ortodoxmezmur | Неотсортированное

Telegram-канал ortodoxmezmur - ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

134932

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . ዝማሬ ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Подписаться на канал

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ምሥጢረ ጥምቀት ክፍል ፪
👉ጥምቀት ለምን ያስፈልጋል

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

✝ማስታወቂያ✝


ዛሬ ምሽት ምሥጢረ ጥምቀትን ትምህርት ስለምንጀምር ሁላችሁም ትዘጋጁ ዘንድ በትኅትና እንጠይቃለን።


👉 ማታ በድምጽ ትምህርቱን ከመላካችን በፊት
ከትምህርተ ተዋሕዶ አፕሊኬሽን ስለ ምሥጢረ ጥምቀት ታነቡ ዘንድ በትኅትና እንጠይቃለን።



⚠️ትምህርታችንን ከአሁኑ በኋላ በስፋት ስለምንቀጥል። ስልካችሁ ላይ ያሉትን ኦርቶዶክሳዊያን ሁሉ አሁን ወደ ቻናላችን በመጫን ለብዙኃኑ ኦርቶዶክሳዊያን ተደራሽ እንሁን።⚠️


ኦርቶዶክሳዊያን ከእዚህ በኋላ በስሜት ብቻ የምንጓዝ ሳንሆን ቤተክርስቲያናችንን ተምረን ለሌሎች የምንደርስ እንሁን። እስከ ማታ በደህና ቆዩን

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የሩሲያ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በ12 ርእሰ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ማድረጋቸው ተገለጸ።

በሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መካከል ለሁለተኛ ጊዜ የሁለትዮሽ ውይይት ከየካቲት 4 ቀን እስከ የካቲት 9 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ በሩሲያ ሞስኮ መደረጉ ይታወሳል።
በጉባኤው በኢትዮጵያ በኩል በብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንትና የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መሪነት በሩሲያ በኩል በብፁዕ አቡነ ሊዮኒድ በአፍሪካ የሩሲያ ቤተ ክርስቲያን የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ እየተመራ ተከናውኗል።
በውይይቱ ላይ ከአራት ዓመታት በፊት በተካሔደው በመጀመሪያው የሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ ወቅት በጋራ ይተገበራሉ ተብለው በተስማሙባቸው ፕሮጀክቶች ዙሪያ ግምገማ ተደርጓል።

እንዲሁም ሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት ክርስትና እና ክርስቲያኖችን መከላከል፣ በዘመናዊው ዓለም ክርስቲያናዊ ዕሴቶች እንዳይጠፉ መጠበቅ፣ በሚዲያ አማካኝነት የልምድ ልውውጥ ማድረግ፣ በትምህርት ዘርፍ መደጋገፍን ጨምሮ በ12 ርእሰ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ፈጽመዋል።
የመነኮሳት ልዑካን ወደ ሁለቱም አብያተ ክርስቲያናት እንዲሔዱና በሁለቱም በኩል ያለውን የገዳማውያን ሕይወት እንዲመለከቱም ዕቅድ ይዘዋል።

ከዚህ በተጨማሪ የሞስኮ የነገረ መለኮት አካዳሚ እና የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ በትብብር እንዲሠሩ ስምምነት ላይ የተደረሰ ሲሆን የሩሲያ ቤተ ክርስቲያን ልዑክ ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲንና ሌሎች የኢትዮጵያ ቦታዎችን እንደሚጎበኝም ተጠቅሷል።
በተጨማሪም የሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት ምእመናን በሩሲያ እና በኢትዮጵያ ያሉ ቅዱሳን ቦታዎችን መጎብኘት እንዲችሉ ለማድረግ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በትብብር ለመሥራት ተስማምተዋል። መረጃው የተሚማ ነው።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🎬  🛑ሁሉም ይስማ! አሳ በጾም ወቅት ይበላል ወይስ አይበላም? ምንድን ነው ማስረጃው? ከምንስ የመጣ ጥያቄ ነው?
👤 ዝማሬ ዳዊት ቲዩብ

