ortodoxmezmur | Неотсортированное

Telegram-канал ortodoxmezmur - ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

134932

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . ዝማሬ ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Подписаться на канал

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እንኳን ለብርሐነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን! መልካም በዓል ይሁንላችሁ ።

📍 አ.አ መስቀል አደባባይ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እንኳን ለብርሐነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን! መልካም በዓል ይሁንላችሁ ።

📍 አ.አ ጎፋ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እንኳን ለብርሐነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን! መልካም በዓል ይሁንላችሁ ።

📍 በመቂ ከተማ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

መስቀል አብርሃ በከዋክብት አሠርገወ ሰማየ፤ መስቀል አበራ ሰማይም በከዋክብት ደመቀ።
እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሰን! አሜን🙏

📍 ሞጆ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እንኳን ለብርሐነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!
📍 ምስራቀ ጸሐይ ቅድስት ኪዳነ ምህረት እና ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

መስቀል አበራ

መስቀል አበራ ሰማይን አስጌጠ
በብርሃኑ ፀዳል ምድር ተለወጠ
ፀሐይን አሳየ ከሁሉም በላይ
ተዓምሩ ድንቅ ነው በምድር በሰማይ

አዝ

የመስቀሉን ነገር ለማያምኑት ሁሉ
ሞኝነት ነው እና እንዳለ በቃሉ
መስቀሉን ፍለጋ እሌኒ ተነሳች
ከተቀበረበት ከቦታው ደረሰች
አዝ

ለሦስት መቶ ዓመታት የተቀበረውን
በቆሻሻ ብዛት ተራራ የሆነውን
ኪራኮስ ነገራት የመስቀሉን ነገር
የደመራው እና የእጣኑን ምስጢር
አዝ

እጣንን አጢሳ ደመራን ደምራ
ማስቆፈር ጀመረች ታላቁን ተራራ
የግራውን መስቀል ቀድማ ብታገኘው
ህሙማን አምጥታ ፈትና ተወችው
አዝ

ሙት የማያስነሳ ህሙማን የሚያድን
መስቀልን አገኘች ሁለተኛውን
በደስታ መንፈስ ቁፋሮን ቀጠለች
ይህን ያሳያትን እያመሰገነች
አዝ

ብርሃን ተሞልቶ ሦስተኛውም መስቀል
ከተቀበረበት ወጣ በታላቅ ኃይል
ሙታንም ተነሱ ድውይ ተፈወሰ
በክርስቶስ መስቀል ዓለም ተቀደሰ
አዝ

ጥልን በመስቀሉ ገደለ (2)
በመስቀሉ ለሰው ልጅ ሰላምን አደለ(2)
አዝ

አማን በአማን(2)
መስቀል ብርሃን ለኩሉ ዓለም መሰረተ ቤተክርስቲያን(2)
አዝ

እውነት በእውነት(2)
መስቀል ብርሃን ነው ለመላው ዓለም መሰረት ነው የቤተክርስቲያን (2)

ዘማሪ ዲያቆን ቀዳሜጸጋ ዮሐንስ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እንኳን ለብርሐነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!
📍 በምዕራብ አርሲ ዶዶላ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

መስቀል

ዮም በዓለ መስቀሉ በሰማያት በላዕሉ(2)
ወዘነግሠ በምድር ( 2) ለአሕዛብ(2)

አዝ

የተዋሕዶ ሰንደቅ የሃይማኖታችን አምድ
መስቀል እፀ ሕይወት መርህ እና መንገድ
ጋሻ መመከቻ የዲያቢሎስን ፆር
መመልከቻችን ነው የገነት ደጅን በር
መስቀሉሰ ለክርስቶስ
ብርሃን እለ እለ ነአምን
ትብል ቤተክርስቲያን
(2)
ዛሕኑ ለባሕር ወመርሶ ለአሕማር
ዝንቱ ውእቱ መስቀል
(2)
አዝ

ርስተ ቤተክርስቲያን ዋልታ ጉልላቷ
ውበትና ጌጥ ነው አለት መሰረቷ
የኃጢዓትን ባህር ከፍለን ያለፍንበት
መስቀል በትረ ሙሴ ጥል የተሻረበት
መስቀል ብርሃን ለኵሉ ዓለም
መሠረተ ቤተክርስቲያን
  (2)
ወሐቤ ሰላም መድኃኔዓለም
መስቀል መድኅን ለእለ ነአምን
(2)
አዝ

የብርሃን አውታር የጽድቅ በር መግቢያ
ለተዋህዶ ልጆች ማህተም መለያ
የሕይወታችን ቅጥር ከጠላት መሸሻ
መስቀል ከለላ ነው በደልን ድል መንሻ
መስቀል ኃይልነ መስቀል ጽንዕነ
መስቀል ቤዛነ
( 2)
እኸ መድኃኒትነ ለእለ አምነ(2)
አዝ

የአዳም ዘርን ወዶ ጌታ የዋለበት
ዲያቢሎስ ተዋርዶ እርቅ የተገኘበት
ለክርስቲያን ወደብ አርማና ምልክት
መስቀል አመልካች ነው የክርስቶስን ሕይወት
ጸጋ ነሳይነ ወሕይወተ ረከብነ
በኃይለ መስቀሉ ለኢየሱስ ክርስቶስ
በኃይለ መስቀሉ
(2)
ኪያከ እግዚኦ ነአኲት ወንሴብሐከ እግዚአብሔር (2)
አዝ

ጸጋን ተቀበልን ሕይወትንም አገኘን
በመስቀሉ ኃይል በኢየሱስ ክርስቶስ
በመስቀሉ ኃይል
(2)
አቤቱ አንተን(2)እናመሰግንሃለን እግዚአብሔር
አቤቱ አንተን ቅዱስ(2)እናመሰግንሃለን ቅዱስ እግዚአብሔር(2)

ዘማሪ ዲ/ን ዘለዓለም ታከለ(ዘጎላ )
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​የደመራው ምሥጢር
በሊቀ ሊቃውንት ስምዐኮነ መልአክ

እግዚአብሔር አምላካችን የሠራቸው ታላላቅ ሥራዎች በምልክት የተገለጡ ናቸው፤ ለምሳሌ የሙሴ መስፍንነት፣ የአሮን ሊቀ ካህንነት የተረጋገጠው በአሮን በትር ምልክትነት ነው፡፡ አብርሃም ልጁ ይስሐቅን ሊሠዋ በታዘዘ ጊዜ የሞርያን ተራራ የመረጠው እግዚአብሔር በተራራው ላይ ካሳየው ብርሃን የተነሣ ነው፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያምና ቅዱስ መስቀልም የድኅነታችን ምልክቶች ናቸው፡፡ የአሮንና የሙሴ በትሮች፣ የይስሐቅ ቤዛ የሚኾን በግ የተገኘባት ዕፀ ሳቤቅ ደግሞ የእመቤታችንና የመስቀል ምልክቶች ነበሩ፡፡ ወደ ፊት የምንወርሰው መንግሥተ ሰማያት ክርስቶስ ነው፤ እርሱን ደግሞ ያገኘነው ከመስቀል ላይ ነው፡፡

