ortodoxmezmur | Неотсортированное

Telegram-канал ortodoxmezmur - ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

134932

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . ዝማሬ ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Подписаться на канал

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ምስባክ ዘትንሣኤ (ዘማሕሌት)

መዝ 77÷65
ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃህ እምንዋም።
ወከመ ኃያል ወኅዳገ ወይን።
ወቀተለ ፀሮ በድኅሬሁ።

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የማርያም ለቅሶ

ልጄ ወዳጄ ሆይ ለእኔ ወዮታ አለብኝ ... በጦር ሲወጉህና ሲገድሉህ ዓይኖቼ ከምያዩ ይልቅ ልጄ ወዳጄ ሆይ ነፍሴን ከስጋዬ ትለያት ዘንድ እማልድሃለሁ።

ልጄ ወዳጄ ሆይ ይህ በራስህ የተቀዳጀኸው የእሾህ አክሊል ምነው እኔ በተቀዳጀሁትና የመከራህ ተሳታፊ በሆንኩ።

ልጄ ወዳጄ ሆይ አንተን በእሱ ላይ በሰቀሉበት መስቀልህ በሰላም እሰናበትሃለሁ።
ልጄ ወዳጄ ሆይ አይሁድ መራቃቸውን በተፉበት ብርሃንንም በተሞላ ፊትህ እሰናበትሃለሁ: ንጉስ ሆይ በሁለት ወንበዴዎች መካከል እርቃኑን ለቆመው አካልህ እጅ እየነሳሁ እሰናበትሃለሁ።

ልጄ ወዳጄ ሆይ እጣ በተጣጣሉበት ክብር ልብስህ እጅ እየነሳሁ እሰናበትሃለሁ።
ልጄ ወዳጄ ሆይ አክሊለ ሶክክን ለተቀዳጀ እራስህ ሰላም እያልኩና እጅ እየነሳሁ እሰናበትሃለሁ።

ምንጭ ግብረ ሕማማት
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

👉 ድርሳነ ማሕየዊ ዘቀዳሚት

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በይስሐቅ ፈንታ
የበገና መዝሙር

በይስሐቅ ፈንታ ኢየሱስ ታረደ/2/
ደሙን ከፈለና አዳምን ታደገ/2/

ተጨነቀ ጌታ ተሰቃየ ጌታ
የኔ መድኃኔዓለም የአዳም ልጅ አለኝታ
እንደሚታረድ በግ ተነዳ ወደ ሞት
ንፁህ ኢየሱስ በደል የሌለበት

በማመን ሲሸከም የአዳምን መከራ
ስቃይ ተቀበለ ደሙ እየተዘራ
ለሚገርፋት ሁሉ ምህረትን ሲቸር
እርሱ ግን ሲገረፍ ብዙ ተቸገረ

የሰማነውን ድምፅ ማን ሰው እኮ አምኗል
የእግዚአብሔርስ ክንድ ለነማን ተገልጿል
ባየነው ጊዜ ህመም ተሸክሞ
ስለበደላችን ተገርፎና ታሞ

እጁ የታሰረው ይስሀቅ ተፈቶ
ኢየሱስ ቀረበ በሰው ልጆች ፈንታ
ንፁህ በግ ቀረበ በደል የሌለበት በደለኛ ሆኖ
ሊሰቀል ሊገደል መስቀሉን ተጭኖ

በእውነት ደዌያችንን እርሱ ተሰቀለ
በሰው ልጆች ፈንታ በእንጨት ተሰቀለ
እኛ ግን ከሰስነው እንደ ወንጀለኛ
ስለ እኛ ቢሰቀል ሰማያዊው ዳኛ

ለሰው ልጆች ህይወት የታሰበውን ሰይፍ
አይተናል ሰምተናል በኢየሱስ አንገት ሲያልፍ
የመስቀሉ ስዕል ኧረ እንዴት ይገርማል
እዩት ንፁህ በግ በአርምሞይነዳል

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​አዘነች ድንግል አለቀሰች

አዘነች ድንግል አለቀሰች ፍጹም አምርራ
በአንድ ልጇ ምክንያት ደርሶባት መከራ
በአንድ ልጇ ምክንያት ደርሶባት መከራ/፪/
#አዝ
በመንጻቱ ወር በዓርባኛው ቀን
ሥምዖን አረጋዊ ታቀፈ እና ጌታን
ትንቢት ተናገረ ተገልጾለት ሞቱ
በነፍስሽ ሠይፍ ያልፋል አንቺም እናቲቱ
ይኽንን መከራ ሲሠማ ጆሮዋ
አምርራ አለቀሰች አልቆም አለ ዕንባዋ
#አዝ
በአሥራ ሁለት ዓመቱ ለማክበር በዓል
በኢየሩሳሌም ቢገኝ አማኑኤል
ሲጠይቅ ሲሠማ በቤተ መቅደሱ
የኦሪት ካኅናት ሲደነቁ በእርሱ
እስከ ሦስት ቀን ድረስ ብትልጣው ፈልጋ
ልቧ ተሠበረ በሐዘን አለንጋ
#አዝ
ጠዋት በማለዳ በጲላጦስ ደጅ
ሲጸናበት አይታ የጨካኞች እጅ
ርቃኑን አድርገው ያለ አንዳች ጥፋት
ከግንድ ጋር አስረው ጀርባውን ሲገርፉት
እንዴትስ አታለቅስ እንዴት አታነባ
ሲገርፉት ሲያዳፉት ልጇን እንደ ሌባ
#አዝ
የዓለሙን ፈጣሪ የዓለሙን ዳኛ
ንጹሑን ጌታ መሥሏቸው ቀማኛ
እጁን እና እግሮቹን በችንካር ወጥረው
በወንበዴ መሐል ሠቅለውን ብታየው
ድንግል አለቀሰች አልቻለች መጽናናት
ዕንባዋ ወረደ እንደ ክረምት ጅረት
#አዝ
ዮሴፍ ኒቆዲሞስ በአንድ ሲማከሩ
ቅዱሥ ሐያል ብለድ ገንዘው ሊቀብሩ
በአዲስ መቃብር በአሥራ አንደኛው ሠዓት
ሥጋውን አኑረው በድንጋይ ቢዘጉት
እያለች ዐነባች አንድ ልጄ እኮ ነው
ከእርሱ የሚቀድም ተከታይ የሌለው።

