ortodoxmezmur | Неотсортированное

Telegram-канал ortodoxmezmur - ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

134932

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . ዝማሬ ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Подписаться на канал

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የተለያዩ ቦታዎች የመንግስት የፀጥታ ሐይሎች ያደርጉ የነበረውን ጥበቃ ባልታወቀ ሁኔታ አቁመዋል!

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🎬  🛑 ምስጢረ ሥጋዌ የክርስቶስ ሰው መሆን የመጨረሻው ክፍል | አምስቱ አዕማደ ምስጢራት |
👤 ዝማሬ ዳዊት ቲዩብ

⚠️ ትምህርቱን ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!
https://youtu.be/ZwEn8GvaEgM
https://youtu.be/ZwEn8GvaEgM

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለሊቀ ጉባኤ አባ ተክለሃይማኖት ወልዱን የሰጠውን የመኖሪያ ቤት ውል አቋረጠ ቤቱንም አሸገ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ሊቀ ጉባኤ አባ ተክለሃይማኖት ወልዱ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ በነበሩበት ወቅት ከጠቅላይ ቤተክህነት በተሰጠ ትዕዛዝ የተሰጣቸውን ከድርጅቱ የተሰጣቸውን መኖሪያ ቤት ውል በማቋረጥ ቤቱን ተረክቧል።

ድርጅቱ ውሳኔውን ያስተላለፈው ሕገ ወጥ መንገድ የቤተክርስቲያናችንን ቀኖናና ሕግጋት በመጣስ በትላንትናው እለት የተሰጠውን ሕገ ወጥ ሹመት ተከትሎ ዋነኛ አስተባባሪና ተሿሚ መሆናቸውን ምክንያት በማድረግ ነው።

ምንጭ: የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ከጀርመን ሀገረ ስብከት ጽ/ቤ በወቅታዊ ጉዳይ የተሰጠ መግለጫ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ከማኅበረ ቅዱሳን በወቅታዊ ጉዳይ የተሰጠ መግለጫ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መግለጫ ተሰጠ።

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#አስቸኳይ_የቅዱስ_ሲኖዶስ_ምልዐተ_ጉባኤ_ተጠራ!

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ሰጥቷል።

ቅዱስ ሲኖዶስ በአገር ውስጥ እና በውጪ አገር  ያሉ ሁሉም ሊቃነ ጳጳሳት በአስቸኳይ ከነገ ጀምሮ  ለአስቸኳይ ስብሰባ እንዲመጡ አሳስቧል።

መንግሥትም በተፈጠረው ችግር አስፈላጊውን ጥበቃ እንያደርግ እንዲሁም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን እንዲረጋጉ መልእክት አስተላልፏል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🎬  🛑 ምስጢረ ሥጋዌ የክርስቶስ ሰው መሆን | አምስቱ አዕማደ ምስጢራት | ክፍል አንድ!
👤 ዝማሬ ዳዊት ቲዩብ

⚠️ ትምህርቱን ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!
https://youtu.be/GhPT-R0G4D0
https://youtu.be/GhPT-R0G4D0

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

👉ጥምቀት_ምንድን_ነው?

ተወዳጆች የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልጆች እንኳን ለጌታችንና ለአምላካችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በሰላም አደረሳችሁ እያልን ነገረ ጥምቀቱን እንዲህ መናገር እንጀምራለን

💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐

✅ ጥምቀት በጽርዕ ቋንቋ ኤጲፋኒያ በግእዝ አስተርዮ በአማርኛ መገለጥ ይባላል።

✅ ጥምቀት “አጥመቀ” ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ፍቺውም በገቢር መንከር፣ መድፈቅ፣ መዘፈቅ፣ በተገብሮ መነከር፣ መደፈቅ፣ መዘፈቅ፣ መላ አካልን በውኃ ውስጥ ማስገባት ማለት ነው።

✅ በሌላ አገላለጽ ጥምቀት ማለት በተጸለየበት ወይም በተለየና በከበረ ውኃ (ማየ ገቦ ወይም ማየ ሕይወት) ውስጥ በሥላሴ (በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ) ስም ከራስ ፀጉር እስከ እግር ጥፍር መጥለቅ፣ መዘፈቅ፣ መነከር ማለት ነው። በመሆኑም የምንጠመቅበት ውኃ ተራ ውኃ አይደለም።

✅ጥምቀት ከሰባቱ ምሥጢራተ ቤተክርስቲያን አንዱ ነው።

💎የጥምቀት በዓል ከዘጠኙ የጌታ ዐበይት በዓላት መካከል አንዱ ነው

💎በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዓተ አክብሮት መሠረት በየዓመቱ ከጥር አሥር እስከ አሥራ አንድ ቀን በደማቅ ሥነ ሥርዓት በካህናት፣ በምዕመናንና በሰንበት ት/ቤት ወጣቶች አገልግሎት ይከበራል።

💎 በዓሉ የሚከበረው ጌታ በዕደ ዮሐንስ በማየ ዮርዳኖስ የተጠመቀበት ምሥጢረ ጥምቀትና ሥርዓተ ጥምቀትን የመሠረተበት ዕለት በመሆኑ ነው። ጌታ የተጠመቀው በተወለደ በሠላሳኛው ዓመት ሲሆን ያ ወራት ዮሐንስ መጥምቁ ሕዝቡን እየሰበሰበ የንስሐ ጥምቀት የሚያጠምቅበት ጊዜ ነበር:: 📗ማቴ. 3:1📗

ታሪካዊ የጥምቀት በዓል አከባበር በኢትዮጲያ

💧ታላቁ የከተራ እና የጥምቀት በዓል ሲነሳ ኢትዮጵያውያን ሩቅ ዘመንን ተሻግረን የቅዱሳን ሰማዕት አባቶችን፣ የሊቃውንት አባቶችን አስተምሮት እናዘክራለን።

💧በቅዱስ ላልይበላ ዘመነ መንግሥት በኢትዮጵያ ምድር እየተመላለሱ በብሕትውና እና በስብከተ ወንጌል ያገለግሉ የነበሩት ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በአክሱም፣ በመቐለና በመርጡለ ማርያም እየተዘዋወሩ ባሕረ ጥምቀቱን ባርከዋል።

💧በዐፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት (1260-1275 ዓ.ም) በጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት (1203-1204 ዓ.ም) አሳሳቢነት የተጀመረው ሥርዐተ በዓል ተጠናክሮ እንዲቀጥል በዐዋጅ ትእዛዝ አስተላልፈዋል።