ጥንተ ጠላት ሰይጣን ይህንን ስለሚያውቅ ቅዱስ መስቀሉን አጥብቆ ይቃወመዋል፤ ስለዚህም አይሁድን አነሳሥቶ ከ፫፻ ዓመታት በላይ ተቀብሮ እንዲቆይ አድርጓል፡፡ በመሠረቱ ለሰይጣን ምሥጢሩ ስለማይገባው ነው እንጂ የመስቀሉ ትክክለኛ መቀበሪያ ሥፍራ የምእመናን ልቡና ነው፡፡ ቀራንዮ ለመስቀሉ መትከያነት የተመረጠችውም ቀዳሜ ፍጥረት አዳም የተቀበረው በዚያ ስለ ነበረ ነው፡፡ ቦታው ‹‹የራስ ቅል ሥፍራ›› /ማቴ.፳፯፥፴፪/ መባሉም የኹላችን ራስ አዳም ዓፅሙ በዚያ ስላረፈ ነው፡፡ መስቀሉ በአዳማውያን ፍጥረታት አእምሮ ውስጥ እንጂ ከዚያ ውጪ የሚኖር ባለመኾኑ ተቀብሮ በቆየባቸው ዓመታት ውስጥም ፍቅሩ ከሰው ልጆች ልቡና አልወጣም፡፡

ጠላት በሠራው ተንኮል ተቀብሮ እንዳይቀር መስቀሉን እንድታወጣ መንፈስ ቅዱስ ንግሥት ዕሌኒን አስነሣት፡፡ ይህች ሴት ቤቷ በሀብት፣ በንብረት ሞልቶ በነበረበት ጊዜና በገረድ፣ በደንገጡር በምትንቀሳቀስበት ወቅት ምን እንደ ሠራች አልተመዘገበላትም ነበር፤ ከክብሯ ወርዳ በተጣለችበት ጊዜ ግን እግዚአብሔር ለሚፈልገው ሥራ ምቹ ኾና ተገኘች፡፡ እርሷ በተጣለችበት ባዕድ አገር ውስጥ ኾና የመስቀሉን ነገር ታስብ፤ ብርሃነ መስቀሉም ዘወትር በልቧ ያንጸባርቅ ነበር፡፡ ሐሳቧን እንዲያሳካላት የለመነችው አምላክም ኪራኮስ የተባለውን አይሁዳዊ ሽማግሌ ልኮ አቅጣጫውን አመላከታት፤ ኪራኮስ የጀመረውን ምሥጢርም መልአኩ ‹‹ደመራ ደምረሽ፣ ሰንድሮስ የሚባል ነጭ ዕጣን ጨምረሽ አቃጥዪው›› ብሎ ተረጐመላት፡፡ እርሷም መልአኩ እንደ ነገራት ብታደርግ ጢሱ ሰማይ ደርሶ ወደ ምድር ተመልሶ መስቀሉ ወደሚገኝበት ተራራ ሰገደ፡፡ በጢሱ ምልክትነት መስከረም ፲፯ ቀን የተጀመረው ቍፋሮ መጋቢት ፲ ቀን አልቆ ዕሌኒ መስቀሉን ከልበ ምድር ለማውጣት ችላለች፡፡

መስቀልና ደመራ እንዲህ ነበር የተገናኙት፡፡ ደመራው ለመስቀሉ መገኘት፣ መስቀሉም ለደመራው መሠራት ምክንያት ናቸው፡፡ በዚህ አንጻር መለኮትና ትስብእት በአንድነት መደመራቸው መስቀሉ እንዲሠራ ምክንያት ኾነዋል፡፡ አምላካችን ሥጋ ለብሶ ‹ክርስቶስ› በሚል የተዋሕዶ ስም ሲጠራ ለመከራ መዘጋጀቱን እንረዳለን፡፡ መስቀሉ የሥጋ ብቻ ነበረ፤ አሁን ግን መለኮትም በሥጋ ባሕርይ የመስቀሉ ተካፋይ ኾነ፡፡ ይህም የደመራው ውጤት ነው፡፡ መለኮት አምስት ሺሕ ከአምስት መቶ ዘመን መስቀል የተሸከመ ሥጋን ሲዋሐድ መስቀሉን አስወግዶ አልነበረም፡፡ ይኸው በዕፀ በለስ ምክንያት የተሸከምነው መስቀል ነው፡፡ ሥጋ ዓቅም አጥቶ መስቀሉን ከትከሻው ላይ ሳያወርድ ለዘመናት የተጓዘውን ጕዞ መለኮት ኀይል ኾኖት ድካሙን ሳይለቅ ኀያል፤ ኀይሉን ሳይለቅ ደካማ ኾነ፡፡ መስቀል ትርጕሙ መከራ ቢኾነም ነገር ግን እግዚአብሔር ሲያመጣውና ሰው ሲያመጣው ግን ትርጕሙ ይለያያል፤ ሰው ያመጣው መስቀል ኹላችንን ለመከራ፣ ለሞት አሳልፎ ሰጥቶናል፡፡ የእግዚአብሔር መስቀል ግን መከራነቱ ለሰይጣን እንጂ ለእኛ ሕይወታችን ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድም ‹‹መስቀል ብሂል ዕፀ ሕይወት ብሂል፤ መስቀል ማለት የሕይወት ዛፍ ማለት ነው›› በማለት የመስቀልን ትርጕም ነግሮናል፡፡

አዳም ከገነት ሲወጣ በመላእክት እንዲጠበቅ የተደረገው የሕይወት ዛፍ የክርስቶስ መስቀል ነው፡፡ በዕፀ በለስ ምክንያት ኹላችንም እንደ ተጎዳን በዕፀ ሕይወቱም ተጠቃሚዎች ኾነናል፤ አስቀድመን በአዳም መከራ እንደ ተባበርን አሁን ደግሞ በደስታው እንተባበራለን፡፡ ሞትም ሕይወትም አንድ አድርጎናል፡፡ የክርስቶስ መስቀል ኹሉንም በሕይወት አስተባብሯልና፡፡

