ortodoxmezmur | Неотсортированное

Telegram-канал ortodoxmezmur - ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

134932

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . ዝማሬ ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Подписаться на канал

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#አርሴማ

አርሴማ አርሴማ ቅድስት ሰማዕት(2)
ሞገስ አግኝተሻል በክርስቶስ ፊት

አርሴማ------ታምርሽ ልዩ ነው
አርሴማ------ገድልሽ አስደናቂ
አርሴማ------ስምሽ ብርሃን ነው
አርሴማ------ማለዳ ፈንጣቂ

አዝ_______________

አርሴማ------ስምሽን እየጠራ
አርሴማ------ጠግቧል የተራበው
አርሴማ------ምስኪኑም ዘመረ
አርሴማ------ባንቺ አልፎ መከራው

አዝ_______________

አርሴማ------ፅኑ ነው ኪዳንሽ
አርሴማ------የተሰጠሽ ከአምላክ
አርሴማ------በአይኔ አይቻለው
አርሴማ------ጠላት ሲንበረከክ

አዝ_______________

አርሴማ------ዓለም ይስማው ዛሬ
አርሴማ------ዜና ተጋድሎሽን
አርሴማ------ይገረም ይደነቅ
አርሴማ------ይመስክር ዝናሽን

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​#አርሴማ_ቅድስት_ሰማዕት

አጠር በጠር ያለ ታረኳ
በቀሲስ ሄኖክ ወልደ- ማርያም

የወለላይቱ እመቤት ልጆች ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ከሚያከብሩ ብሩካን ከሆኑ፤በጾም በጸሎት በስግደት በትጋት ከሚኖሩ ከአባቷ ከቅዱስ ቴዎድሮስ ከእናቷ ከቅድስት አትናስያና በጥር 6 ቀን የተወለደች ደገኛ የገድል አርበኛ ናት፡፡

በተለይ ስትወለድ ይህ ቀረሽ የማትባል እጅግ መልከኛ እና ግርማዋ የሚያስፈራ ነበር፡፡ እናት እና አባቷም በጾም በጸሎት በስዕለት ስላገኟት እስከ 3 ዓመት ካሳደግዋት በኃላ በእመቤታችን በድንግል ማርያም ስም በተሰራች ቤተ ክርስትያን ታገለግል ዘንድ ሰጧት፡፡ እመቤታችንን 12 ዓመት አገልግላ ያለፈቃድዋ በቤተሰቦችዋ ግፊት በ15 ዓመቷ ዳሯት፡፡ ሰማዕቷ ግን ዓለማዊ ሕይወት ባለመፈለግዋ ወደ ገዳማዊ ምናኔ ህይወት ገብታለች፡፡

በዚያን ዘመን ብዙ ሰማዕታት ያስፈጀ ጨካኙ የሰው አውሬ ካሃዲው ዲዮቅልጥያኖስ መላኳ ውብ የሆነ ብላቴና ድንግል ሴት ሊያገባ ሽቶ በየአገሩ ሁሉ ፈልገው መርጠው ያመጡለት አንድ አሽከሮቹን አዘዘ፡፡

እንግዲህ የሰማቷ አሳዘኝ የመከራ ሕይወት ከዚህ ነው የሚጀምረው፡፡

የዲዮቅልጥያኖስ ሠራዊቶች አርሴማ የምትባል ውብ ሴት በሮሜ በአንድ ገዳም እንዳለች ሰሙ፡፡ አዋቂዎችም የሰማዕቷን ውብ መልኳን ስለው ለንገሡ ለዲዮቅልጥያኖስ ላኩለት፡፡ ንጉሡም ስዕሏን ባየ ጊዜ እጅግ ደስ አለውና በሥጋዊ ጋብቻ አብሯት ሊኖር እንዳሰበ ለመኳንንቱ ነግሮ ለሠርግ እንዲመጡ አዘዘ፡፡

