ortodoxmezmur | Неотсортированное

Telegram-канал ortodoxmezmur - ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

134932

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . ዝማሬ ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Подписаться на канал

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ቀጥታ ሥርጭት ከመንበረ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት

https://www.youtube.com/live/wMgJaj5pn4o?feature=share

የEOTC TV YOUTUBE ቻናል SUBSCRIBE አድርጉት ሁላችሁም 1Million እናድርሰው

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ማኅበረ ቅዱሳን በሁለት አኅጉረ ስብከቶች የሚገኙ አዳዲስ አማንያንን አስጠመቀ።

የማኅበረ ቅዱሳን ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ማስተባበሪያ በጎ አድራጊ ኦርቶዶክሳውያንን በማስተባበር ያሠራቸውን በሁለት አኅጉረ ስብከቶች ውስጥ የሚገኙ ሦስት አብያተ ክርስቲያናት ማለትም

1. በከምባታ ጠምባሮ ሀላባ ሀገረ ስብከት የቡጌ ኢየሱስና የጀባ ዶዶባ ቅዱስ ሩፋኤል አብያተ ክርስቲያናት

2. በቤንች ሸኮ፣ሸካ እና ምዕራብ ኦሞ ዞን ሀገረ ስብከት ጋሮ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያንን
በየካቲት 5 እና 6 ቀን 2015 ዓ.ም አስመረቀ፡፡

በምረቃው ዕለታትም 163 አዳዲስ አማንያን ሥርዓተ ጥምቀት ተፈጽሞባቸዋል።

በዕለቱም የአኅጉረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ እና የመምሪያ ኃላፊዎች፣ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ሕገወጡ ስብስብ አሁን በቲክቶክ ላይ Live መግለጫ እየሰጡ ይገኛል

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልዑካን እና የሩሲያ ቤተ ክርሰቲያን አገልጋዮች እንዲሁም የመንግስት ባለ ስልጣናት በእንዲህ አይነት መልኩ እየመከሩ ይገኛሉ።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የኦርቶዶክሳውያን እስር እንደቀጠለ ነው

የማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማእከል አባል የሆነው ዶ/ር እንዳሻው ዘርፉ በጸጥታ አካላት ተወስዳል

ዛሬ 5:00 አከባቢ ደ/ር እንዳሻዉ ዘርፉን ለጥያቄ እንፈልግሃለን በማለት በማለት አፍነው ወስደውታል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🎬 "በምግብ ሰዓት የሚጸለይ ጸሎት" - |ቀሲስ ሳሙኤን እሸቱ እንዳዘጋጀው ዮሴፍ በሪሁን እንዳነበበው|
👤 ዝማሬ ዳዊት ቲዩብ

⚠️ ጸሎቱን ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!
https://youtu.be/pjBReIJQ-Q4
https://youtu.be/pjBReIJQ-Q4

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ይህ ቻናል የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሊቃውንት ቃለ መጠይቅ የሚደረግበት እንዲሁም የተለያዩ ትምህርቶች የምናገኝበት ቻናል ነው።


👉ይህንን ቻናል Subscribe ማድረግ ለነፍሳችን ይጠቅመናል።


❓❓❓ጥያቄ❓❓❓

👉ስንት አይነት የነጠላ አደራረግ መንገዶች አሉ? ምሥጢሮቹንስ እናውቃለን? በእዚህ ቪድዮ ላይ መልሱን ታገኙታላችሁ

👉ስለ ዘፈን ከመጽሐፍ ቅዱስ አንጻር እንዲሁም ምዕራባውያን በዘፈን ምን ደረጃ ላይ ደርሰዋል? እንዴትስ ማቆም እንችላለን የሚለውን በተለየ መልኩ የተዘጋጀ ትምህርት አለ

👉ጸሎት ስንጸልይ እንዴት ሀሳባችንን ከመሰራረቅ መጠበቅ እና እግዚአብሔር የሚወደውን ጸሎት እንዴት መጸለይ እንችላለን? የጸሎት ቅድመ ዝግጅቶችስ ምን እንደሆኑ እናውቃለን?

