ortodoxmezmur | Неотсортированное

Telegram-канал ortodoxmezmur - ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

134932

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . ዝማሬ ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Подписаться на канал

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የምሥጢረ ሥላሴ ትምህርትን አሁን እንልካለን።


እንደ ክለሳ እንዲሆን። በደንብ አዳምጡት ከእዛም እንደተረዳችሁት ለማወቅ ጥያቄ አዘጋጅተናል እንጠይቃለን።👇👇👇👇

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ሰበር ዜና

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕገወጡ ቡድን በፈጠረው ቀኖናዊ ጥሰት እና ህገ ወጥ እንቅስቃሴ ከሁለት ቀናት በፊት ሰላም መቋጨቱ መታወጁ ይታወሳል። አሁን ግን የምንሰማቸው  ነገሮች ነገሮች  ሁሉ እንደገና ጆሮን ጭው የሚያደርጉ ቤተ ክርስቲያንን የሚከፋፍል አባቶችን ከልጆች ልጆችን ከአባቶች የሚያሻክሩ ነገሮችን ሆነዋል።

በዛሬው እለት ወደ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ "አዲሱ ሲኖዶስ" በሚል አዲስ ስም እስካሁን ከሚጠቀሙበትም ለየት ባለ ስም የተሰጠ መግለጫ በሚል በሰጡት ባስተላለፉት

ሁሉም በአንድነት ጵጵስናው የሚመለከታቸውም የማይመለከታቸውም የኤጲስ ቆጶስነቱ ደረጃም በስምምነቱም በጋራ የጠፋ ወይም የተሻረ የተደመሰሰ መሆኑን እያወቁም የቅድስናውን ልብስ በመልበስና ሌሎችም የስምምነቱ አካል ሆነው ስምምነቱን ያነበቡት ሳይቀሩ በአንድ ላይ ስምምነቱን ጥሰውታል ቀኖናውን እንደገና ደግመው ጥሰውታል።

ሹመታቸው ሕጋዊ እንደሆነና በምንም ይሁን በምን የማይሻር መሆኑንም መልእክት አስተላልፈዋል።ይህ ከዕለት ወደ ዕለት የሚታይ የሚሰማ ከንቱ ክስ ሆኗል። ከሃይማኖታዊ ይልቅ ፖለቲካዊ ይዘትን ተጎናጽፏል። በሃይማኖታዊ መንገድ በሰላምና በፍቅር በክርስቶስ ደም የተመሠረተችውን ቤተ ክርስቲያን ከመጠበቅ በክርስቶስ ደም የተዋጁትን ምእመናን ከማስተማር ይልቅ በኃይልና በጉልበት ሁሉንም በነገረ ሰሪነት ግጭት በመፍጠር ሁሉንም ለመቆጣጠር ከዕለት ወደ ዕለት ደፋ ቀና ሲሉ ታይተዋል።

ወደ ተዋህዶ ማንም ቢመጣ ተጠቃሚው ራሱ ግለሰቡ ነው ከሄደም ተጎጂው ራሱ ነው!!
ስለዚህ አይናችን ወደ ቤተክርስቲያን ጆሯችን ወደ ቅዱስ ሲኖዶሳችን እናድርግ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ

የዐቢይ ጾምን ምክንያት በማድረግ ያስተላለፉት መልእክት!

• በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናንና ምእመናት እንዲሁም ኢትዮጵውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ!
እንደ ስሑትና ደካማ ሰብአዊ ባሕርያችን ሳይሆን እንደ አባታዊ ቸርነቱ ሁል ጊዜ በምሕረቱ የሚጐበኘን አምላካችን እግዚአብሔር እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዐቢይ ጾም አደረሰን፤ አደረሳችሁ!

• “ንጹም ጾመ፣ ወናፍቅር ቢጸነ፣ እስመ ከማሁ አዘዘነ፤ ጾምን እንጹም፤ ባልንጀራችንንም እንውደድ፣ እንዲህ አዞናልና” (ቅዱስ ያሬድ)

እግዚአብሔር በዚህ ዓለም ስንኖር እንድናደርገው ያዘዘን ዐቢይ ነገር ቢኖር ፍቅር ነው፡፡ እግዚአብሔር ፍጥረታትን ፈጥሮ እየመገበ የሚገኘው በፍቅር ነው፡፡ እኛንም ከፍዳ ኃጢአት ያዳነን በፍቅር ነው፤ ሕይወታችንና ንብረታችን ተጠብቆ የሚኖረው ፍቅር ሲኖር ነው፡፡

ግላዊና ማኅበራዊ ኑሮአችን እንዲሁም ሃይማኖታዊ አምልኮአችንና የተግባር እንቅስቃሴአችን በሙሉ ውጤታማ ሊሆን የሚችለው ፍቅር ሲኖር ነው፡፡

በፍቅር ውስጥ በረከት እንጂ ጉድለት የለም፤ በፍቅር ውስጥ ጤና እንጂ በሽታ የለም፤ በፍቅር ውስጥ ጽድቅ እንጂ ኃጢአት የለም፤ በፍቅር ውስጥ እግዚአብሔር እንጂ ዲያብሎስ የለም፡፡ ይህም በመሆኑ ቅዱስ መጸሐፍ ፍቅርን ‹‹የሁሉም ነገር ማሰሪያ ነች›› በማለት ይገልጻታል፡፡
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ከሁሉም የምትበልጠው ታላቋ ትእዛዝ ‹‹ፍቅር›› እንደሆነች ከመግለጹም በላይ ኦሪትና ነቢያት ሁሉ በእርሷ እንደሚጠቃለሉ አስተምሮናል፡፡