ቅድስት አርሴማ ይህንን በሰማች ባወቀች ጊዜ ከደናግሉ ጋር የንጉስ ድርጣድስ ግዛት ወደ ሆነው አርመንያ አገር ሸሸች፡፡ ንጉስ ዲዮቅልጥያኖስ የከበረች አርሴማን አስፈልጎ ባጣት ጊዜ በአርመንያ እዳለች ሰማ፡፡

ዲዮቅልጥያኖስም ለአርመንያው ንጉሥ ለድርጣድስ ከእሱ ሸሽታ እንደሄደች እና ባስቸኳይ አስጠብቆ እንዲልክላት አዘዘው፡፡ ደናግሉ ይንን በሰሙ ጊዜ ወደ ሌላ ቦታ ተሰወሩ፡፡ ንጉሡም ቅድስት አርሴማን በክብር ያመጧት ዘንድ አዘዘ፡፡ ሰማዕቷም ወደ እርሱ መምጣትን እንቢ ባለች ጊዜ በመሬት እየጎተቱ ወደ ንጉሡ አቀረቧት፡፡

ድርጣድስ የቅድስት አርሴማን ደም ግባት እና ውበት ባየ ጊዜ ድንግልናዋን ሊያረክስ ሽቶ የመንፈስ እናቷን አጋታን አባብላ እሺ ታሰኛት ዘንድ አዘዛት፡፡ አጋታም ወደ ሰማዕቷ ሄዳ ልቧን አስጨከነች እንዲህም አለቻት ‹‹እወቂ ይህ ርኩስ አረሚ እንዳያረክስሽና ሰማያዊ ምሽራሽን ክርስቶስን እንዳትተይ›› ብላ አጸናቻት፡፡

ንጉሥ ድርጣድስም ሰማዕቷን ይዞ ወደ እልፍኝ ሊያስገባት ከአደባባይ መካከል ተነስቶ ድንግል አርሴማ በእጁ ያዛት፡፡ በዚያን ጊዜ በቅድስት አርሴማ ላይ የእግዚአብሔር ኃይል አደረባትና በምድር ላይ ጣለችው፡፡ ድርጣድስም በጦትነት እጅግ የጸና አርበኛ ስለነበር በታናሽ ብላቴና ስለተሸነፈ መኳንንቱ ፊት ስለተዋረደ አፈረ፡፡

ከዚህ በኃላ በሰው አንደበት ለመናገር የሚከብድ መከራና ስቃይ አጸናባት፡፡ ሰማዕቷም ከንጉሡና ከጋሻ ጃግሬዎቹ የሚደርስባትን መከራ በመታገስ በረታች፡፡ ንጉሥ ድጣድስ በሰማዕቷ ላይ የሚያደርሰውን ሥጋዊ መከራ የልቡ ስላልደረሰለት ጡቷን በማስቆረጥ ዓይኗን በወረንጦ በማስወጣት ቢያሰቃያትም ሰማዕቷ ይበልጥ በክርስቶስ ፍቅር ጸናች፡፡ በሚደርስባትም ነገር ደስ ተሰኘች፡፡

ወዳጆቼ እኛ በሚደረስብን ሥጋዊ ህመም ስቃይ መከራ ፈተና እንደሰታለን? አንደሰትም ይልቁንም እናማርራለን፡፡ ምንያቱም የክርስቶስ የመከራ ሕይወት ውስጣችን ስላልገባ ነው፡፡ ክርስቶስ ጋር ለመድረስ መንገዱ፣በአጋንንት እና በሥጋ እየተጎዱ መሆኑን ስለማንረዳ ነው፡፡ ብንረዳም የደስታ እንጂ የመከራ ትከሻ ስለሌለን ነው፡፡ የመከራ ትከሻ ቢኖረንም ትዕግስት ስለሌለን በመከራችን አንጸናም፡፡

በመጨረሻም ንጉሥ ድርጣድስ የሚያደርገውን ሲያጣ አንገቷን በሰይፍ ሊያስቆርጥ ወሰነ፡፡ ከዚህ በኃላ ንጉሥ ድርጣድስ ቡርክት ቅድስት አርሴማን ወደ መገደያ ወንዝ እንዲወስዷትና በዚያም የከበረ ራሷን ይቆርጧት ዘንድ አዘዘ፡፡ ንጉሡም ቅድስት አርሴማን ወታደሮች አንገቷን ሲቆርጧት ያይ ዘንድ ከእርሷ ጋር ወጣ፡፡ ሰማዕቷ በምትገደልበት ትይዩ ከሠራዊቱ ጋር ተቀመጠ፡፡