👉በእዚህ በመከራ ጊዜ ንስሐ መግባት ፈልገናል ግን እንዴት ንስሐ መግባት እንዳለብን አናውቅም?

በዚህ የዩቲዩብ ቻናላችን ላይ ተለቋል subscribe በማድረግ ትምህርቶቹን ይከታተሉ።

👉 ቶ መስቀል የቤተክርስቲያናችን ነው ወይስ የግብጽ ጣዖታት እስከ ማስረጃው የተዘጋጀ ቪድዮ አለ


👉 እግዚአብሔርን በዓይኖቻችን ማየት እንፈልጋለን? የአባታዊ እቅፉን ማጣጣም እንፈልጋለን? እንግዲያውስ እግዚአብሔርን እንዴት መውደድ እንችላለን በሚል የተዘጋጀ ትምህርት አለ።

ይህንን ሊንክ ይጫኑት👇👇👇
Hadafe_nefese" rel="nofollow">https://youtube.com/@Hadafe_nefese

ከእዛም subscribe በማድረግ ይቀላቀሉ
🔴ሰብስክራይብ/Subscribe🔴

አሁን በማድረግ አገልግሎቱን ይደግፉ እናንተም የእግዚአብሔርን ቃል ተመገቡ።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የተመራ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልዑክ ለሁለትዮሽ ውይይት ሩሲያ /ሞስኮ/ መግባቱ ተገለፀ ።

በብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት እና የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የተመራ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልዑክ ከብፁዕ ወቅዱስ ኪሪል ጋር ለመወያየት እና የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት መልዕክትን ለማድረስና በሁለትዮሽ የአብያተ ክርስቲያናቱ ቀጣይ ግንኙነት ላይ ውይይት ለማድረግ ሞስኮ መግባቱ ነው የተገለፀው።

የልዑካን ቡድኑ አባላት የኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ የውጭ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ መምህር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል እና የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ጊዜያዊ እና ቋሚ ፕሮጀክቶች መምሪያ ኃላፊ መልአከ ሕይወት አባ ወ/ኢየሱስ ሰይፉ እንደሚገኙበት ተገልጿል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ሰበር ዜና

ጥር 14 በሕገ ወጥ መንገድ በመሾማቸው በቅዱስ ሲኖዶስ ከተወገዙት መካከል አንደኛው ዛሬ የካቲት 5/2015 ዓ.ም የይቅርታ ደብዳቤ ለማስገባት ጠቅላይ ቤተ ክህነት እንደሚገኙ ሰምተናል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#ሰልፉ_ተራዝሟል "

ቅዱስ ሲኖዶስ ምንም እንኳን የአቋም ለውጥ ባያደርግም ትላንት በነበረው ውይይት መንግሥት የቤተክርስቲያናችንን ጥሪ በመቀበል የቤተክርስቲያናችንን ችግር ለመፍታት #በመስማማቱ ነገ ሊደረግ የታሰበው ሰላማዊ ሰልፍ መራዘሙን አሳውቋል።

በትናትናው ዕለት ከመንግሥት ጋር ባደረግነው ውይይት መንግሥት የቤተ ክርስቲያኒቱን አቋም ሙሉ በሙሉ የተቀበለ ቢሆንም ይህንን ለማስፈጸም የሚያስችል የአፈጻጸም የድርጊት ጊዜ የሚያስፈልግ በመሆኑ እሁድ የካቲት ፭ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም እንዲካሔድ የተወሰነው ሀገር ዓቀፍ እና ዓለም አቀፍ የአደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ ለተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እግድ ተሰጠ ማለትም ክስ ቆመ ማለት እንዳልሆነ ያስታወሰው ኮሚቴው የምንጠይቃቸው የወንጀልና የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ይቀጥላሉ ብሏል።

የፌደራል ፖሊስ ፣ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት፣ የኦሮሚያ ፖሊስና ሰላም ሚኒስቴር እግዱን እንዲያስፈጽሙ ኃላፊነት የተጣለባቸው ተቋማት ናቸው።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

"በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት በፍፁም መንፈሳዊ መሪነትና ክብር ሄደናል፤ እግዚአብሔር ሰምቶናል፤ ከጠቅላይ ሚኒስትሩም ለጥያቄዎቻችን መልስ ተሰጥቶናል::" ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ