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​በዝማሬ ዳዊት Tube የተላለፉ ትምህርቶች

1⃣ ኦርቶዶክስ እና የዓለም እምነቶች
https://youtu.be/HXh1IUuBOrE
2⃣ እግዚአብሔርን እንዴት መውደድ እንዳለብን
https://youtu.be/Asx80GdsDDE
3⃣ 666 እና የውጭ ዘፋኞች
https://youtu.be/3iFggkALrws
4⃣ ዘፈን እንዴት ተፈጠረ? ማንስ አስተማረን?
https://youtu.be/1P421kYHutU
5⃣ ስለ ቶ መስቀል ክፍል 1
https://youtu.be/qevNJ5hYQ90
6⃣ ስለ ቶ መስቀል ክፍል 2
https://youtu.be/3H0FkrKbg9A
7⃣ ስለ ቶ መስቀል የመጨረሻው ክፍል
https://youtu.be/2QB2Ra7FHf8
8⃣ ሴጋ የፈጸመ የተክሊል ጋብቻ ይገባዋልን?
https://youtu.be/hnt5Y1F4TDY
9⃣ በጸሎት መሀል ወሬ ማውራት
https://youtu.be/2VsM6cVwgcU
1⃣0⃣ ቅዠት ምንድን ነው?
https://youtu.be/m6eD1pzyIWM
1⃣1⃣ የምግብ ሰዓት ጸሎት
https://youtu.be/pjBReIJQ-Q4
1⃣2⃣ የምእመናን አለባበስ ምን ይመስላል
https://youtu.be/fKuDfxWKUyY
1⃣3⃣ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እና ፕሮቴስታንት ክፍል አንድ
https://youtu.be/HBb3vZBZqzs
1⃣4⃣ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እና ፕሮቴስታንት ክፍል ሁለት
https://youtu.be/PbmNFCYro4I
1⃣5⃣ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እና ፕሮቴስታንት የመጨረሻው ክፍል
https://youtu.be/1NKzUoqtucs
1⃣6⃣ ስለ ቅዱስ ቁርባን ክፍል አንድ
https://youtu.be/Oji7daT4obw
1⃣7⃣ ንስሐ መግባት ለምን እንፈራለን?
https://youtu.be/kIkhOnUJm_A
1⃣8⃣ ሕማማት
https://youtu.be/NMHnlH0YLEE
1⃣9⃣ ስለ ዓቢይ ጾም
https://youtu.be/uErRRCkMsU0
2⃣0⃣ ዘጠኙ አጾማት
https://youtu.be/ZV7iwQS8mEk
2⃣1⃣ ለፓስተር ዳዊት የተሰጠ ምላሽ
https://youtu.be/hK473EGk0qs
2⃣2⃣ ለዮናታን አክሊሉ የተሰጠ ምላሽ
https://youtu.be/m8sFeVaja4I
2⃣3⃣ ጸሎት ምንድን ነው?
https://youtu.be/ZFYd4X-eGBo
2⃣4⃣ ክርስቲያናዊ የሆነ ጾም እንዴት እንጹም
https://youtu.be/ZV7iwQS8mEk
2⃣5⃣ ከፍቅረኛዬ ጋር ወደፊት ስለምንጋባ አሁን ግንኙነት ብንፈጽምስ?
https://youtu.be/ZV7iwQS8mEk
2⃣6⃣ ግብረ አውናን ምንድነው?
https://youtu.be/1XgZf6hq8bs
2⃣7⃣ ቅዱስ ቁርባን ለመቀበል ማድረግ ያለብን ዝግጅት?
https://youtu.be/TQeWVmN47PY
2⃣8⃣ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ? 81 ወይስ 66
https://youtu.be/Iggo8ws7quM


በዝማሬ ዳዊት የተላለፉ አጭር ታሪኮች

1⃣ የሰይጣን ጥያቄ
https://youtu.be/mHGEluQCJNY
2⃣ ባላገሩ
https://youtu.be/Kcftb4CReyg

👉 የልደት (ገና) መዝሙሮች
https://youtu.be/iSWmxwIJAac
👉 የጥምቀት መዝሙሮች
https://youtu.be/ESAE29ZvF3o
👉 አጫብር ወረብ
https://youtu.be/phssFP3KCRg
👉 መጾሙን ይጾማል - የበገና መዝሙር
https://youtu.be/q0TcGVnRGb4
👉 ማን ይመራመር - የበገና መዝሙር
https://youtu.be/dHqXNw_27R8
👉 የሰርግ መዝሙሮች
https://youtu.be/Xyc7R1Gk2Fs
👉 ዓለምን ዞሬ አየሁት? - የበገና
https://youtu.be/YP5ugEAYQRg
👉 ስለ ቸርነትህ - የበገና
https://youtu.be/KGBhL_7pA1c

ለሁሉም ሼር ያድርጉ ላላወቁት እናሳውቅ!
Subscribe ማድረግዎን እንዳይዘነጉ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ለ ሕጋዊ የሚድያ ተቋማት በሙሉ፤