በአንጻሩ ሰውና ዲያብሎስን ለያይቷል፡፡ የኀጢአት ቁራኝነትን አጥፍቷል፡፡ ጌታችን በማኅፀን ሲፀነስ ጀምሮ የእኛን መስቀል መሸከም ሲጀምር የእርሱ የኾነውን ለእኛ ስለ ሰጠን ከሰይጣን ጋር መለያየታችን በመስቀሉ ተረጋግጧል፡፡ የአምላካችን መስቀል ምልክቱ ደመራ መኾኑ የእኛን ወደ እርሱ መሰብሰብና የጠላታችንን መበተን የሚያረግጥልን ነው፡፡ ጌታችንም ‹‹ወብየ ካልዓትኒ አባግዕ እለ ኢኮና እምዝንቱ ዐፀድ ወኪያሆንሂ ሀለወኒ አምጽኦን ዝየ፤ ከዚህ በረት ያልኾኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱንም ላመጣቸው ይገባኛል›› በማለት ሊሰበስበን እንደ መጣ ነግሮናል /ዮሐ.፲፥፲፮/፡፡ መስቀሉ ፍጥረት አንድ ደመራ ኾኖ የተሠራበት ስለ ኾነ በደመራ እንዲገለጥ የእግዚአብሔር ፈቃዱ ኾነ፡፡
መስቀሉ አንድ ደመራ ያደረጋቸው ፍጥረታት

፩. ነቢያትና ሐዋርያት

ነቢያት የሚባሉት ከአዳም እስከ ዮሐንስ መጥምቅ ያሉ አባቶች ሲኾኑ፣ ከክርስቶስ ደቀ መዛሙርት ጀምሮ ለቤተ ክርስቲያን የወንጌልን የምሥራች እንዲነግሩ የተላኩ አባቶች ደግሞ ሐዋርያት ይባላሉ፡፡ በእርግጥ ሐዋርያ የኾነ ነቢይ የለም እንጂ ነቢይ የኾነ ሐዋርያ አለ፡፡ ነቢያትና ሐዋርያት በዘመን፣ በክብር እና በግብር የማይገናኙ ፍጥረታት ናቸው፡፡ መንፈሰ ረድኤት የተሰጣቸው ነቢያት ለሐዋርያት የተሰጠውን መንፈሰ ልደት ለማግኘት አልተቻላቸውም፡፡ ሐዋርያት ግን ኹሉንም አንድ አድርገው ይዘዋል፡፡ ለዚህም ነው ሐዋርያው ስለዚህ ሲመሰክር ‹‹በጸጋ ላይ ጸጋ ተሰጠን›› በማለት አጕልቶ የተናገረው /ዮሐ.፲፥፲፰/፡፡ ነቢያት በዚህ ምድር የእግዚአብሔርን መንግሥት በመፈለግ ብዙ ደክመዋል፡፡

ሊቃውንቱ ነቢያትን በክረምት፣ ሐዋርያትን በበጋ ገበሬ ይመስሏቸዋል፡፡ የክረምት ገበሬ ላዩ ውሃ፣ ታቹ ውሃ ኾኖበት በጭቃ ወጥቶ በጭቃ ይመለሳል፡፡ ወደ ቤቱ ሲገባም ሚስቱ ጨምቃ ያቆየችለትን ጐመን በልቶ ደስ ሳይለው ይተኛል፡፡ ነቢያትም በዚህ ዓለም በጣዖት አምላኪ ነገሥታት፣ በነቢያተ ሐሰት ስብከት ሲንገላቱ ኖረው ሲሞቱም ሲዖል ይገባሉ እንጂ ገነትን አይወርሱም ነበር፡፡ የበጋ ገበሬ በደረቅ ወጥቶ፣ እሸት በልቶ፣ ተደስቶ ወደ ቤቱ ይመለሳል፤ ከቤቱ ሲገባም እንጀራው በሌማት፣ ጠላው በማቶት፣ ሲቀርብለት ደስ ብሎት ይበላል፤ ይጠጣል፡፡ ሐዋርያትም ልጅነትን አግኝተው ለማስተማር ተልከዋል፤ በሔዱበት ኹሉ ተአምራትን እንዲያደርጉ፣ ልጅነትንም እንዲሰጡ ሥልጣን ተሰጥቷቸዋል፡፡ ሞታቸው ሲደርስም መንግሥተ ሰማያት ተከፍቶ ይጠብቃቸዋል፡፡

ይቀጥላል!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

መስቀሉ አበራ
ውድ የዝማሬ ዳዊት ቤተሰቦች እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሰን።

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

መስከረም  ፲፮


በዚች ቀን በኢየሩሳሌም አገር ንግሥት ዕሌኒ የገለጠቻቸው የከበሩ ቦታዎች ሁሉ የተሠሩበትና የከበሩበት ሆነ ።

ቆስጠንጢኖስ ከነገሰ በኋላ እናቱ ቅድስት ዕሌኒ ልጄ ሆይ እኔ ወደ ቅድስት አገር ኢየሩሳሌም በመሔድ የክርስቶስን ዕፀ መስቀል ፈልጌ አወጣ ዘንድ ለእግዚአብሔር ስዕለትን ተስያለሁ አለችው ።

ቆስጠንጢኖስም ሰምቶ ደስ አለው ብዙ ሠራዊትና ገንዘብ ሰጥቶ ላካት። ኢየሩሳሌምም በደረሰች ጊዜ ከከበሩ ቦታዎች ተባረከች ። ከዚህም በኋላ የከበረና አዳኝ  የሆነ የክርስቶስን ዕፀ መስቀል ከብዙ ፍለጋ በኋላ አገኘች እግዚአብሔርንም አመሰገነች።

ከዚህም በኋላ በጎልጎታ፣ በቤተልሔም፣ በጽርሐ ጽዮን፣ በጌቴሴማኔ፣ በደብረ ዘይት እና በከበሩ ቦታዎች ሁሉ በዕንቁ በወርቅና በብር የቤተ መቅደስ መሠዊያዎች እንዲሠሩ አዘዘች።

ጻድቅ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስም በነገሠ በ፴ ዓመቱ የከበሩ ቦታዎች ሕንፃቸው በተፈጸመ ጊዜ ለቁስጥንጥንያ፣ ለአንጾኪያ፣ለእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ኤጲስቆጶሶቻቸውን በመያዝ ሁሉም በኢየሩሳሌም የታነፁትን አብያተ ክርስቲያናት እንዲያከብሩ አዘዘ። ንጉሡም እንዳዘዘ ሁሉም ተሰበሰቡ የቁርባን ቅዳሴንም ቀድሰው ለምእመናን ሥጋውንና ደሙን አቀበሉ በዚችም ቀን ከቶ እንደርሱ ሆኖ የማያውቅ ታላቅ ደስታ ሆነ።

የቅዱሳን በረከታቸው ይደርብን! አሜን!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ሰላም ውድ የዝማሬ ዳዊት ቤተሰቦች እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ።

አምና እንዳደረግነው ዘንድሮም በየ አካባቢያችሁ የደመራ በዓልን በምን መልኩ እያከበራችሁ እንደሆነ ጥራት ባለው ፎቶ ከእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ጋር በማድረግ በ 📩 @Zimaredawitmessanger ብትልኩልን፣ ለመላው የዝማሬ ዳዊት ቤተሰብ እናደርሳለን።

