ortodoxmezmur | Неотсортированное

Telegram-канал ortodoxmezmur - ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

134932

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . ዝማሬ ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Подписаться на канал

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🤲🤲🤲ስለ ነገረ ማርያም🤲🤲🤲


ዛሬ ማታ 2:00 ላይ ትምህርታችንን የምንጀምር ስለሚሆን ሁላችሁም 2:00 ላይ ተሰብስባችሁ እንድትገኙ እናሳስባለን።

መምህር ዲያቆን ዳግማዊ ሰለሞን

ይሄንን ትምህርት ጓደኞቻችሁ እንዲማሩ ይሄንን ማስታወቂያ ላኩላቸው ከታች ያለውን ሊንክ በመግባት ይቀላቀሉን።


🌙 የማታ ሰው ይበለን 🌙

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

✝እንድታማሩ ያዘጋጀናቸው የትምህርት ርዕሶች ከታች የተዘረዘሩት ናቸው✝

ከእነርሱ ውስጥ መማር የምትፈልጉትን ተራ ቁጥር፤ ቁጥሩን ብቻ ትልኩልናላችሁ።

1.ትምህርተ ሃይማኖት(ስለ ሥነ ፍጥረት)
2.አምስቱ አእማደ ምሥጢራት(ከእዚህ በፊት የተማርነው አለ ይላክልናል)
3.ነገረ ማርያም
4.ነገረ ክርስቶስ(ክርስቶስ ፈራጅ ወይስ አማላጅ)
5.ነገረ መልአክት
6.ታቦት፣ጽላት፣ቤተክርስቲያን


መማር የምትፈልጉትን ተራ ቁጥር ላኩልን

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​እንኳን ለታላቁ ነቢይና ሰማዕት ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ዓመታዊ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ

#ቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቅ

ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የነ ዘካርያስን ቤተሰብ ያህል ክብሩ የተገለጠለት ፍጡር ይኖራል ብሎ መናገሩ ይከብዳል:: #ቅዱስ_ሉቃስ ወንጌሉን የጀመረው በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ሲል አጽፎታል:: "#ዘካርያስ ካህኑና #ቅድስት_ኤልሳቤጥ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ" ይላቸዋል:: (ሉቃ. 1:6)

¤የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ መኖር ምን ይረቅ? ለዚህ አንክሮ (አድናቆት) ይገባል!

¤እሊህ ቅዱሳን ባልና ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ 90 የዘካርያስ 100 ደግሞ ደርሶ ነበር::

¤ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ: ትንቢት ለብቻው የተነገረለት (ኢሳ. 40:3, ሚል. 3:1) ታላቅ ነቢይን ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው::

¤ቅዱስ ዘካርያስ ሰው ነውና ከደስታ ብዛት በመከራከሩ ድዳ ሆነ:: ቅድስቲቷ ግን መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው ጸንሳ ለ6 ወራት ራሷን ሠወረች:: በ6ኛው ወር የፍጥረት ሁሉ ጌታ በተጸነሰ ጊዜ የአርያም ንግሥት ድንግል #እመቤታችን ደጋ ደጋውን ወደ ኤልሳቤጥ መጣች:: ሁለቱ ቅዱሳት የእህትማማች ልጆች ናቸው::

¤የአምላክ እናቱ ስትደርስና "#ሰላም" ስትላቸው መንፈስ ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ ኤልሳቤጥ በምስጋና: ዮሐንስ ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘለለ (ሰገደ):: ከዚህ በሁዋላ ሰኔ 30 ተወልዶ: አባቱ ዘካርያስ "ዮሐንስ" ሲለው አንደበቱ ተፈትቶለታል::

¤ቅዱስ ዮሐንስ ከተወለደ 2 ዓመት ከ6 ወር በሆነው ጊዜ #ሰብአ_ሰገል በመምጣታቸው በእሥራኤል ምድር የሚገኙ ሕጻናትን ሔሮድስ ቁዝ አስፈጀ:: ትንሽ ቆይቶም አይሁድ ለሔሮድስ ስለ ቅዱሱ ሕጻን ነገሩት:: "ሲጸነስ የአባቱን አንደበት የዘጋ: ሲወለድ ደግሞ የከፈተ 'ዮሐንስ' የሚባል ሕጻን አለና እሱንም ግደል" አሉ::

¤እናቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ ይዛው ስትሸሽ ካህኑን ዘካርያስን ግን በቤተ መቅደስ መካከል ገድለውታል:: አረጋይት ኤልሳቤጥም ሕጻኑን እያሳደገች በገዳመ ዚፋታ ለ3 (5) ዓመታት ቆይታለች:: ቅዱስ ዮሐንስ 5 (7) ዓመት ሲሞላው ግን እዚያው በበርሃ እናቱ ዐረፈች:: ከሰማይ ዘካርያስና #ስምዖን ወርደው ቀበሯት::

¤ሕጻኑ ዮሐንስ ሲያለቅስ #ድንግል_ማርያም ስንት አገር አልፋ ሰማችው:: እርሷም ስደት ላይ ነበረችና:: ከጌታ ጋር በደመና ሒደው ድንግል አቅፋ አጽናናችው:: ጌታንም "እንውሰደው ይሆን?" አለችው:: ጌታችን ግን "ለአገልግሎት እስክጠራው እዚህ ይቆይ" አላት:: ባርካው: አጽናንታውም ተለያዩ::

¤ቅዱስ ዮሐንስ ከዚህ በሁዋላ በዚያ ቆላ የግመል ጠጉር ለብሶ: ጠፍር ታጥቆ ተባሕትዎውን ቀጠለ:: ለ25 (23) ዓመታትም በንጽሕና ሲኖር ከምድር አራዊትና ከሰማይ መላእክት በቀር ማንንም አላየም:: ይሕችን ዐመጸኛ ዓለምም አልቀመሳትም::

¤ከዚህ በሁዋላ 30 ዘመን ሲሞላው እግዚአብሔር ከሰማይ ተናገረው:: "ሒድ! የልጀን ጐዳና ጥረግ" አለው:: ነቢያት ስለዚህ ነገር ተናግረው ነበርና:: (ኢሳ. 40:3, ሚል. 3:1) አባቱ ዘካርያስም "ወአንተኒ ሕጻን ነቢየ ልዑል ትሰመይ: እስመ ተሐውር ቅድመ እግዚአብሔር ከመ ትጺሕ ፍኖቶ" (ሉቃ. 1:76) ብሎ መንገድ ጠራጊነቱን ተናግሮ ነበርና::

¤ቅዱስ ዮሐንስ በዚያ ጊዜ በኃይለ #መንፈስ_ቅዱስ እየገሰገሰ ከበርሃ ወደ ይሁዳ መጣ:: ያዩት ሁሉ ፈሩት: አከበሩት:: ቁመቱ ቀጥ ያለ: ጽሕሙ እንደ ተፈተለ ሐር የወረደ: ጸጉሩ የቁራ ያህል የጠቆረ: መልኩ የተሟላ: ግርማው የሚያስፈራ ገዳማዊ ነውና::

