ortodoxmezmur | Неотсортированное

Telegram-канал ortodoxmezmur - ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

134932

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . ዝማሬ ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Подписаться на канал

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​የቀጠለ 👆

በመሆኑም የባለ አምስትና የባለ ሁለት መክሊት ባለቤቶች የሆኑት ወጥተው ወርደው ደክመው፣ መከራ መስቀልን ሳይሳቀቁና ሳይፈሩ፤ ወድደው ፈቅደው የጀመሩትን አገልግሎት በማክበር ሕይወታቸውን ለታመነው አምላክ አደራ በመስጠት የተማሩትን ፍጹም ትምህርት ለሌላው አስተምረው፣ ሠርተው ያገኙትን ለሌላው አካፍለው ወገናቸውን እንደራሳቸው አድርገው ሲመለከቱ

ባለ አንድ መክሊት የተባለው ግን ዓላውያን እሳት ስለት አሳይተው ሃይማኖቴን ሲያስክዱኝ መናፍቃን ተከራክረው ምላሽ ቢያሳጡኝ ብሎ ፈርቶ ሃይማኖቱን በልቡ ከመደበቅና ከመሠወር በቀር የተማረውን ትምህርት ሠርቶ ያገኘውን ሀብት ንብረት ለሌላው ሊያካፍልና የተሰጠውን አደራም ሊወጣ አልወደደም፡፡

ይህ የመክሊቱ ባለቤት የተባለው ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን የተሰጣቸውን ሓላፊነት በአግባቡና በጽንአት ለተወጡት ሁሉ እርሱ ፍጹም ዋጋን የሚሰጣቸው መሆኑን ያመለክታል፡፡

ይህም ሁኔታ “አንተ በጎ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሾምሃለሁ። ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” በሚል ታላቅ የምስጋና ቃል ተገልጧል፡፡ ይህ ቃል በሃይማኖትና በበጎ ምግባር ለእግዚአብሔር የታመኑ ሁሉ ዘለዓለማዊና ፍጹም ደስታ ወደሚገኝበት መንግሥተ ሰማያት ለመግባት ለሚያደርጉት የእምነት ጉዞ እጅግ ተስፋ የሆነ ቃል ነው፡፡

በዚህ ምንባብ ላይ እንደተገለጸው እግዚአብሔር አምላክ ለሁላችንም እርሱን የምናገለግልበትንና ለእርሱ በመታመን ዘለዓለማዊ ክብርን የምናገኝበትን ዕውቀትን፣ ማስተዋልን፣ እምነትን፣ ተስፋን፣ የሥነ ምግባር ሀብትን፣ ልዩ ልዩ ስጦታዎችን እንጠቀምባቸው ዘንድ ለእኛ ለሰው ልጆች እንደየዓቅማችን መጠን ሰጥቶናል፡፡

እነዚህ ሁሉ ነገሮች የሥጋችንን ምኞት
ለማስፈጸም የተሰጡ ሳይሆኑ ነፍሳችን የምትከብርበትን መልካም ሥራን የምንሠራባቸው መሣሪያዎቻችን ናቸው። በመሆኑም እርሱ በሰጠን የአገልግሎት በር ጸጋ በታማኝነት በማገልገል በሕይወት ዘመናችን ሁሉ መንፈሳዊውን ሀብት የምናተርፍ እንሆን ዘንድ የተላለፈልን አምላካዊ ምክር ነው፡፡

ምክንያቱም እኛ የተጠራነው ፍሬ ልናፈራና ሌላውንም ልናተርፍ መልካም ሥራን ልንሠራ እንጂ የሥጋችንን ፈቃድ በመከተል የኃጢአት ባሮች ልንሆን አይደለም፡፡ መጽሐፍ እንዲህ አለ “ወኲሉ ዘከመ ተጸውአ ከማሁ ለየሀሉ፤ ሁሉ እንደተጠራ እንዲሁ ይኑር” /፩ኛ ቆሮ. ፯፥፳/

ከላይ እንደተመለከትነው በልዑል አምላክ በእግዚአብሔር አንደበት አንተ በጎ ታማኝ አገልጋይ በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሃለሁ መባልን የመሰለ አስደሳችና አስደናቂ ነገር የለም፡፡

ይህ ደግሞ የሚገኘው ሃይማኖትን በሥራ በመግለጥ እንጂ ሃይማኖትን በልቡና በመያዝ ብቻ /ሙያ በልብ ነው/ በማለት ብቻ የሚገኝ አይደለም፡፡ ከእነዚህ እንደ አቅማቸው መጠን መክሊት ተሰጥቷቸው በትጋታቸውና በቅንነታቸው ሌላ መክሊት ካተረፉት በጎና ታማኝ አገልጋዮች የምንማረው እውነታም ይህ ነው፡፡

በብዙ ለመሾም ለማደግ ለመጽደቅ በጥቂቱ መታመን መፈተን መጋደል ግድ ነው፡፡ አንድ መክሊት የተሰጠውን ሰው ስንመለከተው ጌታውን ጨካኝና ፈራጅ አድርጎ ከመቁጠር ውጪ በተሰጠው መክሊት ወጥቶ ወርዶ ሊያተርፍ አልወደደም፡፡

መክሊቱንም ባስረከበ ጊዜ በጌታው ላይ የተናገራቸው ቃላት የእርሱን አለመታዘዝና አመጸኝነት ይገልጡ ነበር፡፡ በመሆኑም ይህ ሰው በጥቂቱ መታመን ያቃተውና በአስተሳሰቡ ደካማነት እጅግ የተጎሳቆለ ሰው ነው፡፡

በዚህ ምሳሌ መሠረት ይህ ባለ አንድ መክሊት የተባለው ሰው ዓላውያን ነገሥታት እሳት ስለት አሳይተው ቢያስክዱኝ መናፍቃን ተከራክረው መልስ ቢያሳጡኝ በማለት ሃይማኖቱን በልቡ ሸሽጎና ቀብሮ በተቀደሰ ተግባር ሳይገልጠው ከመያዙ ባሻገር በጌታ ፊት በድፍረት ቆሞ አንተ ሕግ ሳትሠራ በአእምሮ ጠባይዕ አውቃችሁ፤ መምህራንንም ሳትመድብ በሥነ ፍጥረት ተመራምራችሁ በሠራችሁ ብለህ የምትፈርድ ጽኑ ጨካኝ መሆንክን አውቃለሁና ፈርቼ ሃይማኖቴን በልቡናዬ ይዠዋለው በአዕምሮዬ ጠብቄዋለሁ የሚል ሃይማኖቱን ግን በሥራ የማይገልጥ ሰነፍ ሰውን ያመለክታል፡፡