💧ታቦታቱም በሕዝብ ጥበቃና እንክብካቤ ተደርጎላቸው በየጥምቀተ ባሕሩ እንዲያድሩ ወስነዋል።

💧የበዓሉ አከባበር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋና አድማሱ ብሔራዊነትን እየያዘ መጣ።

💧ከዐፄ ገብረ መስቀል ጀምሮ የአደባባይ በዓል የሆነው የጥምቀት በዓል በ15ኛው ክ/ዘመን በደገኛው ኢትዮጵያዊው ንጉሠ ነገሥት ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ (1426-1460 ዓ.ም) አማካኝነት ታቦታቱ ወደ ወንዝ ወርደው ዕለቱን እንዳይመለሱ፣ በዚያ ፈንታ በጥምቀት ዋዜማ ጥር 10 ቀን ከሰዓት በኋላ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ ወርደው እንዲያድሩ፣ አገሩን በኪደተ እግር ይባርኩም ዘንድ በሄዱበት መንገድ እንዳይመለሱ በዐዋጅ ወሰኑ።

💧ይህን ታሪክ በመከተል ዐፄ ናዖድ (1486-1500) ዓ.ም) ማንኛውም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ምእመን ታቦተ ሕጉ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ በሚወርድበት እና ከባሕረ ጥምቀቱ ወደ ቤተ መቅደሱ በሚመለስበት ጊዜ አጅቦ አውርዶ፣ አጅቦ መመለስ እንዳለበት timqet celebration በዐዋጅ አስነግረው ነበር።

💧ሕዝቡም ታቦታተ ሕጉን በሆታና በእልልታ ከቤተ መቅደስ አጅቦ ካወጣ በኋላ በባሕረ ጥምቀት ከትሞ ማደር ጀመረ ።

💧ኢትዮጵያ ዜና ጥምቀተ ክርስቶስን ከሰማችበት ከመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን አንሥቶ በተለይም ከአጤ ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት (6ኛው መ/ክ/ዘ) ወዲህ የጥምቀትን በዓል ዛሬ በሚታየው አኳኋን ስታከበር እንደ ቆየች ይታመናል።

💧በክብረ በዓሉ ከመንበረ ክብራቸው ወጥተው ወደ ባሕረ ጥምቀት የሚወርዱት ታቦታት በካህናቱ ሃሌታ፣ በምእመናኑ እልልታ እና በየአጥቢያ አብያተ ክርስቲያኑ በተቋቋሙ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች መዝሙሮች ታጅበው በተመሳሳይ አኳኋን እንደሚመለሱ ይታወቃል።

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን።

መዝሙረ ዳዊት ፻፶፥፮

💎ጌታችን በተጠመቀ ጊዜ የዮርዳኖስ ወንዝ የላይኛው ሸሽቶ ወደ ላይ ተመልሶ ሽቅብ ፈሷል። የታቹም ወደ ታች ሸሽቷል። የላይኛው ፈሳሽ ተቋርጦ እንደ ክምር ተቆልሎ ቀርቷል።

💎ቅዱስ ዳዊት የተመለከተውም ይህንኑ ነው።

✅ከአዳም ጀምሮ እስከ ክርስቶስ ድረስ በዘር ይወርድ የነበረው ፍዳ መርገም በክርስቶስ ቤዛነት ተቋርጦ፤ የታቹም ፈጽሞ መድረቁ ኃጢአተ አዳም የመጥፋቱ ምሳሌ ነው።

✅እስራኤል ፈለገ ዮርዳኖስን ተሻግረው ወደ ኢያሪኮ መሔዳቸው ምእመናን በጥምቀት ከኃጢአት ቍራኝነት ተላቀው እግራቸውን ወደ ልምላሜ ገነት ወደ ዕረፍት መንግሥተ ሰማያት አቅንተው ለመሔዳቸው ምሳሌ ነው።

✅ኢያሱ የጌታ፣

✅እስራኤል የምእመናን፣

✅ዮርዳኖስ የጥምቀት፣

✅ምድረ ርስት የገነት መንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ነው።

✅ታቦቱን አክብሮ የሚሔደው ካህን የቅዱስ ዮሐንስ፣

✅ታቦቱ የጌታችን፣

✅ባሕረ ጥምቀቱ የዮርዳኖስ ወንዝ፣

✅ታቦታቱን አጅበው የሚሔዱትና በዓሉን የሚያከብሩት ምእመናን ወደ ቅዱስ ዮሐንስ እየመጡ የንስሐ ጥምቀት ሲጠመቁ የነበሩት ሰዎች ምሳሌዎች ናቸው።

✅ታቦታቱ በጥምቀት ዋዜማ ከመንበራቸው ወደ ጥምቀተ ባሕር መውረዳቸውና በዚያ ማደራቸው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ በፈለገ ዮርዳኖስ ከማታው ጀምሮ መውረዱንና ተሰልፎ ተራውን ሲጠብቅ ማደሩን ያጠይቃል።

✅‹‹ጥምቀት የሞቱና የትንሣኤው ምሳሌ ነው።

👉ከኃጥአን ጋር ተቆጥሮ እንዲጠመቅና እንዲሰቀል የተጻፈውን ቃል ንስሐና ጥምቀት የማያስፈልገው ሲሆን ነገር ግን ፍጹም ኃጥእ መስሎ በዮሐንስ እጅ ጥምቀትን ለመፈጸም በማየ ዮርዳኖስ እግር ተጠመቀ።››።

💎ጌታችን የተጠመቀበት ወርኀ ጥር በእስራኤላውያን ዘንድ የዝናብ፣ የበረዶ ወራት ነው። ከወንዝ ዳር ያለ መጠለ

ያ መዋልና ማደር አይቻልም። በመኾኑም ከዮሐንስ ለመጠመቅ የሚሄዱ ሰዎች ሁሉ በዮርዳኖስ ዙሪያ ድንኳናቸውን ተክለው ያርፉ ነበር። በዚህ አንጻር ዛሬም በባሕረ ጥምቀት ዙሪያ ድንኳኖች ዳሶች ይጣላሉ።

በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች በተለይ በአክሱም የንግሥት ሳባ መዋኛን ‹‹ማይ ሹም›› በጎንደር የዐፄ ፋሲል መዋኛን፣ በላስታ የላሊበላ መዋኛን፣ በሸዋ የዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ፍርድ መስጫ አደባባይን፣ አርባ አራት ታቦታት የሚያድሩበትን የሸንኮራ ሜዳን “ራቡቴ ወንዝ” በአዲስ አበባ ደግሞ ጃንሆይ ሜዳን /ጃንሜዳን/ ወዘተ ለአብሕርተ ምጥማቃት እንደ ምሳሌ መጥቀስ ይቻላል። እኒህ ቦታዎች ዛሬም ድረስ ተከብረው ይገኛሉ።

💎እኛ በዚህ ወቅት ታቦት ይዘን፣ ከወንዝ ወርደን፣ ድንኳን ተክለን በማክበራችን ይፈጸማል፡፡


💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐
ምንጭ ፦ ሥርዓተ ተዋህዶ ርትዕት
💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

Watch "ጥምቀት ❤" on YouTube
https://youtube.com/shorts/Szx1FRbkrEk?feature=share

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#በጎል_በጎል

በጎል በጎል ሰብአ ሰገል /4/
በጎል ሰብአ ሰገል ሰገዱለት /4/
ፀሐይ /2/ ፀሐይ ሰረቀ /2/
ፀሐይ ሰረቀ ክርስቶስ ተጠምቀ /4/
#አዝ
አንቺ ዮርዳኖስ ምንኛ ታደልሽ /2/
የእግዚአብሔር መንፈስ ከላይ ወርዶብሽ
የዓለም መድኃኒት ተጠመቀብሽ /2/
#አዝ
ድንግል ማርያም ንፅህት ቅድስት /2/
የጌታዬ እናት ምስጋና ይገባሻል
ከሴቶች ሁሉ አንቺን መርጦሻል /2/
#አዝ
አዲስ ሙሽራ ሲመጣ እያያችሁ/2/
የዮርዳኖስ ወንዞች ስለምን ሸሻችሁ/2/
#አዝ
እናንት ተራሮች እግር ሳይኖራቹ/2/
እንዴት እንደ ጊደር ሽቅብ ዘለላችሁ/2/
#አዝ
ድንግል ማርያም ያስገኘሽው ፍሬ/2/
ሕዝቦቹን ለማዳን ተወለደ ዛሬ
ሕዝቦቹን ለማዳን ተጠመቀ ዛሬ /2/
#አዝ
እልል እልል ደስ ይበለን /2/
ወልድ ተወልዶ ነጻ ወጣን
ዮሐንስ አጥምቆ ድል አገኘን /2/

ዜማው በዚሁ ነው የሚወርደው
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

👉 "የምወደው ልጄ ይህ ነው!"
✍ ጸሐፊ:- ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
🎤 አንባቢ:- ብንያም ብርሃኑ

#ሼር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#አጥምቆ_ዮሐንስ

አጥምቆ ዮሐንስ/2/
ለኢየሱስ አጥምቆ ዮሐንስ/2/

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#ኧኸ_ኀዲጎ

ኧኸ ኀዲጎ ተሰአ
ኧኸ ወተሰዓተ ነገድ/2/ 
ኧኸ ማእከለ ባሕር
ቆመ ማእከለ ባሕር/2/

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​​​✞ እንኳን ለአጋእዝተ ዓለም "ሥላሴ" እና "ቅዱስ ሶል ዼጥሮስ" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ

#ሥሉስ_ቅዱስ

ምሥጢራት በእምነት ለማይኖር: በትሕትናም ለማይቀርብ የሚገለጡ አይደሉም::

+እግዚአብሔር አንድም ነው: ሦስትም ነው:: ጊዜ ሣይሠፈር ዘመንም ሳይቆጠር እግዚአብሔር በስም: በአካል: በግብር ሦስትነቱ: በባሕርይ: በሕልውና: በመለኮትና በሥልጣን አንድነቱ የጸና አምላክ ነው::

+ከዓለም መፈጠር በፊት ስለ ነበረው ነገር የሚያውቅ ራሱ ሥላሴ ብቻ ነው:: ዓለምን ከፈጠረ በሁዋላም ምሥጢረ ሥላሴ (መለኮት) ብለን የምንማረው ትምሕርት እንድንና እንጠቀም ዘንድ እርሱ የገለጠልንን ያህል ብቻ ነው::

+ይኼውም በየጊዜው እርሱ ለወደዳቸውና ደስ ላሰኙት ቅዱሳኑ የገለጠው ምሥጢር ነው:: ከዚህ አልፈን በሥጋዊ አዕምሯችን ጌታን "እንመርምርሕ" ብንለው ግን ፍጻሜአችን ሞት: ማደሪያችንም ገሃነመ እሳት መሆኑ አይቀርም::

+እግዚአብሔር በአንድነቱና ሦስትነቱ ሳለ ይህንን ዓለም ፈጠረ:: እግዚአብሔር ዓለምን ለምን ፈጠረ ቢሉ:- ስሙን ቀድሰን ክብሩን እንድንወርስ ነው:: ከዚህ የተረፈውን ምክንያት ግን ራሱ ያውቃል::

በአንድነቱ ምንታዌ (ሁለትነት): በሦስትነቱ ርባዔ (አራትነት) የሌለበት የዘለዓለም አምላክ: የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ እግዚአብሔር ነው:: አብ: ወልድ: መንፈስ ቅዱስ በስም: በአካል: በግብር ሦስትነት በባሕርይ: በሕልውናና በፈቃድ አንድነት የጸኑ ናቸው:: በዚህ ጊዜ ተገኙ: በዚህ ጊዜ ያልፋሉ አይባሉም:: መጀመሪያም መጨረሻም እነርሱ ናቸውና::

+ርሕሩሐን ናቸውና በእናት ሥርዓት "ቅድስት ሥላሴ" እንላቸዋለን:: የሚጠላቸው (የማያምንባቸውን) አይጠሉም:: የሚወዳቸውን ግን እጽፍ ድርብ ይወዱታል:: በቤቱም መጥተው ያድራሉ::

+ከፍጥረታት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የአብርሃምን ያህል በሥላሴ ዘንድ የተወደደ ፍጡር የለም:: አባታችን ቅዱስ አብርሃም የደግነት ሁሉ አባት ነውና በኬብሮን : በመምሬ ዛፍ ሥር ሥላሴን ተቀብሎ አስተናግዷል::