¤ፈጥኖም ሕዝቡን ለንስሃ ሰበከ:: ለንስሃም በርካቶችን አጠመቃቸው:: በዚህ አገልግሎት ለ6 ወራት ቆይቶ ጌታችን ወደ እርሱ ዘንድ መጣ:: ዮሐንስ ሰማይን ከነግሱ: ምድርን ከነ ልብሱ የያዘ ፈጣሪ 'አጥምቀኝ' ብሎ ሲመጣ ደነገጠ:: የሚገባበትም ጠፋው::

¤"እንቢ ጌታየ! አንተ አጥምቀኝ" አለው:: ጌታ ግን "ፈቅጄልሃለሁ" አለው:: አጠመቀው:: በዚህ ምክንያት ይሔው እስከ ዛሬም "#መጥምቀ_መለኮት" ሲባል ይኖራል:: ቅዱስ ዮሐንስ በመጨረሻ ሔሮድስን ገሰጸው:: ንጉሡም ተቀይሞ ለ7 ቀናት አሠረው::

ሔሮድስን ልደቱን ባከበረ ጊዜ ወለተ ሔሮድያዳ በዘፈን አጥምዳ አስማለችው:: እርሱም የታላቁን ነቢይ ራስ አስቆርጦ በወጪት አድርጐ ሰጣት:: አበው "እምሔሶ ለሔሮድስ ይብላዕ መሐላሁ - ሔሮድስ መሐላውን በበላ በተሻለው ነበር" ይላሉ:: የቅዱስ ዮሐንስ ራሱ በርራ ስትሔድ አካሉን ግን ደቀ መዛሙርቱ ቀብረውታል:: (ማቴ. 3:1, ማር. 6:14, ሉቃ. 3:1, ዮሐ. 1:6)

ርጉም ሔሮድስ አንገቱን ካስቆረጠው በሁዋላ የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ራሱ የጸጋ ክንፍ ተሰጥቷት ጌታችን ወዳለበት #ደብረ_ዘይት ሔዳ በፊቱ ሰገደች:: #ቅዱሳን_ሐዋርያት በአዩት ነገር ተገርመው ራሱን እጅ ነሷት::

ከዚሕ በሁዋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱስ ዮሐንስ ራስ የማስተማር ስልጣን ሰጥቶ አሰናበታት:: በመላው ዓለም ለ15 ዓመታት ስትሰብክ ኑራ በዚህች ቀን ዓረቢያ ውስጥ ዓርፋለች::

<< አስማተ-ዮሐንስ መጥምቅ (የመጥምቁ ዮሐንስ ስሞች) >>
1.ነቢይ
2.ሐዋርያ
3.ሰማዕት
4.ጻድቅ
5.ካሕን
6.ባሕታዊ/ገዳማዊ
7.መጥምቀ መለኮት
8.ጸያሔ ፍኖት (መንገድ ጠራጊ)
9.ድንግል
10.ተንከተም (የብሉይና የሐዲስ መገናኛ ድልድይ)
11.ቃለ አዋዲ (አዋጅ ነጋሪ)
12.መምሕር ወመገሥጽ
13.ዘየዐቢ እምኩሉ (ከሁሉ የሚበልጥ)

ጌታችን #መድኃኔ_ዓለም የመጥምቁ ዮሐንስን ምትረት አስቦ ይቅር ይበለን:: ጸጋውን: በረከቱንና ክብሩንም ያሳድርብን::

ምንጭ - ዝክረ ቅዱሳን
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🌺 ሰላም፡ለኵልክሙ
እነሆ ግእዝን በክረምቱ ጊዜ በልዩ ዝግጅት የሚማሩበት የግእዝ ቋንቋን ኮርስ ለመስጠት ምዝገባ ጀመርን።

📜 እርስዎም የግእዝ ቋንቋን ቀለል ባለና ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅታችንን አጠናቀናልና ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመመዝገብ ጥንታዊና ውዱ ቋንቋችንን እናጥና ፥ ዕንወቅ።


✅ ምዝገባውን ለማካሄድ ከታች ባለው የቴሌግራም አድራሻ ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር በመላክ የመማማሪያ ቦታዎችን ያገኛሉ  ✅

ለመመዝገብ 👇
@Geez202
@Geez202
@Geez202 👈
                

ትምህርቱን ከ14 ዓመት ዕድሜ በላይ የሆነ ማንኛውም ሰው ፤  ስልክ፣ ላፕቶፕ ወይም ዴስክቶፕ በመጠቀም መማር ይቻላል።

📲 የበለጠ መረጃ በምዝገባው ሂደት ይደርስዎታል። ጥያቄ ሲኖር ከታች በተቀመጠው በስልክ ያግኙን። ሠናይ፡ጊዜ።

🌺 መሠረተ፡ግእዝ 🌺
@MesereteGeez - 0918026533
ለሌሎችም ሼር በማድረግ እንድናዳርስ በአክብሮት እንጠይቃለን

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🌸🌸🌸🌸መፍትሔዎች🌸🌸🌸🌸🌸

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🌺 ሰላም፡ለኵልክሙ
እነሆ ግእዝን በክረምቱ ጊዜ በልዩ ዝግጅት የሚማሩበት የግእዝ ቋንቋን ኮርስ ለመስጠት ምዝገባ ጀመርን።

📜 እርስዎም የግእዝ ቋንቋን ቀለል ባለና ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅታችንን አጠናቀናልና ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመመዝገብ ጥንታዊና ውዱ ቋንቋችንን እናጥና ፥ ዕንወቅ።


✅ ምዝገባውን ለማካሄድ ከታች ባለው የቴሌግራም አድራሻ ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር በመላክ የመማማሪያ ቦታዎችን ያገኛሉ  ✅

ለመመዝገብ 👇
@Geez202
@Geez202
@Geez202 👈
                

ትምህርቱን ከ14 ዓመት ዕድሜ በላይ የሆነ ማንኛውም ሰው ፤  ስልክ፣ ላፕቶፕ ወይም ዴስክቶፕ በመጠቀም መማር ይቻላል።

📲 የበለጠ መረጃ በምዝገባው ሂደት ይደርስዎታል። ጥያቄ ሲኖር ከታች በተቀመጠው በስልክ ያግኙን። ሠናይ፡ጊዜ።

🌺 መሠረተ፡ግእዝ 🌺
@MesereteGeez - 0918026533
ለሌሎችም ሼር በማድረግ እንድናዳርስ በአክብሮት እንጠይቃለን

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

✝ሰላም የተወደዳችሁ የዝማሬ ዳዊት ቤተሰቦች✝

👉ከእዚህ በፊት ስናደርግ እንደነበረው
⁉️የጥያቄ እና መልስ ፕሮግራም አዘጋጅተናል⁉️

🤔ሁላችሁም በሃይማኖታችሁ ሊሆን ይችላል ወይም በመንፈሳዊ ሕይወታችሁ ጥያቄ የሆነባችሁ ወይም ግራ የገባችሁ እንዲመለስላችሁ የምትፈልጉትን ጥያቄዎች ሁሉ🤯