የእጃቸው ክንድ የበረታ ልባቸው ግን የጨከነ ሮማውያን ወታደሮች ሰይፍ ይዘው ወደ ሰማዕቷ ቀረቡ፡፡ ሰማዕቷ ሞቷ ሰማያዊ እረፍቷ ስለሆነ በደስታ ትመለከታቸው ነበር፡፡ ቅድስት አርሴማም ወታደሮቹን የጸሎት ጊዜ እንዲሰጧት ጠይቃቸው ፈጣሪዋን ካመሰገነች በኃላ ፊቷን ወደ ምስራቅ መልሳ ወገቧን ታጥቃ አንገቷን ከፍ አድርጋ ለሚቆርጧት ታመቻችላቸው ነበር፡፡

ቆራጮች ወታደሮች ከቅድስት አርሴማ ግርማ የተነሳ ደንግጠው ሰይፋቸውን እንደያዙ በምድር ላይ ወደቁ ሰይፋቸውንም ጣሉ፡፡ ሰማዕቷም እያበረታታች ‹‹የታዘዛችሁትን ፈጽሙ›› ትላቸው ነበር፡፡ ወታደሮቹም ‹‹እኛስ ወዳንቺ መቅረብ እና አንገትሽን መቁረጥ አልቻልንም በግንባርሽ ላይ ያለው ትዕምርተ መስቀል አስፈርቶና፤ግንባርሽን ካልሸፈንሽልን አንገትሽን ፈጽሞ ልንቆርጥ አንችልም›› አሏት፡፡

ሰማዕቷም ለወታደሮቹ ፊቴን የምሸፍንበት ቁራጭ ልብስ ወይም ቁራጭ ጨርቅ ስጡኝ አለቻቸው፡፡ እነሱም ቁራጭ ጨርቅ ጣሉላት እሷም ፊቷን ሸፈነች፡፡

ቅድስት አርሴማም ንጉሥ ድርጣድስ እና ሠራዊቱ ሕዝቡም እየተመለከቱ ምስከረም 29 ቀን አንገቷን በሰይፍ ቆረጡ፡፡ ወዳጆቼ እኛን ጌታችን እንደ እነ ቅድስት አርሴማ፣ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ፣ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ወዘተ አንገታችሁን ተቆረጡልኝ ሰማዕት ሁኑልኝ አላለንም፡፡ ኃጢአትን ከእናንተ ሰውነት ቆርጣችሁ ጣሉት ነው ያለን፡፡

የዝሙትን ፍላጎት ከሰውነታችሁ ቁረጡና ደም አላባ ሰማዕት ሁኑ ነው የተባልነው፡፡ የኃጢአቶችን ተቀጽላ ከሥጋችሁ ላይ ቁረጡና በንስሐ ጻድቅ ሁኑ ነው ያለን፡፡ እንደ ሰማዕታት በደማችሁ ዋጋ ገነት ግቡ ሳይሆን በደሜ ፈሳሽት መንግስቴን ውረሱ ነው ያለን፡፡ እንደ ሰማዕታት ጽኑ መከራን በሥጋችሁ ተቀበሉ ሳይሆን ቅዱስ ሥጋዬን ብሉና የርስቴ ተካፋይ ሁኑ ነው ያለን፡፡ ሰማዕት ሁኑ ሳይሆን በእኔ መስዋዕትነት ዳኑ ወደ መንግስቴ ጎዳና አቅኑ ነው ያለን፡፡ አወይ አለመጠቀማችን እንደ እኛ ያደለው ማን አለ?