መሟላት ያለባቸው

1. በስልካችሁ ፎቶ ስታነሱ ጥራት ባለው መልኩ (ጥራቱ በቂ ካልሆነ አይለቀቅም)
2. የአካባቢውን (ቦታ) ስም መግለጽ
3. ስርዐቱን የጠበቀ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት።

ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን! መልካም በዓል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

መስቀል ቤዛነ

መስቀል ኃይልነ መስቀል ፅንዕነ
መስቀል ቤዛነ መድኃኒትነ
የዓለም ቤዛ (3) ለእኛ
ሰጠን መዳኛ (2)

አዝ

ከሰማያት (2) ወርዶ
ከድንግል ማርያም ተወልዶ
ጨለማውን ገፎ ብርሃን አሳይቶናል
የመስቀሉን ፍቅር ለእኛ ገልጦልናል
አዝ

እንደ ሄዋንማ እንደ አዳም ስህተት
ነበርን በግዞት ቤት ገሃነመ እሳት
የአዳምን እንባ ለቅሶ ተመልክቶ
ዓለምን አዳነ በመስቀል ላይ ሞቶ
አዝ

ፃድቃን ሰማዕታት የሰማይ መላእክት
ዘወትር በምስጋና ቅኔ የሚቀኙለት
አልፋ እና ኦሜጋ የሚኖር ዘለዓለም
የመስቀሉ ንጉስ ጌታ መድኃኔዓለም

ዘማሪ ሰሎሞን በዜ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እሰይ እልል በሉ

እሰይ እልል በሉ ተገኘ መስቀሉ (2)
እሰይ እልል በሉ ተገኘ መስቀሉ (2)

አዝ

የጥል ግድግዳ አበባ
የፈረሰበት አበባ
ሰው ከእግዚአብሔር ጋር  አበባ
የታረቀበት አበባ
የእግዚአብሔር ልጅ አበባ   
የነገሰበት አበባ
የሞት አበጋዝ  አበባ      
የወደቀበት አበባ
አዝ

አይሁድ በቅናት አበባ         
መስቀሉን ቀብረው አበባ
ቢከድኑት እንኳን አበባ
በቆሻሻቸው አበባ
ጌታን መቃወም አበባ
ስለማይችሉ አበባ
ይኸው ተገኘ አበባ
ወጣ መስቀሉ አበባ
አዝ

ደጉ ኪራኮስ   አበባ      
ሽማግሌው  አበባ
እሌኒን መራ አበባ
በደመራው አበባ
ጌታ በእርሱ ላይ አበባ
በመሰቀሉ አበባ
ጭሱ ሰገደ አበባ
ወደ መስቀሉ አበባ      
አዝ

የእምነት ምልክት አበባ       
መስቀል ነውና  አበባ
ተራራው ሜዳ  አበባ
ሆነ እንደገና አበባ
እንደተነሳ አበባ
ጌታ እንደቃሉ  አበባ
ከጉድጓድ ወጣ አበባ
ዕፀ መስቀሉ አበባ 
አዝ

እኛም በመስቀል አበባ
እንመካለን  አበባ
በእግዚአብሔር ጥበብ አበባ
መቼ እናፍራለን አበባ
ሞኝነት እንኳን አበባ
ቢሆን ለዓለም አበባ
ኃይል ጸወን ነው አበባ
ለዘለዓለም አበባ
አዝ

ግድግዳው ፈርሷል  አበባ
የልዩነቱ አበባ                          
ምድርና ሰማይ አበባ                 
ሆኑ እንደ ጥንቱ  አበባ                
ነፍስና ስጋ አበባ                     
በእርሱ ታርቀዋል አበባ                
ሕዝብና አሕዛብ አበባ                  
ወንድም ሆነዋል አበባ                   

ዘማሪ ዲ/ን አበበ ታዬ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

መስከረም ፲፭


በዚችም ቀን ጠራው ከሚባል አገር ለከበረ ጻድቅ አባት አባ ጴጥሮስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆነ። ይህም ቅዱስ ከእናቱ ማሕፀን ጀምሮ ለእግዚአብሔር የተሰጠ የስእለት ልጅ ነው። በአደገም ጊዜ ለታላቅ ተጋድሎ ከልቡ በቆራጥነት ተነሣ። በቀንና በሌሊትም በጾም በጸሎት ተወስኖ ሁል ጊዜ እግዚአብሔርን የሚያገለግል ሆነ።

ሰው የሚመገበውንም ምንም አይመገብም በዱር ያገኘውን ጥቂት ሣርን ይመገባል እንጂ። ደገኛው ምግቡ ግን ክብር ይግባውና የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ስም ማመስገን ነበረ። በዚህም ምግባቸው የእግዚአብሔር ምስጋና የሆነ መላእክትን መሰላቸው።

አሎን በሚባል የወንዝ ውኃ ላይም ይመላለስ ዘንድ ውሀ ውስጥ የገቡት እግሮቹ አይርሱም ነበር ሥጋ እንደሌለው መንፈስ እስከሚሆን በሕይወቱ ዘመን ሁሉ ከችግር ብዛትና ከሚለብሰው የብረት ልብስ ክብደት የተነሣ ሥጋው እጅግ ደርቆ የረቀቀም ሁኖ ነበርና በእንዲህ ያለ ተጋድሎም እግዚአብሔርን ከአገለገለው በኋላ በዚህች ቀን በክብር አርፏል።

የቅዱሳን በረከታቸው ይደርብን አሜን!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳቹ🙏

ደቡብ ምዕራብ ~ ከፋ ክልል ~በቦንጋ  ከተማ የመስቀል በዓል አከባበር

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እንኳን ለብርሐነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን! መልካም በዓል ይሁንላችሁ ።

📍 ባህርዳር

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🌼🌼🌼                                       🌼🌼🌼
                            🌼🌼🌼
                            🌼🌼🌼
                 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
                 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
                 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
                            🌼🌼🌼
                            🌼🌼🌼
                            🌼🌼🌼
                            🌼🌼🌼
                            🌼🌼🌼
"ደስ ይበለን እልል በሉ፣
       አልቀረም ተቀብሮ ተገኘ መስቀሉ፣
              በብርሃን መላት ዓለምን በሙሉ"


በዓሉ የደስታ፣ የሰላም የፍቅር እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን፡፡

                           🌼🌼🌼

የአስኮ መካነ ሕይወት ቅዱስ አማኑኤል እና አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ፈለገ ሕይወት ሰንበት ት/ቤት

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

መስቀል አብርሃ በከዋክብት አሠርገወ ሰማየ፤ መስቀል አበራ ሰማይም በከዋክብት ደመቀ።
እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሰን! አሜን🙏