ለዚህ ዓይነት ሰው የጌታ መልስ ደግሞ በምሳሌው መሠረት የሚከተለው ነው። እኔ ሕግ ሳልሠራ በአእምሮ ጠባይዕ አውቃችሁ ፤ መምህር ሳልሰጥ በሥነ ፍጥረት ተመራምራችሁ አውቃችሁ በሠራችሁት ብዬ የምፈርድ ጽኑ ጨካኝ መሆኔን ታውቃለህን? እንዲህስ ካወቅህ ሹመትክን ልትመልስልኝ ይገባኝ ነበር፡፡

ወጥቶ ወርዶ ለሚያስተምር በሰጠሁት ነበር፡፡ አሁንም የእርሱን መምህርነት ሹመት ነሥታችሁ (ወስዳችሁ) ለዚያ ለባለ ዐራቱና ለባለ ዐሥሩ ደርቡለት!

እርሱን ግን አውጡት የሚል ነው። ምክንያቱም ከበጎ ምግባር የተለየች እምነት የሞተች እንደሆነ ተጽፏልና። ዛሬም እያንዳንዳችን በዓቅማችን መጠን መክሊት ተሰጥቶናል፡፡ ነገር ግን መክሊቱን እንደቀበረው እንደዚያ ሰው የተሰጠንን ቀብረን ለወቀሳና ለፍርድ እንዳንሰጥ በአገልግሎታችን ልንተጋ ይገባናል፡፡

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህንኑ ሲገልጥ “ወዘሂ ይትለአክ በመልእክቱ፤ ወዘሂ ይሜህር በትምህርቱ. . .፤ አገልግሎት ቢሆን በአገልግሎታችን እንትጋ የሚያስተምርም በማስተማሩ ይትጋ የሚሰጥም በልግሥና ይስጥ›› (ሮሜ. ፲፪፥፯) በማለት ተናግሯል፡፡

ለመሆኑ አሁን ባለንበት የስግብግብነት ወቅት ዛሬ ‹‹አንተ በጎ ታማኝ አገልጋይ…›› ተብሎ በእግዚአብሔር ሊመሰገን የሚችል ሰው ማን ይሆን? በእውነት እንዲህ ተብሎ የሚመሰገን በጎና ታማኝ ካህን በጎና ታማኝ መምህር በጎና ታማኝ ምእመን ታማኝ ሰባኪና ታማኝ ዘማሪ ማግኘት ይቻል ይሆንን?

ነገር ግን መቼም አምላካችን ቸር ነውና በየዘመናቱ አንዳንድ ታማኝ አባቶችን እንደማያሳጣን ተስፋ አለን። ምክንያቱም ዛሬም ቢሆን እንደአባቶቻችን እንደቅዱሳን ሐዋርያት በእምነት፣ በትዕግሥት በፍቅር በተጋድሎ በየውሐት በትሕርምት በጸሊዓ ንዋይ በትሕትናና በትጋት በማገልገል የተሰጣቸውን መክሊት የሚያበዙ አገልጋዮች አሉ፡፡

የእነዚህ ክብራቸው በምድርም በሰማይም እጅግ የበዛና ራሳቸውን አስመስለው በትምህርት የወለዷቸው ልጆቻቸውም ለቤተ ክርስቲያን የተወደዱ የተከበሩ ልጆች ናቸው፡፡

ለምሳሌ ነቢየ እግዚአብሔር ሙሴ ነቢየ እግዚአብሔር ኢያሱን ፤ ቅዱስ ጴጥሮስ ቀሌምንጦስን፣ ቅዱስ ጳውሎስም ቅዱስ ጢሞቴዎስን ለቤተ ክርስቲያን አበርክተዋል፡፡ ሌሎችም አበው ቅዱሳን በወንጌል ቃል መንፈሳውያንና ትጉሃን የሆኑ ምእመናንን በሚገባ አፍርተዋል፡፡

ያላመኑትንም አሳምነው ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመመለስ ለዘለዓለማዊ ክብር የበቁ እንዲሆኑ አስችለዋቸዋል። በተሰጣቸው ጸጋም አትርፈው አትረፍርፈው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሀብተ መንፈስ ቅዱስ እንድትጎበኝ አድርገዋል፡፡ የእነርሱም በረከታቸው ረድኤታቸው ቃል ኪዳናቸው ለሌሎች እንዲተርፍ ሆኖላቸዋል፡፡

በመሆኑም ክርስቶስ በደሙ የከፈለውን ወደር የሌለውን ዋጋ ዓለም አምኖና ተቀብሎ በክርስትና ሃይማኖት እንዲድንበትና እንዲጠቀምበት በማድረግ እንዲሁም በታማኝነትና በበጎነት አገልግሎታቸው ጥንትም ዛሬም ላለችዋና ወደፊትም ለምትኖረዋ ቅድስት ቤተክርስቲያን ድምቀትም ውበትም የሆኑት ቅዱሳን አበው ሊገኙ የቻሉት ከእግዚአብሔር ይልቅ ሰውን ደስ ለማሰኘት በመድከማቸው ሳይሆን የተጠሩበትን ዓላማና የጠራቸውን እርሱን በሚገባ አውቀውና ከልብ ተረድተው ለዘለዓለማዊ ሕይወት ተግተው በመሥራታቸው ነው።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የምትወዱት ሰዎች አልቅሱለት

ብክይዎ ወላሕውዎ
እለ ታፈቅርዎ
ወይቤ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ ኤልማስ
ዘበ እደ አይሁድ ተአስረ
አመ ጸምአ ማይ ይሰቲ
ሀሞተ ወከርቤ መሪረ
ወይቤ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ

ጌታዬ አምላኬ በደል ሳይኖርበት ተገፋ
የአዳምን መርገም ሊያጠፋ
በአይሁድ እጅ ታሰረ
እንደ ወንጀለኛ ተቆጠረ
ጌታዬ አምላኬ ሞተልኝ ስለኔ
አልቅሱለት ስለ መከራው የምትወዱት

አዕንቃዕደ ወሰማየ
ኀበ አቡሁ ነጸረ
ሶበመንፈሱ ትወጽዕ
በላዕለ መስቀሉ ገአረ
ወይቤ ወይቤ ተፈጸመ ኲሉ

ውሃን የፈጠረ ተጠማ
ሀሞትን አጠጡት እየደማ
የሾህ አክሊል ደፍቶ ቀና አለ
መራራውን ጽዋ ተቀበለ
ጌታዬ አምላኬ ሞተልኝ ስለኔ
አልቅሱለት ስለ መከራው የምትወዱት

በእናቱ ፊት ሰቀሉት
በጥፊ እየመቱ ዘበቱበት
ሐዘኑንስ እንዴት ትቻለው
መተኪያ የሌለው ልጇ እኮ ነው

እውነት ወደ ምድር ቢመጣ
በሀሰት ዳኝነት ተመታ
በጀርባው ላይ ጅራፍ አረፈ
ደሙ እንደ ውሃ ጎረፈ
ጌታዬ አምላኬ ሞተልኝ ሰለኔ
ወይቤ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ
ወይቤ ኤሎሄ ተፈጸመ ኲሉ

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ሠላም የተወደዳችሁ ኦርቶዶክሳዊያን!