+አባታችን አብርሃም በ99 ዓመቱ: እናታችን ሣራ በ89 ዓመቷ ሥላሴን በድንኩዋናቸው አስተናገዱ:: አብርሃም እግራቸውን አጠበ:: (ወይ መታደል!) በጀርባውም አዘላቸው:: (ድንቅ አባት!) ምሳቸውንም አቀረበላቸው:: እንደሚበሉ ሆኑለት:: በዚያው ዕለትም የይስሐቅን መወለድ አበሠሩት::

+ሥላሴን ያስተናገደች ድንኩዋን (ሐይመት) የድንግል እመቤታችን ማርያም ምሳሌ ናት:: በድንግል ላይ አብ ለአጽንኦ: መንፈስ ቅዱስ ለአንጽሖ: ወልድ በተለየ አካሉ ለሥጋዌ በእርሷ ላይ አርፈዋል / አድረዋልና::

በዓለ ሥላሴ በዚህ ቀን የሚከበረው ስለ 2 ምክንያቶች ነው:: ቀዳሚው ሕንጻ ሰናዖርን ማፍረሳቸው ሲሆን 2ኛው ደግሞ ቅዳሴ ቤታቸው ነው::

#ሕንጻ_ሰናዖር

ሰናዖር ከሺዎች ዓመታት በፊት በአሁኗ ኢራቅ አካባቢ እንደ ነበረ የሚነገርለት ግዛት ሲሆን ስሙ ለሃገሪቱም: ለንጉሡም በተመሳሳይ ያገለግል ነበር:: ከናምሩድ ክፋት በሁዋላ ሰናዖርና ወገኖቹ ከሰይጣን ተወዳጁ::

+ከጥፋት ውሃ (ከኖኅ ዕረፍት) በሁዋላ በሥፍራው በአንድነት ይኖሩ ነበርና እርስ በርሳቸው "ኑ ሳንበተን ስማችን የሚጠራበትን ሕንጻ እንሥራ:: በዚያውም አባቶቻችን በውሃ ያጠፋ እግዚአብሔርን እንውጋው" ተባባሉ::

+ቀጥለውም ሰማይ ጠቀስ ፎቅን ገነቡ:: ከሕንጻው መርዘም የተነሳ በጸሐይ አብስለው በልተዋል ይባላል:: ቀጥለውም ጦር እያነሱ ፈጣሪን ሊወጉ ወርውረዋል::

+መቼም የእነዚህን ሰዎች ክፋትና ቂልነት ስንሰማ ይገርመን ይሆናል:: ግንኮ ዛሬ ሰለጠንኩ በሚለው ዓለም እየተሠራ ያለው ከዚህ የከፋ ነው:: ቸርነቱ ቢጠብቀን እንጂ እንደ ክፋታችንስ ጠፊ ነበርን::

+ርሕሩሐን ሥላሴ ግን የሰናዖር ሰዎች የሠሩትን አይተው ማጥፋት ሲችሉ አላደረጉትም:: የባሪያቸውን የኖኅን ቃል ኪዳን አስበዋልና:: ይልቁኑ "ንዑ ንረድ ወንክአው ነገሮሙ ለከለዳውያን-ቁዋንቁዋቸው እንደባልቀው" አሉ እንጂ::

+ከለዳውያን ልሳናቸው ተደበላልቆ 71 ቁዋንቁዎች ተፈጠሩ:: እነርሱም ስምምነት አጥተው ተበተኑ:: ሥላሴም ያን ሕንጻ በነፋስ ትቢያ እንዲሆን በተኑት:: ስለዚህም እስከ ዛሬ ሥፍራው "ባቢሎን (ዝሩት)" ሲባል ይኖራል::

#ቅዳሴ_ቤት

ልክ የዛሬ 324 ዓመት: አድያም ሰገድ ኢያሱ በኢትዮዽያ በነገሡ በ10ኛው ዓመት: (በ1684 ዓ/ም) በጐንደር ከተማ ንግሥተ አድባራት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ተሰርታ ተጠናቃለች::

+ጥር 7 ቀንም ሊቁ ክፍለ ዮሐንስን ጨምሮ በርካታ ምዕመናን: ሠራዊት: መሣፍንትና ሊቃውንት ባሉበት ቅዳሴ ቤታቸው ተከብሯል:: በዕለቱም ታላቅ ሐሴት ተደርጉዋል:: ኢያሱ አድያም ሰገድ ኃያል: ደግ: ጥበበኛ: አስተዋይ: መናኝ ንጉሥ ነውና::

+ቤተ ሥላሴን አስጊጿታልና ከዚህ ቀን ጀምሮ ጥር ሥላሴ በድምቀት የሚከበር ሆኗል:: ነገር ግን በተሠራች በ16 ዓመቷ ደጉ ኢያሱ ከተገደለ በሁዋላ ቤተ ክርስቲያኑ በአደጋ ፈርሷል:: ዛሬ የምናየው በ1708 ዓ/ም በልጁ በአፄ ዳዊት ሣልሳዊ የታነጸውን ነው::

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የተለያዩ ቦታዎች የመንግስት የፀጥታ ሐይሎች ያደርጉ የነበረውን ጥበቃ ባልታወቀ ሁኔታ አቁመዋል!

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

"የኖላዊነት ኃላፊነታችሁን የዘነጋችሁ ወንድሞቻችን እና ሌሎችም ሰዓቱ ከማለቁ አስቀድሞ ወደ ልባችሁ በመመለስ ወደ ቀድሞው ማንነታችሁ ተመለሱ" ሲሉ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ አሳሰቡ።

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል የበላይ ጠበቂ በትናንትናው ዕለት በተፈፀመው ኢ-ቀኖናዊ "ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳትን" አስመልክቶ በይፋዊ የፌስቡክ ገጻቸው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

እውነት እውነት እላችኋለሁ ወደ በጎች በረት በበሩ የማይገባ በሌላ መንገድ ግን የሚወጣ እርሱ ሌባ ወንበዴም ነው (ዮሐ.10፥1)በሚል የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል መልዕክታቸውን የጀመሩት ብፁዕነታቸው በትናንትናው ዕለት በወሊሶ በተፈጸአው ኢ-ቀኖናዊ "ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት" ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በእጅጉ አዝናለች ብለዋል።

መከራና ፈተና ከቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ተለይተው የማያውቁ ቢሆንም ካለን መከራንና ችግርን የማለፍ ልምድ በመማር ይህንን አስቸጋሪ እና ፈታኝ ወቅት በጥበብ እና ብስለት በተመላበት አኳኋን ልናሳልፈው ይገባል ሲሉ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ
አሳስበዋል።

ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ ብዙ መናገር ቢቻልም ያለንበት ወቅት ይህንን ለመናገር ጊዜው ባለመሆኑ ምዕመናን ልጆቻችን ሁሉ ለቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ አፈጻጸም ራሳችሁን ዝግጁ በማድረግ ፤ መንፈስ ቅዱስ እና ቅዱስ ሲኖዶስ የሚወስኑትን ውሳኔ በትዕግስት እንድትጠብቁ እናሳስባለን ብለዋል።

ብፁዕነታቸው በዚህ ስህተት ውስጥ የገባችሁ የኖላዊነት ኃላፊነታችሁን የዘነጋችሁ ወንድሞቻችን እና ሌሎችም ሰዓቱ ከማለቁ አስቀድሞ ወደ ልባችሁ ተመልሳችሁ ወደ ቀድሞው ማንነታችሁ ትመለሱ ዘንድ ጸሎታችን መሆኑን እንገልጻለን ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል ሲል የዘገበው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ነው።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት በአዲስ አበባ የሚገኘውን የ"አባ" ሳዊሮስ ፣ የ"አባ" ኤዎስጣቴዎስን እና የ"አባ" ዜና ማርቆስን ማረፊያ ቤት አሸገ፡፡

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በአዲስ አበባ የሚገኘውን የ"አባ" ሳዊሮስ፣ የ"አባ" ኤዎስጣቴዎስን እና የ"አባ" ዜና ማርቆስን ማረፊያ ቤት መታሸጉን ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል በፌስቡክ ገጽ አስነብቧል።

በትናንትናው ዕለት 3ቱ አባቶች ሕገ ቤተ ክርስቲያንን እና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ለመናድ እና ሲኖዶሳዊ አንድነትን ለመከፋፈል በማቀድ 26 መነኮሳትን ሾመናል በማለት መግለጫ መስጠታቸው ይታወሳል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ትላንት በተመለከትነው አስነዋሪ እና ሥርዐተቢስነት የተሞላበት ጉባኤ /ጉባኤ ከለባት/ የመንግስት እጅ እንዳለበት ግልጽ ነው። በቅርቡ በሌሎች እምነቶች የሰራውን የመከፋፈል ሴራ በኦርቶዶክስ ላይ ሊሳካ እንደማይችል ማወቅ ይኖርበታል።

ይህ ንግግር ዝግጅቱ በሃይማኖታዊ የመንግሥት ኔትዎረክ ውስጥ መረጃ እንደነበረ ይጠቁማል። ከሳምንት በፊት ቤተክርስቲያንን ለማዘናጋት ይቅርታ እንጠይቃለን ሲሉ የነበሩና አንዲጠይቁ የላኳቸው አካላት ለዚህ ሤራ እየተዘጋጁ ነበር ማለት ነው። የማስመሰል ጭምብል ወልቋል።

ጉዳዩ ከአሁን በኋላ የእውነተኛ ክርስቲያኖችና አባቶች፣ አንዲሁም ዋናው የአግዚአብሔር ነው። ቁማርተኞቹ በእምነትም በኩል እንዲህ ያሉ ጎበዝ ተጫዋቾች ናቸው።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በጉባኤ ከለባት በህገወጡ ቡድን ከተሾሙት የስልጣን ጥመኞች ዝርዝር መካከል 👇👇የሚገኙበት

1. አባ ተክለ ሃይማኖት ።።።።።።። የቀድሞ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ

2. አባ ገብረ እግዚአብሔር ።።።።።። የአየር ጤና ኪዳነ ምሕረት አስተዳዳሪ

3. አባ ሽኖዳ ።።።።።።።።። አለም ገና ኢየሱስ አስተዳዳሪ

4. አባ ወልደ ጊዮርጊስ ።።።።።።። ወለቴ ዮሐንስ አስተዳዳሪ

5. አባ ገብረ ኢየሱስ ።።።።።። አለም ገና ሚካኤል አስተዳዳሪ

6. አባ ገብረማርያም ነጋሳ ።።።።። የኦሮምያ ቤተ ክህነት መስራች

7. አባ ጳውሎስ ከበደ ።።።።። የሐረር ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ የነበረና በተሐድሶነት የተባረረ

8. አባ ጸጋ ዘአብ አዱኛ ።።።።።።። የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል መጽሐፍ መምህር

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መግለጫ ተሰጠ ።

መግለጫውን ለኢኦተቤ ቴቪ (EOTC TV) የሠጡት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፖትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት; ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ : በመንበረ ፓትርያርክ የተገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ናቸው።

ቅዱስነታቸው ዛሬ ማለዳ በተሰማው ሕገ ወጥ "ሢመተ ጳጳሳት" ጉዳይ በሰጡት መግለጫ ጉዳዩ ከቅዱስ ሲኖዶስ እውቅና ውጪ በሕገወጥነት የተከናወነ መሆኑን በመግለጽ :-
1. በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ያሉ ሊቃነ ጳጳሳት በአስቸኳይ ወደ መንበረ ፓትርያርክ እንዲመጡ ጥሪ ቀርቧል።
2. መንግሥት ክስተቱ በሀገር ላይ ጭምር የሚያስከትለውን ጉዳት ተመልክቶ በጉዳዩ ላይ ሕጋዊ ሓላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
3. ምዕመናን ቤተክርስቲያንን ከመቸውም ጊዜ በላይ በንቃት በሀሣብና በጸሎት እንዲጠብቁ ቅዱስነታቸው ጥሪ አቅርበዋል።

ምንጭ: EOTC TV

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እጅግ አሳዛኝ ዜና!

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የምስካየኅዙናን መድኃኒአለም ገዳም የበላይ ጠባቂ በዛሬው ዕለት እራሳቸውን ፓትሪያርክ በማድረግ 25 ኤጲስ ቆጶሳትን ሾመዋል!!!