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ሕማማት ክፍል 36

👉 ለሚፈሩት ምልክትን ሰጣቸው
✍ ጸሐፊ ፦ ዲ/ሄኖክ ኃይሌ
🎤 ተራኩ ፦ ኢዮብ ዮናስ

#ሼር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ሕማማት ክፍል 34

👉 በእጅህ መሃከል ያለው ቁስል ምንድር ነው
✍ ጸሐፊ ፦ ዲ/ሄኖክ ኃይሌ
🎤 ተራኩ ፦ ኢዮብ ዮናስ

#ሼር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ንሴብሖ

ንሴብሖ /2/ ለእግዚአብሔር /2/ 
ስቡሐ ዘተሰብሐ /4 
እናመስግነው /2/ እግዚአብሔርን /2/ 
ምስጉን ነው የተመሰገነ /4/ 

ባህሩን ተሻግረን ወንዙ ደረቅ ሆነ
በጠላታችን ላይ ድሉ የኛ ሆነ
ከባርነት ቀንበር ፍፁም ነፃ ወጣን
ህይወት የሚሰጠን መና ነው ምግባችን

አስፈሪ ነው ያልነው ብዙ ነገር ነበር
ሁሉንም አለፍነው አምላካችን ይክበር
ጉልበታችን ቢዝል መከራም ቢበዛ
ሃይላችን ጌታ ነው የዓለም ቤዛ

ከአለት ላይ ውሃ ፈልቆ እንደጠጣነው
ይህን ታላቅ አምላክ ኑ እናመስግነው
ሰዎች ደስ ይበለን ሕይወታችን ድኗል
ሰይጣን ጠላታችን አፍሮ ተመልሷል

አስፈሪ ነው ያልነው ብዙ ነገር ነበር
ሁሉንም አለፍነው አምላካችን ይክበር
ጉልበታችን ቢዝል ፈተናው ቢበዛ
ሃይላችን ጌታ ነው የዓለሙ ቤዛ

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ኪራላይሶን

ኪራላይሶን ኪራላይሶን/3/
ኪራላይሶን /2/ አማኑኤል ጌታ
ኪራላይንሶ /2/ በጥፊ ተመታ
ኪራላይሶ /2/ አለምን ሊታደግ
ኪራላይሶን /2/ ተነዳ እንደበግ
ኪራላይሶን /2/ አዳምን ሊፈውስ
ኪራላይሶን /2/ ቆመ ከጵላጦስ
ኪራላይሶን ኪራላይሶን

ኪራላይሶን/3/

ኪራላይንሶ /2/ እጁን ቸነከሩት
ኪራላይሶን /2/ አጥንቱን ቆጠሩት
ኪራላይሶን /2/ የእሾህ አክሊል ደፍቶ
ኪራላይሶን /2/ ገዳዩን እረቶ
ኪራላይሶን /2/ የሁላችን በደል
ኪራላይሶን /2/ ተሻረ በእርሱ ቁስል
ኪራላይሶን ኪራላይሶን

ኪራላይሶን/3/

ኪራላይሶን /2/ እጣ ተጣጣሉ
ኪራላይሶን /2/ ልብሱን ተካፈሉ
ኪራላይሶን /2/ ለፍርድ ተወሰደ
ኪራላይሶን /2/ እንደበግ ታረደ
ኪራላይሶን /2/ ለብሶ ከደም ሜዳ
ኪራላይሶን /2/ ተከፈለ እዳ
ኪራላይሶን ኪራላይሶን ኪራላይሶ

ኪራላይንሶ /3/

ኪራላይንሶ /2/ ሆምጣጤ አጠጡት
ኪራላይሶን /2/ በገመድ ጎተቱት
ኪራላይሶን /2/ በወንበዴው ፈንታ
ኪራላይሶን /2/ ተሰቀለ ጌታ
ኪራላይሶን /2/ ሁሉም ዘበቱበተ
ኪራላይሶን /2/ በዘላለም ህየወት
ኪራላይሶን ኪራላይሶን ኪራላይሶን

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#በዕጸ_መስቀል_ላይ

በዕጸ መስቀል ላይ በዚያ አደባባይ 
አምላክ ሆይ ጌታ ሆይ ተንገላታህ ወይ 
አምላክ ሆይ ጌታ ሆይ መከራ አየህ ወይ 
#አዝ
መስቀል አስይዘው ኪራያላይሶን 
ወደ ጎልጎታ   " "
ሲገራፉ ሲዳፉ  " "
ስትንገላታ  " "
#አዝ
ያንን አቀበት ኪርያላይሶን 
ያንን ዳገት  " "
ጀርባህ ተገርፎ  " "
ስትቃትት  " "
#አዝ
አንተን እያዩ ኪርያላይሶን 
ሴቶች ሲያለቅሱ  " "
እናቶች ቀርበው  " "
ላብህን ዳበሱ  " "
#አዝ
መስቀል አስይዘው ኪያላይሶን 
እንዲያ ሲያዳፉህ  " "
የቀሬናው ሰው  " "
ስምኦን አገዘው  " "

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

"ኢየሱስም በታላቅ ድምፅ ጮኾ። አባት ሆይ፥ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ አለ። ይህንም ብሎ ነፍሱን ሰጠ።"
(የሉቃስ ወንጌል 23:46)

"ኢየሱስም ሁለተኛ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ነፍሱን ተወ።"
(የማቴዎስ ወንጌል 27:50)

"ኢየሱስም በታላቅ ድምፅ ጮኸ ነፍሱንም ሰጠ።"
(የማርቆስ ወንጌል 15:37)

"ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ። ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።"
(የዮሐንስ ወንጌል 19:30)