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለዘመናት ያካበተቻቸውን መንፈሳዊ፣ ቁሳዊ፣ ታሪካዊ እና ኪናዊ ሀብቶቿን በተለያዩ የብዙኅን መገናኛ ተቋማት የሚዲያ ሽፋን በመስጠት ጉልህ አስተዋጽኦ ስታበረክቱ መቆየታችሁ ይታወቃል።

ስለሆነም ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከብዙኅን መገናኛ ድርጅቶች ጋር ተቀራርባ የምትሠራባቸው የተሻለ አሠራር መዘርጋት ትችል ዘንድ የብዙኋን መገናኛ ድርጅቶች በቤተ ክርስቲያኒቱ እውቅና ተሰጥቷቸውና  ሕግና ሥርዓትን በጠበቀ መልኩ  ከቤተ ክርስቲያናችን የሚወጡ መረጃዎችን በኃላፊነት እና መርሕን ባከበረ መንገድ፤ ለተዛባ ትርጉም ሳይጋለጡ እንዲዘገቡ የሚያስችል ሥርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ ኃላፊነት የሚሰማቸው ሚዲያዎች መረጃዎችን በትክክል እንዲያደርሱ የግንኙነት መዋቅር መዘርጋት ይቻል ዘንድ የምክክር መድረክ ለማዘጋጀት በዝግጅት ላይ ትገኛለች።

ስለሆነም ይህ ማሳሰቢያ ከወጣበት ጊዜ አንስቶ ተቀማጭነታቸው በአዲስ አበባ የሆኑ የግል እና የመንግሥት ብዙኅን መገናኛ ተቋማት ምዝገባ እንዲያካሂዱ ጥሪ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል።

በዚህም መሰረት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የዐውደ ምሕረት እና የአደባባይ በዓላትን ለመዘገብ፤  ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በየጊዜው የምትሰጣቸውን መግለጫዋች የሚዲያ ሽፋን ለመስጠት፤ በየአብያተ ክርስቲያናት የሚገኙ ቅርሶችን፣ ወቅታዊ ሁኔታዎችን እና በርካታ ሀብቶችን መሠረት ያደረገ የሚዲያ ሽፋን በመስጠትና  ልዩ ልዩ የሕዝብ ግንኙነት ሥራ ለመሥራት ወዘተ... የሚፈልግ ማንኛውም   የመንግሥትም ይኹን የግል ሚዲያዎች ከዛሬ የካቲት 9ቀን 2015 ዓ.ም እስከ የካቲት 15 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ብቻ  በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሕዝብ ግንኙነት  መምሪያ  በመገኘትና  የተዘጋጀውን ቅጽ በመሙላት ምዝገባ እንድታካሂዱ እያሳሰብን አዲስ የሚመሠረት የሚዲያ ተቋምና ተቀማጭነታቸው አዲስ አበባ  ካልሆኑት  በስተቀር ማንኛውም  የሚዲያ ተቋም በእነዚህ ቀናት ተገኝቶ ምዝገባ በማከናወን ቤተ ክርስቲያናችን በምታዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ  ካልተካፈለ በምንም አይነት መንገድ  ለቅድስት ቤተክርስቲያን የሚዲያ አገልግሎት ጥያቄ ቢያቀርብ የማይስተናገድ መኾኑን ለማሳሰብ እንወዳለን።

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክጠቅላይ ቤተ ክህነት የህዝብ
ግንኙነት  መምሪያ
የካቲት 9 ቀን 2015

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

አንድ ፓትርያርክ፣ አንድ ሲኖዶስ፣ አንዲት ቤተ ክርስቲያን

Patiraarikii Tokkicha, Sinoodoosii Tokkicha, Mana Kiristaanaa Tokkittii

ሓደ ፓትርያርክ፣ ሓደ ሲኖዶስ፣ ሓንቲ ቤተ  ክርስቲያን

one church, one patriarch, eotc one holy synod

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የሆነ ቅር ያለኝ ነገር ቢሆርም ይቅርታን ያስተማረን ክርስቶስ ነው እና እኛ ልጆችም ይቅር ብለናል! ቤተክርስቲያናችንን ግን አሁንም መጠበቃችንን እንቀጥላለን!

የአባቶቼን ትዕዛዝ እቀበላለው አከብራለሁ ቤተክርስቲያኔን እጠብቃለሁ ❤

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ቀጥታ ሥርጭት ከመንበረ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት

https://www.youtube.com/live/wMgJaj5pn4o?feature=share

የEOTC TV YOUTUBE ቻናል SUBSCRIBE አድርጉት ሁላችሁም 1Million እናድርሰው

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ማኅበረ ቅዱሳን በሁለት አኅጉረ ስብከቶች የሚገኙ አዳዲስ አማንያንን አስጠመቀ።

የማኅበረ ቅዱሳን ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ማስተባበሪያ በጎ አድራጊ ኦርቶዶክሳውያንን በማስተባበር ያሠራቸውን በሁለት አኅጉረ ስብከቶች ውስጥ የሚገኙ ሦስት አብያተ ክርስቲያናት ማለትም