🕝ከአሁን ጀምሮ መጠየቅ ትችላላችሁ እዚሁ ላይ።

ጥያቄዎቹን ሰብስበን በእዚህ ሳምንት መመለስ እንጀምራለን


🫵ከአንተ/ከአንቺ ምን ይጠበቃል?🫵

1ኛ የፈለጋችሁትን ጥያቄዎች መጠየቅ
2ኛ እነዚህን ጥያቄዎች እንዲሁም ሌሎች ትምህርቶችን እንዲያገኙ ለምትወዷቸው እህት👩‍🦰ወንድም👨 ጓደኞቻችሁ ሁሉ የቻናላችንን ሊንክ በመላክ እንዲቀላቀሉ እና እነርሱም ከመልሶቹ እንዲማሩ፣ በተጨማሪም እነርሱም ጥያቄዎች ያሏቸውን በመጠየቅ ቤተሰብ እንዲሆን በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን።

🏃‍♂አሁን ቶሎ ቶሎ ቢያንስ ለ10 ሰው እና ከእዛ በላይ ይህንን መልእክት በመላክ እንዲቀላቀሉ እናድርግ🏃‍♂

እኛም ታሪክ እንስራ 135,809 አባላት አሉ።

በእዚህ ሳምንት እጅግ ከፍ ያለ ቁጥር እናስመዝግብ።

                 🎁ተጀምሯል⌛️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🌺 ሰላም፡ለኵልክሙ
እነሆ ግእዝን በክረምቱ ጊዜ በልዩ ዝግጅት የሚማሩበት የግእዝ ቋንቋን ኮርስ ለመስጠት ምዝገባ ጀመርን።

📜 እርስዎም የግእዝ ቋንቋን ቀለል ባለና ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅታችንን አጠናቀናልና ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመመዝገብ ጥንታዊና ውዱ ቋንቋችንን እናጥና ፥ ዕንወቅ።


✅ ምዝገባውን ለማካሄድ ከታች ባለው የቴሌግራም አድራሻ ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር በመላክ የመማማሪያ ቦታዎችን ያገኛሉ  ✅

ለመመዝገብ 👇
@Geez202
@Geez202
@Geez202 👈
                

ትምህርቱን ከ14 ዓመት ዕድሜ በላይ የሆነ ማንኛውም ሰው ፤  ስልክ፣ ላፕቶፕ ወይም ዴስክቶፕ በመጠቀም መማር ይቻላል።

📲 የበለጠ መረጃ በምዝገባው ሂደት ይደርስዎታል። ጥያቄ ሲኖር ከታች በተቀመጠው በስልክ ያግኙን። ሠናይ፡ጊዜ።

🌺 መሠረተ፡ግእዝ 🌺
@MesereteGeez - 0918026533
ለሌሎችም ሼር በማድረግ እንድናዳርስ በአክብሮት እንጠይቃለን

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

✝ሰላም የተወደዳችሁ የዝማሬ ዳዊት ቤተሰቦች✝

👉ከእዚህ በፊት ስናደርግ እንደነበረው
⁉️የጥያቄ እና መልስ ፕሮግራም አዘጋጅተናል⁉️

🤔ሁላችሁም በሃይማኖታችሁ ሊሆን ይችላል ወይም በመንፈሳዊ ሕይወታችሁ ጥያቄ የሆነባችሁ ወይም ግራ የገባችሁ እንዲመለስላችሁ የምትፈልጉትን ጥያቄዎች ሁሉ🤯

🕝ከአሁን ጀምሮ መጠየቅ ትችላላችሁ እዚሁ ላይ።

ጥያቄዎቹን ሰብስበን በእዚህ ሳምንት መመለስ እንጀምራለን


🫵ከአንተ/ከአንቺ ምን ይጠበቃል?🫵

1ኛ የፈለጋችሁትን ጥያቄዎች መጠየቅ
2ኛ እነዚህን ጥያቄዎች እንዲሁም ሌሎች ትምህርቶችን እንዲያገኙ ለምትወዷቸው እህት👩‍🦰ወንድም👨 ጓደኞቻችሁ ሁሉ የቻናላችንን ሊንክ በመላክ እንዲቀላቀሉ እና እነርሱም ከመልሶቹ እንዲማሩ፣ በተጨማሪም እነርሱም ጥያቄዎች ያሏቸውን በመጠየቅ ቤተሰብ እንዲሆን በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን።

🏃‍♂አሁን ቶሎ ቶሎ ቢያንስ ለ10 ሰው እና ከእዛ በላይ ይህንን መልእክት በመላክ እንዲቀላቀሉ እናድርግ🏃‍♂

እኛም ታሪክ እንስራ 135,769 አባላት አሉ።

በእዚህ ሳምንት እጅግ ከፍ ያለ ቁጥር እናስመዝግብ።

🎁ተጀምሯል⌛️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​ሰኔ 21/10/2016 ዓ.ም

በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌልና ምስባክ።

ምስባክ ፦ መዝ 45፥4-6
ቀደሰ ማኅድሮ ልዑል
እግዚአብሔር ውስተ ማዕከላ ኢትትሀወክ
ወይረድኣ እግዚያብሔር ፍጹመ

ትርጉም
ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ
እግዚያብሔር በመካከሏ ነው አትናወጥም
እግዚያብሔርም ፈጥኖ ይረዳታል

ወንጌል ፦ ማቴ 16÷13-20
ቅዳሴ ፦ ዘእግዝእትነ(የጌታ ቅዳሴ)

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

👉 የሰኔ ማርያም ዚቅ

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

👉 የሰኔ ማርያም ዋዜማ

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​ፆመ ሐዋርያት

አንዳንዶች የሰኔ ፆም የቄስ ፆም ነው በሚል ከመፆም ወደኋላ ሲሉ ይታያሉ ነገር ግን ቅድስት ቤተክርስቲያን በአዋጅ ከምትፆማቸው ሰባት አፅዋማት አንዱ እንደመሆኑ መጠን እያንዳንዱ ክርስቲያን ቢፆመው እጅግ በርካታ በረከቶችን ያገኝበታል ከነዚህም ጥቂቶችን እነሆ

1.በረከተ ሐዋርያት ይገኝበታል
ይህን ፆም መጀመርያ ፆመው እንድንፆመው ሰርዐት የሰሩልን ሐዋርያት ናቸዉ ስለዚህም ፆሙ መታሰቢያነቱ የሐዋርያት ነው የጻድቅ መታሰቢያ ደግሞ ለበረከት ነው ። ምሳ.10፥7 እኛም የሰኔን ፆም ብንፆም የሐዋርያቱን በረከት እናገኛለን ሐዋ.13፥1-3 ሐዋ.14፥23