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ዓርብ ስድስት ሰዓት

በዚህች ዕለት በዚህች ሰዓት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አይሁድ መስቀል አሸክመው፣ ከለሜዳ አልብሰው፣ ምራቅ እየተፉ ከተዘባበቱበት በኋላ ከለሜዳውን ገፍፈው፣ ልብሱን አልብሰው፣ እየገፉ፣ እያዳፉ ቀራንዮ አደባባይ አደረሱት፤ ልብሱንም ገፍፈው ራቁቱን በሁለት ወንበዴዎች መካከል በመስቀል ላይ ሰቀሉት።

“ከዚህም በኋላ የመስፍኑ ጭፍሮች ጌታችን ኢየሱስን ተቀብለው ወደ ፍርድ ሸንጎ ወሰዱት፤ ጭፍራውንም ሁሉ ወደ እርሱ ሰበሰቡ። ልብሱንም ገፈው ቀይ ልብስ አለበሱት። የእሾህም አክሊል ጎንጉነው በራሱ ላይ አቀዳጁት፤ በቀኝ እጁም ዘንግ አሲያዙት፤ በፊቱም ተንበርክከው፥ “የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን” እያሉ ተዘባበቱበት፤ በላዩም ተፉበት፤  ዘንጉንም ነጥቀው ራሱን መቱት። ከተዘባበቱበትም በኋላ ቀዩን ልብስ ገፍፈው ልብሱንም አለበሱት፤ ሊሰቅሉትም ወሰዱት።” (ማቴ ፳፯÷፳፯-፴)
“በወሰዱትም ጊዜ የቀሬና ሰው ስምዖንን ከዱር ሲመለስ ያዙት ከጌታችን ከኢየሱስ በስተኋላ መስቀሉን አሸከሙት።” (ሉቃ.፳፫÷፳፮)

“ከዚህ በኋላ ሊሰቅሉት አሳልፎ ሰጣቸው፤ ጌታችን ኢየሱስንም ተቀብለው ወሰዱት። መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው ቀራንዮ ወደሚባል ቦታ ወጣ። በዚያም ሰቀሉት፥ ከእርሱም ጋር አንዱን በቀኝ፥ አንዱንም በግራ አድርገው ሌሎች ሁለት ወንበዴዎችን ሰቀሉ፤ ኢየሱስንም በመካከላቸው ሰቀሉ። ጲላጦስም ጽሕፈት ጽፎ በመስቀሉ ላይ አኖረ፤ ጽሕፈቱም። ‘የአይሁድ ንጉሥ የናዝሬቱ ኢየሱስ’ የሚል ነበር።” (ዮሐ.፲፱÷፲፮-፲፱)

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​​​​​"​​ሕማማት መስቀል" ተብለው የሚዘከሩት አሥራ ሦስት ሲሆኑ እነዚህም፦

1. በብረት ሐብለ መጋፊያና መጋፊያው እስኪጋጠም ድረስ የኋሊት መታሰሩ
2. ከአፍንጫው ደም እስኪውጣ ድረስ 25 ጊዜ በጡጫ መመታቱ
3. 65 ጊዜ ከግንድ ማጋጨታቸው
4. 120 ጊዜ በድንጋይ ፊቱን መመታቱ
5. 365 ጊዜ በሽመል መደብደቡ
6. 80 ጊዜ ጽህሙን መነጨቱ
7. 6666 ጊዜ መገረፉ
8. አክሊለ ሦክ በራሱ ላይ መደፋቱ
9. 136 ጊዜ በምድር ላይ መውደቁ
10. ሳዶር፡ አላዶር፡ ኤዴራ፡ ዳናትና ሮዳስ በሚባሉ 5ቱ ቅንዋተ መስቀልበችንካር መቸንከሩ
11. መራራ ሐሞትን መጠጣቱ
12. መስቀሉን ተሸክሞ መንገላታቱ
13. በመስቀል መሰቀሉ ናቸው።

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በርባን ነኝ

በርባን ነኝ/3/ባንተ መስቀል የዳንኩኝ/2/
በኃጥያት በበደል የኖርኩኝ በክፋት
ወንበዴ ነበርኩኝ የሚገባኝ መሞት
ሁሉንም እረስተህ በፍቅር ያየኸኝ
ንገረኝ አምላኬ እንደምን ወደድከኝ

ጌታዬ በርባን ነኝ በሞትህ ያዳንከኝ
አምላኬ በርባን ነኝ በመስቀል ያዳንከኝ


ወንበዴው እኔ ነኝ ሀገር ያስቸገርኩኝ
እጆቼን በበደል በደም የታጠብኩኝ
አንተ ግን ራርተህ ተሰጠህ ስለ እኔ
ዋጋ ከፈልክልኝ ክርስቶስ ስለ እኔ

ጌታዬ በርባን ነኝ በሞትህ ያዳንከኝ
አምላኬ በርባን ነኝ በመስቀል ያዳንከኝ


ሞቴን ስጠባበቅ እኔ እንደ ስራዬ
ትክክል ነውና የክፋት ዋጋዬ
አንተ ግን ንጹሁ እኔን የወደድከኝ
ለነፍስህ ሳትሳሳ እንከ ሞት ደረስክ

ጌታዬ በርባን ነኝ በሞትህ ያዳንከኝ
አምላኬ በርባን ነኝ በመስቀል ያዳንከኝ


በዋጋ ገዝተኸኝ ዳግመኛ እንዳልሞት
ብርታት ሁነኝ እና ልለይ ከኃጥያት
መልካምም እንዳስብ መልካም እንድሰራ
በጽድቅ ልመላለስ ልቦናዬን አብራ

ጌታዬ በርባን ነኝ በሞትህ ያዳንከኝ
አምላኬ በርባን ነኝ በመስቀል ያዳንከኝ

ዘማሪ አቤል ተስፋዬ የበገና ዝማሬ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

(የሉቃስ ወንጌል ምዕ. 23)