✝በዓብይ ጾም በገና፣ክራር ወይም መሰንቆ መማር ትፈልጋላችሁ?✝

እንግዲያውስ ማኅበራችን ማኅበረ ኀዳፌ ነፍስ
በዓብይ ጾም ምዝገባ ጀምረናል የ6 ወር እና የ3ወር ትምህርቶችን።


🫴መማር ለምትፈልጉ ቶሎ ይደውሉ እና ይመዝገቡ ☎️ 0956861468 ወይም 0912085085

በቴሌግራም ለማውራት ደግሞ @Orthodoxtewahed0


👉በገና፣ክራር እና መሰንቆ መሳሪያዎችን መግዛት ለምትፈልጉም ደውሉልን

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እውነት ስለሆነ

እውነት ስለሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ 
ዋለ ባደባባይ ሲሰደብ ሲከሰስ 
የሀሰት ዳኝነት አምላክን ወቀሰው 
ህይወት ሰጠን እንጂ ጥፋቱ ምንድነው/2/ 
#አዝ
ከቃሉ እብለትን ባያገኙበትም 
ዝምታውን አይተው አላዘኑለትም 
ባላወቁት መጠን ጠሉት ካለበደል 
ጥፋቱ ምን ይሆን የሚያደርስ ከመስቀል/2/ 
#አዝ
የልቡን ትህትና ፍቅሩን ሳያስተውሉ 
ቸሩ ጌታችንን አቻኩለው ሰቀሉ 
እሩህሩሁን ጌታ ቸንክረው ሰቀሉት 
ሞትን አስውግዶ ቢሰጣቸው ህይወት/2/ 
#አዝ
ስለ ቸርነቱ ስድብን ከፈሉት 
ስለ ርህራሄው የሾህ አክሊል ሰጡት 
ሀሞትና ከርቤ ሆምጣጤ ደባልቀው 
መራራ አስጎነጩት ጨክኖልባቸው/2/ 
#አዝ
ፈውስን ለሰጣቸው ልባቸውን ሞልተው 
አሉት ወንበዴ ነው ስቀለው ስቀለው 
ከጁ በረከትን የተሻሙ ሁሉ 
ይጮሁ ነበረ ይገደል እያሉ/2/

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ድንግል የዚያን ጊዜ

ድንግል የዚያን ጊዜ(2) ሐዘንሽ በረታ
በመስቀል ላይ ሆኖ ልጅሽ ሲንገላታ(2)

የግፍ ግፍ ደርሶበት የዚያን ጊዜ ተጠማሁ ሲልሽ
ለውሻ ያጠጣሽ በወርቅ ጫማሽ(2)

ሴቶች ሲያባርሩት የዚያን ጊዜ
ራርቶ ሆድሽ
ለፍጡር በማዘን ውሀ ያጠጣሽ (2)

ተጠማሁ እያለ የዚያን ጊዜ
ሲናገር ልጅሽ
ታድያ እንደምን ቻለው ወላድ አንጀትሽ(2)

እንደዚያ ስታለቅሽ የዚያን ጊዜ
ሐዘን ሲውጥሽ
እነማን ነበሩ ቀርበው ያፅናኑሽ(2)

ስታለቅሽ በማየት የዚያን ጊዜ
ራርቶ ልጅሽ
ዮሐንስን አፅናኝ አንድ ልጅ ሰጠሽ (2)

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ጌታ ሆይ

ጌታ ሆይ አይሁድ አማጽያን
ሰቀሉህ ወይ 
የዓለም መድኃኒት የዓለም ሲሳይ
ሰቀሉህ ወይ /2/ 

የአዳም በደል አደረሰህ
አንተን ለመሰቀል 
የሔዋን ስህተት አበቃህ ለሞት
ቸሩ አባት/2/
አዝ
ንጹሕ ክርስቶስ ሆንክ ወንጀለኛ
ብለህ ስለእኛ 
መሰቀል አሸክመው
አስረው ገፈፉህ እያዳፉህ/2/ 
አዝ
እጅና እግርህን በብረት ተመታ
የዓለም ጌታ 
የሾህ አክሊል ደፍተህ
ጎንህን ተወጋህ አልፋ ኦሜጋ/2/
አዝ
ግብዞች እንደራሳቸው መስሏቸው 
ምራቅ እየተፉ በፊትህ ቀለዱ
አንተን ሊጎዱ/2/
አዝ 
በመሰቀል ላይ ተጠማሁ ስትል
ታላቅ በደል 
ሀሞትና ከርቤ ሰጡህ ቀላቅለው
ጠጣ ብለው/2/
አዝ
ይቅር ባይ ግልጽ በደላችንን ሁሉ ሳታይ 
አንተ ይቅር በለን
በእኛ ሳትከፋ እንዳንጠፋ /2/ 

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን

ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን አባት ሆይ
በመስቀል ሆነህ አባት ሆይ
ድምጽህን በማሰማት አባት ሆይ
ነፍስህን ሰጠህ አባት ሆይ

ከዋክብተ ሰማይ በሙሉ ረገፉ
ጨረቃና ፀሐይ ደምን አጎረፉ
ብርሃናት ጨለሙ ጠፍተው ተለያዩ
ሥጋህን በመስቀል ተገልጦ ስላዩ
#አዝ
ጌታችን ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ
አሰምቶ ጮኸ ተጠማሁ እያለ
ማርና ወተትን ለሚመግበው
ሐሞት አመጡለት ይቅመሰው ብለው
#አዝ
አካሉ ሲወጋ ውኃ ደም ፈሰሰ
በምድር ተረጭቶ ዓለምን ቀደሰ
የእሥራኤል ሴቶች ዋይ ዋይ ሲሉልህ
ለእነርሱ አዘንክ እንጂ ለአንተስ አላሰብክም
#አዝ
እናትህ ስታለቅስ በመስቃል ሥር ሆና
ዮሐንስን ሰጠህ ጠብቆ እንዲያፅናና
መላእክትም ታዩ አጋንንትም ሸሹ
የአይሁድ ሠራዊት ፈርተው ተረበሹ