📍 ጌቴሴማኒ ቅድስት ኪዳነምህረት> ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን
አያት ደራርቱ አደባባይ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እንኳን ለብርሐነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን! እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይጠብቅ።
📍 በወላይታ ሶዶ ሀገረ ስብከትና ባሕታ ለማርያም ቤተክርስቲያንን

ትንሽ ስለቦታው :-
እኔ እንግዳ ነኝ ከአ.አ ለስራ ሄጄ ነው ቦታው በተወሰኑ ግለስቦች (ኢ-አማንያን) በሆኑ ሰዎች በልማት አሳበው ደብሯን ለተወሰነ ግዜ ቦታ ተቀይሮ ነው ያለው ህዝቡም ተበታትኖ በዚህ መልኩ ሲያከብሩ እንዲው ድምፅ ከሆናችኋቸው በማለት ነው!! ፈጣሪ ያክብርልኝ መልካም በዓል

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እንኳን ለብርሐነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!
📍 ፈረንሳይ ለጋሲዮን አደባባይ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የደመራ ዓመት


መስቀል የከበረው ትናንት መስሏቸው
ያዩ ተገረሙ ክብሩ አስደንቋቸው
ትናንትና አይደለም የበራው ደመራ
ዘንድሮ ዓመት ፈጀ የመስቀሉ ሥራ

ስንት አይሁድ ተነሥተው መስቀሉን ቀበሩ?
ስንትስ እሌኒዎች ሊያወጡት ቆፈሩ?
ጅጅጋ ሲዳማ ውጡ ተናገሩ

ቤተ ክርስቲያን ልክ እንደ ደመራ
በእሳት ተለኩሳ ደምቃ ስታበራ
ካህናት ምእመናን እንደ ችቦ ነድደው
ስንቴ አከበሩት ለመስቀሉ ታርደው?

ስንት ጊዜ አፏጨ ዲያቢሎስ ተቆጣ
ስንት ሟርት ተሰማ ስንት ቁጣ መጣ?
በዕጣን ያልተገኘ ጌታ ያልሞተበት
ቅርፁ መስቀል ሆኖ መዳን የሌለበት
የወንበዴው መስቀል መስቀሉ መስሏቸው
ስንቶች ትተው ሔዱ ከእሌኒ እናታቸው?

ዓለም የዳነበት መስቀሉን ጨብጦ
ስለዘር የሚሰብክ እጅግ ተመስጦ
የተቃጠለውን መቅደስዋን እያየ
"ራስሽን አድኝ" ሲል ሲስቅ የታየ
ዘንድሮ አይደለም ወይ አይሁዱ የለየ?

ዘንድሮ ከበረ ለአንድ ዓመት ደመራ
በማያቆም ጥቃት በማያቆም ሴራ
ቅድስት ተዋሕዶ በጭንቅ ተወጥራ
አባቶችዋን ከፊት እንደ ጦር ሰድራ
በልጆችዋ ጩኸት በገና ደርድራ

በሰማዕታትዋ ደም ተረጭታና ርሳ
በየአደባባዩ ምሕላን አድርሳ
በፓትርያርክዋ ዓይን በምሬት አልቅሳ
እንደ ራሔል ለአምላክ ዕንባዋን አፍስሳ

ለመስቀሉ ቀን ግን ነጭ ልብስዋን ለብሳ
እንደ ቆስጠንጢኖስ በድል ልትነሣ
አምላክዋን ከፍ አድርጋ ኀዘንዋን ልትረሳ
ተስፋ ያደረገችው በመስቀል ታድሳ

ዘንድሮ ነው በዓል ዘንድሮ ደመራ
በዚህ ዓመት ተገኘን ከመስቀሉ ሥፍራ!!

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
መስከረም 17 2012 ዓ.ም.
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​👆የቀጠለ

ቅዱስ ያሬድም ‹‹ኖትያት ነቢያት ራግናት ሐዋርያት›› በማለት ነቢያትን በዋናተኛ፣ ሐዋርያትን በጀልባ ቀዛፊ መስሎ ይናገራል፡፡ ከቀዛፊዎች ይልቅ ዋናተኞች ይደክማሉ፡፡ ዋናተኞች ውሃው አጥልቋቸው፣ መተንፈስ ተስኗቸው አንዳንዶቹ ከዳር ይደርሳሉ፤ አንዳንዶቹም በድካም በውሃ ውስጥ ሰጥመው ይቀራሉ፡፡ ቀዛፊዎች ግን ምናልባት ሞገድና ማዕበል ካላሰጋቸው በስተቀር ይህ ኹሉ ውጣ ውረድ የለባቸውም፤ በጀልባዋ የተመሰለችው ቤተ ክርስቲያን ለነቢያት በተስፋ እንጂ በአካላ አልተሰጠችም፡፡

ነቢያት ከእርሷ ሳይደርሱ ሞት ቀድሟቸዋል፡፡ ሐዋርያትም በነቢያት ድካም ገብተው ነቢያት የዘሩትን የትንቢት ዘር አጭደዋል፡፡ ወንጌል የነቢያት ዘር ናት፤ ዳሩ ግን ፍሬውን ለመብላት የታደሉት ሐዋርያት ናቸው፡፡ እሸቱ ሲደርስ የገበሬዎቹ የነቢያት ጌታ ክርስቶስ ዘሩን እንዲሰበስቡና እንዲያከማቹ ሐዋርያቱን በእርሻ መካከል ይዟቸው ገብቷል /ማቴ.፲፪፥፩/፡፡ በአበው ፋንታ ውሉድን ለመተካት የመጣው መምህራችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነቢያትንና ሐዋርያትን በመስቀሉ አንድ ማኅበር አደረጋቸው፡፡ ሐዋርያው መስቀሉን ‹‹ገባሬ ሰላም›› በማለት ይጠራዋል /ኤፌ.፪፥፲፫/፡፡ ነቢያትንና ሐዋርያትን አንድ አድርጎ የእግዚአብሔርን መንግሥት ያወረሰ የክርስቶስ መስቀል ነውና፡፡