1. በከምባታ ጠምባሮ ሀላባ ሀገረ ስብከት የቡጌ ኢየሱስና የጀባ ዶዶባ ቅዱስ ሩፋኤል አብያተ ክርስቲያናት

2. በቤንች ሸኮ፣ሸካ እና ምዕራብ ኦሞ ዞን ሀገረ ስብከት ጋሮ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያንን
በየካቲት 5 እና 6 ቀን 2015 ዓ.ም አስመረቀ፡፡

በምረቃው ዕለታትም 163 አዳዲስ አማንያን ሥርዓተ ጥምቀት ተፈጽሞባቸዋል።

በዕለቱም የአኅጉረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ እና የመምሪያ ኃላፊዎች፣ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ሕገወጡ ስብስብ አሁን በቲክቶክ ላይ Live መግለጫ እየሰጡ ይገኛል

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልዑካን እና የሩሲያ ቤተ ክርሰቲያን አገልጋዮች እንዲሁም የመንግስት ባለ ስልጣናት በእንዲህ አይነት መልኩ እየመከሩ ይገኛሉ።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የኦርቶዶክሳውያን እስር እንደቀጠለ ነው

የማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማእከል አባል የሆነው ዶ/ር እንዳሻው ዘርፉ በጸጥታ አካላት ተወስዳል

ዛሬ 5:00 አከባቢ ደ/ር እንዳሻዉ ዘርፉን ለጥያቄ እንፈልግሃለን በማለት በማለት አፍነው ወስደውታል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🎬 "በምግብ ሰዓት የሚጸለይ ጸሎት" - |ቀሲስ ሳሙኤን እሸቱ እንዳዘጋጀው ዮሴፍ በሪሁን እንዳነበበው|
👤 ዝማሬ ዳዊት ቲዩብ

⚠️ ጸሎቱን ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!
https://youtu.be/pjBReIJQ-Q4
https://youtu.be/pjBReIJQ-Q4

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ይህ ቻናል የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሊቃውንት ቃለ መጠይቅ የሚደረግበት እንዲሁም የተለያዩ ትምህርቶች የምናገኝበት ቻናል ነው።


👉ይህንን ቻናል Subscribe ማድረግ ለነፍሳችን ይጠቅመናል።


❓❓❓ጥያቄ❓❓❓

👉ስንት አይነት የነጠላ አደራረግ መንገዶች አሉ? ምሥጢሮቹንስ እናውቃለን? በእዚህ ቪድዮ ላይ መልሱን ታገኙታላችሁ

👉ስለ ዘፈን ከመጽሐፍ ቅዱስ አንጻር እንዲሁም ምዕራባውያን በዘፈን ምን ደረጃ ላይ ደርሰዋል? እንዴትስ ማቆም እንችላለን የሚለውን በተለየ መልኩ የተዘጋጀ ትምህርት አለ

👉ጸሎት ስንጸልይ እንዴት ሀሳባችንን ከመሰራረቅ መጠበቅ እና እግዚአብሔር የሚወደውን ጸሎት እንዴት መጸለይ እንችላለን? የጸሎት ቅድመ ዝግጅቶችስ ምን እንደሆኑ እናውቃለን?

👉በእዚህ በመከራ ጊዜ ንስሐ መግባት ፈልገናል ግን እንዴት ንስሐ መግባት እንዳለብን አናውቅም?

በዚህ የዩቲዩብ ቻናላችን ላይ ተለቋል subscribe በማድረግ ትምህርቶቹን ይከታተሉ።

👉 ቶ መስቀል የቤተክርስቲያናችን ነው ወይስ የግብጽ ጣዖታት እስከ ማስረጃው የተዘጋጀ ቪድዮ አለ


👉 እግዚአብሔርን በዓይኖቻችን ማየት እንፈልጋለን? የአባታዊ እቅፉን ማጣጣም እንፈልጋለን? እንግዲያውስ እግዚአብሔርን እንዴት መውደድ እንችላለን በሚል የተዘጋጀ ትምህርት አለ።

ይህንን ሊንክ ይጫኑት👇👇👇
Hadafe_nefese" rel="nofollow">https://youtube.com/@Hadafe_nefese

ከእዛም subscribe በማድረግ ይቀላቀሉ
🔴ሰብስክራይብ/Subscribe🔴

አሁን በማድረግ አገልግሎቱን ይደግፉ እናንተም የእግዚአብሔርን ቃል ተመገቡ።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የተመራ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልዑክ ለሁለትዮሽ ውይይት ሩሲያ /ሞስኮ/ መግባቱ ተገለፀ ።

በብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት እና የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የተመራ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልዑክ ከብፁዕ ወቅዱስ ኪሪል ጋር ለመወያየት እና የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት መልዕክትን ለማድረስና በሁለትዮሽ የአብያተ ክርስቲያናቱ ቀጣይ ግንኙነት ላይ ውይይት ለማድረግ ሞስኮ መግባቱ ነው የተገለፀው።

የልዑካን ቡድኑ አባላት የኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ የውጭ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ መምህር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል እና የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ጊዜያዊ እና ቋሚ ፕሮጀክቶች መምሪያ ኃላፊ መልአከ ሕይወት አባ ወ/ኢየሱስ ሰይፉ እንደሚገኙበት ተገልጿል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ስለ አባቶቻችን?

መልእክቱን አዳምጡት

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!