ቅድስት አርሴማም በሰይፍ ስትሰየፍ ከአንገቷም ደም፣ውኃ፣ወተትና ማር እንደ ክረምት ነጠብጣብ እየተንጠባጠበ መነጨ፡፡

ደም ከአንገቷ የመነጨው ስለ ሃይማኖትዋ ቆራጥነት ስለ ሞት አለመፍራት እና የጌታችንን መከራ ተሸክማ ሰማዕት ስለሆነች ነው፡፡

ውኃ የፈሰሰው ስለ ብዙ ጸሎትዋ፤ስለልመናዋና የቤተ ክርስትያን መጻሕፍትንና ምስጢራትን ሁሉ ልብ ስለምታደርግ ነው፡፡

ወተት የመነጨላት ስለ ክብሯ ስለ ከፍታዋ እና ንጽሃ ድግልናዋን ስለጠበቀች ነው፡፡

ማር የወረደው ስለሚያስደንቅ የፊቷ ወዝ፣ደም ግባቷ፣ስለ ጣፋጭ የከንፈሯ ቃልና የሰማዕታት ሁሉ እህት ስለሆነች ነው፡፡

ከዚህ በኃላ ብሩህ የሆነ የደመና አምድ ወረደና በላይዋ ጋረዳት፡፡ ወደ ሰማይም እንደ መብረቅ ሳባት፡፡ የቅዱሳን መላእክትም ማህበር ነፍሷን አሳረጓት፡፡ በክብር በእልልታ በዝማሬና በማህሌት ሃሌ ሉያ እያሉ ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም አስገቧት፡፡

እርሷ እንደ ሞተች ባወቁ ጊዜ ወታደሮቹ ደናግሉን ሁሉ ጫማቸውን እየበሱ እራሳቸውን ቆረጡ፡፡ ቁጥራቸውም ሰባ ሁለት ነፍሳት ነበሩ፡፡

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

📚ሚተራሊዮን በpdf የምታገኙበትን ከ 75,000 በላይ አንባቢያን ያሉበትን ቻናል ይቀላቀሉ።

ከ350 በላይ ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍ በPDF ያገኙበታል።
👇🏾👇🏾👇🏾
/channel/+iJJR03jZN9FkMjg0
/channel/+iJJR03jZN9FkMjg0

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#አዘክሪ_ድንግል

አዘክሪ ድንግል አዘክሪ 
ለልጅሽ አሳስቢ አዘክሪ 
ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን /2/ 

ካንቺ መወለዱን አዘክሪ 
በቤተልሔም አዘክሪ 
በጨርቅ መጠቅለሉን አዘክሪ 
መኝታው ግርግም አዘክሪ 
ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን 

በዚያ በብርድ ወራት አዘክሪ 
የገበሩለትን አዘክሪ 
የአድግና የላም አዘክሪ 
እስትንፋሣቸውን አዘክሪ 
ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን 

በግብጽ በረሃ አዘክሪ 
መሠደድሽን አዘክሪ 
የአሸዋውን ግለት አዘክሪ 
ርሃቡና ጥሙን $ አዘክሪ 
ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን 

በመቃብሩ ዘንድ አዘክሪ 
ባነባሽው እንባ አዘክሪ 
አሳስቢ ድንግል ሆይ አዘክሪ 
ገነት እንድንገባ አዘክሪ 
ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​#ፆመ_ፅጌ / የፅጌ ፆም

የእመቤታችን ስደት በጾም በጸሎት የምታስቡ ወይም የምታሳልፉ የእመቤታችን የድንግል ማርያም የቃልኪዳን ልጆች ከወዲሁ እንኳን አደረሳችሁ

ለጽጌ ጾም ካላቸው ፍቅር የተነሳ አንዳንድ ምዕመናን ጽጌ ጾም መቼ ነው የሚገባው እያሉ የሚጠይቁ ስላሉ ከወዲሁ ለማስታወስ ጾመ ጽጌ ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 5 ያለው አንድ ወር ከዐሥር ቀን ወይም 40 ቀን ወርኃ ጽጌ፣ ዘመነ ጸጌ፣ ተብሎ ይጠራል፡፡