2. በስራችንና በአገልግሎታችን በረከት እናገኛለን
ሐዋርያት ይህን ፆም የፆሙት አገልግሎታቸው እንዲከናወንላቸው እንዲባረክላቸው ነው ነብዩ ነህምያም እየሩሳሌምን የመስራት ተግባሩ እንዲባረክለት በፆመው ፆም ስራው ሁሉ ተባርኮለታል። ነህም.1፥4። እኛም የሰኔን ፆም ብንፆም በዕለት ተዕለት ተግባራችን በረከት እናገኛለን።

3. ዝናብ ምህረትን ጠለ በረከትን እናገኛለን
የሰኔ ፆም በአገራችን የክረምቱ መግቢያ ላይ የሚፆም ፆም ነው ይህም መጪው የክረምቱ ወራት የተስተካከለ የምህረት ዝናም እንዲኖረው ያደርጋል በነብዩ ኢዩኤል ዘመን ዝናብ ጠፍቶ ዛፎቹ ሳይቀር በደረቁ ጊዜ በፆም በፀሎት ወደ እግዚአብሔር በተማፀኑ ሰዓት ዝናመ በረከትን አግኝተዋል። ኢዩ.1፥13-14

4. በረከተ ምርትን እናገኛለን
የሰኔ ፆም በሃገራችን ገበሬው ዘር መዝራት በሚጀምርበት ጊዜ የሚፆም ፆም ነው ሰለዚህም በዚህ ሰዓት የሚፆመው ፆም ዘርን እንዲባረክ በረከት እንዲበዛ ያደርጋል ይህም አገር ወገን ከረሃብ ከችግር ነፃ እንዲወጣ ያደርጋል በነብዩ ኢዩኤል እንደተገለጸው በፆም የዕህል የመጠጥ በረከት ይገኛል ። ኢዩ.2፥12-14

5. የነፋስ በረከትን እናገኛለን
ፆም በመንፈስ የደከመች የዛለች ነፍስን ያበረታል የነፍስን ቁስል ይፈውሳል ስጋዊ ኃይልን ያደክማል የሥጋን ፈቃድ ለነፍስ ያስገዛል መዝ.108፥24 ፤ ገላ.5፥24 የዓለምን ሃሳብ ያስወግዳል ከእግዚአብሔር ያስታርቃል ማቴ. 17፥21 ሚስጥር ይገልጣል ዘስ.34፥27-28 ፤ ዳን. 10፥1-3 "በአምላካችን ፊት እራሳችንን እናዋርድ ዘንድ ከርሱም የቀናውን መንገድ ለእኛና ለልጆቻችን ለንብረታችንም ሁሉ እንለምን ዘንድ ...... ፆምን አውጃለሁ " መጽሐፈ ዕዝራ.8፥21 ከመዋዕለ ፆሙ ረድኤት በረከት ያሳትፈን !

ፆሙን የኃጢአት መደምሰሻ የዲያብሎስ ድል መንሻ የመንግሥተ ሰማያት መውረሻ ያድርግልን አሜንንንን !!!

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#አሥራ_ሁለቱ_ሐዋርያት ✞

አሥራ ሁለቱ ሐዋርያት
ምንኛ ዕድለኞች ናቸው (፪)
ጸጋ መንፈስቅዱስ በጽዮን
አዳራሽ የወረደላቸው (፪)

ዞረው እንዲያስተምሩ በየምድባቸው(፪)
የዓለም ሁሉ ቋንቋ (፪)ተገለጸላቸው
#አዝ
ጴጥሮስ ሲጠባበቅ ያንን የተስፋ ቃል(፪)
መጣ መንፈስቅዱስ(፪) በነበልባል አምሳል(፪)
#አዝ
ደቀ መዛሙርቱ በመንፈስ ቢሰክሩ(፪)
ጉሽ ጠጅ ነው ብለው(፪)አይሁድ ተናገሩ
#አዝ
በጴጥሮስ ስብከት ጽድቅን የተመኙ(፪)
ሦስት ሺ አማኞች(፪) ባንድ ቀን ተገኙ
#አዝ
እንደ ባረክኻቸው ሐዋርያትን(፪)
አቤቱ ጌታ ሆይ(፪)እኛንም ባርከን(፪)

ከዚህም በኋላ እንዲህ ይሆናል፤ መንፈሴን በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ አፈስሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፥ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልምን ያልማሉ፥ ጐበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፤
፤ ደግሞም በዚያ ወራት በወንዶችና በሴቶች ባሪያዎች ላይ መንፈሴን አፈስሳለሁ፤
ኢዩ፪-፳፰፥፳፱

#ሼር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​ጾመ ሐዋርያት/የሰኔ ጾም

ጾመ ሐዋርያት ሐዋርያት በጽራሐ ጽዮን መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ወደ አገልግሎት ከመግባታቸውና ወደ ሀገረ ስብከታቸው ከመበተናቸው በፊት የጾሙት ጾም ነው፡፡ የጾሙበትም ምክንያት በማርቆስ ፪፥፳ እና በማቴወስ ፱፥፲፬ ላይ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረውን መሰረት በማድረግ ነው፡፡ ይኸውም የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ ቀርበው እኛና ፈሪሳዊያን ብዙ ጊዜ የምንጾመው ደቀመዛሙርትህ ግን የማይጾሙት ስለ ምንድን ነው? አሉት፡፡ ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፡-ሚዜወች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን ? ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል ያን ጊዜ ይጾማሉ፡፡››ብሎ እንደመለሰላቸው፡፡

በዚህ ምሳሌያዊ አነጋገር ሙሽራ የተባለው ካባ በመደረብ ፈንታ ዕርቃኑን ሆኖ በአክሊል ፈንታ የእሾህ አክሊል ደፍቶ በሚዜወቹ ፈንታ በጠላት ተከቦ በመዝሙርና በደስታ ፈንታ በልቅሶና በዋይታ ታጂቦ በክብር ዙፋን መቀመጥ ፈንታ በመስቀል ተሰቅሎ በጭንካር ተወጥሮ በቀራንይዎ አደባባይ ስለ እኛ የተሞሸረው/የተሰቀለው/ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ሚዜዎቹ የተባሉት ደግሞ ምንም እንኳን በሰርጉ እለት ከአንዱ በቀር (ከወንጌላዊ ዮሐንስ/ ከጎኑ ባይገኙም ኋላ መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው በሕይወትም በሞትም ሙሽራውን/ኢየሱስ ክርስቶስን/ የመሰሉ ሐዋርያት ናቸው፡፡