ፍቅርን እንደ ዓይን ብሌን ስንጠብቃት በእጅጉ የምትጠቅመንን ያህል ስንተዋት ደግሞ በእጅጉ ትጎዳናለች፡፡ በፍቅር እጦት የሚደርሰው ጉዳት በተወሰነ ነገር ብቻ ሳይሆን በነፍስም ሆነ በሥጋ፣ በምድርም ሆነ በሰማይ እጅግ በጣም የገዘፈና የሰፋ ነው፡፡

በሀገራችን የሆነውና እየሆነ ያለውም ይኸው ነው፡፡ ፍቅርን ባጣንባቸው ዓመታት ከየት ወዴት እንደደረስን ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚገነዘበው ነው፡፡ ያተረፍነው ነገርም ምን እንደሆነ የምናውቀው ነው፡፡

ይሁንና የፍቅር እጦት ምን ያህል እንደጎዳን ራሳችን ተገንዝበን ወደ ሰላሙ መንገድ መመለሳችን የተሻለ አማራጭ መሆኑን ሳንመሰክር አናልፍም፡፡ የተጀመረው የፍቅርና የሰላም ጉዞም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ልባዊ ምኞታችንና ጸሎታችን ነው፡፡

ይህንን ሰላም እንዲመጣ ያደረጉ ወገኖችም ሁሉንም ሳናመሰግን አናልፍም፡፡ ምክንያቱም በሰዎች መካከል ፍቅርንና ሰላምን የሚያደርጉ የእግዚአብሔር ልጆች እንደሚባሉ ጌታ እንደ አስተማረን ብፅዕና ይገባቸዋልና ነው፡፡ (ማቴ.፭፥፱)

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!

የፍጹም ፍቅር መገኛ የሆነው ቅዱስ ወንጌል የሚያስተምረው ፍቅር ራስን ማፍቀር ወይም መውደድ ሳይሆን ራስን መጥላት ባልንጀራን ግን መውደድ እንደሆነ ነው፡፡ “ወንጌላዊ-ፍቅር ፍጹም ነው” የሚያሰኘውም ቅሉ ይህ ነው፡፡

ለሁለት ሺህ ዘመናት ያህል በቅዱስ ወንጌል አስተምህሮ ላይ የተገነባው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ባህልም ይህን ፍቅር ጠብቆ የሚጓዝ ነው፡፡ ይህም በመሆኑ የኢትዮጵያ አበው መነኮሳት ከነበራቸው ፍቅርና ትሕትና የተነሣ፣ የሹመት ሽሚያ አያውቁም ነበር፡፡ ከዚህ አንጻር ትልቁን ሥልጣን ይቅርና የአንድ ገዳም መሪ ለመሆንም በእግር ብረት ታስረው በግድ ካልሆነ በቀር እሺ ብለው በፈቃደኝነት ሹመትን አይቀበሉም ነበር፡፡

ራሱን በራሱ መሾም ወይም እኔን ሹሙኝ ብሎ መናገርና የሌላን ድጋፍ መጠየቅ ለኢትዮጵያውያን መነኮሳት ጭራሽ ነውርና ጸያፍም ነበር፡፡ ከዘመነ ብሉይ ጀምሮ ለሦስት ሺህ ዘመናት የዘለቀው ሃይማኖታችን ምንም ዓይነት መለያየት ሳያጋጥመው አንድ ሆኖ ሊዘልቅ የቻለው ያም በመሆኑ ነው፡፡ ይህ የቤተ ክርስቲያናችን ጠንካራ አንድነት ለሕዝቡም በመትረፉ የሀገሪቱን አንድነትና ነጻነት አስጠብቆ እስከ ዘመናችን ሊደርስ ችሎአል፡፡ በዚህም ቤተ ክርስቲያናችን የሕዝብንና የሀገርን አንድነትና ነጻነት ለማስጠበቅ ያደረገችውና የምታደርገው ጥረት ሊያስመሰግናት እንጂ ሊያስወቅሳት አይገባም፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!

ከቅርብ ቀናት ወዲህ በቤተ ክርስቲያናችን ተከሥስቶ የነበረውን ሕጋዊ ያልሆነ ድርጊት የቤተ ክርስቲያናችንን ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊና ባሕላዊ መርሕን የናደ፣ እንደዚሁም በኢትዮጵያ ይቅርና በዓለም ታሪክ ተደርጎ የማያውቅ ድርጊት እንደሆነ ቤተ ክርስቲያናችን በአጽንዖት ስትገልጽ ቆይታለች፡፡

ይህንን የቤተ ክርስቲያን ድምፅ በመስማትና በመቀበል ሕዝበ ክርስቲያንና ኢትዮጵያውያን ሁሉ ለእግዚአብሔር ባቀረቡት ኀዘንና ጸሎት እንደዚሁም ባደረጉት መጠነ ሰፊና ዙርያ መለስ የሆነ የድጋፍ ርብርብ ስሕተቱ ሊታረም ችሏል፡፡

ለተገኘው መንፈሳዊ ውጤትም ጠቅላይ ሚንስትርና መንግሥታቸውን፣ የቤተ ክርስቲያን አንድነትና ሉዓላዊነት እንዲከበር ከፍተኛ መሥዋዕትነት ለከፈለው መላው ሕዝበ ክርስቲያን እንዲሁም ይህ ስሕተት እንዲታረም ከቤተ ክርስቲያናችን ጎን ተሰልፈው ድምፃቸውን ላሰሙ ኢትዮጵያውያንና የውጭ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ በቤተ ክርስቲያናችን ስም ከፍ ያለ ምስጋና እናቀርብላቸዋለን፡፡