በነዚህም ቀናት በየቤተክርስቲያኑ የሚነበቡ ምንባቦች፣ የሚዘመሩት መዝሙሮች፣ የሚሰበከው ስብከት፣ የሚቆመው ማኅሌት በጠቅላላው የሚነገረው ስብሐት እግዚአብሔር ሁሉ ሰማይ በከዋክብት ምድር በጽጌያት አሸብርቀው የሚታዩ መሆናቸውን የሚገልጽ ነው፡፡

ወርኃ ጽጌ ለሚከናወነው መንፈሰዊ አገልግሎት መነሻው "መልአኩ ሕፃኑንና እናቱን ወደ ግብፅ ይዘሃቸው ሽሽ፣ የሕፃኑን ነፍስ ሊገድሉት ይፈልጋሉና" ሲል ለዮሴፍ በሕልሙ በነገረው መሠረተ ዮሴፍም ሕፃኑንና እናቱን ድንግል ማርያምን ይዞ ወደ ግብፅ መሰደዱና እመቤታችንና ሕፃኑ ሦስት ዓመት ከመንፈቅ በስደት ከኖሩ በኋላ /ራእይ.12፣6/ ወደ አገራቸው ወደ ናዝሬት የመመለሳቸው መታሰቢያ ነው፡፡ /ማቴ 2፣13-23፣ ት.ኢሳ.19፣1፣ እንባቆም 3፣6-7፣ መዝ.83፣3/፡፡

ይህንንም በ14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተነሡ አባ ጽጌ ብርሃን ፍሬ ከአበባ አበባም ከፍሬ እንደሚገኝ ሁሉ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምንና ልጇን ኢየሱስ ክርስቶስን በአበባና በፍሬ እየመለሰ በሚያስረዳው ድርሰታቸው እንዲህ በማለት ገልጸውለታል፡፡ "አፈወ ሮማን ማርያም ጽጌ ቀናንሞ ወአበሜ፣ እስከ ተጸምሐየየ በጾም ዘመልክዕኪ ጊዜ ድክታሜ፣ እምተመነይኩ ተሳትፎ ከመ አኅትኪ ሰሎሜ፣ ወፍሥሓኪ ዘአልቦ ፍጻሜ"፡፡ ሲተረጎምም የሮማን ሽቱ የቀናንሞ አበባ የምትሆኚ ማርያም ሆይ፣ በርሃብ በጾም አበባ የመሰለ የመልክሽ ደም ግባት እስኪጠወልግ ድረስ በስደትና በልቅሶ የደረሰብሽን ችግርና ድካም መከራሽንም ሁሉ እንደ እኅትሽ እንደ ሰሎሜ አብሬሽ ብቀበል ምኞቴ ነበር፤ በዚህ ፍጻሜ የሌለውን ደስታሽን እሳተፍ ነበር፡፡

እንዲሁም አባ አርክ ሥሉስ በስደቷ የደረሰባትን ኀዘን ፣ ልቅሶና ሰቆቃ አስመልክተው በደረሱት "ሰቆቃወ ድንግል" በሚለው ድርሰታቸው እንዲህ አሉ፣ ፀሐይን የምትለብሽ የብርሃን ልጅ ቅድስት ድንግል ማርያም ከክፉ ከሄሮድስ ዘንድ ልጅሽን ባሸሸሽ ጊዜ የደረሰብሽን ችግሮች ጨረቃን የሚጫሙ እግሮችሽ በመንገድ ብዛትና በአሸዋ ግለት እንደ ጎበጎቡ ሲሰማ ሰው ይቅርና ድንጋዩም ባለቀሰ ነበር”

የእመቤታችን የስደቷ መታሰቢያ ወር በቤተ ክርስቲያናችን የሚከበረው በማኅሌት፣ በቅዳሴና በዝክር ነው፡፡ በወርኃ ጽጌ ባሉት ሳምንታት ከቅዳሜ ማታ እስከ እሑድ ጠዋት አበው ካህናት የሚያቀርቡት ዝማሬ ከቅዱስ ያሬድ ድጓ፣ ከማኅሌት ጽጌና ከሰቆቃው ድንግል የተውጣጣና ሦስት ወገን ያለው ነው፡፡ ዝክሩም፣ በአሁኑ ወቅት በከተሞች አካባቢ እየተረሳ ቢመጣም፣ ዘወትር እሑድ የአንድ አካባቢ ሰዎች ማዕከላዊ በሆነ ቦታ ተሰባስበው በእመቤታችን ስም የሚዘክሩት ነው፡፡