25፤ ያንን የለመኑትንም፥ ስለ ሁከት ሰውንም ስለ መግደል በወኅኒ ታስሮ የነበረውን አስፈታላቸው፥ ኢየሱስን ግን ለፈቃዳቸው አሳልፎ ሰጠው።
26፤ በወሰዱትም ጊዜ ስምዖን የተባለ የቀሬናን ሰው ከገጠር ሲመጣ ይዘው ከኢየሱስ በኋላ መስቀሉን እንዲሸከም ጫኑበት።
27፤ ዋይ ዋይ ከሚሉና ሙሾ ከሚያወጡ ሴቶችና ከሕዝቡ እጅግ ብዙዎች ተከተሉት።
28-29፤ ኢየሱስ ግን ወደ እነርሱ ዘወር ብሎ እንዲህ አለ። እናንተ የኢየሩሳሌም ልጆች፥ ለእኔስ አታልቅሱልኝ፤ ዳሩ ግን። መካኖችና ያልወለዱ ማኅፀኖች ያላጠቡ ጡቶችም ብፁዓን ናቸው የሚሉበት ጊዜ እነሆ ይመጣልና ለራሳችሁና ለልጆቻችሁ አልቅሱ።
30፤ በዚያን ጊዜ ተራራዎችን። በላያችን ውደቁ፥ ኮረብቶችንም። ሰውሩን ይሉ ዘንድ ይጀምራሉ፤
31፤ በእርጥብ እንጨት እንዲህ የሚያደርጉ ከሆኑ፥ በደረቀውስ እንዴት ይሆን?
32፤ ሌሎችንም ሁለት ክፉ አድራጊዎች ደግሞ ከእርሱ ጋር ይገድሉ ዘንድ ወሰዱ።
33፤ ቀራንዮም ወደሚባል ስፍራ በደረሱ ጊዜ፥ በዚያ እርሱን ክፉ አድራጊዎቹንም አንዱን በቀኝ ሁለተኛውንም በግራ ሰቀሉ።

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​​​የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም 5ቱ ታላላቅ ሀዘናት

ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን በእኔ ምክንያት ካገኙሽ ኅዘናት የትኛው ይበልጣል ብሎ በጠየቃት ጊዜ እመቤታችንም ልጄ ወዳጄ ሆይ ባንተ ምክንያት ካገኙኝ ኅዘናት እነዚህን አምስቱ ይበልጣሉ ብላ እመቤታችን የጠቀሰቻቸው ታላላቅ ኅዘናት የሚከተሉት ሲሆኑ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እነዚህን ያንችን ኅዘናት እያሰበ የጸለየ ኃጢአቱን ይቅር እለዋለሁ ብሎ ቃል ኪዳን ሰጥቷታል።

፩ኛ - ስምዖን በቤተ መቅደስ ትንቢት በተናገረ ጊዜ።

=> ስምዖን የተባለው ፦ አረጋዊው ስምኦን ነው የእመቤታችን ሐዘን የሚጀምረው ገና አንድዬ ልጇን ከመውለዷ በስምተኛው ቀን ነው ቤተመቅደስ ይዛው በሄደች ጊዜ አረጋዊው ስምዖን “በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል (ልጅሽ በቀራንዮ ይሞታል)” ሉቃስ 2፥34-35 ብሎ በነገራት ጊዜ ድንግል ማርያም አምርራ አዘነች አለቀሰች።

እነሆ፥ የብዙዎች ልብ አሳብ ይገለጥ ዘንድ፥ ይህ በእስራኤል ላሉት ለብዙዎቹ ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው ለሚቃወሙትም ምልክት ተሾሞአል፥ በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል አላት። ሉቃ (2፡34-35)

፪ኛ - ከቤተ መቅደስ ፈልጌህ ባጣሁህ ጊዜ።

ወላጆቹም በያመቱ በፋሲካ በዓል ወደ ኢየሩሳሌም ይወጡ ነበር። የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ በሆነ ጊዜ፥ እንደ በዓሉ ሥርዓት ወደ ኢየሩሳሌም ወጡ፤ ቀኖቹንም ከፈጸሙ በኋላ፥ ሲመለሱ ብላቴናው ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ቀርቶ ነበር፥ ዮሴፍም እናቱም አላወቁም ነበር።

ከመንገደኞች ጋር የነበረ ስለመሰላቸው የአንድ ቀን መንገድ ሄዱ፥ ከዘመዶቻቸውም ከሚያውቋቸውም ዘንድ ፈለጉት፤ ባጡትም ጊዜ እየፈለጉት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ።

ከሦስት ቀንም በኋላ በመምህራን መካከል ተቀምጦ ሲሰማቸውም ሲጠይቃቸውም በመቅደስ አገኙት፤ የሰሙትም ሁሉ በማስተዋሉና በመልሱ ተገረሙ። ባዩትም ጊዜ ተገረሙ እናቱም። ልጄ ሆይ፥ ለምን እንዲህ አደረግህብን? እነሆ፥ አባትህና እኔ እየተጨነቅን ስንፈልግህ ነበርን አለችው። ሉቃ (2፡41-48)

፫ኛ - በጲላጦስ አደባባይ በገረፉህ ጊዜ።

በዚያን ጊዜም ጲላጦስ ኢየሱስን ይዞ ገረፈው። ወታደሮችም ከእሾህ አክሊል ጐንጕነው በራሱ ላይ አኖሩ ቀይ ልብስም አለበሱት፤ እየቀረቡም።

የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን ይሉት ነበር፤ በጥፊም ይመቱት ነበር። ጲላጦስም ደግሞ ወደ ውጭ ወጥቶ። እነሆ፥ አንዲት በደል ስንኳ እንዳላገኘሁበት ታውቁ ዘንድ እርሱን ወደ ውጭ አወጣላችኋለሁ አላቸው። ኢየሱስም የእሾህ አክሊል ደፍቶ ቀይ ልብስም ለብሶ ወደ ውጭ ወጣ። ዮሐ (19፡1-5)