በዚህ አጋጣሚ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ልጆቻችን ግልጽ ማድረግ የምንፈልገው ከቤተ ክርስቲያናችን ዶግማ፣ ቀኖና እና ሥርዓት መከበር እንደዚሁም ከሉዓላዊ አንድነቷ መጠበቅ በመለስ ያለው ጥያቄ ለማስናገድ ቤተ ክርስቲያናችን ዝግጁ መሆኗን ነው፡፡
ቤተ ክርስቲያናችን ሕዝቦች በቋንቋቸው የመማር፣ የማስተማርና የማምለክ እንዲሁም የመተዳደር መብትን ካሁን በፊትም፣ አሁንም፣ ካሁን በኋላም የምትነፍግበት መሠረት እንደሌለም ሁሉም ሊያውቀው ይገባል፡፡

ይህም በመሆኑ በቋንቋ የመጠቀም መብት በሕገ ቤተ ክርስቲያናችን ምዕራፍ ፪ አንቀጽ ፭ ከቁጥር ፩ እስከ ፫ ባለው አንቀጽ በሚገባ ተቀምጦ ይገኛል፡፡ ስለሆነም በቋንቋ የመጠቀም ጥያቄ በሕግ ደረጃ ተመልሶ በተግባር እየተሠራበት የሚገኝ መሆኑን ሁሉም ሊገነዘበው ይገባል፡፡

የተወዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!

ዛሬ ታላቁን ጾም በፍቅር ሆነን የምንጾምበት ወቅት ነው፡፡ ሁላችንም እንደምናውቀው ጾም ማለት ሥጋዊ ፈቃድን በመግታት ከእግዚአብሔር ጋር ጥብቅ ግንኙነት ለማድረግ የሚካሄድ መንፈሳዊ ተጋድሎ ነው፡፡

በጌታችን ጾም በተግባር እንዳየነው ጾም ማለት ዲያብሎስ የሚሸነፍበት በአንጻሩ ደግሞ የእግዚአብሔር ሕዝብ አሸናፊዎች የሚሆኑበት ኃይል ነው፡፡

ስለሆነም ጾም የተጋድሎና የሙዓት ሜዳ ነው ማለት ይቻላል፡፡ የምንታገለውም ልብሰ ሥጋ ሰውን ሳይሆን ረቂቅ ፍጡር የሆነው ሰይጣን በሰው አድሮ የሚነዛውን አጥፊ ሐሳቡንና ድርጊቱን ነው፡፡ ከዚህም ጋር ሰውነታችን ለዚህ ክፉ መንፈስ ታዛዥ እንዲሆን የሚገፋፉ ጥሉላት መባልዕትን መተው፣ ኃይለ ሥጋን መቈጣጠር፣ ኃይለ መንፈስን ደግሞ ማጎልበት ያስፈልጋል፡፡ በጾም ወቅት የተራቡትን ማጉረስ፣ የታረዙትን ማልበስ፣ የተበደሉትን መካስ፣ ፍትሕና ርትዕ በማኅበረ ሰብ ውስጥ ማንገሥ ያስፈልጋል፡፡

በጾም ወቅት ኅሊናችን ማሰላሰል ያለበት ሰው ምን አለ? ወይም ምን አደረገ? በሚለው ሳይሆን እግዚአብሔር በፊቱ ምን ዓይነት ሰው እንድንሆንለት ይፈልጋል? በሚለው ላይ ነው፡፡ ስለዚህ ጾማችን በዚህ መንፈስ የተቃኘ ፍቅረ፣ እግዚአብሔርንና ፍቅረ ቢጽን ማእከል ያደረገ፣ መጠራጠርንና አለመተመማንን ያስቀረ፣ የተለያዩትን ያቀራረበ፣ የተሳሳቱትን ያረመ በአንጻሩ ደግሞ ሁላችንን በሰላምና በፍቅር አንድ አድርጎ ያስተሳሰረ ይሆን ዘንድ በዚህ መንፈስ ተነቃቅተን እንድንጾመው አባታዊ ጥሪያችንን ለሕዝበ ክርስቲያኑ እናስተላልፋለን፡፡

በመጨረሻም

በሀገራችን እየታየ ያለው የሰላም ጭላንጭልና ችግሮችን በውይይት የመፍታት ዝንባሌ ለሁለንተና ልማታችንና ለዕድገታችን እንደዚሁም ለተሟላ አንድነታችን ጠቃሚነቱ የጎላ ስለሆነ እግዚአብሔር ለዘለቄታው እንዲያሳካልን ከልብ እንድናዝንና ወደ አምላካችን በተመሥጦ እንድንጸልይ በአጽንዖት በማሳሰብ አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡

መልካም የጾም ወራት ያድርግልን!
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር! አሜን
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስምወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
የካቲት ፲፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የፈለጋችሁትን አርዕስት በመምረጥ ከስራቸው ባለው Link በመግባት ማዳመጥ ትችላላችሁ። ታዲያ በዛው Subscribe ማድረጋችሁን እንዳትረሱ።

