ፍርድ ተወሰነበት።

የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ክልል ልዩ ቦታው 15 ሜዳ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ነው።

የወንጀሉ ሰለባ የሆነችው የ17 አመት እድሜ ያላት አዶናይት ይሄይስ የተከሳሽ ሚካኤል ሽመልስ የፍቅረኛው ልጅ ነበረች።

መስከረም 19 ቀን 2015 ዓ/ም ከቀኑ 6:00 ሰአት ሲሆን ታዳጊ አዶናይት ይሄይስ መኖሪያ ቤቷ እያለች ተከሳሽ " ለምን አስገድዶ ደፈረኝ ብለሽ ለፖሊስ ክስ መሰረትሽ " በሚል ሰበብ በቢላዋ የተለያየ የሰውነት ክፍሏን 16 ቦታ በመውጋት ምንም እንዳልተፈጠረ ወደ መኖሪያ ቤቱ በመሄድ ልብሱን በመቀየር ሊሰወር ሲሞክር በአካባቢው ማህበረሰብ እና በወንጀል መከላከል ስራ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት ሊያዝ ችሏል።

ፖሊስም በተያዘው ተከሳሽ ላይ ባደረገው ምርመራ ከ2005 እስከ 2007 ዓ.ም ባልታወቀ ጊዜና ሰዓት ታዳጊዋን " ነይ ሱቅ ልላክሽ " እና ሌሎች ማታለያዎችን እየተጠቀመ በመኖሪያ ቤቱ በተደጋጋሚ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ሲፈፅምባት የቆየ መሆኑንና በወቅቱ እድሜዋ በግምት 10 አመቷ እንደነበረ የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል፡፡

ግለሰቡ የእናቷ የፍቅር ጓደኛ የነበረ ሲሆን ይህንን አፀያፊ ድርጊት ለአንድ ሰው ብትናገሪ እናት እና አባትሽን እገላለሁ እያለ ሲያስፈራት የቆየ ስለመሆኑ የሚዘረዝረው የምርመራ መዝገቡ በተጨማሪም ሟችን " በሞባይል ካሜራ ቪዲዮ ቀርጬሻለሁ በሚዲያ እና በቴሌግራም እለቀዋለሁ " እያለ ለአመታት የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ሲፈፅምባት መቆየቱንና በዚህም ታዳጊዋ ከተከሳሽ በመፀነሷ ፅንሱን እንድታስወርድ ማድረጉን የተከሳሽ የምርመራ መዝገብ ያስረዳል።

ፖሊስ ባከናወነው ተጨማሪ የምርመራ ስራ ተከሳሽ ሚካኤል ሽመልስ የወንጀል ድርጊቱን መፈፀሙን አምኖ ቦታው ድረስ በመሄድ መርቶ ያሳየ ሲሆን የምርመራ መዝገቡን በማደራጀትና በማጠናቀቅ ለዓቃቤ ህግ በመላክ ክስ ተመስርቶበታል።

የወንጀል መዝገቡን ሲከታተል የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ ወንጀል ችሎት ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ሚካኤል ሽመልስ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ
#የሞት_ቅጣት እንዲቀጣ እና የዘወትር ህዝባዊ መብቶቹ እንዲሻሩ ውሳኔ አስተላልፎበታል፡፡

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

አፖሎ ከአቢሲንያ ባንክ የቀረበ ደህንነቱ የተጠበቀ የዲጀታል ባንክ መተግበሪያ ሲሆን በቅድሚያ እርስዎ ተመዝግበው ለወዳጅ ዘመዶችዎ የተመዘገቡበትን መለያ ስልክ ቁጥር በመላክ እነሱንም ያስመዝግቡ።                                                                                                                                                                                   የሽልማቱ ዕጣ አሸናፊ ለመሆን አዲስ አካውንት መክፈትና ከ1000 ብር ጀምሮ መቆጠብ ይኖርብዎታል።
ወዳጅ ዘመዶችዎንም ወደ አፓሎ በመጋበዝ  የዕጣ ቁጥሮችን በመሰብሰብ ባንኮክን የማየት ህልምዎን እውን ያድርጉ ። በተጨማሪም አይፎን 16 ፣ ሳምሰንግ S24 እና ሌሎች አጓጊ ሽልማቶች በዕጣዎቹ ተካትተዋል።  መልካም ዕድል! 
አፖሎ ዲጅታል ባንክ  መተግበሪያውን ለማውረድ https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo   ይጫኑ! 
ደንብ እና ግዴታዎች /channel/apollodigitalproduct/248
#ApolloReferral #መጣሁልሽ #አምሮኛል_መጣሁልሽ #ApolloWinBig #DepositAndWin #JoinApolloGetRewards