፬ኛ - በዕለተ ዓርብ በሰቀሉህ ጊዜ።

ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት፤ መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሉት ወጣ። በዚያም ሰቀሉት፥ ከእርሱም ጋር ሌሎች ሁለት፥ አንዱን በዚህ አንዱን በዚያ ኢየሱስንም በመካከላቸው ሰቀሉ።

ጲላጦስም ደግሞ ጽሕፈት ጽፎ በመስቀሉ ላይ አኖረው፤ ጽሕፈቱም። የአይሁድ ንጉሥ የናዝሬቱ ኢየሱስ የሚል ነበረ። ኢየሱስም የተሰቀለበት ስፍራ ለከተማ ቅርብ ነበረና ከአይሁድ ብዙዎች ይህን ጽሕፈት አነበቡት፤ በዕብራይስጥና በሮማይስጥ በግሪክም ተጽፎ ነበር።

ስለዚህ የአይሁድ ካህናት አለቆች ጲላጦስን እርሱ። የአይሁድ ንጉስ ነኝ እንዳለ እንጂ የአይሁድ ንጉሥ ብለህ አትጻፍ አሉት። ጲላጦስም። የጻፍሁትን ጽፌአለሁ ብሎ መለሰ። ዮሐ. (19፡17-2

፭ኛ- ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ገንዘው ወደ አዲስ መቃብር ባወረዱህ ጊዜ።

ከዚህም በኋላ አይሁድን ስለ ፈራ በስውር የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የነበረ የአርማትያስ ዮሴፍ የኢየሱስን ሥጋ ሊወስድ ጲላጦስን ለመነ፤ ጲላጦስም ፈቀደለት። ስለዚህም መጥቶ የኢየሱስን ሥጋ ወሰደ።

ደግሞም አስቀድሞ በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ መቶ ንጥር የሚያህል የከርቤና የእሬት ቅልቅል ይዞ መጣ። የኢየሱስንም ሥጋ ወስደው እንደ አይሁድ አገናነዝ ልማድ ከሽቱ ጋር በተልባ እግር ልብስ ከፈኑት።

በተሰቀለበትም ስፍራ አትክልት ነበረ፥ በአትክልቱም ማንም ገና ያልተቀበረበት አዲስ መቃብር ነበረ።ስለዚህ መቃብሩ ቅርብ ነበረና ስለ አይሁድ ማዘጋጀት ቀን ኢየሱስን በዚያ አኖሩት። ዮሐ (19፡38-42)

እንዚህን አምስቱን የእመቤታችን ሐዘናት እያሰበ ያዘነ ዝክሯን የዘከረ በአማላጅነቷ የታመነ ዋጋው ከቶ አይጠፋበትም፡፡

ቅድስት ሆይ ለምኝልን
ቅድስት ሆይ ለምኝልን
ቅድስት ሆይ ለምኝልን
አሜን

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​በዝማሬ ዳዊት Tube የተላለፉ ትምህርቶች

1⃣ ኦርቶዶክስ እና የዓለም እምነቶች
https://youtu.be/HXh1IUuBOrE
2⃣ እግዚአብሔርን እንዴት መውደድ እንዳለብን
https://youtu.be/Asx80GdsDDE
3⃣ 666 እና የውጭ ዘፋኞች
https://youtu.be/3iFggkALrws
4⃣ ዘፈን እንዴት ተፈጠረ? ማንስ አስተማረን?
https://youtu.be/1P421kYHutU
5⃣ ስለ ቶ መስቀል ክፍል 1
https://youtu.be/qevNJ5hYQ90
6⃣ ስለ ቶ መስቀል ክፍል 2
https://youtu.be/3H0FkrKbg9A
7⃣ ስለ ቶ መስቀል የመጨረሻው ክፍል
https://youtu.be/2QB2Ra7FHf8
8⃣ ሴጋ የፈጸመ የተክሊል ጋብቻ ይገባዋልን?
https://youtu.be/hnt5Y1F4TDY
9⃣ በጸሎት መሀል ወሬ ማውራት
https://youtu.be/2VsM6cVwgcU
1⃣0⃣ ቅዠት ምንድን ነው?
https://youtu.be/m6eD1pzyIWM
1⃣1⃣ የምግብ ሰዓት ጸሎት
https://youtu.be/pjBReIJQ-Q4
1⃣2⃣ የምእመናን አለባበስ ምን ይመስላል
https://youtu.be/fKuDfxWKUyY
1⃣3⃣ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እና ፕሮቴስታንት ክፍል አንድ
https://youtu.be/HBb3vZBZqzs
1⃣4⃣ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እና ፕሮቴስታንት ክፍል ሁለት
https://youtu.be/PbmNFCYro4I
1⃣5⃣ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እና ፕሮቴስታንት የመጨረሻው ክፍል
https://youtu.be/1NKzUoqtucs
1⃣6⃣ ስለ ቅዱስ ቁርባን ክፍል አንድ
https://youtu.be/Oji7daT4obw
1⃣7⃣ ንስሐ መግባት ለምን እንፈራለን?
https://youtu.be/kIkhOnUJm_A
1⃣8⃣ ሕማማት
https://youtu.be/NMHnlH0YLEE
1⃣9⃣ ስለ ዓቢይ ጾም
https://youtu.be/uErRRCkMsU0
2⃣0⃣ ዘጠኙ አጾማት
https://youtu.be/ZV7iwQS8mEk
2⃣1⃣ ለፓስተር ዳዊት የተሰጠ ምላሽ
https://youtu.be/hK473EGk0qs
2⃣2⃣ ለዮናታን አክሊሉ የተሰጠ ምላሽ
https://youtu.be/m8sFeVaja4I
2⃣3⃣ ጸሎት ምንድን ነው?
https://youtu.be/ZFYd4X-eGBo
2⃣4⃣ ክርስቲያናዊ የሆነ ጾም እንዴት እንጹም
https://youtu.be/ZV7iwQS8mEk
2⃣5⃣ ከፍቅረኛዬ ጋር ወደፊት ስለምንጋባ አሁን ግንኙነት ብንፈጽምስ?
https://youtu.be/ZV7iwQS8mEk
2⃣6⃣ ግብረ አውናን ምንድነው?
https://youtu.be/1XgZf6hq8bs
2⃣7⃣ ቅዱስ ቁርባን ለመቀበል ማድረግ ያለብን ዝግጅት?
https://youtu.be/TQeWVmN47PY
2⃣8⃣ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ? 81 ወይስ 66
https://youtu.be/Iggo8ws7quM