ሼር በማድረግ ለሁሉም አድርሱልን
ሠላመ እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን❤

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

መምህር ዓቢይ መኮንን ከእስር ተፈታ፡፡
መምህር ዓብይ መኮንን ለጥያቄ እንፈልግሀለን በሚል የጸጥታ ኃይሎች ወስደውት ላለፉት 14 ቀናት በእስር መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ዛሬ የካቲት 9 ቀን 2015 ዓ.ም ከእስር መፈታቱ ታውቋል፡፡

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በእሥር ላይ የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያንን በተመለከተ በጥቂት ቀናት ጉዳያቸው ታይቶ እንደሚፈቱ ከመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር መግባባት ላይ ተደርሷል።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🎬  🛑 ማሕተብ ማሰር እንዴት መቼ እና ማን ጀመረው! |Mahiteben albetisim| በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ
👤 ዝማሬ ዳዊት ቲዩብ

⚠️ ትምህርቱን ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!
https://youtu.be/EOBUB-0eW3c
https://youtu.be/EOBUB-0eW3c

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ሰበር ዜና

በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩት በቀድሞ ስማቸው እነ አባ ሳዊሮስ በዛሬው ዕለት በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ተገኝተው የይቅርታ ደብዳቤ አስገቡ።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

https://youtu.be/S6ydqpliJXQ

የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ በተመለከተ
👉የእሑድ ሰላማዊ ሰልፍ ከመቅረጡ አንጻር
👉ቤተክርስቲያን ላይ አሁን ምን አይነት ችግሮች ሊጋረጡ ይችላሉ? ምንስ ጥሩ ጎን አለው?
👉አሁንም ቤተክርስቲያንን ለማጥፋት የሚጥሩ የመንግስት አካላት እነማን ናቸው?

👉 እንደ አንድ ኦርቶዶክስ ከእኛ ምን ይጠበቃል የሚለውን በተከታታይ ክፍሎች የተካተተ ነው የሚሆነው።


ሁላችንም የዩቲዩብ ቻናሉን ሰብስክራይብ በማድረግ እንቀላለቀል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​VALENTINE'S DAY
ሼር በማድረግ ትውልዱን ከጥፋት እንታደግ❗

አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኛ ቤዛ ሆኖ በፍቅሩ የገዛን እጃችንን ለጣኦት እንድንሰጥ አይደለም ብዙ ዋጋ የተከፈለብን እስከ ሞት እንከን በሌለው ፍቅሩ የወደደን መንግስቱን እንድንወርስ እንጂ እንድንጠፋ አይደለም።

የቫላንታይ ቀን ድብቅ እውነታ ስንቶቻችን እናውቃለን? ይህን የቫላታይን ቀን (የፍቅረኛሞች ቀን) ብለን ስንቶቻችን ነን የምናከብረው ? ወይስ ሰው ስላከበረውና የስልጣኔ መገለጫ መስሎን ነው የምናከብረው ???

ከክርስቶስ ልደት በፊት በባቢሎን ፤ቤልዘቡል ፤በግሪክ ፓን ፤ ሮማ ሞሎቅ ፤ በላቲን ሳተርን ለሚባሉት ሰይጣኖች ያላገቡ ሴቶች ደም የሚፈስላቸው ቀይ ልብስ የሚለበስላቸው ጣኦቶች ናቸው ይህ ዛሬ ቫለንታይን ተብሎ የመጣው ማለት ነው።

የሚገርመው ደሞ ሴቶቹ በዚህ ቀን ለመደፈር ብለው እራቁታቸውን ጫካ መግባታቸው ነው በዚህ ቀን የተደፈረች እና ደሟን ያፈሰሰች ሴትም ሆነ ወንድ በጣኦቱ የተመረጠ እና የተባረከ ነው መባሉ ነው ይበልጥ ነገሩን ሰይጣናዊ የሚያደርገው።

ግሪክ አርኬዲያ ብለው በሚጠሩት አስቀያሚ ትርጉም ባለው ተራራቸው ላይ በዚህ ቀን ላይ ነው ያላገቡ ወንድ እና ሴቶቻቸውን ጣኦቱ ስር ወሲብ በመፈጸም ገላቸውን አርክሰው ለሰይጣን የሚገብሩት።

ይህ የሰይጣን ቀን ነው ክርስትና ይሄን ትከለክላለች ታወግዛለች። (ሁሉም ቀን የእግዚአብሔር ነው ግብሩ ነው የሰይጣን የሚያደርገው)

ኢየሱስ ክርስቶስ ከመውለዱ ከዘመናት በፊት አረማውያን ሮማውያኖች Feb 14 ማታ እና ለ Feb 15 ንጋት አጥቢያ የተኩላ አዱኚ ለሚሉት ሉፐርካልያ (luperkalya ) ጣኦት የሚዘጋች ክብረ በአል ነው፡፡

ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ክርስትና ተቀብሎ እውነተኛ የጽድቅ ሃይማኖት መሆኑን በማውጁ ማንኛውም የጣኦት አምልኮ እንዲቀር ቢያስጠነቅቅም የተውሰኑ የሮማውያን ሰዎች ግን በአሉን ማክበር አልተውም።