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

“ ይሳቅ ህሩይ የትግራዋይ ነው። ከፋኖ ጋር ሊያገናኘው የሚችል አንዳችም ነገር የለም።  ” - ኢሕአፓ ስለታሰረው አመራሩ

የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) የአዲስ አበባ ኮሚቴ ሥራ አስፈጻሚ አባሉ አቶ ይሳቅ ወልዳይ እንደታሰሩበት ገልጿል።

ፓርቲው አመራሬ “በሐሰተኛ ፍረጃ ነው” የታሰሩብኝ ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የፓርቲው ተቀዳሚ ፕሬዜዳንት መጋቢብሉይ አብርሃም ሃይማኖት በሰጡት ቃል ፥ "  የካቲት 6/2017 ዓ/ም ከቤታቸው በፓሊስ ተወስደው ነው የታሰሩት።  ' ፋኖ ይደግፋል '  በሚል ሐሰተኛ ውንጀላ ነው የተወነጀለው " ሲሉ
ገልጸዋል።

የፓርቲው ተቀዳሚ ፕሬዜዳንት በዝርዝር ምን አሉ ? 

“ ሰላማዊ ታጋዮችን በሐሰተኛ መረጃ እያሸማቀቁ እያሰሩ፤ ጋዜጠኞችን እያሳደዱ ሀገር ሰላም ማድረግ አይቻልም። ስለዚህ ሰላም ጠሉ ራሱ መንግስት እንደሆነ ነው እያረጋገጠልን ያለው።

አቶ ይሳቅ ከተባለበት ጉዳይ ጋር የሚያያይዘው አንዳችም ነገር የለም። መንግስት ሕግ ማክበር እንዳለበት የዘነጋው ይመስለኛል። መንግስት ሕገ መንግስቱን አክብሮ ነው የሚያስከብረው፤ ራሱ እየደፈጠጠ መሆን የለበትም።

ይሳቅ ህሩይ የትግራዋይ ነው። ከፋኖ ጋር ሊያገናኘው የሚችል አንዳችም ነገር የለም። ግን ‘የአፍሪካ ህብረትን ለመበጥበጥ፣ መሪዎችን ለመግደል’ የሚል ሐሰተኛ ፈጠራ ሲያቀናብሩ አእምሯቸው እንዴት አቀናበረው ? ብለን እንድንጠይቅ አድርጎናል።

ከዚህ በፊት ዓርዓያ ተስፋማርያም በሚባል ጋዜጠኛ ነኝ በሚል ግለሰብ ይሄው አባላችን ታስሮ በጩኸት ወጥቷል። አሁንም በሐሰተኛ ቅንብር፣ ከመንግስት አካላት ጋር ያላቸው ግንኙነትን በመጠቀም ታስሯል ” ብለዋል።

አመራሩ ከ“ፋኖ” ጋር በተገናኘ የተጠረጠሩት ፌደራል ፓሊስ ጉዳዩን ከምን ጋር አገናኝቶት ነው ? ለሚለው ጥያቄ በምላሻቸው፣ በኮሪደር ልማት አዲስ አበባ ቤት የፈረሰባቸው ነዋሪዎች ካሳ እንዳልተከፈላቸው በማጋለጣቸው ነው ሲሉ ጠቅሰዋል። 