ዛሬ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር የነበረውን ውይይት አስመልክቶ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ መግለጫ ተሰጥቷል፡፡

በመግለጫውም ብፁዕነታቸው እንደገለጹት ትናንት በሰጠነው መግለጫ “በአስቀመጥነው ቅድመ ሁኔታ መሠረት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጠርተን ጥያቄያችንን አቅርበናል፡፡ ጥያቄያችንም አንድ ነው ሕገ ቤተ ክርስቲያን ይከበር፤ በሀገሪቱ ያለው ኦርቶዶክሳውያን መብት ይጠበቅ፤ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሀብትና ንብረት በሀገሪቱ ሕግ መሠረት ንብረቷ ይጠበቅ፤ እነዚህ ካልሆኑ ወደ ሰላማዊ ሰልፍ እንሄዳለን ማለታችን ይታወሳል፡፡ በዚህም በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት በፍፁም መንፈሳዊ መሪነትና ክብር ሄደናል ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር በነበረን ቆይታ በደንብ ተወያይተንበት ለጥያቄዎቻችንም መልስ ተሰጥቶናል ብለዋል ብፁዕነታቸው፡፡ እንዲሁም ዝርዝር መግለጫውን ነገ የምንሰጥ ይሆናል ብለዋል፡፡

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

"የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕመም ሕመማችን ክብሯ ክብራችን ነው::" የሮም ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን

የሮም ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን የአጋርነት ደብዳቤ በፖፑ የክርስቲያን አንድነት ፕሬዝደንት በኩል ላከች::

ብፁዕ ካርዲናል ኩርት ኮህ የፖፕ ፍራንሲስ የክርስቲያኖች አንድነት ፕሬዝዳንት (President Pontifical Council for Prompting Christian Unity) እንደገለጹት "በተፈጠረው ችግር እና ሁኔታ ጥልቅ ሐዘን የተሰማን ሲሆን ለቅዱስ ሲኖዶስ ያለንን አጋርነት በመግለጽ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን አንድነት ለመጠበቅ የሚደረግ ጥረትን በሙሉ እንደግፋለን" ብለዋል::

በመልእክታቸው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንጦስ በላከው የመጀመሪያ መልእክት “አንድም ብልት ቢሰቃይ ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ይሣቀያሉ፤ አንድ ብልትም ቢከበር ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ደስ ይላቸዋል።” 1ኛ ቆሮንጦስ 12፥26 ያለውን ጠቅሰው ሕመሟ ሕመማችን ክብሯ ክብራችን ነው ሲሉ በአጽንዖት ገልጸዋል።

በመጨረሻም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ እና የቤተ ክርስቲያን አንድነት እናት በምልጃዋ እጅግ የተከበረች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አንድነቷና ደህንነቷ እንዲጠበቅ ታድርግልን ብለዋል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ዛሬ ጠዋት የማኅበረ ቅዱሳን ደቡብ ማእከላት ማስተባበሪያ አስተባባሪ የሆነውን ዲ/ን መልካሙ ጸጋዬ ማንነታቸው ባልታወቁ አካላት ታፍነው ተወስደዋል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የተወደዳችሁ የዝማሬ ዳዊት ተከታታዮች።

👉የእሑዱ ሠላማዊ ሰልፍ የማይቀርበት ነው ስለዚህ ሁላችሁም ሀሞታችሁን ዋጥ አድርጋችሁ አንድ ላይ እንውጣ እና ለቤተክርስቲያን የከበርን ሙሽሪቶች እንሁን።

ግን ጥልቅ ማሳሰቢያ ንስሐ ያልገባን ካለን እባካችሁ ዛሬ እና ነገ ወደ ንስሐ አባቶቻችን በመሄድ ንስሐ እንግባ።

👉 የንስሐ አባትም ያልያዝን ወደ ቤተክርስቲያን ሄደን አባት እንያዝ እና ንስሐ እንግባ።


ሰማዕትም ብንሆን ንስሐ ገብተን ነው መሆን ያለበት። የሰማይ ቤታችንን በክብር እንድንገባበት

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

https://youtu.be/S6ydqpliJXQ

የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ በተመለከተ
👉የእሑድ ሰላማዊ ሰልፍ ከመቅረጡ አንጻር
👉ቤተክርስቲያን ላይ አሁን ምን አይነት ችግሮች ሊጋረጡ ይችላሉ? ምንስ ጥሩ ጎን አለው?
👉አሁንም ቤተክርስቲያንን ለማጥፋት የሚጥሩ የመንግስት አካላት እነማን ናቸው?