⚠️ ትምህርቱን ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!
https://youtu.be/CdFJrQM8DyI
https://youtu.be/CdFJrQM8DyI

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🎬  🛑 ሰበር‼️ ይህን የማያደርግ ኦርቶዶክሳዊ አይኑር!
👤 ዝማሬ ዳዊት ቲዩብ

⚠️ ከስር ባስቀመጥነው LINK ይመልከቱ!
https://youtu.be/nPekyNuW1Ek
https://youtu.be/nPekyNuW1Ek

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#ሰው_ለሰው

ሰው ለሰው/2/ ቢፋቀር ምነው /2/

ለሰው ይመስለዋል ብዙ የሚቆይ
ግን በድንገት ያልፋል ሁሉንም/2/ ሳያይ
ሀብትን ያከማቻል ቀኑን ሳያውቀው
በድንገት ሲጠራ/2/ ላይከተለው
#አዝ
የሰው ልጅ በተራው መጠራቱ ላይቀር
ምነው አንዱ ለአንዱ መቃብር/2/ ባይቆፍር
አይጠቅምም መጨነቅ እንዲያው ለውበት
ይረግፋል ይጠፋል ሁሉም/2/ ከመሬት
#አዝ
ዋ! ቁንጅና ከንቱ ማማርም ብላሽ
አፈር ትቢያ ሲሆን ሲጨለም/2/ ሲመሽ
ደሀ ባለጸጋ አንድ ነው መንገዱ
በጨርቅ ተገንዞ በሳጥን/2/ መሄዱ
#አዝ
ሰው ዙሪያውን ቢያጥር መዝጊውን ቢሠራ
በሕንፃ ላይ ሕንፃ ቢያስመስል ተራራ
አይቀርም መሄዱ ሁሉም/2/ በየተራ

ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

https://youtu.be/TQeWVmN47PY

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እነዚህን ጥያቄዎች መልሷቸው።👆👆👆

የምሥጢረ ሥላሴ ጥያቄ ናቸው

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

https://youtu.be/uErRRCkMsU0

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

✥ የዐቢይ ፆም የመጀመሪያ ሳምንት ✥

• በመምህር ዶ/ር ዘነበ ለማ •
═════●◉❖◉●══════
✥ ዘወረደ ✥
═════●◉❖◉●══════
✢ Share ✢

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🎬  🛑 ሰበር‼️ ይህን የማያደርግ ኦርቶዶክሳዊ አይኑር!
👤 ዝማሬ ዳዊት ቲዩብ

⚠️ ከስር ባስቀመጥነው LINK ይመልከቱ!
https://youtu.be/nPekyNuW1Ek
https://youtu.be/nPekyNuW1Ek

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​​​ዐቢይ ጾም

ጾም ማለት ሰውን ከምግብ መከልከል ነው፡፡ (ፍትሃ ነገስት አንቀፅ.15) “ጾምሰ ተከልኦተ ብዕሊ ዕምመብልዕ በጊዜ እውቅ” ጾም ማለት በታወቀው ዕለት በታወቀው ሰዓት ሰው ከምግብ የሚከለከለው መከልከል ነው፡፡

መብል መጠጥ የኀጢአት መሠረት ነው በመብል ምክንያት ሞት በሰው ልጆች ላይ መጣ “ይችን ዕፀ በለስ ብትበሉ ሞትን ትሞታላችሁ” ዘፍ.2፥17 ጾም ማለት ሰውነት ከሚፈልጋቸው ነገሮች ሁሉ መከልከል ለሰውነት የሚያምረውን የሚያስጐመዥውን ነገር መተው ማለት ነው። መብል መጠጥ ከልክ ሲያልፍ ከተዘወተረም ከእግዚአብሔር ይለያል፤ “ያዕቆብ በላ ጠገበ ወፈረ ገዘፈ ደነደነ ፈጣሪው እግዚአብሔርን ተወ ሕይወቱ ከእግዚአብሔር ተለየ” ዘዳ.32፥15-17 “የእግዚአብሔር መንግሥት መብልና መጠጥን አትሰብክም” ሮሜ.14፥16፣ 1ቆሮ.8፥8-13 “ዛሬ የሚራቡ የሚጠሙ ብፁአን ናቸው ይጠግባሉና ማቴ.5፥6 ጾም የሥጋ መቅጫ ነው፤ “ነፍሴን /ሰውነቴን/ በጾም ቀጣኋት መዝ.68፥10