ይወሰዳል መባሉም እርገቱን ለመናገር ሲሆን ከዚያ በኋላ ይጾማሉ መባላቸው ደግሞ መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ለማለት ነው፡፡ ምክንያቱም ኢየሱስ ሲያርግ መንፈስ ቅዱስ ይመጣልና፡፡ በዚህ ላይ ልብ ልንል የሚገባን ጉዳይ ጾም በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበረ በሐዲስ ኪዳንም የቀጠለ ሥርዓት መሆኑን ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን የነበረ ስለመሆኑ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት እና አይሁድ ብዙ ጊዜ ይጾሙ እንደነበረ ተጽፏል፡፡

ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት"እናንተና አይሀድ የጾማችሁት ባለማወቅ ወይም በስህተት ስለሆነ ደቀ መዛሙርቴ አይጾሙም" አላለም፡፡ ነገር ግን ለጊዜው ከእኔ ጋር ናቸው ደስ ሊላቸው ይገባል፡፡ ከሄድኩ በኋላ ግን ይጾማሉ ብሏል፡፡ ይኸውም ጾም ከአዳም ጀምሮ እስከ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እና ደቀ መዛሙርቱ ከዚያም በክርስቶስ ታድሶና ተቀድሶ ለደቀ መዛሙርቱ የተሰጠ ከዚያም ለእኛ ለተከታይዮቻቸው የተላለፈ ሥርዓት መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡

ለጊዜው ሐዋርያት ሊጾሙበት ያልቻሉበት ምክንት ሊቃውንት ሲያብራሩ ፡-አንደኛ ጾም ሐዘን ነውና ሐዘኑም ኃላፊነትን ከመሸከም ጋር ተያያዥነት ያለው ነውና፡፡ ምክናያቱም መጾም አላማው ንስሐ እንደመሆኑ እንደ ቅዱስ ዳዊት ለግል ኃጢያት አሊያም እንደነነዌ ሰዎች ስለሀገር ጥፋት የሚያለቅሱበት የሚያዝኑበት ሁኔታ አለው፡፡ ክርስቶስ ደግሞ በስጋው ወራት ከአምላክነቱና ከሁሉ አባትነቱ ባሻገር ለሐዋርይት እንደ ሥጋ አባትም ወንድምም በመሆን የእነርሱን ኃላፊነት ተሸክሞላቸዋልና እርሱ በአካለ ሥጋ በአጠገባቸው እስካለ ድረስ ማዘን አልተገባቸውም፡፡

በሁለተኛነት ደግሞ ጾም ኃላፊነት ነው፡፡ኃላፊነቱን ለመሸከም ደግሞ ኃይል የሚሆናቸው መንፈስ ቅዱስ ያስፈልጋቸው ነበርና መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ እንዲጾሙ ጊዜ ሰጣቸው፡፡ ሦስተኛው ምክነያት አይሁድ ይጾሙት የነበረው በብሉይ ኪዳን ስርዓት ውስጥ ሆነው ነበር፡፡ ሐዋርያት ደግሞ የሐዲስ ኪዳን ልጆች ስለሆኑ መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው አሊያም አዲሱ ሰው በተባለው በክርስቶስ ደም ተጽናንተውና ሥጋውንና ደሙን ተቀብለው አዲሱን ሰው ለብሰው በአዲስ መንፈስና ኃይል በአዲስ ስርዓት መጾም ስለነበረባቸው በጊዜው አልጾሙም ነበር፡፡/ማቴ ፱፥፲፮-፲፯/

ይቀጥላል
ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እሺ በጣም ጥሩ በጠየቃችሁት ጥያቄ መሰረት።


በእዚህ ሳምንት ነገረ ማርያምን ወይም ስለ ድንግል ማርያም የምንማማር ይሆናል።

👉ይህ ክፍል እጅግ ሰፊ ስለሆነ በመጠኑ እንደ አቅማችን የምንማር ይሆናል። ይሄንን ትምህርት ለመማር እንዲረዳችሁ እንደ ንባብ ማጣቀሻ ሁላችሁም መጠቀም ያለባችሁ Application አለ እርሱም፦
⛔️ትምህርተ ተዋሕዶ ይባላል⛔️

ከታች እንልክላችኋለን አፕሊኬሽኑን እርሱን አውርዳችሁ በእዛ ማንበብ ትጀምራላችሁ ማለት ነው። ተዘጋጁ።👇👇👇👇👇👇

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🤲ሰላም የተወደዳችሁ የዝማሬ ዳዊት ተከታታዮቻችን🤲

በባለፈው ማንኛውም አይነት ጥያቄዎች ካላችሁ እንድትጠይቁ ያዘጋጀን ሲሆን የጠየቀ ሰው ግን አልነበረም።

👉አሁን ይሄንን ክረምት መሠረት በማድረግ የሃይማኖት ትምህርት በእዚሁ በቻናላችን መማር ልንጀምር ስለሆነ።

መማር የምትፈልጉ ኦርቶዶክሳዊያን በቅድሚያ

መማር እንፈልጋለን

ብላችሁ ኮመንት ላይ ሁላችሁም ላኩልን

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

አምላከ ተክለሃይማኖት ማረን

አምላከ ተክለሐይማኖት ማረን 2×
አምላከ ቅዱሳን ታረቀን 2×
ስለቃልኪዳንህ በቁጣ አታጥፋን
አዝ
ሐዋርያው ቅዱስ ተክለሃይማኖት
የኢቲሳ አንበሳ የኔ አባት
ቁጣውን አብርደው ተክለሐይማኖት
ለምልጃ ተነሳ የኔ አባት
ከሰማይ ካህናት ተክለሐይማኖት
ቤተሰብ ሆነሃል የኔ አባት
የሥላሴን መንበር ተክለሐይማኖት
ለማጠን በቅተሀል የኔ አባት
አዝ
ከከርቤ ከሚያ ተክለሃይማኖት
ከሰሊክም በልጧል የኔ አባት
የፃድቁ ፀሎት ተክለሐይማኖት
በእግዚአብሔር ፊት ሸቷል የኔ አባት
ስለቃልኪዳንህ ተክለሐይማኖት
አምላክ ይለመናል የኔ አባት
ፀሎትህ ሲደርስ ተክለሐይማኖት
እኛን ይታረቃል የኔ አባት
አዝ
ተማፅነንብሃል ተክለሃይማኖት
ጌታ ሆይ በስሙ የኔ አባት
በፃዲቁ ፀሎት ተክለሐይማኖት
በሰባረ አፅሙ የኔ አባት
ኢትዮጲያን በሙሉ ተክለሐይማኖት
አስተምሮ ሲመለስ የኔ አባት
አፅመ ርስቱ ሆነች ተክለሐይማኖት
ደብረ ሊባኖስ የኔ አባት
አዝ
የፃዲቁ መንፈስ ተክለሃይማኖት
ከቅዱሳን ጋራ የኔ አባት
ከልባችን ገብተህ ተክለሐይማኖት
ብርሃንን አብራ የኔ አባት
በፀሎት ስቆም ተክለሐይማኖት
ስምህን ስጠራ የኔ አባት
ነፍሴ ተደሰተች ተክለሐይማኖት
ሲርቀኝ መከራ የኔ አባት

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️ይህንን አስደናቂ ቪዲዮ ሁላችሁም እንድታዩት እለምናለሁ
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን✝

በእግዚአብሔር ፍጹም ሠላም እንደምን አላችሁ?