በዛሬው ዕለት በወሊሶ መድኃኒአለም ቤተክርስቲያን ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ እራሳቸውን ፓትሪያርክ በማድረግ ለስልጣን ጥማት ያደረባቸውን 25 ኤጲስ ቆጶሳት አድርገው ሾመዋል።

ከአንድ የቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ የማይጠበቅ እና ህገ ቤተክርስቲያንን የሚፃረር ድርጊት ይፈፅማሉ ብለን የማንጠብቃቸው አቡነ ሳዊሮስ ይሄንን አድርገዋል።

ቤተክርስቲያኒቷ በራሷ ስርዓት እና ህግ የምትገዛ ሆኖም ሲኖዶሳዊት የሆነችውን ይቺ ሀገር የሆነችውን ቤተክርስቲያን ብትንትኗን ለማውጣት ይሄን ያህል መንገድ መራመዳቸው እጅግ የሚያሳዝን ተግባር ነው።

በአስቸኳይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ለምመናኗ መፍትሔ ሊሰጥ እንደሚገባ በታላቅ ትህትና እንጠይቃለን ።

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​#ቃና_ዘገሊላ

በዛሬው ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከቅድስት ድንግል ማርያምና ከሐዋርያቱ ጋር የገሊላ ክፍል በሆነችው በቃና በሰርግ ቤት ተገኝቶ ውሃውን ወይን ጠጅ ያደረገበት ነው። ሰርግ ደግሶ የነበረው ዶኪማስ አዘጋጅቶት የነበረው ወይን ጠጅ አልቆ በተጨነቀ ጊዜ ችግሩን ቀርቦ ሳይነግራት ማለቁን አውቃ ልጄ ሆይ ወይን ጠጅ እኮ አልቆባቸዋል በማለት ተናግራ ውሃው ወደ ወይን ጠጅ እንዲለወጥ የማማለድ ተግባር የፈጸመችበት ዕለት ነው።

አምላካችን ጋብቻ ክቡር መሆኑን ዓለም እንዲረዳ ያደረገበት፣ ሰዎች ያዘጋጁት ነገር ተንጠፍጥፎ አልቆ በተጨነቁ ጊዜ እመቤታችን ለልጇ አሳስባ ጎደሏቸው እንዲሞላ ፣ጭንቀታቸው እንዲወገድ የምታደርግበት በዓል ነው።

ጥንቱ ዕለቱ የካቲት 23 ቀን ቢሆንም ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን የውሃን በዓል ከውሃ በዓል ጋር ማክበር ይገባል ብለው የሚጠጡት አልቆባቸው ተጨንቀው የነበሩበት ቃና ዘገሊላ የውሃ በዓል በመሆኑ ከውሃ በዓል ከሆነውና የእዳ ደብዳቤያችን ከተደመሰሰበት ከጥምቀት ጋር እንዲከበር በማድረጋቸው በዛሬው ዕለት እናከብረዋለን።

ዛሬ የዶኪማስ ጭንቀት ብቻ ሳይሆን በጋብቻ ምክንያት የሚከሠት የክርስቲያኖች ሁሉ ጭንቀት የተቃለልበት ዕለት ነው። እመቤታችን ዶኪማስ ሳይለምናት ጭንቀቱን እንዳቃለለችለት ለልጅሽ አሳስቢልን ብለን ብንማጸናት የማይፈጸምልን ነገር፣ የማይወገድልን ጭንቀት አለመሆኑን የተረዳበት ዕለት ነው። በዓሉን ማክበር የሚገባንም ይህን እያሰብን ነው። አምላካችን ከበዓሉ በረከት ይክፈለን።

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ውሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት እንኳን አደረሳችሁ እያለህ

                      ማስታወቂያ
ለጥምቀት በዓል ልብስ አዘጋጅተው ሊሆን ይችላል። የሰ/ት/ቤታችን የጥምቀት ቲሸርት ግን የግድ ሊኖሮት ይገባል ምክንያቱም

1ኛ የሰ/ት/ቤቱን ዘርፈ ብዙ የሆነውን አገልግሎት ይደግፋሉ
2ኛ የደብራችንን ጥምቀተ ባህር ይደግፋሉ
3ኛ ቲሸርቶቻችን ለጥምቀት በዓል ብቻ ሣይሆን በተለያዩ በዓላት ወቅት የሚለበሱ ናቸው። ከፍተኛ በሆነ ጥራት ስለምናትማቸው ለቲሸርቶቻችን ጥራት ምስክር እናንተ ናችሁ።
4ኛ በረከት ለእርሶም ለቤተሰቦም ይዘው ይገባሉ  ደቤትዎ።

ስለሆነም በከፍተኛ ጥራት ጥቂት ቲሸርቶችን አዘጋጅተናል።

ለበለጠ መረጃ
09 27 43 42 37
09 93 51 29 98
09 12 33 01 26
09 04 15 82 43
09 22 58 05 95

እንዲሁም የሰ/ት/ቤቱ መዝሙር ቤት ቢመጡ በሚፈልጉት ሳይዝ ያገኛሉ።
ዋጋው 399 ብር ብቻ

ቦታ: በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ውሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ሰላም ውድ የዝማሬ ዳዊት ተከታታዮች እንደምን ቆያችሁ? እግዚአብሔር ይመስገን

በዓለ ጥምቀትን በያላችሁበት እንዴት ልትቀበሉት አሰባችሁ? እስቲ በየሰፈራችሁ የሰራችሁትን ወይም የተሰራውን የበረከት ሥራ ከ1 ደቂቃ ባልበለጠ ቪድዮ አጋሩን! ለመላው ዓለም እናዳርሰዋለን።

ከምትሉኩልን መሐከል በጥሩ አቀራረጽ የተላኩትን መርጠን በTelegram, YouTube እንዲሁም በTiktok እናጥለቀልቀዋለን። ከምትልኩልን ቪድዮ ጋር የሰፈሩን ስም አብራችሁ መላክ እንዳይረሳ።

ለመላክ ይህን ይጠቀሙ! እንደደረሰን Seen ብለን በመላክ እናሳውቃለን።
@zmaredawit_messengerbot

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🎬  🛑 ለምን ኢትዮጵያ ብቻ በኦርቶዶክስ ላይ ተዋህዶ ተብሎ ተቀጠለ?
👤 ዝማሬ ዳዊት ቲዩብ

⚠️ መልሱን ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!
https://youtu.be/5ObRY_PMmis
https://youtu.be/5ObRY_PMmis

እናንተም ያላችሁን ጥያቄዎች መጠየቅ ትችላላችሁ!