፪. ሙታንና ሕያዋን

አዳም በዕፀ በለስ ምክንያት የተሸከመው መስቀል ሞትን አምጥቶብናል፤ ክርስቶስ ስለ ሰው ልጆች ድኅነት ሲል የተሸከመው መስቀል ግን ሞትን ገድሎ ሕይወትን ሰጥቶናል፡፡ በዚህ ምክንያት የሞት መውጊያ ሲሰበር፣ የመቃብር ስቃይ ሲቋረጥ፣ የጨለማ ኀይል ሲሻር ከመስቀሉ ሥር ብዙ ሙታን እንደ አሸን ብቅ ብቅ አሉ፡፡ ምድር እስከዚያች ቀን ድረስ ሙታንን ትቀበል ነበር እንጂ ሕያዋንን ማስገኘት አትችልም ነበር፡፡ ሙታንና ሕያዋን የተፈላለጉበት መስቀል የመጀመሪያው ቀን ነው፡፡ በመስቀል ሙታን ሕያዋንን ፍለጋ ከመቃብር ወጥተው ወደ ከተማ ገቡ፡፡ ከታደለው የሕይወት ስጦታ የተነሣ ሞት አካባቢውን ለቆ ስለጠፋ በሩ እንደ ተከፈተለት እሥረኛ ሙታን ከመቃብር እየወጡ ከተማውን ሞልተውታል፡፡ ይህ ዕለት ሙታንን ከሕያዋን ጋር አፍ ለአፍ ያነጋገረ ዕለት ነው፡፡ ደመራው ሙታንን ከሕያዋን የሚለይ አይደለም፤ ታላቅነቱም እስከ ሲዖል ድረስ የሚታይ ነው፡፡

፫. ጻድቃንና ኀጥአን

የአዳም በደል በሕይወት የሚኖሩ ወንድማማቾችን በሁለት ሐሳብ ከፋፍሏቸው ነበር፡፡ የክርስቶስ የጽድቅ መስቀል ግን አንድ ሐሳብ ፈጠረላቸው፡፡ ጻድቁ አቤል ሳይበድል በደል የደረሰበት፣ ሳይገድል የተገደለ መኾኑ ከክርስቶስ ጋር ቢያመሳስለውም ሞቱ ግን ለሰው ልጆች ድኅነት አልጠቀመም፤ የፍጡር ደም ከእግዚአብሔር ጋር ሊያስታርቀን አይችልምና ኹላችንም በመከራ ውስጥ ለመቆየት ተገደናል፡፡

የክርስቶስ ሞት ግን የድኅነታችን መሠረት ኾነልን፡፡ በቤት ውስጥ የሚዘጋጅ መብራት ከፍ ብሎ ሲቀመጥ ኹሉን እንዲያሳይ ከምድር ከፍ ብሎ የተሰቀለው ክርስቶስም ጻድቃነ ብሊትንና ጻድቃነ ሐዲስን በዓይን እንዲተያዩ አድርጓቸዋል፡፡ በመስቀል ላይ የተፈጸመው ዕርቅ የኀጥአንን በደል ደምስሶላቸዋል፤ የጻድቃንን ጽድቅ አረጋግጦላቸዋል፡፡ ጻድቃንም ኀጥአንም አንድ ኾነው መንግሥቱን በጸጋው ወረሱ፡፡

ኢያሱ በኢያሪኮ እንዳደረገው አሞራውያን ወጥተው እስራኤል ብቻ ምድሪቱን የወረሷት አይደሉም፡፡ መስቀሉ ለኹሉም አንድ መንግሥትን አውርሷቸዋል፤ ጊዜው የደመራ ነውና፡፡ በምድር ደምቆ የታየው ይህ ደመራ እስከ መንግሥተ ሰማያት ድረስም ይቀጥላል፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
Share አድርጉት ሌላውም እንዲማርበት።
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

መስቀል ብርሃን

ኧኸ መስቀል ብርሃን ኧኸ ለኩሉ ዓለም(2)
ኧኸ መሠረተ (2)ቤተክርስቲያን(2)

አዝ

መስቀል ኃይላችን ነው
መስቀል መጽናኛችን
መስቀል የነፍሳችን መድኃኒት
ሚጠብቀን ከክፉ ከጠላት
ኧኸ መሠረተ (2)ቤተክርስቲያን(2)
አዝ

መስቀል አይሁድ ቢክዱትም
መስቀል እኛ እናምነዋለን
መስቀል ያመነውም እኛ
በመስቀሉ ከደዌ ድነናል
ኧኸ መሠረተ (2)ቤተክርስቲያን(2)
አዝ

መስቀል ለብዙ ዘመናት
መስቀል ሲኖር ተሰውሮ
መስቀል ለዓለሙ ሁሉ
ብርሃን ሆነ አልቀረም ተቀብሮ
ኧኸ መሠረተ (2)ቤተክርስቲያን(2)
አዝ

መስቀል የመዳን አርማ ነው
መስቀል አዳኝ የዋለበት
መስቀል ከጠላት አገዛዝ
ከዲያቢሎስ ነፃ የወጣንበት
ኧኸ መሠረተ (2)ቤተክርስቲያን(2)
አዝ

መስቀል ለብዙ ዘመናት
መስቀል ሲኖር ተሰውሮ
መስቀል ለዓለሙ ሁሉ
ብርሃን ሆነ አልቀረም ተቀብሮ
ኧኸ መሠረተ (2)ቤተክርስቲያን(2)

ዘማሪ ዲያቆን አድማሱ ዘሪሁን
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​መስቀሉ_አበራ

እዮሐ አበባዬ መስከረም ጠባዬ(2)
መስከረም ሲጠባ ተተክሎ ደመራ
ህዝበ ኢትዮጵያን እዩት ችቦውን ሲያበራ
በታላቁ ብርሃን በመስቀል ደመራ(2)


በኃጢአት ጨለማ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ተውጠን ሳለን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የክርስቶስ መስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ብርሃን ሆነልን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ትምህርተ መስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ሆኖን ላመንነው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
በቃሉ ለምንድን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የእግዚአብሔር ኃይል ነው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

✞ መስቀል ባንዲራችን
የነጻነት አርማችን(2)

በኢየሩሳሌም አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
አይሁድ አብረው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ያዳናቸውን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
አናውቅም ብለው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የድሉን መስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ከመሬት ቀብረው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
መስሏቸው ነበር አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ውጦ የሚያስቀረው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

በቀራንዮ ጎልጎታ
ጠላታችን ድል ተመታ(2)


ንግሥቲቷ እሌኒ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
በጣም የታደለች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ደመራን አቁማ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ፍለጋ ጀመረች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
መስቀለ ክርስቶስ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ወዴት ነው እያለች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
በጣን ጢስ ተመርታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
መስቀሉን አገኘች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

በመስቀል መከታ
ቆስጠንጢኖስ ድል ተመታ(2)

ነገር ግን መስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ተቀብሮ አልቀረም አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ተራራ አፍርሶ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ጠላት አሳፈረ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
መስቀል ሲወጣ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ታላቅ ሁካታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ድውይ ሲፈወስ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
አንካሳው ዳነ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ሙታን ተነሱ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ይመስገን ጌታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

ብርሃን ወጣ ከመስቀሉ
ክርስቲያኖች እልል በሉ (2)


መስቀል መከታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ይሁን ጋሻችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
እንዳይደፈር አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ዳር ድንበራችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ኢትዮጵያ ኑሪ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
በእምነት ፀንተሽ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ጌታ በመስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የባረከሽ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