አክለው፣ “ ያንን ተከትሎ ኢሕአፓን ለማሸማቀቅና ቀጣይ የሚያደርጋቸውን ጠንካራ ሰላማዊ ትግል እንዳያደርግ ሆን ተብሎ ለማስፈራራት የተቀናበረ ቅንብር ነው ” ብለው፣ ፓርቲው በዚህ እንደማይሸማቀቅ ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው የፌደራል ፓሊስ የምርመራ ጊዜ ማጣሪያ የጠየቀበት ደብዳቤ፣ ከአቶ ይሳቅ ጋር 13 ግለሰቦችን ጠቅሶ " በአማራ ክልል ለሚንቀሳቀሰው " ቡድን ግንኙነት አላቸው በሚል ይወነጅላል።

ፓሊስ፣ “ ምርመራውን በሰውና በሰነድ ማስረጃ በስፋት ለማጣራት ” የ14 ቀናት የቀጠሮ ጊዜ እንዲሰጠው ለፍርድ ቤት ጥያቄ ማቅረቡን ደብዳቤው ያትታል።

የፓርቲው ተቀዳሚ ከንቲባ በበኩላቸው፣ “ ሰኞ ፍርድ ቤት ለኛ ቀጠሮ ሰጥቶናል የፌደራል ፓሊስ የ14 ቀን ቀጠሮን ውድቅ በማድረግ ‘ተጨባጭ መረጃ ካላችሁ አምጡ’ በማለት” ብለዋል። 

“ ፍርድ ቤቱም ‘እንደዚህ አይነት ሐሰተኛ ቅንብሮች እየተለመደ ስለመጡ ተጨባጭ ነገር ካለ አምጡ አለዚያ ጊዜ ቀጠሮ አልሰጣችሁም’ ብሎ ጥያቄ አቅርቦላቸዋል ” ነው ያሉት።

13ቱም “ተጠርጣሪዎች” የፓርቲው አካላት ናቸው ? ስንል የጠየቅናቸው ተቀዳሚ ፕሬዛዳንቱ፤ ከአቶ ይሳቅ ውጪ ያሉት 12 ተጠረጠሩ ተብለው የታሰሩ ግለሰቦች ከፓርቲው ጋ ግንኙነት እንደሌላቸው አስረድተዋል።

“ ነጋዴዎች አሉ ምንም ፓለቲካ ውስጥ የሌሉ። በተጨባጭ መረጃ ያለን አንድ ካድሬ ከጠላ ይፈርጅህና ለወራት ታሽተህ ትለቀቃለህ። ዜጎችን ማሸማቀቂያ፣ ማሰቃያ ሆኗል የፍትህ ስርዓቱ ” ሲሉ ወቅሰዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ብርሃን_ባንክ
ብርሃን ልዩ ካርድን በመጠቀም በተለያዩ ቦታዎች ከሚገኙ ኤቲኤም ማሽኖች ገንዘብዎን ወጪ ያድርጉ፣ በፖስ ማሽኖች ክፍያዎችን በቀላሉ ይፈጽሙ!
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ስራችን!
#berhanatm #berhanpos #payment #cashout #liyucard #berhanliyucard #berhanbank
#bank #finance #Stressfreebanking #bankinethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

“የባለስልጣናት ያልተገሩ ንግግሮችና የመንግስትም ተቀዳሚ ተግባሩን ፍጹም መርሳት ሕዝብን ለእልቂት እየዳረገ ነው”- ፓርቲው

እናት ፓርቲ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ባወጣውና ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ፣ “መልኩንና ቦታውን እየቀያየረ መላ ኢትዮጵያውያንን የደኅንነት ዋስትና ያሳጣው ሀገራዊ እልቂት አሁን አሁን ወደ ሀገራዊ ቀውስነት እያደገ ነው ለማለት ያስደፍራል” ሲል ተችቷል።

አክሎ፣ “ለዚህ ደግሞ ብዙ የተጠራቀሙና ያልተፈቱ የችግር ቋጠሮዎች ቢኖሩም በዋናነት ባለስልጣናት የሚያደርጓቸው አደገኛ የእልቂት ጠመቃ ንግግሮች ዋነኞቹ ናቸው” ብሏል።

“መንግስት በተደጋጋሚ ቢነገር ችላ ያለውን የዜጎችን ደኅንነት መጠበቅ የቅድሚያ ቅድሚያ ሰጥቶ አለመስራት አሁን ያለንበት ሁኔታ ምን አልባት ወደ ማይቀለበስበት ደረጃ እያደረሰው ይገኛል” ሲል ወንጅሏል።