ዐቅመ ደካሞች፣ ድሆችና መንገደኞች ተጠርተው በእመቤታችን ስም እንዲበሉና እንዲጠጡ ይደረጋል፡፡ ይህም ትውፊት እመቤታችን ወደ ኢትዮጵያ በመጣች ጊዜ ኢትዮጵያውያን አባቶችና እናቶች ያደረጉላትን መስተንግዶ ለማሰብ ነው፡፡

ከእመቤታችን በረከት ያሳትፈን አሜን!!!
ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ዘመነ ጽጌ
 
ዘመነ ጽጌ የሚባለው ከመስከረም ፳፮ እስከ ኅዳር ፭ ያለው ነው። ይህ ወቅት ዐቢይ የምስጋና ቀናት ያለው ሊቃውንቱ በማሕሌት፣ ምእመናን በፍቅር ሆነው የእናታችን የድንግል ማርያምን ስደት ከተወዳጅ ልጇ ጋር የሚያዘክሩበት ወር ነው። ከማሕሌቱም በተጨማሪ ምንም እንኳን የዐዋጅ ጾም ባይሆንም የእመቤታችን ፍቅር የበዛላቸው በጾም ሆነው የሚያሳልፉት ዐቢይ የምስጋና ወቅት ነው።
 
ጽጌ ማለት ጸገየ አበበ ከሚል የግእዝ ግስ የተገኘ ቃል ሲሆን አበባ፣ ውበት፣ ደም ግባት ማለት ነው። አበቦች ውብ፣ ማራኪና አስደሳች ከመሆናቸው የተነሣ የሰው ልጆች በሙሉ አበቦችን ይፈልጋሉ። ምድርም በአበቦች አጊጣ ተሸልማ ስትታይ ክረምት ከለበሰችው ልምላሜ ይበልጥ ታስደስታለች። ዘመነ ጽጌ ዝናምና ወጨፎ፣ ዶፍና ጎርፍ፣ መብረቅና ነጎድጓድ የሚፈራረቅበት የክረምት ቀናት አልፎ ምድር በአበቦች የምትሸለምበት፣ ደመናው ከሰማይ ተወግዶ ሰማይ በከዋከብት የሚያሸበርቅበት፣ የሰው ልጆች ይህንን በማየት እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ደስ የሚሰኙበት ወር ነው።
 
ወርኃ ጽጌ የዘመናት ባለቤት ዘመነ ክረምቱን አሳልፎ የደስታ እና የመልካም ምኞት መግለጫ በሆኑ አበቦች ወደ አሸበረቀው ዘመነ ጸደይ ስላደረሰን "ኀለፈ ክረምት ቆመ በረከት ተሠርገወት ምድር በሥነ ጽጌያት፤ ክረምት አለፈ በረከት ተተካ ምድርም በአበቦች አጌጠች” እየተባለ የሚዘመርበት ወቅት ነው። በዚህ ወራት ሰውም ዕድሜው እንደ አበባ አጭር በመሆኑ ሞቱን ማሰብ እንዳለበት ማስገንዘብ ተገቢ ነው። አበባ የሚወድቀው የሚረግፈው ፍሬ ለማፍራት ነው፤ አበባ ሲኖር በመዓዛው፣ ሲረግፍ በፍሬው ያስደስታል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​ኢሬቻ/ዋቄፈና/ ለክርስቲያን ምኑ ነው?
(በዲ/ን ሕሊና በለጠ)