ጾም በነቢያት የተመሠረተ በክርስቶስ የጸና በሐዋርያትም የተሰበከና የተረጋገጠ ለክርስቲያኖች ዲያብሎስን ድል የምንነሣበት መንፈሳዊ የጦር ዕቃ ነው፡፡ ስለዚህ ሐዋርያዊትና ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እንደምታስተምረን ይህን ጾም ከምግብ ለመከልከል ጋር ጸሎትን፥ ስግደትን፥ ምጽዋትንና የንስሐ ዕንባን ጨምረን እንጹመው፡፡ ጌታችንና ነቢያት፣ ሐዋርያት የተውልን መንፈሳዊ መሣሪያ ነውና፡፡

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ጾም የጾመው ለአብነት፣ ለማስተማር፣ ለአርዓያ ነው፡፡ በዚህ ታላቅ ጾም ጥንተ ጠላታችን ዲያብሎስ፣ ከሰው የሥጋ ጠባይ የሚመጣ ስስትና ፍቅረ ንዋይ ድል የተነሱበት ነው፡፡ እኛም ይህን እያሰብን በተለያየ መንገድ የሚመጣብንን ፈተና ለማራቅ ከዚህ ታላቅ ጾም በረከት እንድናገኝ እንጾማለን፡፡ ጸልዮ ጸልዩ፣ ጾሞ ጹሙ ብሎናል፡፡ ማቴ.6-16፡፡ ስለዚህም ትእዛዙን ለማክበር እንጾማለን፡፡

የዚህ ታላቅ ጾም ስያሜዎች የሚከተሉት ናቻው ፡-

ዐቢይ ጾም
ባሕርይ አምላክ በሆነዉ በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተመሠረተ በመሆኑ ዐቢይ ወይም ታላቅ ጾም ይባላል፡፡

ጾመ ሁዳዴ
በጥንት ጊዜ ገባሮች ለባለ ርስት የሚያርሱት መሬት ሁዳዴ ተብሎ ይጠራ ነበር፡፡ እኛም ባለቤቱ ኢየሱስ ክርስቶስን እያሰብን የምንጾመው በመሆኑ ጾመ ሁዳዴ ተብሏል፡፡

የካሳ ጾም
አዳምና ሔዋን ከገነት የተባረሩት ለውርደት ሞት ለሲዖል ባርነት የበቁት በመብል ምክንያት ነው፡፡ በመብል ምክንያት የሞተውን የሰው ልጅ ጌታችን በፈቃዱ በፈጸመው ጾም ካሰው፤ መንፈሳዊ ረሃብን በረሃቡ ካሰለት፡፡ ስለዚህም የካሳ ጾም ተባለ፡፡

የድል ጾም
አርዕስተ ኃጣውእ /ማቴ. 4/ ድል የተነሱበት በመሆኑ የድል ጾም ተብሏል፡፡

የመሸጋገሪያ ጾም
ጌታችን ከሕገ ኦሪት ወደ ሕገ ወንጌል ሊያሸጋግረን የጾመው ጾም በመሆኑ የመሸጋገሪያ ጾም ተብሏል፡፡

ጾመ አስተምህሮ
ጌታችን የጾመው ለትምህርት ነው፡፡ እርሱ መጾም ያለበት ሆኖ አይደለም፡፡ ስለዚህም ይህ ጾም ጾመ አስተምህሮ ይባላል፡፡ አርባ መአልትና አርባ ሌሊት ጾመ ማቴ.4፥2

የቀድሶተ ገዳም ጾም
ጌታችን ከከተማ ርቆ ከሰው ተለይቶ /በገዳመ ቆሮንጦስ/ በመጾም ከከተማ ርቆ ከሰው ተለይቶ በብሕትውና መኖርን ቀድሶ የሰጠበት፣ የመጥምቁ ዮሐንስና የነቢዩ ኤልያስን ገዳማዊነት የባረከበት በመሆኑ የቀድሶተ ገዳም ጾም ተብሏል፡፡