ሊቀ-መዘምራን
ኪነ-ጥበብ ወልደ-ቂርቆስ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#ታላቅ_መንፈሳዊ_ጉዞ
የማር ፀበል ሚሰጥበት መጋቢት 16 ቅዳሜ አብረውን ይጋዙ መጋቢት 16 ደርሶ መልስ አዘጋጅተናል ይመዝገቡ
❖ በፍፁም የእናታቸን ኪዳነ ምህረት  ወዳጆች የማንቀርበት የማር ፀበል ሚሰጥበት ❖
     ➠ መነሻ ➺ ቅዳሜ መጋቢት 16 መመለሻ በእለቱ ➠  +251907748876
      +251986677077
                    #መመለሻ_በእለቱ
#የጉዞ ዋጋ>400 ብር
                ( መስተንግዶን ጨምሮ )
       <የጉዞ ሂሳብ ያካተተው>
     🚎 ትራንስፖርት
     🍲 ምሳ
     🥤ውሃ
#መነሻ ቦታ
          1 ፒያሣ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን
          2 መገናኛ ውሃ ታንከር 12:00
          3 ጣፎ አደባባይ 1:00
ለጉዞ ሲመጡ ኦርቶዶክሳዊ ተዋህዶ
አለባበስ እንዳይለዮ !!➠   +251907748876
       +251986677077
         ለበለጠ መረጃ >     ውስን ቦታ ስላለን ፈጥነው ይደውሉ።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ድንግል የዚያን ጊዜ

ድንግል የዚያን ጊዜ(2) ሐዘንሽ በረታ
በመስቀል ላይ ሆኖ ልጅሽ ሲንገላታ(2)

የግፍ ግፍ ደርሶበት የዚያን ጊዜ ተጠማሁ ሲልሽ
ለውሻ ያጠጣሽ በወርቅ ጫማሽ(2)

ሴቶች ሲያባርሩት የዚያን ጊዜ
ራርቶ ሆድሽ
ለፍጡር በማዘን ውሀ ያጠጣሽ (2)

ተጠማሁ እያለ የዚያን ጊዜ
ሲናገር ልጅሽ
ታድያ እንደምን ቻለው ወላድ አንጀትሽ(2)

እንደዚያ ስታለቅሽ የዚያን ጊዜ
ሐዘን ሲውጥሽ
እነማን ነበሩ ቀርበው ያፅናኑሽ(2)

ስታለቅሽ በማየት የዚያን ጊዜ
ራርቶ ልጅሽ
ዮሐንስን አፅናኝ አንድ ልጅ ሰጠሽ (2)

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

2ኛ ዙር ጉዞ ምዝገባ
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
                     ❖ታላቅ የበረከት ጉዞ❖
ወደ ➡ ነብስና ስጋን የሚለየው ሲኦልን እና ገነትን የምናይበት ተአምር አድራጊው ፈዋሹ  ቋራ ደጎሎ  አሸዋ  ማዶ በርሚል ቅዱስ ጊዮርጊስ ጸበል
መነሻ ቀን➡ መጋቢት 22/2015 ዓ.ም
መመለሻ ቀን ➡ መጋቢት  29/2015 ዓ.ም
መነሻ ሰአት ➡ ንጋት 10:00 ሰአት
መነሻ ቦታ ➡አዲስ አበባ ፒያሳ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በር ላይ
በክልል ከተሞች
✟✟✟በጉዞው ላይ የምንሳለማቸው ገዳማት✟✟✟ ባህርዳር ቅዱስ ሚካኤል
       የጉዞ ዋጋ 4000 ብር ትራንስፖርት ብቻ

እና ሌሎችንም ገዳማትን እናሳልማለን
ጉዞው ከወዲሁ ምዝገባ ስለተጀመረ  እስከ  21 ድረስ እናቆማለን ስለዚህ ከወዲሁ  ይመዝገቡ መኪና ለማስተካከል
       ጥቂት ቦታ ነው የቀረን ፈጥነው ይመዝገቡ
#ሼርርርርርርርርርር_በማድረግም_የበረከቱ_ተካፋይ_ይሁኑ
ሰልክ :--->09   07    74     88    76
☎️   :--->09   86    67     70    77 
ቴሌግራም ቻናላችን ላይ የጉዞ መረጃ ያገኛሉ
/channel/chorapictures

         አዘጋጅ :->❖ማዕዶት መንፈሳዊ ጉዞ ማህበረ ❖‌‌

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#አቤት_የዚያን_ጊዜ

አቤት የዚያን ጊዜ
ክርስቶስ ሲመጣ (፪)
ትንሹም ትልቁም (፫)
መድረሻውን ሲያጣ

ከምስራቅ ከምዕራብ
ከሰሜን ከደቡብ (፪)
አየራት/መላእክት/ ሲላኩ (፫)
መአትን ለማዝነብ፤
ሰማይና ምድር በአንድ ሲዋሐዱ (፪)
የት ይሆን መድረሻው(፫)
የት ይሆን መንገዱ

አዝ

ጻድቃን በቀኝ በኩል
ኃጥአን በግራ (፪)
ሲነፋ መለከት (፫)
ሲደለቅም ዕንዚራ
ምድር ቀውጢ ስትሆን
አጽም ሲሰበሰብ (፪)
ሐፍረት ይይዘዋል (፫)
ሰው ለፍርድ ሲቀርብ

አዝ

ጩኸት ሲበረታ
የማይጠቅም ለቅሶ (፪)
እንደ ቍራ ጠቁሮ (፫)
ጽልመትን ተላብሶ
ገነትን ሲያገኙ
ጻድቃን በስራቸው (፪)
ኃጥአን ወደ ሲኦል (፫)
ተፈረደባቸው።

መዝሙር
ሊቀመዘምራን
ኪነጥበብ ወልደቂርቆስ

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ደብረ ዘይት - ምጽዓተ እግዚእነ
🎤 በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ

🙏ለመምህራችን ቃለ ሕይወት ያሰማልን

#ሼር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

https://youtu.be/TQeWVmN47PY

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

https://youtu.be/4npUzXLWxFg

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

✝ሠላም የተወደዳችሁ የዝማሬ ዳዊት ቻናል ተከታታዮቻችን✝


👉አምስቱ አእማደ ምሥጢርን እየተማርን የነበረ ሲሆን እስከ አሁን። ዛሬ ደግሞ አራተኛውን ምሥጢር

#ምሥጢረ ቁርባንን እንቀጥላለን

ስለ ቅዱስ ያዘጋጀነው ትምህርት አለ እርሱን መጀመሪያ ታደምጡ ዘንድ በትኅትና እንጠይቃለን።


ከእዛም ከትምህርተ ተዋሕዶ አፕሊኬሽን ማጠቃለያ ድምጽ እንልካለን

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​​​​​የዐብይ ጾም ስድስተኛ ሳምንት ገብርኄር ይባላል፡፡

ገብርኄር ማለት ታማኝ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ ስለ ታማኝ አገልጋይ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም ስንኖር ለፈጣሪያችን ያለንን ታማኝነትና የምናገኘውን ዋጋ በመዋዕለ ሥጋዌው
አስተምሯል፡፡

ቅዱስ ያሬድ ለዜማ መክፈያነት የዐብይ ጾምን ሳምንታትን ሲከፍል ገብርኄርን ተጠቅሟልና እኛም ስለ ገብር ሄር ጥቂት እንበል፡፡ ልዑል እግዚአብሔር አምላካችን በነቢዩ አንደበት አድሮ፤ “እከሥት በምሳሌ አፉየ፤ ወእነግር አምሳለ ዘእምትካት፤ አንደበቴን /ነገሬን/ በምሳሌ እገልጣለሁ፤ ከቀድሞ ጀምሮ የነበረ
ታሪክና ምሳሌ እናገራለሁ” አለ፡፡

ይህም ማለት ወንጌልን በምሳሌ አስተምራለሁ፤ በመልከ ጼዴቅ ዘመን አስቀድማ የተሠራችና ታይታ የጠፋችውን ወንጌልን እናገራለሁ፡፡ ይህን ታላቅ ምሥጢር ሐዋርያው ሲያብራራ “ከመ በአሚን ያጸድቆሙ እግዚአብሔር ለአሕዛብ አቅደመ አሰፍዎቶ ለአብርሃም ከመ ቦቱ ይትባረኩ ኲሎሙ አሕዛብ ፤ በአንተ አሕዛብ ሁሉ ይባረካሉ ብሎ ወንጌልን ለአብርሃም አስቀድሞ ሰበከ” ብሏል፡፡ /ገላ. ፫፥፰፣ መዝ. ፸፯፥፪

በዚሁ መሠረት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን ለልዩ ልዩ ወገኖች በልዩ ልዩ ምሳሌ አስተምሯል፤ ከላይ በተገለጠው ኃይለ ቃል መነሻነት ሁለት ምሳሌያትና አንድ ቃለ ትንቢት ቀርበዋል፡፡ ከምሳሌያቱ
የመጀመሪያው በዐሥሩ ደናግል አንጻር የቀረበው ምሥጢር ሲሆን፤ ሌላኛው ደግሞ ወጥተው ወርደው ነግደው ያተርፉበት ዘንድ ገንዘቡን ስለሰጠ አንድ ነጋዴ የሚናገረው ነው፡፡

የትንቢቱ ምሥጢራዊ ይዘት የሚያስረዳውም ስለ ኅልቀተ ዓለም አይቀሬነት ነው፡፡ ስለሆነም በዚህ ዕትማችን ወጥተው ወርደው ነግደው እንዲያተርፉበት ከጌታቸው የተሰጣቸውን መክሊት ስለተቀበሉት አገልጋዮች ሕይወት እንመለከታለን፡፡ ፈጣሪያችን አእምሮውን ለብዎውን /ማስተዋሉን/ ያድለን፡፡

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ ያስተማራቸው ምሳሌያዊ ትምህርቶች በቅዱስ መጽሐፋችን በሰፊው ተጽፈው እናገኛለን፡፡ የእነዚህ ትምህርታዊ ምሳሌዎች መሠረታዊ ሀሳብና ዓላማም የእግዚአብሔርን መንግሥት የምናገኝበትን የታማኝነትን ሥራ እንዴት መሥራት እንደሚገባንና መሥራትም እንደምንችል ማስተማር ነው፡፡

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለመንግሥተ ሰማያት ምሥጢር ያስተማራቸው ብዙ ምሳሌዎች ያሉ ሲሆን ከእነዚህ ብዙ ምሳሌያዊ ትምህርቶች መካከልም እንዲያተርፉበት መክሊት ስለተሰጣቸውና ስለተመሰገኑት መልካም አገልጋዮች፣ እንዲሁም መክሊቱን በመቅበሩ ምክንያት በጌታው ስለተወቀሰውና ፍርድን ስለተቀበለው ሰነፍ ሰው ታሪክ፣ የታሪኩም ምሥጢር ምን እንደሚመስል የተጻፈው ትምህርት ነው።

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህንን ምሳሌ የተናገረው /ያስተማረው/ በሚከተለው መልኩ ነበር፤ ‹‹ወደ ሌላ ሀገር የሚሔድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንደሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና ለእያንዳንዱ እንደ ዓቅሙ ለአንዱ አምስት መክሊት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ ሀገር ወዲያውኑ ሔደ፡፡

አምስት መክሊትም የተቀበለው ሔዶ ነገደበት ሌላም አምስት አተረፈ፣ እንዲሁም ሁለት የተቀበለው ሌላ ሁለት አተረፈ፣ አንድ የተቀበለው ግን ሔዶ ምድርን ቆፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ፡፡

ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው፡፡ አምስት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምስት መክሊት አስረክቦ፡- ጌታ ሆይ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ ሌላ አምስት መክሊት አተረፍሁበት አለ፡፡
ጌታውም፡- መልካም አንተ በጎ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው፡፡

ሁለት መክሊት የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፡- ጌታ ሆይ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፡፡ እነሆ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍሁበት አለ፡፡
ጌታውም፡- መልካም አንተ በጎ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው።

አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፡- ጌታ ሆይ ካልዘራህበት የምታጭድ ካልበተንህበትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ፈራሁም ሔጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት ፤ እነሆ መክሊትህ አለልህ አለው፡፡
ጌታውም መልሶ እንዲህ አለው፡- አንተ ክፉና ሐሰተኛ ባሪያ ካልዘራሁበት እንዳጭድ ካልበተንሁበትም እንድሰበስብ ታውቃለህን? ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር።

እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር፡፡ ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት ዐሥር መክሊትም ላለው ስጡት። ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል። ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳ ይወሰድበታል፡፡

የማይጠቅመውንም ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል የሚል ነው፡፡

መክሊት ጥንት የክብደት መለኪያ ነበር:: አንድ መክሊት 30 ኪሎ ግራም ያህል ነው፡፡ በዚህ ምሳሌ ላይ እንደተገለጸውም መክሊት የሚለው ቃል ገንዘብን ያመለክታል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምሳሌ ውስጥ እርሱን የምናገለግል ሁላችን እንደየዓቅማችን ማድረግ የሚገባንን መንፈሳዊ የአገልግሎት ሥራንና በአገልግሎታችን ውጤታማ በመሆናችንም ከእርሱ የምናገኘውን ዘለዓለማዊ ክብርና ዋጋን እንዲሁም መሥራት የሚገባንን ባለማድረጋችንም ምክንያት የሚገጥመንን መለኮታዊ ቅጣትን አመልክቶናል፡፡

በዚህ ምሳሌ ውስጥ ባለ አምስት የተባለው በቂና ፍጹም ትምህርት ተምሮ ሌላውን መክሮ አስተምሮ ራሱን አስመስሎ የተካ ያወጣ ነው፡፡

በተመሳሳይም ባለ ሁለት የተባለው እንደ መጀመሪያው ሁሉ ተምሮ ሌላውን መክሮ አስተምሮ ራሱን አስመስሎ ያወጣ ሲሆን ባለ አንድ የተባለው ደግሞ ተምሮ ሳያስተምር የቀረ በስንፍና በቸልተኝነት በማን አለብኝነት ሕይወት ተገድቦ የቀረ ሰው ነው፡፡

ይቀጥላል
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🚌 ተመዝግበዋል ? 
      ማዕዶት መንፈሳዊ ጉዞ ማኅበር    🚎

⛪️   ወደ ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለሃይማኖት አንድነት ገዳም
   📆 መጋቢት 24 ቀን 2015 ዓ.ም
                 ደርሶ መልስ
💵 የጉዞ ዋጋ - 450 ብር መስተንግዶን ጨምሮ።
👉  ምዝገባ ፒያሣ ጊዮርጊስ ሕንፃ ዮቶር ህትመት ቤት
👉በዚህ ጉዞ ላይ በመሳተፍ በረከት ያገኙ ዘንድ ፈጥነው ባሉበት ቦታ በኢት.ንግድ ባንክ ትኬቱን ይቁረጡ ‼    1000184714257  አበባ ኪሮስ

ለበለጠ መረጃ 📱 09 07  74  88  76
                      📱 09 86  67  70  77 ይደውሉ።

          ‼️ ፈጥነው ይመዝገቡ  ‼️
/channel/ENATEZ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በአዲስ አበባ ኃይሌ ጋርመንት አካባቢ መጋቢት 14/2015 ዓ.ም ቀሲስ ዐባይ መለሰ የተባሉ ካህን ቅዳሴ ጨርሰው ወደ ቤታቸው በመሄድላይ እንዳሉ በድንጋይ ተወግረው ሕይወታቸው ማለፉን የዐይን እማኞች ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ገለፁ።

የሆርሲሳ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የነበሩት ቀሲስ ዐባይ መለሰ ሕይወታቸው ሲያልፍ ችግሩ ታወቀ እንጂ አስቀድሞ በአካባቢው አገልጋዮች ላይ ዛቻ እና ማስፈራሪያ ይደርስ እንደነበር መረጃ ሰጭዎቻችን በቦታው ለተገኘው ዘጋቢያችን ገልፀዋል።

ካህኑ በድንጋይ ተደብድበው እያሉ ምስልና ቪዲዮ ለማስረጃ ለመያዝ ቢሞክሩም በአካባቢው የፀጥታ ኃይሎች ሞባይል እየተሰበሰበ መሰረዙንም ነግረውናል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የኪዳነምህረት ወዳጆች ሼር በማድረግ ለሁሉም አድርሱ
የማሩ ፀበል መጋቢት 16 ቅዳሜ ይሰጣል!!!
ስለዚህ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል
በህመም ለሚሰቃዩ፡ የህይወት ጭንቅ ውስጥ ላሉ  ሸር በማድረግ ኦርቶዶክሳዊ ግዴታውን ይወጡ🙏🙏


ጉዞ ስለተዘጋጀ
0907748876
  
0986677077
በመደወል ተመዝገቡ
/channel/ENATEZ
ሰሚነሽ ኪዳነምህረት ገዳም

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የኪዳነምህረት ወዳጆች ሼር በማድረግ ለሁሉም አድርሱ
የማሩ ፀበል መጋቢት 16 ቅዳሜ ይሰጣል!!!
ስለዚህ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል
በህመም ለሚሰቃዩ፡ የህይወት ጭንቅ ውስጥ ላሉ  ሸር በማድረግ ኦርቶዶክሳዊ ግዴታውን ይወጡ🙏🙏


ጉዞ ስለተዘጋጀ
0907748876
  
0986677077
በመደወል ተመዝገቡ
/channel/ENATEZ
ሰሚነሽ ኪዳነምህረት ገዳም

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#ታላቅ_መንፈሳዊ_ጉዞ
የማር ፀበል ሚሰጥበት መጋቢት 16 ቅዳሜ አብረውን ይጋዙ መጋቢት 16 ደርሶ መልስ አዘጋጅተናል ይመዝገቡ
❖ በፍፁም የእናታቸን ኪዳነ ምህረት  ወዳጆች የማንቀርበት የማር ፀበል ሚሰጥበት ❖
     ➠ መነሻ ➺ ቅዳሜ መጋቢት 16 መመለሻ በእለቱ ➠  +251907748876
      +251986677077
                    #መመለሻ_በእለቱ
#የጉዞ ዋጋ>400 ብር
                ( መስተንግዶን ጨምሮ )
       <የጉዞ ሂሳብ ያካተተው>
     🚎 ትራንስፖርት
     🍲 ምሳ
     🥤ውሃ
#መነሻ ቦታ
          1 ፒያሣ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን
          2 መገናኛ ውሃ ታንከር 12:00
          3 ጣፎ አደባባይ 1:00
ለጉዞ ሲመጡ ኦርቶዶክሳዊ ተዋህዶ
አለባበስ እንዳይለዮ !!➠   +251907748876
       +251986677077
         ለበለጠ መረጃ >     ውስን ቦታ ስላለን ፈጥነው ይደውሉ።
ለበለጠ መረጃ /channel/ENATEZ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🎞 ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) አረፉ 🕯🕯🕯
https://youtu.be/zfMwQA2fCGk
https://youtu.be/zfMwQA2fCGk
https://youtu.be/zfMwQA2fCGk

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

😭😭✝የሀዘን ዜና✝😭😭

ብጹዕ አቡነ አረጋዊ(ዶ/ር) ከእዚህ ዓለም ድካም በዛሬዋ ዕለት አረፉ።

ብጹዕ አባታችን ከባለፈው አመት የሆሳዕና በዓል ጀምሮ በህመም ላይ የቆዩ ሲሆን ዲያለሲስ ሲደረግላቸው ቆይተው በዛሬዋ ዕለት ከመንፈስ ልጆቻቸው ተለይተዋል።


የቅድስት ድንግል ማርያም ምልጃ የልጇ ቸርነት የቅዱሳን ጸሎት ከእርሳቸው ጋር ይሁን።

በረከታቸው ይደርብን!!!