ቤተ ክርስቲያን በባሕርይዋ የአንድ ማኅበረሰብን ባሕል ንቃም ኾነ ተቃውማ አታውቅም። በተቻላት መጠን ማኅበረሰቡ ከነ ባሕሉ ድኅነትን ያገኝ ዘንድ ሃይማኖቷንና ሥርዓቷን አስተምራ ታስተናግደዋለች እንጂ። ከእርሷ አምልኮ በተቃራኒው የሚያመልክ የአንድን ተገዳዳሪ የእምነት ተቋም አምልኮም በማይገባ መልኩ ተችታና አኮስሳ አታውቅም፤ እውነተኛውን መንገድ ግን በተገቢው መልኩ በጥብዓት ታስተምራለች። የዚያ የእምነት ተቋም አምልኮና እምነት ስሕተት ከኾነ ሰዎች ኹሉ ይድኑ ዘንድ እውነትን ትሰብካለች፤ ወደ እውነት ትመራለች፣ ታደርሳለች።

ኢሬቻ ምንድን ነው? ባሕል ነውን?

መልካም፣ ባሕልስ ከኾነ ቤተ ክርስቲያን የባሕሉን አክባሪ ባሕሉን ሳይዘነጋ ይቀበላት ዘንድ አይገዳትም። እርሷም ከነ ባሕሉ ዐቅፋና ደግፋ ትቀበለዋለች።

ግን ኢሬቻ ባሕል ነው?

አይመስለኝም። ሰሞንኛ ተናጋሪዎችን እንዘንጋቸውና እስኪ እንዴት እንደተከበረ እንመርምር። የመርሐ ግብሩ ተሳታፊዎች ውኃ ውስጥ ሣር እየነከሩ ወይም ዛፍን ቅቤ እየቀቡ ፈጣሪን ሲያመሰግኑ የሚያሳዩ ፎቶዎችንና ቪዲዮዎችን ስናይ ነበር። ስለዚህ ይህ በዓል:-

#1ኛ ፈጣሪ የሚመሰገንበት ነው (ይህም ተደጋግሞ በአክባሪዎቹ እየተነገረ ነው)። በፈጣሪ መኖር ማመን ደግሞ: ለሃይማኖት ህልውና የመጀመሪያው መስፈርት መኾኑን ልብ ይሏል። ስለዚህ ኢሬቻ/ዋቄፈና/ ለሃይማኖትነት ትልቁን መሥፈርት አሟልቷል ማለት እንችላለን።

#2ኛ የታወቀ የምስጋና (አምልኮ?) ሥርዓት (ለምሳሌ:- ሣር ውኃ ውስጥ መንከር፣ ቅቤ መቀባት ...) አለው። ይህም እስልምናም ኾነ ክርስትና የታወቀ የአምልኮ ሥርዓት እንዳላቸው ማለት ነው።

#3ኛ እስልምና መስጊድ፣ ክርስትናም ቤተ ክርስቲያን እንዳላቸው ኹሉ: ኢሬቻም /ዋቄፈናም/ ይህ ሥርዓት የሚፈጸምበት ቦታ (Sacred Place, ለምሳሌ:- ውኃና ዛፍ ያለበት ሥፍራ) አሉት።

#4ኛ ሃይማኖታዊ የአምልኮ ሥርዓት በካህናት እንደሚመራ: ክብረ በዓሉን የሚመሩ የሥርዓት መሪዎች (አባ ገዳዎች?) አሉት።

ስለዚህ ወይ አምልኮ ነው፣ ወይም ደግሞ ከቆይታ ብዛት ወደ ባሕልነት የተቀየረ አምልኮ ነው።

#ዐቢይነጥብ - ከላይ ከጠቀስናቸው ከዐራቱ ለጊዜው አንዱን ብቻ እንምረጥ -

-ፈጣሪ የሚመሰገንበት መኾኑ

ይህ ብቻ "ባሕል ነው" ለሚሉት ቆም ብለው እንዲያስቡ የሚያስገድድ ምክንያት ነው።

ፈጣሪን ማመስገን የሚቻለው በእምነት ነው። በመጀመሪያ ይህን ፈጣሪ ማመንና በጥቂቱም ቢኾን በእምነት ማወቅ ይገባል። ቢያንስ ፈጣሪ መኾኑን በእምነት መረዳት ያሻል። ከዚያም እርሱ በሚፈልገው ሥርዓት እርሱን ማመስገን/ማምለክ ይከተላል። እርሱን ማምለኪያ ውሱን ሥርዓት የለም ቢባል እንኳን: የማመስገኛ ሥርዓቱ "ሥርዓት የለሽ በመኾን" ይገለጻል፤ (non-religiousness is my religion) እንዲል አንድ የፍልስፍና መምህር /ፈላስፋ ላለማለት ነው/)።