የመዘጋጃ ጾም
ሕዝበ እሥራኤል የፋሲካውን በግ ከመመገባቸው በፊት ዝግጅት ያደርጉ ነበር፡፡ እኛም ትንሣኤን ከማክበራችን፣ ሥጋና ደሙን ከመቀበላችን በፊት በጾምና በጸሎት ዝግጅት የምናደርግበት በመሆኑ የመዘጋጃ ጾም ተብሏል፡፡

የሥራ መጀመሪያ ጾም
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ሥጋ ለብሶ በምድር ሳለ ስብከት፣ ተዓምራት ከመጀመሩ በፊት የጾመው ጾም ነውና የሥራ መጀመሪያ ጾም ይባላል።

ሼር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🎬  🛑ሁሉም ይስማ! አሳ በጾም ወቅት ይበላል ወይስ አይበላም? ምንድን ነው ማስረጃው? ከምንስ የመጣ ጥያቄ ነው?
👤 ዝማሬ ዳዊት ቲዩብ

⚠️ ትምህርቱን ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!
https://youtu.be/CdFJrQM8DyI
https://youtu.be/CdFJrQM8DyI

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

✝✝✝ምሥጢረ ሥጋዌ✝✝✝


አሁን ደግሞ ምሥጢረ ሥላሴን ከእዚህ በፊት ከእኛ ጋር ተምራችሁ ምሥጢረ ሥጋዌ ላለፋችሁ እህት ወንድሞቻችን ምሥጢረ ሥጋዌን እንልካለን ተከታተሉ።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

አምስቱ አእማደ ምሥጢራት መግቢያ ፩

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ምሥጢረ ጥምቀት መግቢያ
👉ለምን ምሥጢር ተባለ
👉ወንዶች በ40 ሴቶች በ80 ቀን ለምን ይጠመቃሉ? መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ሁላችሁም Subscribe አድርጉ አሁን!

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

Hadafe_nefese" rel="nofollow">https://youtube.com/@Hadafe_nefese

ሠላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን እያልን ከላይ የላክንላችሁ የዩቲዩብ ቻናላችን። Warning ወይም ማስጠንቀቂያ ላይ ይገኛል።

ለ1000 ሰብስክራይበር 40 ሰዎች ብቻ ነው የቀሩት እናም deadline የቀረው አንድ ሳምንት ስለሆነ እዚህ ዩቲዩብ ላይ በመግባት

🙏ቻናሉን subscribe ብቻ በማድረግ ከማስጠንቀቂያ ታስወጡት ዘንድ እንጠይቃለን።

ሁላችሁም አሁን ሊንኩን በመጫን ወደ ዩቲዩብ በመግባት "ኀዳፌ ነፍስ" የሚለውን ቻናል subscribe ብቻ አድርጉት።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🎬  🛑 በዐቢይ ጾም ይህንን ማድረግ በጣም ከባድ ነው እስከ ውግዘትም ያደርሳል! ሁላችሁም መስማት ይኖርባቹሀል!
👤 ዝማሬ ዳዊት ቲዩብ

⚠️ ከስር ባስቀመጥነው LINK ይመልከቱ!
https://youtu.be/D1bTSYbnGaM
https://youtu.be/D1bTSYbnGaM

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ድንግል ማርያም ብዬ

ድንግል ማርያም ብዬ
ስማጸን በስምሽ (፪)
በቅድመ እግዚአብሔር
ልመናዬን አድርሽ (፪)