እንደ አምላካችን መልካም ፈቃድ በእዚህ ድምጽ:-
🤲የክርስቶስ ዳግም መምጣት ምልክቶቹ ምንድናቸው?
🤲በዓለም ላይ አሁን ላይ እየተከናወኑ ያሉ ለውጦች ምን ምን ናቸው?
🤲ስለ ሀሰተኛ ክርስቶሶች ታሪካዊ አመጣጦች
🤲ምን ማድረግ እንችላለን?

🤲በቅርብ ቀን ይጠብቁን🤲

በይሳኮር

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ይሄንን ማስታወቂያ ትላንት የለቀቅን ሲሆን እስከ አሁን 3 ጥያቄ ተጠይቋል። ሌሎችም ጥያቄ መጠየቅ የምትፈልጉ ካላችሁ መጠየቅ ትችላላችሁ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#ድንግል_ማርያም_ብዬ

ድንግል ማርያም ብዬ
ስማጸን በስምሽ (፪)
በቅድመ እግዚአብሔር
ልመናዬን አድርሽ (፪)

እኔ ደካማ ነኝ ኃጢአቴ የበዛ
እኔ ጎስቋላ ነኝ በደሌ የበዛ
ጊዜዬን ያባከንኩ በዋዛ ፈዛዛ
ጊዜዬን ያሳለፍኩ በከንቱ በዋዛ

እመብርሃን ስልሽ ፈጥነሽ ድረሽልኝ(፪)
ልመናዬን ሰምተሽ ቆመሽ ለምኝልኝ
ኃጢአቴ ቢበዛም ይዣለሁ አንቺን(፪)
አስምረሻልና በላዒ ሰብን
#አዝ
አንገት የሚያስደፋ በዝቶብኝ ኃጢአቴ
ምልጃሽን ፈለኩኝ ድንግል ሆይ እናቴ
ያን ክፉ ጨለማ እንዳላይ አደራ(፪)
ድንግል ሆይ ከልይኝ ከዲያብሎስ ጭፍራ
#አዝ
እመብርሃን እያልኩ ቆሜ ከደጅሽ
በብርሃን እጆችሽ እንባዬን አብሽ
ዓለም አታላይ ነች ወደሷ ተሳብኩኝ
ታማልጂኝ ብዬ አንቺኑ ተራብኩኝ

ሊቀ መዘምራን
ኪነጥበብ ወልደቂርቆስ

"ጻድቃን እኔን ይጠብቃሉ"
መዝ፻፵፩፥፯

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#የያረድ_ዉብ_ዜማ

የያረድ ዉብ ዜማ ድንግል እመቤቴ
ስጦታዬ ነሺ /2/ በምን አንደበቴ
እንዴትስ ባለ ቃል ማርያም ልበልሽ/2/

ምድርና ሰማዩ ተአምርሺን ይንገሩ 
ፍጥረታት በሙሉ ስለ አንቺ ይመስክሩ 
ተነግሮ የማያልቅ ድንቅ ነው ስራሽ 
ድንግል ሆይ እናቴ አምሳያም የለሺ 
ማርያም ድንግል እረዳቴ
የምትደርሺልኝ ነይ ስልሽ በጭንቀተ 
ታምርሺንም በአይነ አይቻለሁ 
ጽዮን ሆይ ስልሽ ድንግል ሆይ እጠግባለሁ 
#አዝ
የእግዚአብሄር ጥበቡ በአንቺ ተገለጠ 
የአዳም ዘር በሙሉ ከሞት አመለጠ 
የመዳን ምክንያት ማርያም አንቺ ነሽ
ለፍጥረቱ ሁሉ መሰላል የሆንሺ
ነገን ባላውቅ እኔን ቢያስፈራኚ 
አንቺ ካለሺኝ በፍጹም አልወድቅም 
በፊትሺም እንድቆም ለምስጋና 
ማርያም ልበልሽ በትህትና 
#አዝ
ትውልዱ በሙሉ ለምስጋና ይቁም 
ባንቺ ስለሆነ የቀረለት መርገም 
አዳም ከነልጁ በሰማይ በምድር 
ማርያም ማርያም ይበል ተአምርሺን ይናገር 
ጨለማው ከፊቴ ተገፈፈ 
ማርያም በምልጃሽ ልቤ አረፈ 
ከጎኔ ነይ ስልሺ እጽናናለሁ 
እሳት ገደሉን ሁሉንም አልፈዋለሁ 

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​​​ሰኔ 21 ለሚከበረው የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

#ሰኔ_20_እና_21

👉 ከእመቤታችን 33ቱ በዓላት አንዱ ነው፤ ህንጸተ ቤተክርስቲያን ይባላል።

የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን የታነጸው በዛሬዋ ቀን ነው አናጺውም እራሱ ባለቤቱ ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤ ቦታው ፊልጰስዩስ ነው፤ ቤተክርስቲያኗ የተሰየመችው ደግሞ በእመቤታችን ስም ነው።

ጴጥሮስ፤ ዮሐንስ በርናባስና ሌሎችም ሐዋርያት በፊልጰስዩስ ተሰብስበው ሳለ ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኪሩቤል ጀርባ ላይ ሆኖ እልፍ አእላፍ መልአክትን አስከትሎ ይወርዳል እመቤታችን በቀኙ ነበረች፤ 3 ድንጋዮችን አንስቶ ጎተታቸው እንደ ሰም ተለጠጡ እንደ ግድግዳም ሆኑ ዳግመኛም የብርሃን ምሰሶ ወረደ በሰማያዊቷ እየሩሳሌም አምሳያ አድረጎ አነጻት ሁለንተናዋም ተጠናቀቀ፤ ዳግመኛ በበነጋው ሰኔ 21 ቀን እመቤታችንን እና ቅዱሳን መልአክትን አስከትሎ ይወርዳል ቅዳሴ ቀድሶ ለሐዋርያቱ አቆረባቸው ፍጹም ደስታም ሆነ።

ከዚህ በኃላ ሐዋርያት ከጌታ እንዳዩት በዓለም ዞረው ቤተክርስቲያን አንጸዋል። ከዚያ በፊት የነበረው የነሶሎሞን ቤተ መቅደስ የአይሁድ ምኩራብ የአይሁድ ስርዓተ አምልኮ መፈጸሚያ እንጂ የአዲስ ኪዳን የቁርባንም ሆነ የጥምቀት ስርዓት መፈጸሚያ አልነበረም፤ ታዲያ ሐዋርያት የት ነበር ህዝቡን የሚያጠምቁት የሚያቆርቡት ካሉ በየሰው ቤት ነበር።