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#በዛሬው_ጥምቀቱ

በዛሬው ጥምቀቱ እሰይ እሰይ 
ተነግሮ አዋጅ እሰይ እሰይ 
ነጻነት አገኘን እሰይ እሰይ 
በእግዚአብሔር አብ ልጅ እሰይ እሰይ 
እሰይ እሰይ ተወለደ
እሰይ እሰይ ተተመቀ/2/ 
ከሰማየ ሰማይ ወረደ/2/ 
ከድንግል ማርያም ተወለደ
አዝ------------
አብም መሰከረ እሰይ እሰይ 
ቃሉን አላበየም እሰይ እሰይ 
የምወደው ልጄ እሰይ እሰይ 
ይሄ ነው እያለ እሰይ እሰይ
አዝ------------ 
ጌታ በዮሐንስ እሰይ እሰይ 
ሊጠመቅ ሲል ገና እሰይ እሰይ 
ወደ ኋላ ሸሸ እሰይ እሰይ 
ዮርዳኖስ ፈራና እሰይ እሰይ 
አዝ------------ 
ተራሮች ዘለሉ እሰይ እሰይ 
እንደ ጊደር ሁሉ እሰይ እሰይ 
እፁብ ነው ድንቅ ነው እሰይ እሰይ 
ምን ይገርም እያሉ እሰይ እሰይ 
አዝ------------ 
ውኃን ወይን አረገ እሰይ እሰይ 
በተጠራበት ቤት እሰይ እሰይ 
የብርሃናት ጌታ እሰይ እሰይ 
የዓለም መድኃኒት እሰይ እሰይ 

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#ልዑል_እግዚአብሔር

ልዑል እግዚአብሔር /2/
ምስጋና ይገባሃል/2/ 
ለጥምቀት በዓል/2/
በሰላም በጤና አደረስከን/2/

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

"ይትባረክ እግዚአብሔር አምላከ አበዊነ ስቡሕኒ ውእቱ ወልዑልኒ ውእቱ ለዓለም"

"እግዚአብሔርን በአፌ እጅግ አመሰነዋለሁ በብዙዎችም መካከል አከብረዋለሁ"

ሥላሴ ትትረመም

ሥላሴ ትትረመም ወትትነከር
ሥላሴ ትትረመም ወትትነከር (፪)

ይገባል ምስጋና ይገባል ውዳሴ
ሁሉን ለፈጠረ ለቅድስት ሥላሴ
ከዘመናት በፊት ቀድሞ የነበረ
ፍጥረትን በሙሉ ለክብሩ ፈጠረ
አዝ
ልበል ሃሌ ሉያ ኪሩቤልን ልምሰል
በእግረ ምስጋና ያሬድን ልከተል
ላቅርብ ምስጋናውን ዘምስለ ሱራፌል
ውዳሴ ምስጋና ነውና ለልዑል
አዝ
በስም ሦስት ሲሆን እንዲሁም በአካል
በግብርም ሦስት ነው ያለመቀላቀል
ፍጥረትን በመፍጠር በአምላክነት
በባሕሪይ እና ደግሞም በመንግሥት
አንድ አምላክ ነው እንጂ አይባልም ሦስት
አዝ
በኪሩቤል ጀርባ ዙፋኑን ዘርግቶ
ክብሩን ጌትነቱን ከፍጥረት ለይቶ
ይኖራል ዘለዓለም በመንግሥቱ ጸንቶ(፪)
አዝ
ይመስክር ዮርዳኖስ ይናገር ታቦር
የአምላክ ጌትነት የሥላሴን ክብር
ይኸው በዮርዳኖስ ወልድ ተገለጠ  
መንፈስ ቅዱስ ታየ አብም ቃሉን ሰጠ

ዘማሪ ዲያቆን ፍሬዘር ደሳለኝ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​​​#እንኳን_አደረሳችሁ_ጥር_6_ግዝረት

ግዝረት ከጌታችን ከመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘጠኙ ንዑሳን በዓላት አንዱ ነው፡፡ እነዚህ ንዑሳን በዓላት የሚባሉትም ስብከት፣ ብርሃን፣ ኖላዊ፣ ግዝረት፣ ቃና ዘገሊላ፣ ልደተ ስምዖን፣ ደብረ ዘይት፣ የመጋቢት መስቀልና መስቀል ናቸው፡፡ ነቢያት ይወርዳል፤ ይወለዳል ብለው በትንቢት ይጠባበቁት የነበረው መሲሕ የዓለም ብርሃን፣ የነፍሳት ጠባቂ መሆኑን አምነን የምናከብራቸው ስብከት፣ ብርሃንና ኖላዊ ይባላሉ፡፡

ከእናቱና ከደቀመዛሙርቱ ጋር በሰርግ ቤት የተገኙበት ቃና ዘገሊላ፣ በአርባ ቀኑ ወደ ቤተ መቅደስ የገባበትና አረጋዊ ስምዖንን የሰላሳ ዓመት ጎልማሳ የሆነበት “ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ ዐይኖቼ ማዳንህን አይተዋልና” በማለት የተናገረበት ልደተ ስምዖን ከንዑሳን በዓላት ይመደባሉ፡፡ የዚህ ጽሑፍ ትኩረት ግዝረት በመሆኑ ሀተታዬን ወደ እሱ እመልሳለሁ፡፡

ፍቅር ወልድን ከዙፋኑ ስቦት ወርዶ ሥጋ ማርያምን ተዋሕዶ፣ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ማሕፀኗን ዓለም አድርጎ ከቆየ በኋላ ታኅሣሥ ሃያ ዘጠኝ በዘመነ ማቴዎስ ተወለደ፡፡ በተወለደ በስምንተኛ ቀኑ ሥርዓተ ኦሪትን ሊፈጽም ተገረዘ፡፡ ግዝረትን በስምንተኛው ቀን መፈጸሙ፣ በተወለደ በአርባ ቀኑ ወደ ቤተ መቅደስ መሔዱ ሕገ ኦሪትን ሊያጸና፣ ሊፈጽም፣ ምሳሌውን በአማናዊው ሊተካ እንጂ ኦሪትን ሊሽር ላለመምጣቱ እማኝ ምስክር ነው፡፡ የተሻረ ነገር መታሰቢያ የለውም የተፈጸመ፣ በምሳሌና በትዕምርታዊነት የተወከለ ግን ጥንተ ታሪኩን፣ ትንቢቱን ጠይቀን ምሳሌውን ከትርጓሜ መጻሕፍት እንረዳለን፡፡