👉 እንደ አንድ ኦርቶዶክስ ከእኛ ምን ይጠበቃል የሚለውን በተከታታይ ክፍሎች የተካተተ ነው የሚሆነው።


ሁላችንም የዩቲዩብ ቻናሉን ሰብስክራይብ በማድረግ እንቀላለቀል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​VALENTINE'S DAY
ሼር በማድረግ ትውልዱን ከጥፋት እንታደግ❗

አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኛ ቤዛ ሆኖ በፍቅሩ የገዛን እጃችንን ለጣኦት እንድንሰጥ አይደለም ብዙ ዋጋ የተከፈለብን እስከ ሞት እንከን በሌለው ፍቅሩ የወደደን መንግስቱን እንድንወርስ እንጂ እንድንጠፋ አይደለም።

የቫላንታይ ቀን ድብቅ እውነታ ስንቶቻችን እናውቃለን? ይህን የቫላታይን ቀን (የፍቅረኛሞች ቀን) ብለን ስንቶቻችን ነን የምናከብረው ? ወይስ ሰው ስላከበረውና የስልጣኔ መገለጫ መስሎን ነው የምናከብረው ???

ከክርስቶስ ልደት በፊት በባቢሎን ፤ቤልዘቡል ፤በግሪክ ፓን ፤ ሮማ ሞሎቅ ፤ በላቲን ሳተርን ለሚባሉት ሰይጣኖች ያላገቡ ሴቶች ደም የሚፈስላቸው ቀይ ልብስ የሚለበስላቸው ጣኦቶች ናቸው ይህ ዛሬ ቫለንታይን ተብሎ የመጣው ማለት ነው።

የሚገርመው ደሞ ሴቶቹ በዚህ ቀን ለመደፈር ብለው እራቁታቸውን ጫካ መግባታቸው ነው በዚህ ቀን የተደፈረች እና ደሟን ያፈሰሰች ሴትም ሆነ ወንድ በጣኦቱ የተመረጠ እና የተባረከ ነው መባሉ ነው ይበልጥ ነገሩን ሰይጣናዊ የሚያደርገው።

ግሪክ አርኬዲያ ብለው በሚጠሩት አስቀያሚ ትርጉም ባለው ተራራቸው ላይ በዚህ ቀን ላይ ነው ያላገቡ ወንድ እና ሴቶቻቸውን ጣኦቱ ስር ወሲብ በመፈጸም ገላቸውን አርክሰው ለሰይጣን የሚገብሩት።

ይህ የሰይጣን ቀን ነው ክርስትና ይሄን ትከለክላለች ታወግዛለች። (ሁሉም ቀን የእግዚአብሔር ነው ግብሩ ነው የሰይጣን የሚያደርገው)

ኢየሱስ ክርስቶስ ከመውለዱ ከዘመናት በፊት አረማውያን ሮማውያኖች Feb 14 ማታ እና ለ Feb 15 ንጋት አጥቢያ የተኩላ አዱኚ ለሚሉት ሉፐርካልያ (luperkalya ) ጣኦት የሚዘጋች ክብረ በአል ነው፡፡

ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ክርስትና ተቀብሎ እውነተኛ የጽድቅ ሃይማኖት መሆኑን በማውጁ ማንኛውም የጣኦት አምልኮ እንዲቀር ቢያስጠነቅቅም የተውሰኑ የሮማውያን ሰዎች ግን በአሉን ማክበር አልተውም።

እንዴት ይህ አረማዊ ባህል ቫለንታይን የሚል ሰያሜ ተሰጠው? ቫለንታይን የሚል ስም በሮማውያን ዘንድ የተለመደ ስያሜ ነው፡፡ ቫለንታይን የጥንታዊ ታዋቂው ሉፐርኩስ ጣኦት ነው።