እኔ ደካማ ነኝ ኃጢአቴ የበዛ
እኔ ጎስቋላ ነኝ በደሌ የበዛ
ጊዜዬን ያባከንኩ በዋዛ ፈዛዛ
ጊዜዬን ያሳለፍኩ በከንቱ በዋዛ

እመብርሃን ስልሽ ፈጥነሽ ድረሽልኝ(፪)
ልመናዬን ሰምተሽ ቆመሽ ለምኝልኝ
ኃጢአቴ ቢበዛም ይዣለሁ አንቺን(፪)
አስምረሻልና በላዒ ሰብን
አዝ
አንገት የሚያስደፋ በዝቶብኝ ኃጢአቴ
ምልጃሽን ፈለኩኝ ድንግል ሆይ እናቴ
ያን ክፉ ጨለማ እንዳላይ አደራ(፪)
ድንግል ሆይ ከልይኝ ከዲያብሎስ ጭፍራ
አዝ
እመብርሃን እያልኩ ቆሜ ከደጅሽ
በብርሃን እጆችሽ እንባዬን አብሽ
ዓለም አታላይ ነች ወደሷ ተሳብኩኝ
ታማልጂኝ ብዬ አንቺኑ ተራብኩኝ

ሊቀ መዘምራን
ኪነጥበብ ወልደቂርቆስ

"ጻድቃን እኔን ይጠብቃሉ"
መዝ፻፵፩፥፯

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

https://youtu.be/1NKzUoqtucs

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ስለ ምሥጢረ ሥጋዌ ደግሞ ከተላከው ትምህርት ላይ የተውጣጣ ጥያቄ ነው መልሱ


👇👇👇👇

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​ዘወረደ

የመጀመሪያ የአቢይ ጾም መግቢያ እሁድ ዘወረደ ይባላል ደግሞም ጾመ ሕርቃል ይባላል፡፡ «ዘወረደ» ማለት «የወረደ» ማለት ነው፡፡ አምላክ ሰው ሆነ፤ ሰው አምላክ ሆነ ማለት ነው። ይህም ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳንና ፍቅሩን ሊገልጽልን ከሰማያት መውረዱን ከድንግል ማርያም የእኛን ሥጋ መዋሐዱን የሚያዘክር፤ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመላክት፣ የሚታወስበት፣ የሚነገርበት የዐቢይ ጾም አንደኛው ሳምንት ነው፡፡ዮሐ.3-13፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ለአዳም በገባዉ ቃልኪዳን መሰረት “ የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ልጁን ላከ”ገላ 4፥4 እንዳለ ሐዋርያዉ ቅዱስ ጳዉሎስ የጠፋዉን አዳም ፍለጋ ከአባቱ እሪና ሳይጎድል ሳይለይ ከሰማይ መዉረዱን የምናዘክርበት በዓል ነዉ።

ይህ ጾም የጾም መግቢያ የመጀመሪያ ሳምንት የምንጾመው ጾም ሲሆን ሕርቃል የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ለአዳም “ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ በመልዕልተ መስቀል ተሰቅየ አድንኃለሁ” ብሎ ለአዳም ቃል ገባለት ፡፡ ዘፍ. ፫ ፥ ፲፭ ይህ ኪዳነ አዳም ይባላል ፡፡ የቃል ኪዳን ሁሉ መሠረት ነው፡፡

ሁለቱን ኪዳናት (ብሉይ ወሐዲስ) በፅኑዕ ተስፋ ያስተሳሰረ የረጅም ዘመናት የድኅነት ሰንሰለት ነው ፡፡ ዘወረደ እርቀ አዳም ፤ ተስፋ አበው ፤ ትንቢተ ነቢያት ፤ ሱባኤ ካህናት መፈፀሙ ፤ ኪዳነ አዳም መሲህ መወለዱ የሚነገርበት የፍቅር አዋጅ ነው። እኛም በዚህ በአብይ ፆም የለመነውና የጠየቅነው ነገር ሁሉ ከኃጢአት በስተቀር እንዲከናወንልን ፆምን ገንዘባችን እናድርግ።

በተለይ አሁን በቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሰ በሚታየው አስቸጋሪ ፈተና እያንዳንዳችን ልባዊ ፆም በመፆም ልዑል እግዚአብሔር የፀሎታችንን ምላሽ እንዲሰጠን እንማፀን።

ጾም ጸሎታችን የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ይቀበልልን አሜን፡፡

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

https://youtu.be/ZV7iwQS8mEk

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

 ✞ ዘወረደ
"በእርሱ ፍቃድ"