ግዝረት አይሁድ የአብርሃም ልጅ መሆናቸውን ማረጋገጫ ማኅተም ነው፡፡ በሕግና በሥርዐት የሚመሩ መሆናቸውን አንድ አምላክ ማመናቸውን የገለጡበት ነው፡፡ አይሁድ በግዝረት የአብርሃም ልጅነታቸውን እንዳረጋገጡ፣ ክርስቲያኖችም በጥምቀት የሥላሴ( ልጅነታቸውን ያረጋግጣሉ፡፡ ይህም የሚሆነው ግዝረት የጥምቀት ምሳሌ መሆኑን ያስረዳል፡፡ በሐዲስ ኪዳን ጥምቀት እንጂ መገረዝ፣ አለመገረዝ አይጠቅምም፡፡ በሐዲስ ኪዳን ግዝረት በፍቃድ እንጂ እንደ አይሁድ እኛም የአብርሃም ልጆች እንድንባል የምንገረዝ አይደለም፡፡

ለእኛ ለክርስቲያኖች ከሥላሴ በመንፈስ ቅዱስ መወለድ እንጂ መገረዝ የአብርሃም ልጆች አያሰኘንም፡፡ አለመገረዝ እንደማይጠቅም ቢያውቅም ጌታችን መገረዝ ያስፈለገው ሕገ ኦሪትን ለመፈጸም ሲሆን በእኔ ግን ምስጢረ ጥምቀትን ፈጽሜ አድናችኋለሁ ሲለን( ነው፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ የማይጠቅምና ለነገረ ድኅነት የማያበቃ ነገር ቢያጋጥመን እንኳ በጥበብና በማስተዋል እንድናደርገው ሲያስተምረን ነው፡፡ ሥርዐተ ኦሪታችንን ስላፈረሰብን ለሞት አበቃነው ብለው ምክንያት እንዳያገኙና ይህንን ስበብ አድርገው ከነገረ ድኅነት ተለይተው እንዳይቀሩ የሚያደርጉትን በማድረግ፣ የሚወዱትን በመውደድና አብሯቸው የሥርዐታቸው ተካፋይ በመሆን በፍቅር ስቦ ወደ አማናዊው ድኅነት፣ ወደ ጥምቀትና የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ወደማመን መልሷቸዋል፡፡

የመምህሩን አሰረፍኖት የሚከተለው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በደርቤን በሚያስተምርበት ወቅት ጢሞቴዎስ( ሲከተለው መገረዝ አለመገረዝ ጥቅምም ጉዳትም እንደሌለው እያወቀ የገዘረው( በዙሪያው ብዙ አይሁድ ስለነበሩ እነርሱን ላለማስከፋትና ላለማስደንበር መሆኑን ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ “.. የኦሪት ሕግ ለማዳን ብቁ አለመሆኗን እየደጋገመ በድፍረት ይሰብክ የነበረው መምህረ አሕዛብ ቅዱስ ጳውሎስ እንኳ አይሁድን( ላለማስደንበር ሲል ሥርዐተ ኦሪትን ይፈጽም ነበር፡፡” /1978፣ 29/ በማለት ገልጸዋል፡፡

ግዝረት ለእስራኤል ከአብርሃም ለመወለዳቸው ምልክት ብቻ ሳይሆን የአብርሃምን ሃይማኖት ለመያዛቸውም መታወቂያ ነበረች፡፡ ጌታችንም ምንም እንኳ የባሕርይ አምላክ ቢሆን በሥጋ( የአብርሃም ልጅ ነውና የአብርሃም ልጅነቱን የአብርሃምን ሃይማኖት ማጽናቱን ለማስረገጥ ግዝረትን ፈጸመ፡፡

አንድም በግዝረት ደም ይፈስሳለና አብርሃም በዘጠና ዘጠኝ ዓመቱ በመገረዝና ደሙን በማፍሰስ አበ ሰማዕታት ተብሏልና ግዝረት የሰማዕትነት ምሳሌም ነው፡፡

ጥር ስድስት በሚነበበው ስንክሳር እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አረጋዊ ዮሴፍን ሕፃኑን የሚገርዝ ባለሙያ ፈልጎ እንዲያመጣ እንደነገረችው፣ አረጋዊውም ባለሙያውን ፈልጎ እንዳመጣ ይናገራል፡፡ ባለሙያውም ሕፃንን በደምብ ያዙልኝ ብሎ ለመግረዝ ሲሰናዳ ባለሙያ ሆይ ደሜ ሳይፈስ መግረዝ ትችላለህን ብሎ እንደጠየቀው፣ ከስቅለቱ በፊት ደሙ እንደማይፈስ እንዳስተማረው፣ በዚህም ምክንያት ለመግረዝ የመጣው ባለሙያ፣ አምላክ ወልደ አምላክ መሆኑን አምኖ እንደሰገደለት ለመግረዣ ያዘጋጀው ምላጭም እሳት ላይ እንደተጣደ ቅቤ መቅለጡን ይተርካል፡፡

በመቀጠልም ክርስቶስ ዘር ምክንያት ሳይሆነው እንደተፀነሰ፣ ማኅተመ ድንግልናዋን ሳይለውጥ እንደተወለደ እንደ ነቢዩ ሕዝቅኤል “ሳይከፈት ገብቶ ሳይከፍት እንደወጣ” ስለት ምክንያት ሳይሆነው፣ በግዝረት ምክንያት ደም ሳይፈስ በተአምራት ተገረዘ፡፡

በአጠቃላይ ግዝረት በኦሪት የአብርሃም ልጅነትን፣ የአብርሃምን ሃይማኖት መያዝን ማረጋጋጫ ማኅተም ሲሆን በሐዲስ ኪዳን በጥምቀት ተተክቷል፡፡ ለአማናዊው ግዝረት /ለጥምቀት/ ምሳሌ በመሆኑም በሥራ የአብርሃም ልጅነትን፣ በእምነት የሥላሴ ልጅነትን አግኝተንበታል፡፡ ወርደህ ተወልደህ፣ በነፍስ በሥጋ፣ ከተቆራኘን ባለጋራ አድነን ብለን የተጣራነው ተሰመቶ፣ ሥርዓተ ኦሪትን ፈጽሞ ወደ ሥርዓተ ሐዲስ የሚያሸጋግረን መሆኑን ያመንበት፣ በጥምቀቱ ቦታ በዮርዳኖስ የተቀበረው የባርነታችን ደብደቤ የሚቀደድ መሆኑን በምሳሌ ያወቅንበት ግዝረት ነው፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…
Подписаться на канал