በዚህም ሰሞኑን በጅማ ዞን ጌራ ወረዳ ቀበሌዎች በአንድ ግለሰብ ግድያ ምክንያት የተስተዋለውን “ቀውስ” ያወሳው ፓርቲው፣ ግድያውን አውግዞ፣ “ድርጊቱም በውል ተጣርቶ አጥፊዎች ከሕግ ፊት እንዲቀርቡ እናሳስባለን” ሲል ጠይቋል።

የስፍራው ነዋሪዎች ዘርፈ ብዙ በደል እየደረሰባቸው መሆኑን ነዋሪዎች እንደገለጹለት ያተተው መግለጫው፣ በጅማው “ቀውስ” “በመቶዎች የሚቆጠሩ ቤቶች ተቃጥለዋል። ወፍጮ ቤቶች፣ ተሽከርካሪዎች፣ ሱቆች እየጋዩ ነው። ‘ይህም ማንነት ተኮር ነው’፣ ‘አማራ ነው ያሉትን ንብረት እየመረጡ ነው የሚያቃጥሉት’ ብለዋል” በሚል ተጠናቅሯል።

“ብዙ ሺህ ሰው አካባቢውን ለቆ ከፋ ዞን ተጠልሏል። በተለይ የአቅመ ደካሞች፣ ሕጻናትና ነብሰ ጡሮች ስቃይ አሳዛኝ ነው፤ በሽሽት ላይ ሳለች የወለደች እናት እንዳለችም ይናገራሉ” በማለት የነዋሪዎቹን እሮሮ ጠቃቅሷል።

የከፋ እለቂት ሳይደርስ መንግስት ድርሻውን እንዲወጣ፣ ተፈናቃዮች እንዲመለሱ እንዲደረግ፣ ገዳዮችና አሳዳጆች ለፍትህ እንዲቀርቡ፣ ‘የሰባብረናቸዋል’ ዓይነት ንግግሮች እንዲቆሙና ማስተባበያዎች ይቅርታ እንዲጠየቅባቸው ፓርቲው በመግለጫው ጠይቋል።

(የፓርቲው ሙሉ መግለጫም ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

“ ድግግሞሹ ቀንሷል፤ እንደድሮው አይደለም። ግን የነበረውን ጥንቃቄ አጠናክሮ መቀጠል ነው ” - አታላይ አየለ (ፕ/ር)

ከዚህ ቀደም ካጋጠሙ ክስተቶች አንጻር በከፍተኛ ሬክተር ስኬል የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ከመተሃራ በቅርበት ላይ አርብ ሌሊቱን ተከስቶ ነበር።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ አርብ ሌሊት መተሃራ አካባቢ 6.0 ሬክተር ስኬል የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን በተመለከተ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉን ተመራማሪ ጠይቋል።

በዩኒቨርሲቲው የመሬት መንቀጥበጥ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ አታላይ አየለ (ፕ/ር)፣  በሰጡት ምላሽ፣ “ አዎ። ልክ ነው ተፈጥሯል። ሌሊት 5 ሰዓት ከ28 ደቂቃ ገደማ ከምሽቱ ” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

“ ነገር ግን ሰው አልሰማውም እንደድሮው ” ሲሉ አክለው፣ “ እንደዚያ የሆነበት ምክንያት ደግሞ ከመሬት ወለል በታች ጥልቅ ስለሆነ ነው እንጂ እንደዛ ባይሆን ኑሮ በጣም ብዙ ጉድ ይሆን ነበር ” ብለዋል።

የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 6.0 የተመዘገበ ነው መባሉ ልክ ነው ? ስልን ላቀረብንላቸው ጥያቄ፣ “ እውነት ነው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ይህ የሚያመላክተው ስኬሉ እየጨመረ እንደመጣ ነው፤ ሰሞኑን ትንሽ ቆም ሲል ጠፋ የሚል ተስፋ ተሰንቆ ነበር፤ አሁንም እንቅስቃሴው አለ ማለት ነው ? የሚል ተጨማሪ ጥያቄም ለተመራማሪው አቆርበናል።