በእርሱ ፍቃድ በአባቱ ፍቃድ
በመንፈስ ቅዱስ ፍቃድ
ከሰማያት ወረደ
ከድንግል ማርያም ተወለደ

ዓለሙን እንዲሁ ወደደና
ከሰማያት በላይ ወረደና
በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት
ተወሰነ አምላከ አማልክት
ከሰማያት የወረደው
ፍቅር ስቦት የመጣዉ
ወልደ አብ ወልደ ማርያም
ኢየሱስ ፈራጅ ነዉ
አዝ
ቅድመ ዓለም ተወልዶ ያለ እናት
ድህረ ዓለምም ያለ አባት
የእግዚአብሔር ልጅ በእርግጥም ሰው ሆነ
ሁሉ በእርሱ ይኸው ተከናወነ
ከሰማያት የወረደው
ፍቅር ስቦት የመጣዉ
ወልደ አብ ወልደ ማርያም
ክርስቶስ አምላክ ነዉ
አዝ
የማይታይ ታየ በምድር
ረቂቁ ገዘፈ ስለፍቅር
ሥጋን ተዋህዶ ሆነልን ፈውስ
አማኑኤል የነገስታት ንጉሥ
ከሰማያት የወረደው
ፍቅር ስቦት የመጣዉ
ወልደ አብ ወልደ ማርያም
እግዚአብሔር እርሱ ነዉ
   
ዲ/ን ቀዳሜጸጋ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​​​ዐቢይ ጾም

ዐቢይ ለምን ተባለ ቢሉ ‹‹ዐበየ›› ማለት ከፍ አለ ማለት ሲሆን ከዚህም ግስ አቢይ የሚለው ቅጽል ይገኛል፡፡ ዐቢይ ማለት ከፍ ያለ ትልቅ ማለት ነው፡፡

ዐቢይ ጾም የተባለበት ምክንያት፡-

. ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ጾም ስለሆነ

. በቀኑ ቁጥር ከሌሎች አጽዋማት የሚበልጥ ስለሆነ

. ሦስቱ ታላላቅ የሰይጣን ፈተናዎች ማለትም 'ትዕቢት' 'ስስት' 'ፍቅረ ነዋይ' ድል የተመቱበት ስለሆነ ነው፡፡

በቤተክርስቲያን ስያሜ መሰረት በዐቢይ ጾም ውስጥ የሚውሉ ሰንበታት እያንዳንዳቸው መጠሪያ ስም ሲኖራቸው እነርሱም፡-

1. ዘወረደ
የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሰንበት ሲሆን ይህም ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን ፈጥሮ የሚኖር አልፋና ኦሜጋ ከሰማየ ሰማያት መውረዱንና ከእመቤታችን ከቅድስተ ቅዱሳን ከንጽሕተ ንጹሐን ከድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመለክት ሥያሜ ነው፡፡

2. ቅድስት
ይህ የሁለተኛው ሰንበት ስያሜ ሲሆን የተባለበትም ምክንያት ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ስለሚያወሳ ነው፡፡ እንዲሁም ይህ ዕለት ዕለተ እግዚአብሔር የተባለች የሰንበት ክርስቲያን ቅድስናን ያመለክታል ምክንያቱም የዚች ዕለት ጌታ እርሱ ቅዱስ እግዚአብሔር ነውና ስለዚህም ዕለተ ሰንበት ቅድስት ተብላለች፡፡

3. ምኩራብ
ይህ የሦስተኛው ሰንበት ስያሜ ሲሆን በዚህ ሰንበት ጌታ በመዋዕለ ትምህርቱ በምኩራብ ገብቶ ማስተማሩ ይነገራል፡፡ እንዲሁም ይህች ዕለት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ ገብቶ እንዳስተማረ የሚታሰብበት ዕለት ነው፡፡ ምኩራብ ማለት የቤተ አይሁዳውያን የጸሎት ቤት ነው፡፡