ዳግመኛ በዛሬዋ ቀን ታላቁ ነብይ ኤልሳዕ አረፈ። ይህ ነብይ በ 12 ጥማድ በሬ ሲያርስ ቴስቢያዊው ነብዩ ኤልያስ ተከተለኝ አለው ምንም ሳያቅማማ ሀብት ንብረቱን ትቶ ተከተለው፤ ኤልያስ በእሳት ሰረገላ ከማረጉ በፊት ምን እንዳደርግልህ ትፈልጋለህ ይለዋል ባንተ ላይ ያደረ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ እጥፍ ድርብ ሆኖ ይደርቢኝ ይለዋል፤ እንደ ቃሉ ሆነለት ተደረገለት፤ ኤልያስ አንድ ሙት ሲያስነሳ ኤልሳዕ ሁለት ሙት አስነስቷል፤ ኤልያስ አንድ ጊዜ ባህር ሲከፍል ኤልሳዕ ሁለት ጊዜ ባህር ከፍሏል።

የእምቤታችንን የኤልሳዕ ጋን ይላታል ኤልሳ የመረረውን ውኃ እንዳጣፈጠ እመቤታችንም ይህን መራራ ዓለም ጌታን በመውለዷ አጣፍጣዋለች፤ የዚህ ነብይ ድንቅ ታሪኩ 2ኛ ነገስት ላይ በስፋት ተጽፏል ሰኔ 20 ቀን እረፍቱ ነው ቤተክርስቲያን የዛሬውን ቀን እመቤታችንን እና ነብዩን አስባ ትውላለች።

ከበዓሉ ያሳትፈን የእመቤታችን ምልጃና ረዳትነት አይለየን!

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

👉 የሰኔ ማርያም ወረብ

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

👉 የሰኔ ማርያም እስመለ ዓለምና
ምልጣን

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

👉 @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#ሐዋርያት_ተባበሩ ✞

ሐዋርያት ተባበሩ
በአዲስ ቋንቋ እየተናገሩ
ቃሉን አስተማሩ

ከዐረገ በኋላ በእስረኛው ቀን
ወደ ዓለም ላከው ጰራቅሊጦስን
በዝግ ቤት ውስጥ ቆዩ ቀኑን ሲጠብቁ
የተሰጣቸውን ተስፋውን እስኪያውቁ
#አዝ
ቀኑም ደረሰና ሃምሳኛው ዕለት
ተሰብስበው ሳሉ በአንድነት ጸሎት
መንፈስ ቅዱስ ታየ በነደ እሳት
#አዝ
ያ የተናገረው ያ የተስፋ ቃል
ወረደ ከሰማይ በእሳት አምሣል
ጴጥሮስ አሳመነ ሦስት ሺ ነፍሳት
ያን ጊዜ ገሊላ በሰጠው ትምህርት
#አዝ
ከሦስት አካል አንዱ መንፈስ ቅዱስን
ልኮ አናገራቸው ሁሉን በልሳን

መዝሙር
ኪነጥበብ ወልደቂርቆስ

"ድንገት እንደሚነጥቅ ዓውሎ ነፋስ ከሰማይ ድምፅ መጣ ተቀምጠው የነበሩበትንም ቤት ሁሉ ሞላው።
እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጡባቸው  በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው"
ሐዋ ፪፥፩-፬

#ሼር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​#የቀጠለ

ሐዋርያት የጾሙት ጾም የኢየሱስ ክርሰቶስን ፈለግ መከተላቸውን የሚያሳይነው፡፡ መምህራቸውና አምላካቸው ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዳኖስ ወንዝ በዮሐንስ እጅ ከተጠመቀ በኋላ ሌላ ሥራ ሳይጀምር ወደ ገዳመ ቆርንቶስ ገብቶ እንደጾመ ሁሉ እነርሱም በመንፈስ ቅዱስ ከተጠመቁ በኋላ አገልግሎታቸውን ከመጀመራቸውና ወደየሀገረ ስብከቶቻቸው ከመበተናቸው በፊት እግዚአብሔር መንገዳቸውን የተቃና ሥራቸውንም የተሳካ ያደርግላቸው ዘንድ ጾመዋል፡፡

ይህን ጾም ሐዋርያት ጾመው በረከት ያገኙበት ከመሆኑ ባሻገር ጌታችን ጾሞ ጹሙ እንዳላቸው እነርሱም ደግሞ ተከታይዎቻቸውን ያንኑ መልዕክት የደገሙበት ነው፡፡ በክርስቶስ ደም መሰረት ላይ እና በሐዋርያት ትምህርትና ትውፊት ላይ የተመሰረተችው ቤተ ክርስቲያናችንም ይህንን ጾም በዐዋጅ እንድንጾመው ሥርዓት ሠርታልናለች፡፡

ጾሙ ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ የጾሙት እንደመሆኑ መጠን ከጌታ ትንሣኤ ከሃምሳኛው ቀን በኋላ ማለትም ከጰራቅሊጦስ ዕሁድ ማግስት ሰኞ ጀምሮ በቅዱስ ጳውሎስና በቅዱስ ጴጥርስ በዓለ እረፍት መታሰቢያ በሆነው ሐምሌ አምስት ቀን ፍጻሜውን ያገኛል፡፡ የቀናቱ ብዛትም በዐቢይ ጾም መባቻ ሁኔታ የሚወሰን ይሆናል፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን ጾሙን የበረከት፣ የንስሐ ፣ ደዌን ማራቂያ፣ ዲያቢሎስን ድል መንሻ ያድርግልን!!!

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
አሜን!

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​​​ሰኔ 12 #የቅዱስ_ሚካኤል ዓመታዊ በዓል!

እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለእናታችን ቅድስት አፎሚያ አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ። ሰኔ 12 ቅዱስ ሚካኤል እናታችን ቅድስት አፎሚያን ከጠላት ዲያብሎስ እጅ ያዳነበት ፣ እናታችን ቅድስት አፎሚያ እረፍቷ ነው ።እግዚአብሔር ከቅዱሱ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ፣ ከእናታችን ቅድስት አፎሚያ በረከት ተካፋይ ያድርገን ።

👉 በወርኃ ሠኔ መታሰቢያ ከሚደረግላቸው ቅዱሳን መካከል እግዚአብሔርን የሚፈራ የአስተራኒቆስ ሚስት የሆነች የቅድስት አፎምያን ታሪክ በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡

ቅድስት አፎምያ በትዳር በነበረችባቸው ዘመናት እግዚአብሔርን ከሚወድ ባለቤቷ ጋር እግዚአብሔርን ስታገለግለው የኖረች ሴት ነበረች፡፡ በየወሩ በ29 ቀን የጌታችንን የልደቱን፣ ወር በገባ በ21 የእመቤታችንንና ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያደረጉ ነዳያንን ይጎበኙ እንደነበር ታሪካቸው ይነግረናል፡፡