በዝማሬ ዳዊት የተላለፉ አጭር ታሪኮች

1⃣ የሰይጣን ጥያቄ
https://youtu.be/mHGEluQCJNY
2⃣ ባላገሩ
https://youtu.be/Kcftb4CReyg

👉 የልደት (ገና) መዝሙሮች
https://youtu.be/iSWmxwIJAac
👉 የጥምቀት መዝሙሮች
https://youtu.be/ESAE29ZvF3o
👉 አጫብር ወረብ
https://youtu.be/phssFP3KCRg
👉 መጾሙን ይጾማል - የበገና መዝሙር
https://youtu.be/q0TcGVnRGb4
👉 ማን ይመራመር - የበገና መዝሙር
https://youtu.be/dHqXNw_27R8
👉 የሰርግ መዝሙሮች
https://youtu.be/Xyc7R1Gk2Fs
👉 ዓለምን ዞሬ አየሁት? - የበገና
https://youtu.be/YP5ugEAYQRg
👉 ስለ ቸርነትህ - የበገና
https://youtu.be/KGBhL_7pA1c

ለሁሉም ሼር ያድርጉ ላላወቁት እናሳውቅ!
Subscribe ማድረግዎን እንዳይዘነጉ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​​​👉 ቅዳሜ

ቀዳም ስዑር ትባላለች ፦
ይህች እለት ከድሮ በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትውል የተሻረች ቅዳሜ ይባላል።

ለምለም ቅዳሜ ይባላል፡-
ካህናቱ ለምእመናን ለምለም ቀጤማ የሚያድሉበት ዕለት በመሆኑም ለምለም ቅዳሜ ይባላል። ምዕመናንም ይህንን ለምለም ቀጤማ እስከ ትንሣኤ ለሊት በራሳቸው ላይ ያስሩታል።

ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል፡-
ቅዱስ የሆነው እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ ፍጥረታትን አከናውኖ ያረፈበት ቀን ሲሆን በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የማዳን ስራውን ሁሉ ፈጽሞ በሥጋው በመቃብር ሲያርፍ በነፍሱ ወደ ሲኦል ወርዶ ሲኦልን በርብሮ ባዶዋን ሲያስቀራት በዚያ የነበሩትን ነፍሳት የዘላለም ዕረፍትን ያወረሰበት ዕለት ስለሆነ ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል።
ዝርዝሩን - https://youtu.be/NMHnlH0YLEE

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

መች ይረሳል
የበገና መዝሙር

መች ይረሳል የዋለልን ውለታ
ቸርነቱ እፁብ ፍቅር የጌታ
የታተመው በልባችን ፅላት
ሞትን ገድሎ የሠጠንን ህይወት

በጥፋቱ ቢወጣ አዳም ከገነት
ቃል ገባለት ዳግም ሊሰጠው ህይወት
ህያው ጌታ አምላክ ፈጣሪ ሳለ
ስለ ቃሉ በእፀ መስቀል ላይ ዋለ
አዝ
በአይሁድ እጅ በፅኑ ተንገላታ
የፍቅር አባት ክርስቶስ የእኛ ጌታ
ሥጋው ደክሞ ቅዱስ ደሙ ፈሰሰ
እዳችንን በሞቱ ደመሠሠ
አዝ
ስንጠላው እርሱ አብዝቶ ወደደን
ስለ ፍቅሩ ሞትን ገድሎ አዳነን
ባርነትን ኃጢአትን ከኛ ጥሎ
ነፃ አወጣን በመስቀል ላይ ተሰቅሎ
አዝ
ሰላማችን የድንግል ማርያም ፍሬ
ይገባዋል ምስጋና ዝማሬ
ስለ ፍቅሩ ስላረገልን ሁሉ
ተቀኙለት ፍጥረታት ዝም አትበሉ

መምህር አቤል ተስፋዬ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እውነት ስለሆነ

እውነት ስለሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ 
ዋለ ባደባባይ ሲሰደብ ሲከሰስ 
የሀሰት ዳኝነት አምላክን ወቀሰው 
ህይወት ሰጠን እንጂ ጥፋቱ ምንድነው/2/ 
#አዝ
ከቃሉ እብለትን ባያገኙበትም 
ዝምታውን አይተው አላዘኑለትም 
ባላወቁት መጠን ጠሉት ካለበደል 
ጥፋቱ ምን ይሆን የሚያደርስ ከመስቀል/2/ 
#አዝ
የልቡን ትህትና ፍቅሩን ሳያስተውሉ 
ቸሩ ጌታችንን አቻኩለው ሰቀሉ 
እሩህሩሁን ጌታ ቸንክረው ሰቀሉት 
ሞትን አስውግዶ ቢሰጣቸው ህይወት/2/ 
#አዝ
ስለ ቸርነቱ ስድብን ከፈሉት 
ስለ ርህራሄው የሾህ አክሊል ሰጡት 
ሀሞትና ከርቤ ሆምጣጤ ደባልቀው 
መራራ አስጎነጩት ጨክኖልባቸው/2/ 
#አዝ
ፈውስን ለሰጣቸው ልባቸውን ሞልተው 
አሉት ወንበዴ ነው ስቀለው ስቀለው 
ከጁ በረከትን የተሻሙ ሁሉ 
ይጮሁ ነበረ ይገደል እያሉ/2/