“ እንደዛ ሆነ ማለት ይቀንሳል ማለት አይደለም። እየቀጠለ ነው ያለው ነገርየው። ሙሉ ለሙሉ ቆመ፣ ሞተ ለማለት አያስደፍርም። እንቅስቃሴው እንዳለ ነው ” ብለዋል።

“ ከመስከረም ጀምሮ እስካሁን አቅም በፈቀደ ሁሉም ሰው ጥንቃቄ እንዲያደርግ ለማድረግ እየተሞከረ ነው። አሁንም ያው ከመሬት ወለል በታች ጥልቅ መሆኑ ነው የበጀን ” ሲሉ ተናግረዋል።

“ ድግግሞሹ ቀንሷል፤ እንደድሮው አይደለም። ግን የነበረውን ጥንቃቄ አጠናክሮ መቀጠል ነው። ጨርሶ ቆመ ማለት እንደማይቻል ነው ዋናው መልዕክት ” ሲሉ አስገንዝበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update : በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር ሰልማ ሃዳዲ የሞሮኮ እና የግብፅ እጩዎችን በማሸነፍ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Breaking : የጅቡቲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሆነው ተመርጠዋል።

ሚኒስትሩ አብረዋቸው ለውድድር የቀረቡትን የኬንያውን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ እንዲሁም የማዳጋስካሩን ሪቻርድ ራንድሪያማንድራቶን አሸንፈው ነው የተመረጡት።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ መካሄድ ጀመረ።

38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በአህጉሪቱ መዲና በሆነችሁ በአዲስ አበባ ዛሬ በይፍ መካሄድ ጀምሯል።

ጉባኤው ከ35 በላይ የሀገር መሪዎች፣ አንድ ንጉስ፣ 19 ቀዳማዊት እመቤቶች፣ ሁለት ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር እና ሁለት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በአዲስ አበባ በአፍሪካ ህብረት ዋና መስሪያ ቤት በጀመረው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ተገኝተዋል።

የአፍሪካ ህብረት አባልነታቸው የታገደባቸው 6 ሀገራት ሱዳን፣ኒጀር፣ጋቦን፣ጊኒ፣ቡርኪናፋሶና ማሊ በጉባኤው ያለተሳተፍ ሀገራት ናቸው።

የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት '' ተለዋዋጭ ከሆነው የዓለም ፖለቲካና ኢኮኖሚ ጋር በፍጥነት ለመራመድ አፍሪካዊያን በጋራ መቆም እንደሚገባቸው '' ገልፀው ገባኤውን የመክፈቻ ንግግር በማረግ አስጀምረውታል።

በዛሬ ውሎውም የአንጎላ ፕሬዝዳንት ዧው ማኑኤል ጎሳዌስ ሎሬንሶ የሞሪታንያ መሀመድ ኦልድ ጋዙዋንን በመተካት የአፍሪካ ህብረት አዲሱ ሊቀመንበር አድርጎ መርጧል።

አፍሪካ ''በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን ተገቢ ቦታ እንድታገኝ በተለይ በተመድ በቂ ውክልና እንድታገኝ በትብብር እንደሚሠሩም '' አዲሱ ሊቀመንበር ቃል ገብተዋል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ እንደተናገሩት"አፍሪካ በፀጥታ ምክር ቤት ሁለት ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት ተመድ ግፊት ማድረጉን ይቀጥላል'' ሲሉ ተናግረዋል።

የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ. በ2030 አህጉሪቱ ላይ የትጥቅ ግጭቶችን ለማስቆም ያለመውን "ጠመንጃዎችን ዝም የማሰኘት" እቅድ የሁለት ዓመት ሪፖርት ላይ ይመለከታል ተብሎ ይጠበቃል።

ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ቀናት የሚመክረው ጉባዔው መሪዎች ለባርነት እና ለቅኝ ግዛት ካሳ አዲስ ግፊት በመጀመር ከገንዘብ ካሳ፣ ያለፉትን ስህተቶች መደበኛ እውቅና መስጠት እስከ ፖሊሲ ማሻሻያዎች ድረስ የባርነት ካሳው ጉዳይ ምን ሊመስል እንደሚችል "የተዋሃደ ራዕይ" ለመቅረጽ እንደሚመክሩ ይጠበቃል።