ሉፐርኩስ በግሪካዎያን ፓን (pan) ተብሎ ሚጠራው ከወገቡ በታች በግ አናቱ ላይ ቀንድ ያለው ጣኦት ነው። በጥንታውያን አይሁድ ደግሞ ይህ ፓን ባል (baal) በሚል ስያሜ ይታወቃል።

ጥንታውያን ሮማውያን ከባቢሎናውያን የቀዱት አረማዊ የልብ (heart) ምልክት ይጠቁማሉ፡፡ በባቢሎናውያን ባል (bal) ልብ የሚል ፍች ነው ያለው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ይህ አረማዊ የልብ ምልክት ለቫለንታይን ቀን (የፍቅረኛሞች ቀን) የምንለው መግለጫነት እንጠቀምበታለን። ባል የባቢሎናውያን ጣኦት ነበር።

በዚህ የሃጥያት ቀን በትንቹ ይህ ይሆናል

1. በዚህ ቀን February 14 በብዙ የሚቆጠሩ እህቶቻችንን ክብረ ንጽህናቸውን (ድንግልናቸውን) ያጣሉ❗

2. በርካታ ወጣቶች በስካር ምክንያት በሚያሽከረክሩት መኪና ህይወታቸውን እና አካላቸውን ያጣሉ❗

3. በአለማችን ላይ በከፍተኛ ሁኔታ የአልኮል መጠጥ ሽያጭ የሚከናወንበት ቀን ነው በአጠቃላይ የዝሙት እና ስካር መንፈስ የሚነግስበት በከፍተኛ ሁኔታ ሰይጣን በደም የሚረካበት ቀን ነው።

Valentine day ማለት ሰይጣን በጥልቅ እና ረቂቅ ሃሳብ ብዙዎችን የሚያጠምድበት ቀን ነው አስተውሉ ሰይጣን ከ7ሺህ አመት በላይ የክፋት ልምድ አለው።

እንግዲህ ምርጫው ያንተ/ቺ ነው :- የእግዚአብሔር ወይም የሰይጣን ልጅ መሆን???

" ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ አንተም እውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፤ የአምላክህንም ሕግ ረስተሃልና እኔ ደግሞ ልጆችህን እረሳለሁ። "
(ትንቢተ ሆሴዕ 4 : 6)

እግዚአብሔር አምላክ ማስተዋሉን ያድለን።
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

አስፈራርተው ወስደውኝ ነው

እንግዲህ ተመልከቱ ክርሰቲያኖች እሁድ እለት ወደ ቅድስት ቤ/ክ በይቅርታ የተመለሱት አባት ያን እለት ቪዲዮውን ያያችሁ አይታቹኋል።ዛሬ ደግሞ ወደ ሕገ ወጡ ሲኖዶስ በድጋሚ ተመልሰዋል።

ጌታ ሆይ ምን ጉድ ነው ???

ምንድነው ቆይ አየሆነ ያለው?

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የዚህ መንግስት ሌላ ራስ ምታት የካቲት 23

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት (EOTC TV) የኦሮምኛ ቋንቋ ጋዜጠኛ ዲ/ን ዮሴፍ ከተማ በጸጥታ ኃይሎች ታፍኖ ተወሰደ።

ዛሬ ሰኞ የካቲት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 አካባቢ በሥራ ጉዳይ በመንቀሳቀስ ላይ እያለ መካኒሳ አካባቢ ለጥያቄ እንፈልግሃለን የሚሉ የመንግሥት የጸጥታ አካላት አፍነው ወስደውታል።

የኦሮምኛ ቋንቋ ጋዜጠኛ ዲ/ን ዮሴፍ ከተማ በወቅታዊ ጉዳይ ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተደጋጋሚ ቃለ ምልልሶች በማድረግ ወደ ምእመናን ሲያደርስ ቆይቷል።

ምንጭ: EOTC TV

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🎬 ግብረ አውናን/ሴጋ/ የፈጸመ ኦርቶዶክሳዊ/ት ጋብቻውን/ዋን በተክሊል መፈጸም ይችላሉን?
👤 ዝማሬ ዳዊት ቲዩብ