የቀብር ስነ-ሥርዓቱ በቤተክርስቲያን ሚዲያዎች የሚገለጽ መሆኑን እናሳውቃለን።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እውነት ስለሆነ

እውነት ስለሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ 
ዋለ ባደባባይ ሲሰደብ ሲከሰስ 
የሀሰት ዳኝነት አምላክን ወቀሰው 
ህይወት ሰጠን እንጂ ጥፋቱ ምንድነው/2/ 
#አዝ
ከቃሉ እብለትን ባያገኙበትም 
ዝምታውን አይተው አላዘኑለትም 
ባላወቁት መጠን ጠሉት ካለበደል 
ጥፋቱ ምን ይሆን የሚያደርስ ከመስቀል/2/ 
#አዝ
የልቡን ትህትና ፍቅሩን ሳያስተውሉ 
ቸሩ ጌታችንን አቻኩለው ሰቀሉ 
እሩህሩሁን ጌታ ቸንክረው ሰቀሉት 
ሞትን አስውግዶ ቢሰጣቸው ህይወት/2/ 
#አዝ
ስለ ቸርነቱ ስድብን ከፈሉት 
ስለ ርህራሄው የሾህ አክሊል ሰጡት 
ሀሞትና ከርቤ ሆምጣጤ ደባልቀው 
መራራ አስጎነጩት ጨክኖልባቸው/2/ 
#አዝ
ፈውስን ለሰጣቸው ልባቸውን ሞልተው 
አሉት ወንበዴ ነው ስቀለው ስቀለው 
ከጁ በረከትን የተሻሙ ሁሉ 
ይጮሁ ነበረ ይገደል እያሉ/2/

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

Watch "🛑 በዐቢይ ጾም ይህንን ማድረግ በጣም ከባድ ነው እስከ ውግዘትም ያደርሳል! ሁላችሁም መስማት ይኖርባቹሀል!" on YouTube
https://youtu.be/D1bTSYbnGaM

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​ሳማ ሰንበት

ወደ ሳማ ሰንበት-ዓመታዊው የመንፈሳዊ ጉዞ መዳረሻ ተጓዡ ጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም በእኩለ ጾም መንፈሳዊ ተጓዦች ሊሳለሙበት የሚያቀኑትን ስፍራ በሀገራችን ከሚገኙ የመንፈሳዊ ቱሪዝም መዳረሻዎች አንዱ ነው ሲል ሳማ ሰንበትን እንዲህ ያስጎበኘናል፡፡
(ሔኖክ ስዮም) 

ይህ ጉዞ ከዛሬ ሁለት መቶ ሃምሳ ዓመታት በፊት እንደጀመረ የሳማ ቀበሌ አባቶች ይናገራሉ፡፡ ይሁን እንጂ ባለፉት ሃያ ዓመታት ከዓመት ዓመት ተአምር እየሆነ መጥቷል፡፡

ከአዲስ አበባ ምስራቃዊ አቅጣጫ የሚገኘውን ሳማ ሰንበት ልንጎበኝ እየሄድን ነው፡፡ ብቻችንን አይደለም እየሄድን ያለንው፤ በሺዎች የሚቆጠሩ አውቶቢሶችና ሚኒባሶች ሰው ሞልተው እንደኛው ጉዞ ላይ ናቸው፡፡ ዋና ዋና ለሚባሉ ከተሞች ማለትም ለአዲስ አበባ፣ ለቢሸፍቱ፣ ለሞጆ፣ ለአዳማ፣ ለዝዋይና ለአረርቲ የሚቀርብ በመሆኑ በዓመት አንዴ ከተሜዎች የማይቀሩበት መንፈሳዊ ስፍራ ሆኗል፡፡

በኦርቶዶክስ ምዕመናን ዘንድ ታላቅ ስፍራ የሚሰጠው የአብይ ጾም እኩሌት ደብረ ዘይት ይባላል፡፡ ይህንን ቀን ደብረ ዘይትን ተሻግረው ሳማ ሰንበት የሚያሳልፉ መቶ ሺዎች ናቸው፡፡ ከአዲስ አበባ 110 ኪሎ ሜትር ተጉዘን መጥተናል፡፡ ሰሜን ሸዋ ዞን ምንጃር ሸንኮራ በሚባለው ወረዳ እንገኛለን፡፡ ይህቺ በዓመት አንድ ቀን ሰው መርፌ ሳያስጥል የሚጠቀጥቃት ስፍራ ሳማ ቀበሌ ውስጥ ትገኛለች፡፡

ሳማ ሰንበት ደርሰናል፡፡ ክቧ ቤተ ክርስቲያን ግንባሯ ላይ እንደሻሽ የጠመጠመችው በሚመስለው አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቀለም አሸብርቃለች፡፡ ይህቺ ቤተ ክርስቲያን ህንጻዋ ዘመናዊ ይሁን እንጂ ሳማ ሰንበት ከተተከለ ሶስት መቶ ዓመታትን ያለፈ እድሜ እንዳለው የአካባቢው አባቶች ይናገራሉ፡፡ ሰው ቁጥር የለውም፡፡ የቤተክርስቲያኗ ቅጥር ጊቢ እንዲህ መፈናፈኛ ያጣው ብዙው ሺ ከደጃፉ ቆሞ ነው፡፡

ሳማ ሰንበት በዓመት አንድ ግዜ የደብረ ዘይት በዓል የሚከበርባት ስፍራ ስትሆን እንደ አንዳንዶች ግምት ይሄ ስፍራ በዚህ መልኩ በዓለም ሁለተኛው ብቸኛ ደብረ ዘይት በድምቀት የሚከበርበት እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ ስፍራውን የተለዩ ካደረጉት ውስጥ ለመውረድ የሚያስፈራው የጠበሉ መንገድና ዋሻው የተለየ ቦታ የሚሰጣቸው ናቸው፡፡