ሌላው ቁልፍ አጀንዳ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምርጫ ሲሆን እጩዎች ለሊቀመንበር እና ለምክትል ሊቀመንበርነት ይወዳደራሉ።

የኬንያውን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋን፣ የጅቡቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማህሙድ አሊ ዩሱፍን እና የማዳጋስካርውን ሪቻርድ ራንድሪያማንድራቶ የወቁቱን የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ መሐመት ለመተካት ይወዳደራሉ።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update #TPLF

" ቦርዱ ከፌደራል መንግስት ጋር የጀመርነውን ተከታታይ ውይይት ከማደናቀፍ እንዲቆጠብ እንጠይቃለን " - በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት 

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ህወሓት በልዩ ሁኔታ ከተመዘገበ ጊዜ አንሥቶ ባሉት  6 ወራት ውስጥ የቦርዱ ታዛቢዎች በተገኙበት ጠቅላላ ጉባዔ ማድረግ ይጠበቅበት ነበር  ፤ ይህንን ባለማድረጉ ለሦስት ወር ከፖለቲካ እንቅስቃሴ እንዲታደግ ፤ በሦስት ወራት የዕግድ ጊዜ የዕርምት ዕርምጃ ሳይወስድ ቢቀር የፖርቲው ምዝገባ እንዲሠረዝ መወሰኑ ተከትሎ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመሩት ህወሓት ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል። 

ህወሓት ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረ አንጋፋ ፓርቲ መሆኑ የገለፅው መግለጫው ፤ " ጥቅምት 23/2015 ዓ/ም በደቡብ አፍሪካዋ የፕሪቶሪያ ከተማ የሰላም ውል ከተፈራረመ ጀምሮ ህጋዊነት የተመለሰ ነው " ብለዋል።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ህወሓት ከነሃሴ 3/2016 ዓ.ም ጀምሮ ህወሓትን በአዲስ ህግ እንደ አዲስ ፓርቲ " መዝግቤዋለሁ ማለቱን " አስገራሚ እና ተቀባይነት የሌለው ፤ ፓርቲው ከፕሪቶሪያ ስምምነት ማግስት ህጋዊነቱ ያረጋገጠ ነው " ብሏል።

" የምርጫ ቦርድ አካሄድ በመሰረቱ ተቀባይነት የሌለው ፤ ህግን መሰረት ያላደረገ ተቀባይነት የሌለው ትርጉም አልባ ውሳኔ ነው " ብሎታል።

" ህወሓት በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት ከኢትዮጵያ መንግስት እውቅና ተሰጣጥቶ የሰላም ውል የፈረመ ፓርቲ ነው " ያለው ህወሓት ፤ " ከኢፌዲሪ መንግስት ተከታታይ የፓለቲካ ውይይት በማካሄድ ላይ ነን። ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ሰላማዊ ውይይቱ ከማደናቀፍ እንዲቆጠብ " ሲል አቋሙ ግልጿል።

ህወሓት ከኢፌዴሪ መንግስት በተከታታይ በማካሄድ ላይ ያለው ውይይት ውጤታማ በቅርቡ ወደ ፍሬ የሚቀየር መሆኑ የገለፀው ህወሓት " የምርጫ ቦርድ ይህንን መልካም ሂደት የሚፃረር አካሄድ በመሄድ ላይ ይገኛል " ሲል ከሷል።

የኢፌዴሪ መንግስት የፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመተግበር ህገ-መንግስቱ እንዲያከብር እና እንዲያስከብር የጠየቀው ህወሓት ፥ የምርጫ ቦርዱ ውሳኔ 50ኛው የፓርቲው የምስረታ በዓል ከማክበር እንደማያግደው በመግለፅ " ህዝቡ በዓሉ ለማክበር የጀመረው እንቅስቃሴ አጠናክሮ ይቀጥል " ብሏል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

🔊 #የሰራተኞችድምጽ

🔴 " ቅሬታችን በአስቸኳይ ምላሽ ያግኝ " - የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሰራተኞች

⚫️ " ለክልሉ መንግስት ቅሬታውን አቅርበናል። ነገር ግን ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ መስጠት አልቻለም " - የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የሰው ኃብት አስተዳደር


የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሰራተኞች " በሀገር አቀፍ ደረጃ ጥቅምት አንድ ተግባራዊ የተደረገው አዲሱ የደመወዝ ማሻሻያ ጭማሪ እስካሁን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ተግባራዊ  ባለማድረጉ ለከፋ ችግር ተጋልጠናል " ሲሉ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል።

በተጨማሪ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሸን ለሁሉም ሲቪል ሰርቫንት የኑሮ ውድነት መደጎሚያ ያደረገውን ጭማሪ እስካሁን አልተጨመረንም ብለዋል።

ሰራተኞቹ  የተለያዩ ጥያቄዎችን ለክልሉ ገቢዎች ቢሮ ማቅረባቸውን የገለፁ ሲሆን ጥያቄያችን በቀጠሮ  የታጀበ የአመታት ችግር ሆኖ ቀጥሏል ብለዋል።

" የክልሉ መንግስት የተቋሙን ሰራተኞች ድካም እና መስዋዕትነት የተረዳው አይመስለንም። እኛ ተስፋ ቆርጠናል ፣ የሚሰማን አካል የለም፣ እየታገትን እና እየተገደልን ነው ፣ ከማህበራዊ ሂወት ተገለናል " ብለዋል።

አክለውም " እንደሰው መቆጠር ናፍቆናል ፣ ችግሮቻችን በዝተዋል ፣  ችግሮችን የሚፈታልን የለም ፣ እባካችሁ የሚሰማን አካል ካለ የሁለት አመት ቅሬታችን ይሰማ " ሲሉ ድምጻቸውን አሰምተዋል።

አያይዘውም ሰራተኞቹ መጋቢት 5 / 2015 ዓ.ም " ይወክሉናል " ያሏቸውን ተወካዮች በመምረጥ ለክልሉ ገቢዎች ቢሮ ፣ ለበጀትና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እና ለብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት አመራር እንዲሁም ለርዕሰ መስተዳድሩ ልዩ አማካሪ ቅሬታቸውን እንዳቀረቡ ገልፀዋል።

ሰራተኞቹ በሰዓቱ ለአመራሮቹ ያቀረቧቸው ጥያቄዎች በርካታ መሆናቸውን የገልፁ ሲሆን ከጥያቄዎቻቸው መካከል ፦
- የገቢ ተቋሙ ሰራተኛ በልዩ ሁኔታ በጥናት ላይ የተመሰረተ ልዩ ጥቅማጥቅም ይደረግልን፣
- የእርከን ጭማሪ በአደረጃጃትና በመመሪያ ደረጃ የወረደ ቢሆንም በአፈጻጸም ተግባራዊ ይደረግ
- የሰራተኛውን ጥቅም የሚመለከት ጥናት ሲጠና እስከ ታችኛዉ መዋቅር ያለ ባለሙያ ተሳታፊ ይደረግ የሚሉ እና መሰል ጥያቄዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል።

በመሆኑም በሰዓቱ አመራሮቹ በምላሻቸው  ጥያቄው " ተገቢነት ያለው የባለሙያውን ሮሮና ብሶት ያዘለ ስለሆነ በቀጣይ የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ ይህንን አካል የግድ ማትጋትና ማበረታታት አስፈላጊ ስለሆነ ጥያቄውን እንፈታለን " ብለውን ነበር ሲሉ አስታውሰዋል።

" ይሁን እንጂ ቅሬታችንን ሰምቶ የፈታልን አካል የለም " ያሉ ሲሆን " አሁንም ለከፋ ችግር ተጋልጠን እንገኛለን " ሲሉ አክለዋል።

በሌላ በኩል ደግሞ ሰራተኞቹ የክልሉን የገቢዎች ቢሮ የሰው ሀብት አስተዳደር ቅሬታችንን ፍቱልን ብለን ጠይቀን ነበር ያሉ ሲሆን ሀላፊውም " ቅሬታችሁ ከአቅማችን በላይ ነው። በአስቸኳይ ምላሽ ይሰጣቸው ስንል ለክልሉ መንግስት ጥያቄ አቅርበናል እስካሁን ግን መልስ የለም " የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።