⚠️ ትምህርቱን ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!
https://youtu.be/hnt5Y1F4TDY
https://youtu.be/hnt5Y1F4TDY

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

Watch "ነጠላ አደራረግ እስከ ምክንያቱ #orthodox #youtubeshorts #tiktok #viral" on YouTube
https://youtu.be/QByZooavA4E

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በቀድሞ ስማቸው አባ ንዋየ ሥላሴ አካሉ የይቅርታ ደብዳቤ በአስገቡ ሰዓት "የተሾሙበትን" አስኬማና አልባሳትም አስረክበዋል።

"እውነትን ተረድተው ስለመጡ ቤተ ክርስቲያን ደስተኛ ናት። ሌሎች በማወቅም ባለማወቅም የሄዳችሁ አሁንም ለመምጣት የተቸገራችሁ ቤተ ክርስቲያን በሯ ክፍት ነው::" ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በዛሬው ዕለት ምእመናን ወደ መንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን /ግቢ ገብርኤል/ እንዳይገቡ ተከለከሉ።

የጸጥታና የደኅንነት ግብረ ኃይል ትናንት ምሽት ከንጋቱ 11:00 እስከ ረፋድ 4:00 ሰዓት ድረስ የተለያዩ የከተማዋ መንገዶች ዝግ እንደሚሆኑ ተናግሮ ነበር።

የአጥቢያው ምእመናን ይህንን በማክበር ከሌሊት 10:00 ጀምሮ ወደ ደብሩ ቢሄዱም ከላይ የመጣ ትእዛዝ ነው በማለት ፖሊሶች እንዳይገቡ ከልክለዋቸዋል።

የደብሩ ሰንበት ትምህርት ቤት ባጋራው መረጃም ምእመናን በሌሉበት ሥርዓተ ቅዳሴ እንደተከናወነ ገልጿል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

https://youtu.be/T3hs_Jxwee0

ሞገሳቸው እግዚአብሔር ነው።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በሕገ ወጡ ሹመት ላይ የተሳተፉ የቀድሞ ሊቃነ ጳጳሳትና ግለሰቦች ከዛሬ የካቲት 3 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት እንዳይገቡ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አግዷል።

ዛሬ በነበረው የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀጠሮ የሕግ አማካሪዎች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በዚህም ሹመት የሰጡት በቀድሞ ስማቸው “አባ ኤዎስጣቴዎስ”፣ “አባ ዜና ማርቆስ”፣ “አባ ሳዊሮስ” እና እነርሱ በሕገ ወጥ መልኩ ሾመናችኋል ብለው ከሕገ ቤተ ክርስቲያን ውጪ አስኬማ ያቀዳጇቸው 25 ግለሰቦች እንዲሁም አቶ ኃይለ ሚካኤል ታደሰ የተባሉ ግለሰብ በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 156 መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ግቢ እንዳይገኙ በጊዜያዊነት አግዷቸዋል። ይህንን እግድ የተላለፈ ማንኛውም አካል የወንጀል ተጠያቂነት ይኖርበታል። በሀገሪቱ የሚገኙ የሕግ አስፈጻሚ አካላት እግዱን እንዲያስፈጽሙ ትዕዛዝ ተሰጥቷል። ቤተ ክርስቲያኗ በቀጣይ በሰብአዊ መብት፣ በአስተዳደር፣ በወንጀልና በፍትሐ ብሔር ለደረሰው ኪሣራ ተጠያቂዎችን በመለየት በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት በሕግ ትጠይቃለች።

በዚህም በሕገ ወጡ ሹመት ላይ የተሳተፉ የቀድሞ ሊቃነ ጳጳሳትና ግለሰቦች ከዛሬ የካቲት 3 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት እንዳይገቡ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አግዷል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#ሰበር_መረጃ

ቅዱስ ፓትርያርኩን ጨምሮ ብፁዓን አባቶች ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ውይይት እያካሔዱ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሕዝብ ግንኙነት አስቸኳይ ሰበር መግለጫ ሰጥቷል።