መስቀሉ አበራ
እንደ ፀሀይ ጮራ (2)


መስቀሉን አምነን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ተሳልመነዋል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ከክብሩ ዙፋን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
በእርሱ ባርኮናል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
እንሰግድለታለን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የፀጋ ስግደት አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
በእርሱ ላይ ስላለ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ኃይለ መለኮት አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

መስቀል የእኛ ጋሻ
የዲያብሎስ ድል መንሻ (2)

የኢትዮጵያን መኩሪያ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ኑ ተመልከቱልን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የመስቀሉን ብርሃን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ነፀብራቁን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
እፀ መስቀሉ ነው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የእኛ መከታችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የተሰጠን ለእኛ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ምልክታችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

በመስቀል እንመካለን
እንድንበታለን(2)


የዳዊት ልጅ ያዕቆብ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የሀገራችን ኩራት አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የኢትዮጵያ ንጉሥ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ጌታን የሚፈራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
መስቀል ተሸክሞ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ሀገሪቱን ሲዞር አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ድካሙን ሳይፈራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
መስቀል ተሸክሞ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ብርሐን እያበራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

የመስቀሉ ፍቅር
በእኛ ላይ ይደር(2)


መናገሻ እንጦጦ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የረር አምባ አመራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ሲፈለግ ሰንብቶ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የመስቀል ተራራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ጊሸን ላይ አገኘ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የአምባሰል ተራራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ግማደ መስቀሉ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
አርፏል ከዚያ ስፍራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

መስቀል መስቀላችን
የክርስቲያን ኃይላችን(2)


የመስቀል ለታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የደመራው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ኢትዮጵያውያን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ተደስተው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
በሀገር ልብሳቸው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
አምረው ደምቀው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
በአደባባዩ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ተሰብስበው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ይዘምራሉ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
መስቀል ብለው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

የመስቀሉ ደመራ
በኢትዮጵያ ሲያበራ(2)


በማኅበረ ፊሊጶስ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​መስቀል አበባ

መስቀል አበባ ነህ ውብ አበባ
አደይ አበባ ነሽ ውብ አበባ(2)

አዝ

መስቀል አበባ ተቀብሮ ሲኖር
አደይ አበባ ሥነ ስቅለቱ
መስቀል አበባ እሌኒ አገኘች
አደይ አበባ ደገኛይቱ
አዝ

መስቀል አበባ ጥራጊ ሞልተው
አደይ አበባ አይሁድ በክፋት
መስቀል አበባ ጢሱ ሰገደ
አደይ አበባ መስቀል ካለበት
አዝ

መስቀል አበባ ወንዙ ጅረቱ
አደይ አበባ ሸለቆው ዱሩ
መስቀል አበባ አሸብርቀው ደምቀው
አደይ አበባ ላንተ መሰከሩ
አዝ

መስቀል አበባ ተቀብሮ ሲኖር
አደይ አበባ ሥነ ስቅለቱ
መስቀል አበባ እሌኒ አገኘች
አደይ አበባ ደገኛይቱ 

ዘማሪ በሱፍቃድ አንዳርጋቸው
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

መስከረም 16/1/2017 ዓ.ም


ምስባክ ፦ መዝ 59÷4-5
ወወሀብኮሙ ትእምርተ ለእለ ይፈርሁከ        
ከመያምስጡ እመገጸ ቅስጥ                     
ወይድኃኑ ፍቁራኒከ
             
ትርጉም ፦
ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ
ለሚፈሩህ ምልክቱን ሰጠሃቸው
ወዳጆችህ እንዲድኑ
              
👉 @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ምልክቴ ነው አርማዬ

ምልክቴ ነው አርማዬ
መስቀሉ መሸሸጊያዬ (3)

አዝ

ከቀስቱ ፊት ያመለጥኩበት መስቀሉ
ገዳዬን የረታሁበት መስቀሉ
በምጥ ወልዶኝ ሰው የሆንኩበት መስቀሉ
በይቅርታው የከበርኩበት መስቀሉ
የመስቀሉ ቃል ለእኔ ኃይሌነው
ጥልቁን ጨለማ በእርሱ አልፋለሁ (2)
አዝ

ሕይወት በዛ ከሰላሙ ጋር መስቀሉ
ተሰበከ ሰላም እና ፍቅር መስቀሉ
የድል አርማ ይዤ ተነሳሁ መስቀሉ
ምልክቴን መስቀሉን አየሁ መስቀሉ
የነሀሱን መዝጊያ ከፍቶታል ደሙ
በፍጥረት መሃል በዝቷል ሰላሙ (2)
አዝ

ሃሌሉያ ስለማዳኑ መስቀሉ
እንዳከበረኝ ተወግቶ ጎኑ መስቀሉ
እሳት መሃል አልፋለሁ ገና መስቀሉ
ምልክቴ መስቀል ነው እና መስቀሉ
ትምክህት የለኝም ከመስቀል ሌላ
ከእርሱ ላልለይ አለኝ መሃላ (2)
አዝ

የጠላቴ መውጊያው ተመታ መስቀሉ
ቀራንዮ ሲያድነኝ ጌታ መስቀሉ
ከእንግዲህ እማ የመስቀሉ ነኝ መስቀሉ
የጠላት ጦር ሞት የማይገዛኝ መስቀሉ
ጥልን ገድሎታል ታውጇል ሰላም
ከፍ አድርጎኛል መድኃኔዓለም (2)

ዘማሪ ገዛኸኝ ኤርባ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እንኳን ለቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን!

​​ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ የሥጋው ፍልሰት

የዲያቆናት አለቃ የሰማዕታት መጀመሪያ የሆነው  ቅዱስ እስጢፋኖስ መስከረም ዐሥራ አምስት የሥጋው ፍልሰት ነው።

የቅዱስ እስጢፋኖስ ሥጋ ባለበት አቅራቢያ የገማልያል ቦታ በትምባል በኢየሩሳሌም በአንዲት ቦታ አንድ ሰው ይኖር ነበር። የዚያም ሰው ስም ሉክያኖስ ነው ተጋዳይ የሆነ እስጢፋኖስም ብዙ ጊዜ በሕልም ተገለጠለት እንዲህም ብሎ አስረዳዉ እኔ እስጢፋኖስ ነኝ ሥጋዬ በዚህ ቦታ ተቀብሮ አለ አለው።