4. መጻጉዕ
ይህ የአራተኛው ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ድውያንን መፈወሱ እውራንን ማብራቱ ለምጻምን ማንጻቱ ሽባዎችን መተርተሩ የሚያነሳ መዝሙር የሚዘመርበት እንዲሁም እነዚህ ሁሉ ድንቅ ገቢራተ ታምራቶች የሚዘከሩበት ዕለት ነው፡፡

5. ደብረ ዘይት
ይህ የአምስተኛው ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሆኖ ነገረ ምጽአቱን እንዳስተማረ የሚወሳበት ሰንበት ነው፡፡ ደብረ ዘይት ማለት ወይራ የበዛበት ተራራ ማለት ነው፡፡

6. ገብርኄር
ይህ የስድስተኛው ሳምንት ሰንበት ስያሜ ሲሆን ይህም ዕለት ለጌታው ታማኝና በጎ የሆነው ባርያ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ ተብሎ እንደተመሰገነ የሚነገርበት ዕለት ነው፡፡

7. ኒቆዲሞስ
ይህ የሰባተኛው ሰንበት ስያሜ ነው፡፡ ይህም ዕለት ኒቆዲሞስ የተባለው የአይሁድ መምህር በሌሊት ወደ ጌታው ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ እየመጣ ይማር እንደነበረ ይታሰብበታል በዚም ዕለት የኒቆዲሞስን ታሪክ የሚያስታውስ መዝሙር ይዘመርበታል፡፡

8. ሆሳዕና
ይህ የስምንተኛው ሳምንት ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት በነቢዩ በዘካርያስ ላይ የተጻፈው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ጌታችም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያይቷ እና በውርንጭላይቷ ላይ ተቀምጦ ሆሳዕና በአርያም ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ ተብ እየተመሰገነ ወደ ቤተ መቅደስ መግባቱ የሚተሰብበት ዕለት ነው፡፡ ሆሳዕና ማለት ‹‹እባክህ አሁን አድን አሁን ባርከን›› ማለት ነው፡፡ በሰሙነ ሕማማት ጸሎተ ፍትሃት ጸሎተ አስተስርዮ ስለማይፈጸም ጸሎተ ፍትሃትና አስተስርዮ የሚደረገው በዚሁ ዕለት ነው::

ጾሙን የበረከት ጾም ያድርግልን፡፡

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

https://youtu.be/1XgZf6hq8bs

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

⚠️ማስታወሻ⚠️


እነዚህን አምስቱን አእማደ ምሥጢራት በጽሑፍ ለማንበብ ከፈለጋችሁ ማኅበረ ቅዱሳን ያዘጋጀውን ትምህርተ ተዋህዶ የሚባል አፕሊኬሽን በመጫን ትምህርቱን በእዛ ተከታተሉ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ስለ ምሥጢረ ሥላሴ በእዚህ አይነት መልኩ አጠናቀናል።

ጥያቄ ካላችሁ ያልገባችሁ ነገር ካለ

@zmaredawit_messengerbot

በዚህ ውስጥ በመግባት ጥያቄያችሁን ልትልኩልን ትችላላችሁ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን✝

የተወደዳችሁ የዝማሬ ዳዊት ተከታታዮች ዛሬ ተከታታይ ትምህርታችንን ክፍል ሁለት እንጀምራለን።

👉 ዛሬ ለማየት የምንሞክረው ርዕስ ምሥጢረ ሥላሴ ይሆናል።

ስለዚህ ባለፈው በላክንላችሁ ትምህርተ ተዋሕዶ በሚባለው አፕሊኬሽን በመክፈት አእማደ ምሥጢራት የሚለውን አምድ በመክፈት ምሥጢረ ሥላሴን ታነቡ ዘንድ እንጠይቃለን።

አሁን ስለ ምሥጢረ ሥላሴ ማጠቃለያ ትምህርት በድምጽ የምንልክ ይሆናል ተከታተሉ።

ይህንን መልእክት ያያችሁ እና ለመማር እና ለማዳመጥ ዝግጁ የሆናችሁ

👍 ይህንን ምልክት ላኩልን

Читать полностью…
Подписаться на канал