በመግለጫው ፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በየካቲት 2 ቀን 2015 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ መሠረት ቤተ ክርስቲያኒቱ መግለጫውን ባወጣች 72 ሰዓታት ውስጥ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሃይማኖት ፤ ቀኖናና አስተዳደራዊ ሕግጋትን ባልጣሰ መልኩ ከመንግሥት ጋር በጉዳዩ ላይ ለመወያየት መንፈሳዊ በሯ ክፍት መሆኑን በመግለጽ ይፋዊ ጥሪ ማስተላለፏን አስታውሷል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ የኢፌዳሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ይህንን የቤተ ክርስቲያን ጥሪ መሠረት በማድረግ ለውይይት ጥሪ ማቅረባቸውን ገልጿል።

ውይይቱ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ ሊሆን የሚገባ ነው በሚል በተነሳው ሐሳብ በጉዳዩ ላይ ከሽማግሌዎች ጋር ጥልቅ ውይይት በማድረግ የደህንነት ተሽከርካሪዎች እና የጸጥታ አካላት ብዛት ሲታይ ምእመናንን ስጋት ላይ እንዳይወድቁ እና ላልተጋባ ጉዳት እንዳይዳረጉ በማሰብ የሰላም ጥሪውን መንግሥት ከተቀበለ እና በቤተ መንግሥት መገኘቱ ለሕዝቡ የሚያመጣው መፍትሔ የሚኖር እንደሆነ በማሰብ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርካችንን ጨምሮ አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ያካተተ ልኡክ በቤተ መንግሥት የሚገኝ መሆኑን ጠቅላይ ቤተ ክህነት አሳውቋል።

ሕዝበ ክርስቲያኑም አባቶች የደረሱበትን ውጤት እስኪያሳውቁ ድረስ በትእግስት እንዲጠባበቁ መልእክት አስተላልፏል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የእሥር ዜና!

የኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ወጣቶችና ጎልማሶች ማኅበራት ኅብረት ዋና ሰብሳቢ ወ/ሪት ፌቨን ዘሪሁን እንዲሁም ዋና ፀሐፊዋ ወጣት ብሩክታዊት ታሥረዋል።

ምንጭ፡ ተሚማ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደርና የከተማው የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጎን መሆናቸውን አሳወቁ።

የጋሞ ዞንና የአርባ ምንጭ ከተማ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በወቅታዊ ጉዳዮችና የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔን  የሚደግፍ ምክክር አካሒደዋል።

የጋሞ ዞንና የአርባ ምንጭ ከተማ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በወቅታዊ ጉዳዮችና የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔን አስመልክቶ በትናንትናው ዕለት ባደረጉት ምክክር  በከተማው የሚገኙ የእስልምና እምነት ተከታዮችና  የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት የሃይማኖት ተወካዮች በኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ በደረሰው ክስተት ማዘናቸውን ገልጸዋል።

ቤተ ክርስቲያን ወደ ቀድሞው ሰላም እስክትመለስ ድረስ ሁሉም ቤተ እምነቶችና ምእመናን  በጾምና በጸሎት ከኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጎን እንደሚሆኑ  አሳውቀዋል።

ከተማ አስተዳደሩም ቅዱስ ሲኖዶሱ በሚያስቀምጠው አቅጣጫ መሠረት የሚጠይቁት ጥያቄ  እስኪመለስ ድረስ በማንኛውም ነገር  ከኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጎን መሆኑን አሳውቋል።

በመሆኑም ኅብረተሰቡ እንደ ከዚህ ቀደሙ የሰላም ማስከበር ሥራውን አጠናክሮ በማስቀጠል  እንግዳ እና አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት ጥቆማ በመስጠት ከጸጥታ አካላት ጎን በመሆን የተለመደ ተግባሩን ሊያከናውን እንደሚገባም ተገልጿል። ዘገባው የአርባ ምንጭ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

"አንተ ግን ወገብህን ታጠቅ፥ ተነሥም! . . . ከአንተ ጋር ይዋጋሉ፥ ነገር ግን አድንህ ዘንድ እኔ ከአንተ ጋር ነኝና ድል አይነሡህም፥ ይላል እግዚአብሔር። " (ኤር. ፩:፲፯)

Читать полностью…
Подписаться на канал