እንደተቋም በቀን እስከ 200 ሚሊየን ገቢ የሚሰበስብ ሰራተኛ አንድ ቀን ስራ ቢያቆም እንኳ ምን ሊፈጠር እንደሚችል መገመት ቀላል መሆኑን ጠቁመዋል።

ከቅሬታ አቅራቢዎቹ መካከል አንደኛው ከደሴ ኮምቦልቻ የደወለልን ባለሙያ ነው።

" ስራችን ከማህበረሰቡ ሂወት ነጥሎናል፣ ከነጋዴዎች አራርቆናል፣ ደመወዝ ሲያልቅብን እንኳ ከነጋዴዎች መበደር አንችልም፣ ቤት ለመከራየት ስንጠይቅ ገቢዎች ቢሮ ከሆነ የምትሰሩት አናከራይም እያሉን ነው፣ አሁን ላይ ችግሮችን መቋቋም አቅቶናል "  ሲል ተናግሯል።

ስሙን መጥቀስ ያልፈለገው የደባርቅ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ሰራተኛ ደግሞ " የደረጃ እርከን እየተሰራልን አይደለም 2012 ዓ.ም የደመወዝ ጭማሪ እንደተደረገ እስካሁን አልተጨመረንም ፤ በስራ አጋጣሚ ሂወታቸውን የገበሩ ጓዶች  አሉ የክልሉን መንግስት ታግሰናል አሁን ላይ ግን ኑሮ ከብዶናል " ሲል ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም የሰራተኞቹን ቅሬታ በመቀበል ለአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የሰው ሃብት አስተዳደር ሀላፊ ለአቶ ሽመልስ አዱኛ ቅሬታቸውን ያቀረበ ሲሆን እርሳቸውም ምላሽ ያሉትን ሰጥተዋል።

" የሰራተኞቹ ቅሬታ ተገቢ ነው። በኛ በኩል ቅሬታውን እናውቃለን ። ለክልሉ መንግስት ቅሬታውን አቅርበናል። ነገር ግን ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ መስጠት አልቻለም በዚህ ጉዳይ የተለየ መረጃ ልሰጥ አልችልም " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የባለሙያዎችን ቅሬታ በተመለከተ የክልሉን መንግስት እና የኮሚኒኬሽን ባለሙያ እንዲሁም የክልሉን ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ በስልክ አግኝቶ ምላሻቸውን ለማካተት ያደረገው ጥረት ባለመሳካቱ ምላሻቸውን ማካተት አልተቻለም።

በመጨረሻም ሰራተኞቹ " ቅሬታችን በአስቸኳይ ምላሽ የማያገኝ ከሆነ ከየካቲት 15/2017 ዓ.ም ጀምሮ  ስራ የምናቆም መሆኑን እንገልፃለን " ብለዋል።

(ቲክቫህ ጉዳዩን እስከመጨረሻው ተከታትሎ መረጃውን የሚያደርሳችሁ ይሆናል )

#TikvahEthiopia

@tikvahethmagazine

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Ethiotelecom

🪪 ከምዝገባ እስከ ካርድ ኅትመት!!
የዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ምዝገባዎን በአገልግሎት ማዕከሎቻችን በነጻ አካሄደው የካርድ ኅትመት በቀላሉ በቴሌብር ሱፐርአፕ ይዘዙ!
📍አዲስ አበባ 📍በቢሾፍቱ 📍ዲላ
📍ሐዋሳ 📍ለኩ 📍ይርጋጨፌ
📍አዳማ 📍ወንጂ 📍ቡሌሆራ
📍ወላይታ ሶዶ 📍ወለንጭቲ 📍ባኮ
📍ነቀምቴ 📍ዱከም 📍አረካ
📍ይርጋለም 📍አለታ ወንዶ

👉 ቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ላይ ‘’NID (Fayda) Printing’’ በሚለው ሚኒ መተግበሪያ!
🔗 የመረከቢያ ቦታዎቹን ለመመልከት፡ https://bit.ly/40efSUZ

ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!

#telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

Читать полностью…
Подписаться на канал