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ሕማማት ክፍል 35

👉 ዕፅ ይገድላል ዕፅ ያድናል
✍ ጸሐፊ ፦ ዲ/ሄኖክ ኃይሌ
🎤 ተራኩ ፦ ኢዮብ ዮናስ

#ሼር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ሕማማት ክፍል 33

👉 የኢየሱስን ልብስ ገፈፉት
✍ ጸሐፊ ፦ ዲ/ሄኖክ ኃይሌ
🎤 ተራኩ ፦ ኢዮብ ዮናስ

#ሼር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ክርስቲያኖች ሁላችሁ ኑ እናፅናናት

"ክርስቲያን ሁላችሁ ኑ ድንግል ማርያምን እናፅናናት፤ በልጇ ስቃይ ሆድ ብሷታልና፥ እንባን ከመጠጧ ጋር አመድንም ከምግቧ ጋር ቀላቅላለችና። የተወደደ ልጇ በመስቀል ተሰቅሎ ስታየው አንድ ጊዜ ከእሾህ አንድ ጊዜ ከድንጋይ ላይ እየወደቀች አለቀሰች። ወንድም የሌለው አንድ ልጇ እንዲህ ሲሰቃይ የወለደ አንጀቷ እንደምን ይቻል? ምንስ ብላ ትፅናና? ያፅናኗት ዘንድ ሊቃነ መልአክት በዙሪያዋ መጡ ግን አልተፅናናችም፤ ልጄ እያለ የሚጠራት አባቷ ዳዊትም መጣ ድንግል ግን እርቃኑን የተሰቀለው ልጇን እያየች መሪር እንባን አፈሰሰች። ስለ ልጇ ብዙ መከራ አሳልፋለች፥ ያሁኑ የልጇ መከራ ግን ከሀዘኖች ሁሉ የከፋ ሆነባት። አንድ ልጇ እየሞተ ምን ብላ ትፅናና ? የእናቱን አለመፅናናት ያየ ጌታ ኢየሱስ ከሃዘን ብዛት እንዳትሞት ያፅናናት ዘንድ ቁጽረ ገፅ ለተባለው ለዮሐንስ እነኋት እናትህ አለው። በእውነት እነኋት እናታችን በልጇ ስቃይ ሆድ ብሷታልና ክርስቲያን ሁላችሁ ኑ እናፅናናት።"

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ጌታ ሆይ

ጌታ ሆይ አይሁድ አማጽያን
ሰቀሉህ ወይ 
የዓለም መድኃኒት የዓለም ሲሳይ
ሰቀሉህ ወይ /2/ 

የአዳም በደል አደረሰህ
አንተን ለመሰቀል 
የሔዋን ስህተት አበቃህ ለሞት
ቸሩ አባት/2/
አዝ
ንጹሕ ክርስቶስ ሆንክ ወንጀለኛ
ብለህ ስለእኛ 
መሰቀል አሸክመው
አስረው ገፈፉህ እያዳፉህ/2/ 
አዝ
እጅና እግርህን በብረት ተመታ
የዓለም ጌታ 
የሾህ አክሊል ደፍተህ
ጎንህን ተወጋህ አልፋ ኦሜጋ/2/
አዝ
ግብዞች እንደራሳቸው መስሏቸው 
ምራቅ እየተፉ በፊትህ ቀለዱ
አንተን ሊጎዱ/2/
አዝ 
በመሰቀል ላይ ተጠማሁ ስትል
ታላቅ በደል 
ሀሞትና ከርቤ ሰጡህ ቀላቅለው
ጠጣ ብለው/2/
አዝ
ይቅር ባይ ግልጽ በደላችንን ሁሉ ሳታይ 
አንተ ይቅር በለን
በእኛ ሳትከፋ እንዳንጠፋ /2/ 

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን

ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን አባት ሆይ
በመስቀል ሆነህ አባት ሆይ
ድምጽህን በማሰማት አባት ሆይ
ነፍስህን ሰጠህ አባት ሆይ

ከዋክብተ ሰማይ በሙሉ ረገፉ
ጨረቃና ፀሐይ ደምን አጎረፉ
ብርሃናት ጨለሙ ጠፍተው ተለያዩ
ሥጋህን በመስቀል ተገልጦ ስላዩ
#አዝ
ጌታችን ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ
አሰምቶ ጮኸ ተጠማሁ እያለ
ማርና ወተትን ለሚመግበው
ሐሞት አመጡለት ይቅመሰው ብለው
#አዝ
አካሉ ሲወጋ ውኃ ደም ፈሰሰ
በምድር ተረጭቶ ዓለምን ቀደሰ
የእሥራኤል ሴቶች ዋይ ዋይ ሲሉልህ
ለእነርሱ አዘንክ እንጂ ለአንተስ አላሰብክም
#አዝ
እናትህ ስታለቅስ በመስቃል ሥር ሆና
ዮሐንስን ሰጠህ ጠብቆ እንዲያፅናና
መላእክትም ታዩ አጋንንትም ሸሹ
የአይሁድ ሠራዊት ፈርተው ተረበሹ

ሊቀ-መዘምራን
ኪነ-ጥበብ ወልደ-ቂርቆስ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ዓርብ ዘጠኝ ሰዓት

በዚህች ዕለት በዚህች ሰዓት የዓለም መድኃኒት ጌታችን ኢየሱስ ለአዳም ልጆች ድኅነት በመስቀል ላይ ሆኖ በታላቅ ድምፅ ጮሆ “ኤሎሄ ኤሎሄ” ብሎ “ሁሉ ተፈጸመ” በማለት በባሕርይው ሞት የሌለበት አምላክ ነፍሱን በፈቃዱ ለሞት አሳልፎ ሰጠ።

“ቀትር በሆነ ጊዜም በስድስት ሰዓት ፀሐይ ጨለመ፤ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስም ዓለም ሁሉ ጨለማ ሆነ። ፀሐዩም በጨለመ ጊዜ የቤተ መቅደሱ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ከመካከሉ ተቀደደ። ያን ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ድምፁን ከፍ አድርጎ፥ “አባት ሆይ፥ ነፍሴን በአንተ እጅ አደራ እሰጣለሁ”’ ብሎ ጮኸ፤ ይህንም ብሎ ነፍሱን ሰጠ።” (ሉቃ.፳፫÷፵፬-፵፮)