ከሳማ ሰንበት እየወጣን ነው፡፡ የሰው ብዛት መንገዳችንን ሰዓት የሚበላ ሊያደርገው ይችላል፡፡ የምንጃርን ሸንኮራ እየከሰከስን በምዕመናኑ ዝማሬ ተመስጠን ዳግም አዲስ አበባን አሰብናት፡፡ በሰላም ለቀዋት የወጡ አውቶቢሶች በሰላም ደጃፏን ርግጠው ተሳላሚዎቹ በየቤታቸው ይገቡ ዘንድ።

የቻላችሁ ነገ ሄዳችሁ አድራችሁ የበረከት ተካፋይ ሁኑ! አላሰብኩበትም አትበሉ ሁሉን ፈፃሚ እግዚአብሔር አምላክ ነው በችግር ምክንያት የማትችሉ ግን እርሱ በፈቀደ ግዜ እንዲያደርሳችሁ ጸልዩ!

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​​​ደብረ ዘይት የዐብይ ጾም አምስተኛ ሳምንት

ደብረ ዘይት ማለት ቃሉ “ደብር” ሲል ተራራ ሲሆን “ዘይት” ሲል የወይራ ዛፍን ያመለከታል።

ባጠቃላይ ደብረ ዘይት የወይራ ዛፍ (የዘይት ዛፍ) የበዛበት ተራራ ማለት ነው። ቦታው በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ከጎለጎታ (ቀራንዮ) ተራራ በስተምስራቅ በግምት ፪ ኪሎሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ታላቅ ተራራ ነው።

በሁለቱ ተራሮች መካከል ጌቴሴማኒ የሚባለው ለምለም ስፍራ ይኸውም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የመቃብር ስፍራ ይገኛል።

የደብረ ዘይት ተራራ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብዙ ጊዜ የሚያድርበት፣ የሚያስተምርበት፣ ውሎ የሚያርፍበት ሥፍራ ነው። ሉቃ ፳፩፥ ፴፯፣ ሉቃ ፳፪፥ ፴፱፣ ዮሐ ፰፥ ፩

ከዚሁ ተራራ ላይ ነው ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያረገው። ኋላም በዳግም ምጽአት እዚሁ ተራራ ላይ ነው ለፍርድ የሚመጣው። /ሐዋ ፩፥፲፫/። "
" በዚህ ቀን ስለ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ወደ ምድር ስለመምጣቱ (ዳግም ምፅአቱ ) ይሰበካል።

ይህን ዓለምንም አሳልፎ ለመረጣቸውና ላከበራቸው ዘላለማዊ መንግሥትን ሊያወርሳቸው እንደሚመጣ ይነገርበታል። ይህ ቀንም እኩለ ፆም በመባል የሚታወቅ ሲሆን በዚህች በተለየች ቀንም ሁሉም እንደ የሥራው ፍርዱን ከአምላክ የሚቀበልበት መሆኑ፤ መልካም ላደረጉ መልካም እንደሚመለስላቸ ክፉም ላደረጉ የክፋታቸውን ዋጋ እንደሚያገኙ ይሰበካል።

ጌታም የአባቴ ቡሩካን የተዘጋጀላችሁን የክብር ቦታ ውረሱ በማለት ወዳጆቹን እንደሚጠራ ይነገራል።
" እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም እሳት በፊቱ ይቃጠላል " ማቴ.፳፬፡፩-፴፮ ኢየሱስም ከመቅደስ ወጥቶ ሄደ፥ ደቀ መዛሙርቱም የመቅደሱን ግንቦች ሊያሳዩት ቀረቡ።

እርሱ ግን መልሶ፦ ይህን ሁሉ ታያላችሁን? እውነት እላችኋለሁ፥ ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ በዚህ አይቀርም አላቸው። እርሱም በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድር ነው? አሉት።

ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ። ብዙዎች። እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፤ ብዙዎችንም ያስታሉ። ጦርንም የጦርንም ወሬ ትሰሙ ዘንድ አላችሁ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነውና ተጠበቁ፥ አትደንግጡ፤ ዳሩ ግን መጨረሻው ገና ነው።

ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፥ ራብም ቸነፈርም የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል፤ እነዚህም ሁሉ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው። በዚያን ጊዜ ለመከራ አሳልፈው ይሰጡአችኋል ይገድሉአችሁማል፥ ስለ ስሜም በአሕዛብ ሁሉ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ።

በዚያን ጊዜም ብዙዎች ይሰናከላሉ እርስ በርሳቸውም አሳልፈው ይሰጣጣሉ እርስ በርሳቸውም ይጣላሉ፤ ብዙ ሐሰተኞች ነቢያትም ይነሣሉ ብዙዎችንም ያስታሉ፤ ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች። እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል። "

#ሼር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

https://youtu.be/Oji7daT4obw

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

✝️በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::✝️

እንደምን አመሻችሁ የተወደዳችሁ ኦርቶዶክሳውያን እህቶቼ እና ወንድሞቼ?


በእዚህ ድምጽ ውስጥ የሚዳሰሱት ነጥብ

🌹ቅዱስ ቁርባን ምንድነው? ምን ማለት ነው?

🌹ቅዱስ ቁርባን መቀበል እፈልጋለሁ ግን በእዚህ እድሜዬ እችላለሁ?

🌹ቅዱስ ቁርባን በሐዲስ ኪዳን እና በብሉይ ኪዳን


🌹ቅዱስ ቁርባን ለመቀበል ምን አይነት ዝግጅት ማድረግ አለብን?(ወደ ሥጋ ወ ደሙ ከመቅረባችን በፊት; በቀረብን ጊዜ; ከተቀበልን በኃላ ምን ማድረግ አለብን?)

🌹የአምላካችንን ቅዱስ ሥጋ ና ደም በመቀበላችን ምንደነው በህይወታችን የምናገኘው ጥቅም?



🗣በይሳኮር🙏

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እንኳን ለአባታችን ለአቡነ ገብረ መንፈስቅዱስ አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ

#ለሀገር_ኢትነ

ለሀገር ኢትነ ሰላማ ኪያከ ተአቅብ
አባ ኦ አባ(2) ገብረ መንፈስ ቅዱስ

በዘማሪት #ገነት

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…
Подписаться на канал