ባለቤቷ አስተራኒቆስ ከዚህ ዓለም የሚያርፍበት ጊዜ እንደደረሰ ባወቀ ጊዜ ይሰጡት የነበረውን ምጽዋት እና የሦስቱን በዓላት መታሰቢያ ማድረግ እንዳታስታጉል ከአደራ ጋር አዘዛት፡፡ እሷም የመልአኩን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ያሥልላት ዘንድ ባለቤቷን ጠይቃ አሠርቶ ሰጣት፡፡ በከበረ ቦታም አኖረችው፡፡

ባሏ ካረፈ በኋላ ያዘዛትን መንፈሳዊ ሥራ ከወትሮው አስበልጣ መሥራት ቀጠለች፡፡ የሰው ልጆች ጠላት የሆነው ሰይጣንም በመልካም አገልግሎት ስትበረታ ባያት ጊዜ ዝም ብሎ ሊተዋት አልወደደም፡፡ በመጀመሪያ ባል ሳታገባ ማገልገሏን ትታ፣ ሌላ ባል አግብታ፣ ልጅ ወልዳ እንድትኖር በብዙ ማባበል ጠየቃት፡፡ ባሏ መንግሥተ ሰማያትን ስለወረሰ ምንም ምጽዋት እንደማይሻ አስመስሎ ነገራት፡፡

ቅድስት አፎምያ ግን ዳግመኛ ትዳር ላለመመሥረት ቃል ኪዳን እንደገባች ርግብንና ዖፈ መንጢጥን አብነት አድርጋ፤ እነሱ እንኳ በሕይወት ዘመናቸው ከአንድ ባል ውጪ ሌላ ባል እንደማያውቁ በመጥቀስ አሳቡን እንደማትቀበለው ገለጸችለት፡፡ ሰይጣንም አስመሳይ መሆኑ አላዋጣ ሲለው ማንነቱን ቀይሮ ሊያንቃት ቢሞክር የእግዚአብሔርንና የቅዱስ ሚካኤልን ስም ጠርታ አባረረችው፡፡ እሱም ተመልሶ መጥቶ እንደሚያጠፋት ዝቶባት እንደአቧራ በኖ፤ እንደ ጢስም ተኖ ጠፋ፡፡

በሠኔ ፲፪ ቀን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያዘጋጀች ሳለች ሰይጣን ብርሃናዊ መልአክ መስሎ መጣ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ገልጾ የመጀመሪያውን የመሰለ ከንቱ ምክሩን አሰማምሮ አቀረበላት፡፡ አሳቡንም የእግዚአብሔር ፈቃድና አሳብ እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን ሞከረ፡፡ ሰይጣን አስቀድሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገዳመ ቆሮንቶስ መጻሕፍትን እየጠቀሰ እንደተፈታተነው ሁሉ ቅድስት አፎምያንም ለማሳመንም አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን፣ ዳዊትን የመሳሰሉ ደጋግ አባቶችን ታሪክ እየጠቀሰ ወደ ትዳር እንድትገባ ደጋግሞ ወተወታት፡፡

ቅድስት አፎምያም በእግዚአብሔር ኃይል ጸንታ በቅዱስ ሚካኤልም ተራዳኢነት ታምና “የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክ መንፈሳዊ ማረጋገጫህ የሆነው የመስቀል ምልክት የታለ?” በማለት በምድራዊ ንጉሥና በጭፍራው መካከል የሚኖርን የጋራ መግባቢያ መንገድ ዋቢ አድርጋ ጠየቀችው፡፡

ለጊዜው “በኛ በመላእክት ዘንድ እንዲህ አይደለም” ብሎ ሊሸነግላትና አቋሟን ሊያስቀይራት ሞከረ፡፡ ከቤቷ ያለ የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ላይ ያለውን ምልክት አብራርታ የእሱ ግን ከዛ ጋር አንድነት እንደሌለው አረጋገጠችበት፡፡ ከቤቷ ላለው ለቅዱስ ሚካኤል ሥዕል እጅ እንዲነሣ ጠየቀችው፡፡ በዚህ ጊዜ መልኩ ወደ ትክክለኛ ማንነቱ ተለወጠና ጨለማ ለብሶ እየዛተ አነቃት፡፡ ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን “ድረስልኝ” እያለች በጠራችው ጊዜ መልአኩም ፈጥኖ በመድረስ ከሰይጣን እጅ አዳናት፡፡

የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለሰይጣኑ ተገቢውን ቅጣት ሰጥቶ ቅድስት አፎምያን ባረካት፡፡ የዕረፍት ቀኗ በዚህ ቀን መሆኑን ነግሮ ቤቷን እንድታዘጋጅ አዘዛት፡፡ የበዓሉን ዝግጅት አከናውና ሥጋ ወደሙን ተቀብላ ኤጲስ ቆጶሱንና ካህናቱን እንደየመዓርጋቸው ጠርታ በቤቷ አክብራ ተቀበለቻቸው፡፡ ለነዳያንና ለጾም አዳሪዎች በኤጲስ ቆጶሱና በካህናቱ እጅ ገንዘቧን መጽውታ መንገዷን አሳመረች፡፡ ስለ ኃጢአቷ እንዲጸልዩላት ተማፅና በፊታቸው ተንበርክካ ጸለየች፡፡ ባሏ ያሠራላትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አቅፋ ስማ ከተማጸነች በኋላ ሠኔ ፲፪ ቀን በሰላም ዐረፈች፡፡

ይህች የታመነች ቅድስት አፎምያ በሰላም እስክታርፍ ጊዜ ድረስ የተጓዘችበትን መንፈሳዊ ጎዳና አስተውለን ይሆን? አስቀድማ ከባሏ ጋር አንድ ሆና በታማኝነት ፈጣሪዋን አገለገለችው፡፡ በኋላም የባሏን ኑዛዜ አክብራ ምንም እንኳን ኃጢአት ባይሆንባትም በሁለተኛ ትዳር ራስዋን ማጠላለፍ አልፈለገችም፡፡ በጎ ሥራ አብልጣ በመሥራት እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት ተፋጠነች እንጂ፡፡

ሰይጣን ልጅ አለመውለዷን ተጠቅሞ ያቀረበላትን የጋብቻ ጥያቄ ውድቅ በማድረግ “መንፈስን ሁሉ አትመኑ፤ መናፍስት ከእግዚአብሔር እንደሆኑ መርምሩ” ተብሎ በቅዱሳት መጻሕፍት የታዘዘውን መመሪያ ተጠቅማ ሰይጣንን በተወክሎ እግዚአብሔር ተቃውማ አሸነፈችው፡፡ የቅዱስ ሚካኤልን ርዳታ ያገኘችውና በሰላም ዐርፋ ወዳገለገለችው እግዚአብሔር በክብር የሔደችው በጽናት ተጋድላ ነው፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በጸሎቷ ይማረን፤ የቅዱስ ሚካኤል የረድኤቱ ኃይል ሁላችንንም ይጠብቀን፣ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…
Подписаться на канал