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​​​👉 ሰባቱ የመስቀሉ ቃላት

1. አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ (ማቴ 27፡46)
2. አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው (ሉቃ 23፡34)
3. ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር እንድትኖር በእውነት እነግርሃለሁ (ሉቃ 23፡43)
4. እነሆ ልጅሽ አነኋት እናትህ (ዮሐ 19፡26-27)
5. ተጠማሁ (ዮሐ 19፡28)
6. አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ (ሉቃ 23፡46)
7. የተጻፈው ሁሉ ደረሰ ተፈጸመ አለ (ዮሐ 19፡30)

👉 ሰባቱ ተዐምራት

ጌታ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈጸሙ ተዐምራት

1. ፀሐይ ጨልሟል
2. ጨረቃ ደም ሆነ
3. ከዋክብት ረገፉ
4. ዐለቶች ተሠነጠቁ
5. መቃብራት ተከፈቱ
6. ሙታን ተነሡ
7. የቤተ መቅደስም መጋረጃ ለሁለት ተቀደደ

👉 አምስቱ ችንካሮች

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቸነከረባቸው አምስቱ ችንካሮች

1. ሳዶር ፦ በሚባል ችንካር ቀኝ እጁን ቸነከሩት
2. አላዶር ፦ በሚባል ችንካር ግራ እጁን ቸነከሩት
3. ዳናት ፦ በሚባል ችንካር ሁለት እግሩን ቸነከሩት
4. አዴራ ፦ በሚባል ችንካር ማሀል ልቡን ቸነከሩት
5. ሮዳስ ፦ በሚባል ችንካር ደረቱን ቸነከሩት

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እስመለአለም ምህረቱ

እስመለአለም ምህረቱ/4/
አያልቅም ብዙነው የአምላክ ቸርነቱ/2/

ከማርያም የነሳው ያቅዱስ ስጋው/2/
ቀራንዮ ሲውል የሚያሳዝን ነው/2/

በፈጠረው ፍጥረት እጅግ ተሰቃይቶ/2/
ነፍሳትን አወጣ ከሲኦል ጎትቶ/2/

የማይሞተው ሞቶ የተቀበረው/2/
ከገሀነም እሳት እኛን ሊያድን ነው/2/

አመስግኑት ጌታን ሁላችሁ በአንድነት/2/
መሀሪ ነውና ለሰው ልጆች ህይወት/2/

በኩረ መዘምራን ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

መስቀል ላይ ያየሁት ፍቅር

መስቀል ላይ ያየሁት ፍቅር (2)
ይቀሰቅሰኛል ለስሙ እንድዘምር (2)

ፊቱን እየፀፉት/ እየተንገላታ (2)
በጦር እየወጉት /ይሰጣል ይቅርታ (2)
እነርሱ እየጠሉት/ እርሱ ይወዳቸዋል (2)
አስረው ሲጎትቱት/ ይከተላቸዋል (2)
#አዝ
ፃድቁን ሃጥእ ነው/ እውነትን ሃሰት (2)
እያሉ ሲጮሁ /ይሰቀል ይሙት (2)
እየመረመረው/ ፍጡር ፈጣሪን (2)
ክርስቶስን አስሮ/ ፈታው በርባንን (2)
#አዝ
ጀርባውን ሲገርፉት በሚያቃጥል ጅራፍ
በምህረት ያዛቸው በይቅርታው እቅፍ (2)
ጨክነው ሲያጠጡት መራራ ሃሞት (2)
ደሙን አፈሰሰ ጎኑን ሲወጉት (2)
#አዝ
ግምጃን አለበሱት/ ቀሚሱን ገፈው (2)
በራሱም አኖሩ/ እሾህ ጎንጉነው (2)
የአይሁድ ንጉስ ሆይ/ እያሉ ዘበቱ (2)
ለህይወት ሆናቸው/ የክርስቶስ ሞቱ (2)

ሊቀ-መዘምራን
ዲያቆን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

(የሉቃስ ወንጌል ምዕ. 23)

24፤ ጲላጦስም ልመናቸው እንዲሆንላቸው ፈረደበት።
25፤ ያንን የለመኑትንም፥ ስለ ሁከት ሰውንም ስለ መግደል በወኅኒ ታስሮ የነበረውን አስፈታላቸው፥ ኢየሱስን ግን ለፈቃዳቸው አሳልፎ ሰጠው።
26፤ በወሰዱትም ጊዜ ስምዖን የተባለ የቀሬናን ሰው ከገጠር ሲመጣ ይዘው ከኢየሱስ በኋላ መስቀሉን እንዲሸከም ጫኑበት።
27፤ ዋይ ዋይ ከሚሉና ሙሾ ከሚያወጡ ሴቶችና ከሕዝቡ እጅግ ብዙዎች ተከተሉት።
28-29፤ ኢየሱስ ግን ወደ እነርሱ ዘወር ብሎ እንዲህ አለ። እናንተ የኢየሩሳሌም ልጆች፥ ለእኔስ አታልቅሱልኝ፤ ዳሩ ግን። መካኖችና ያልወለዱ ማኅፀኖች ያላጠቡ ጡቶችም ብፁዓን ናቸው የሚሉበት ጊዜ እነሆ ይመጣልና ለራሳችሁና ለልጆቻችሁ አልቅሱ።
30፤ በዚያን ጊዜ ተራራዎችን። በላያችን ውደቁ፥ ኮረብቶችንም። ሰውሩን ይሉ ዘንድ ይጀምራሉ፤
31፤ በእርጥብ እንጨት እንዲህ የሚያደርጉ ከሆኑ፥ በደረቀውስ እንዴት ይሆን?
32፤ ሌሎችንም ሁለት ክፉ አድራጊዎች ደግሞ ከእርሱ ጋር ይገድሉ ዘንድ ወሰዱ።
33፤ ቀራንዮም ወደሚባል ስፍራ በደረሱ ጊዜ፥ በዚያ እርሱን ክፉ አድራጊዎቹንም አንዱን በቀኝ ሁለተኛውንም በግራ ሰቀሉ።

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…
Подписаться на канал