እንዴት ይህ አረማዊ ባህል ቫለንታይን የሚል ሰያሜ ተሰጠው? ቫለንታይን የሚል ስም በሮማውያን ዘንድ የተለመደ ስያሜ ነው፡፡ ቫለንታይን የጥንታዊ ታዋቂው ሉፐርኩስ ጣኦት ነው።

ሉፐርኩስ በግሪካዎያን ፓን (pan) ተብሎ ሚጠራው ከወገቡ በታች በግ አናቱ ላይ ቀንድ ያለው ጣኦት ነው። በጥንታውያን አይሁድ ደግሞ ይህ ፓን ባል (baal) በሚል ስያሜ ይታወቃል።

ጥንታውያን ሮማውያን ከባቢሎናውያን የቀዱት አረማዊ የልብ (heart) ምልክት ይጠቁማሉ፡፡ በባቢሎናውያን ባል (bal) ልብ የሚል ፍች ነው ያለው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ይህ አረማዊ የልብ ምልክት ለቫለንታይን ቀን (የፍቅረኛሞች ቀን) የምንለው መግለጫነት እንጠቀምበታለን። ባል የባቢሎናውያን ጣኦት ነበር።

በዚህ የሃጥያት ቀን በትንቹ ይህ ይሆናል

1. በዚህ ቀን February 14 በብዙ የሚቆጠሩ እህቶቻችንን ክብረ ንጽህናቸውን (ድንግልናቸውን) ያጣሉ❗

2. በርካታ ወጣቶች በስካር ምክንያት በሚያሽከረክሩት መኪና ህይወታቸውን እና አካላቸውን ያጣሉ❗

3. በአለማችን ላይ በከፍተኛ ሁኔታ የአልኮል መጠጥ ሽያጭ የሚከናወንበት ቀን ነው በአጠቃላይ የዝሙት እና ስካር መንፈስ የሚነግስበት በከፍተኛ ሁኔታ ሰይጣን በደም የሚረካበት ቀን ነው።

Valentine day ማለት ሰይጣን በጥልቅ እና ረቂቅ ሃሳብ ብዙዎችን የሚያጠምድበት ቀን ነው አስተውሉ ሰይጣን ከ7ሺህ አመት በላይ የክፋት ልምድ አለው።

እንግዲህ ምርጫው ያንተ/ቺ ነው :- የእግዚአብሔር ወይም የሰይጣን ልጅ መሆን???

" ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ አንተም እውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፤ የአምላክህንም ሕግ ረስተሃልና እኔ ደግሞ ልጆችህን እረሳለሁ። "
(ትንቢተ ሆሴዕ 4 : 6)

እግዚአብሔር አምላክ ማስተዋሉን ያድለን።
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

አስፈራርተው ወስደውኝ ነው

እንግዲህ ተመልከቱ ክርሰቲያኖች እሁድ እለት ወደ ቅድስት ቤ/ክ በይቅርታ የተመለሱት አባት ያን እለት ቪዲዮውን ያያችሁ አይታቹኋል።ዛሬ ደግሞ ወደ ሕገ ወጡ ሲኖዶስ በድጋሚ ተመልሰዋል።

ጌታ ሆይ ምን ጉድ ነው ???

ምንድነው ቆይ አየሆነ ያለው?

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የዚህ መንግስት ሌላ ራስ ምታት የካቲት 23

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት (EOTC TV) የኦሮምኛ ቋንቋ ጋዜጠኛ ዲ/ን ዮሴፍ ከተማ በጸጥታ ኃይሎች ታፍኖ ተወሰደ።

ዛሬ ሰኞ የካቲት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 አካባቢ በሥራ ጉዳይ በመንቀሳቀስ ላይ እያለ መካኒሳ አካባቢ ለጥያቄ እንፈልግሃለን የሚሉ የመንግሥት የጸጥታ አካላት አፍነው ወስደውታል።

የኦሮምኛ ቋንቋ ጋዜጠኛ ዲ/ን ዮሴፍ ከተማ በወቅታዊ ጉዳይ ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተደጋጋሚ ቃለ ምልልሶች በማድረግ ወደ ምእመናን ሲያደርስ ቆይቷል።

ምንጭ: EOTC TV

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🎬 ግብረ አውናን/ሴጋ/ የፈጸመ ኦርቶዶክሳዊ/ት ጋብቻውን/ዋን በተክሊል መፈጸም ይችላሉን?
👤 ዝማሬ ዳዊት ቲዩብ

⚠️ ትምህርቱን ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!
https://youtu.be/hnt5Y1F4TDY
https://youtu.be/hnt5Y1F4TDY

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

Watch "ነጠላ አደራረግ እስከ ምክንያቱ #orthodox #youtubeshorts #tiktok #viral" on YouTube
https://youtu.be/QByZooavA4E

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በቀድሞ ስማቸው አባ ንዋየ ሥላሴ አካሉ የይቅርታ ደብዳቤ በአስገቡ ሰዓት "የተሾሙበትን" አስኬማና አልባሳትም አስረክበዋል።

"እውነትን ተረድተው ስለመጡ ቤተ ክርስቲያን ደስተኛ ናት። ሌሎች በማወቅም ባለማወቅም የሄዳችሁ አሁንም ለመምጣት የተቸገራችሁ ቤተ ክርስቲያን በሯ ክፍት ነው::" ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ

Читать полностью…
Подписаться на канал