ያም ሉክያኖስ የሚባል ሰው የኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ ወደ ሆነው መጥቶ በራዕይ ያየውን ይህን ነገር ነገረው ኤጲስቆጶሱም ሰምቶ እጅግ ደስ አለው ያን ጊዜም ሁለት ኤጲስቆጶሳትን፣ ካህናትንና፣ የቤተ ክርስቲያንን ሰዎች ሁሉ ከእርሱ ጋራ ይዞ ተነሣ የቅዱስ እስጢፋኖስ ሥጋ በውስጡ ወዳለበት ወደዚያ ቦታ ደርሰው ሊቆፍሩ ጀመሩ ታላቅ ንውጽውጽታም ሆነ የቅዱስ እስጢፋኖስ ሥጋ በውስጡ ያለበት ሣጥን ተገለጠ ከእርሱ እጅግ በጎ የሆነው የሽቱ መዓዛ ሸተተ።

በሰማያት ለእግዚአብሔር ምስገና ሆነ በምድርም ሰላም ለሰው ነፃነቱ ይሰጠው ዘንድ በጎ ፍቃድ እያሉ ሲያመሰግኑ የመላእክትን ቃሎች ሰሙ። ኤጲስቆጶሳቱና ካህናቱም የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥጋ በያዘ ሣጥን ፊት ለጌታ ሰገዱ ከዚያም በኋላ ወደ ጽርሐ ጽዮን እስኪያደርሱት ብዙ መብራቶችን አብርተው በመያዝ በማኀሌት ምስጋና እየዘመሩ ተሸከሙት።

ከዚህም በኋላ እንዲህ ሆነ በኢየሩሳሌም ነዋሪ የሆነ የቊስጥንጥንያ ተወላጅ ስሙ እለእስክንድሮስ የሚባል ሰው ነበር፤ ለቅዱስ እስጢፋኖስም ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያንን ሠርቶለት ሥጋውን አፍልሰው ወደርሷ ወስደው አኖሩት ከአምስት ዓመት በኋላም እለእስክንድሮስ አረፈ ሚስቱም በቅዱስ እስጢፋኖስ አስከሬን ጕን ቀበረችው። ከአምስት ዓመቶችም በኋላ የእለእስክንድሮስ ሚስት የቧላን አስከሬን ወደ ቊስጥንጥንያ አገር ይዛ ልትሔድ አሰበች ባሏንም ወደ ቀበረችው፤ እርሱ ባሏ ወደ ሠራት ቤተ ክርስቲያን ሔደች የባሏ ሥጋ ሣጥን ግን የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥጋ በያዘ ሣጥን አምሳል ነበር በእግዚአብሔር ፈቃድ የቅዱስ እስጢፋኖስን ሣጥን ወስዳ እስከ አስቃላን ከተማ ተሸከመችው ከዚያም ወደ ቊስጥንጥንያ ልትጓዝ በመርከብ ተሳፈረች።

በመርከብ ስትጓዝ ከሣጥኑ ጣዕም ያለው ምስጋናን የምትሰማ ሆነች እጅግም አድንቃ ያን ሣጥን ልታየው ተነሣች በውስጥ የቅዱስ እስጢፋኖስ ሥጋ ያለበት ሣጥን እንደሆነ ተረዳች ይህም የሆነው ክብር ይግባውና በእግዚአብሔር ፈቃድ እንደሆነም አወቀች ወደ ኢየሩሳሌም ትመለስ ዘንድ አልተቻላትም፤ ይህንንም ታላቅ ጸጋ ስለሰጣት ልዑል እግዚአብሔርን አመሰገነች።

ወደ ቍስጥንጥንያ አገርም በደረሰች ጊዜ ይቺ ሴት ወደ ንጉሡ ሒዳ የቅዱስ እስጢፋኖስን ዜና ከእርሱ የሆኑትን ተአምራት ወደ ቍስጥንጥንያ አገር ወደብም እንደደረሰ ነገረችው ሰምቶም እጅግ ደስ አለው ንጉሡም ከሊቀ ጳጳሳቱና ከካህናቱ ከብዙ ሕዝቦችም ጋር ወጣ ከወደቡም በክብር አንሥተው ወደ መንግሥት አዳራሽ እስከ አስገቡት ድረስ በፍጹም ደስታ እየዘመሩና እያመሰገኑ ተሸክመውት ተጓዙ።

ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በእርሱ ተአምራትን ገለጠ በሠረገላ ሥጋውን ጭነው በሁለት በቅሎዎች በሚስቡት ጊዜ ቍስጣንጢንዮስ ከሚሉት ቦታም ሲደርሱ የቅዱስ እስጢፋኖስንም ሥጋ በዚያ እንዲያኖሩ ስለ ፈቀደ የሚስቡት በቅሎዎች ቆሙ። አልተንቀሳቀሱም በቅሎዎችንም ይመቷቸው ጀመሩ የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥጋ በዚህ ሊያኖሩ ይገባል የሚል ቃል ከአንዱ በቅሎ ሰሙ ይህንንም ያዩና የሰሙ ሁሉም አደነቁ።

እግዚአብሔርንም አመሰገኑት የበለዓምንም አህያ ያናገራት እርሱ እነዚህን የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥጋ የተሸከሙትን በቅሎዎች ያናገራቸው እርሱ እንደሆነ አወቁ። ንጉሡም በዚያ መልካም የሆነች ቤተ ክርስቲያን ሠርተው ይህን የከበረና ንጹሕ የሆነ ዕንቈ ባሕርይ በውስጧ እንዲያኖሩ አዘዘ። ይኸውም የተመሰገነና የተባረከ ሐዋርያ የዲያቆናት አለቃና የሰማዕታት መጀመሪያ የሆነው የእስጢፋኖስ ሥጋው ነው።

የሰማዕቱ በረከት ይደርብን
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

መስቀል አርማ ለክርስቲያን

መስቀል አርማ ለክርስቲያን
ክርስቶስ በደሙ አትሞ የሰጠን

አዝ

የመስቀሉን ነገር ላመንንበት ለእኛ
ጠላትን ድል መንሻ ሆኖናል መዳኛ
የመስቀሉን ነገር ላላመኑ
ሆናቸው ሞኝነት ራቁ ከካህኑ
አዝ

መስቀል ላይ ነበረ የቀኙ ቀማኛ
እድሜውን የጨረሰ ሆኖ ወንጀለኛ
የመስቀሉን ነገር ቢረዳ እና ቢያምን
አዳምን በመቅደም ወረሰ ገነትን
አዝ

አይሁድ ነገሥታቱ የኦሪት ካህናት
ምስጢረ ስጋዌ ያልተረዱ በእውነት
መስቀሉን ቢያደርጉት መቅጫ ወንጀለኛ
ክርስቶስ በደሙ አረገው መዳኛ
አዝ

የመስቀሉ ፍቅር በእውነት የገባን
የእሌኒ ልጆች ተባልን ክርስቲያን
ተሸክመነዋል መስቀሉን አውጥተን
በአንገታችን አስረን በልባችን ቀርፀን

ዘማሪ ዲያቆን ሄኖክ ሞገስ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…
Подписаться на канал