ሙስሊሙ ፈጣሪን የሚያመሰግንበት ሥርዓትና ቦታ አለው፤ ሳምንታዊ(ጁምዓ) እና ዓመታዊ (ኢድ አል ፈጥር፣ ኢድ አልአድሃ) የበዓላት ዕለታትም አሉት። ክርስቲያኑም እንዲሁ ከሳምንታዊ ሰንበትን፣ ከዓመታዊ ልደትና ትንሣኤን የመሰሉ (ዕለታዊና ወርኃዊውን ጨምሮ) ብዙ በዓላት አሉት። ሙስሊሙም ክርስቲያኑም በየበዓላቱና በየታወቀ ሥርዓቱ ፈጣሪን ያመሰግናሉ፣ ያመልካሉ። ነገር ግን ክርስቲያኑ ኢሬቻ የሚል ፈጣሪን የማመስገኛ በዓል በዚቁ (liturgical Calendar) ውስጥ የለም። ሙስሊሙም እንደዚያ።

ሌላው ነጥብ: ኹሉም እምነት ፈጣሪን የተመለከተ መሠረተ-ትምህርቱ (Doctrine/Creed) ከሞላ ጎደል ይለያያል። ሙስሊሙም (ካልተሳሳትኩ) "ላ ኢላህ ኢለላህ መሐመዱር ረሱለላህ" የሚል ሸሀዳ (Creed) አለው። ይህንን አዘውትሮ ያደርሳል። ፕሮቴስታንቱ "ክርስቶስ አማላጄ" (ሎቱ ስብሃት) ይላል። እኛ ኦርቶዶክሳውያን ደግሞ "ኹሉን የፈጠረ አንድ አምላክ በሚኾን በእግዚአብሔር አብ እናምናለን" ከሚለው ጀምሮ የክርስቶስንና የመንፈስ ቅዱስን አንድ የባሕርይ አምላክነትና ከአብ ጋር መተካከል፣ የቤተ ክርስቲያንን ኲላዊነት፣ አንድነት፣ ቅድስናና ሐዋርያዊነት፣ የጥምቀትን የኃጢአት ማስተሥሪያነት፣ የትንሣኤ ሙታንን ተስፋነት የምንመሠክርበት የዘወትር ጸሎተ ሃይማኖት (Creed) አለን።

እነዚህ እምነቶች ይለያያሉ ብቻም ሳይሆን ይቃረናሉ። እንዴት በአንድነት ምስጋናቸውን ለአምላክ ያደርሳሉ?

እኔ አምላክ የምለውን ክርስቶስን አንዱ ከአጠገቤ "አማላጄ" እያለው እንዴት አንድነት ይኖረኛል? አንዱስ "ነቢይ" እያለው እንዴት አብረን እናመሰግናለን? የኔን አምላክ አማላጅም ፣ ነቢይም ማለት እርሱን ማሳነስ ለእኔም ንቀት ነው።

ሙስሊሙም አላህን አምላክ ይላል። ኢሳን ነቢይ ይላል። እኔ ከጎኑ ቆሜ ኢየሱስ ክርስቶስን "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" ስል እንዴት ይዋጥለታል?

አብረን ቡና የምንጠጣ፣ አብረን ኳስ የምንጫወት፣ በንግድ የምንተባበር ሙስሊሞችና ፕሮቴስታንቶች ይኖራሉ። በጣም የምንዋደድ ጓደኛሞችና የሥራ ባልደረቦች ልንሆን እንችላለን። ግን ለአምልኮ ሙስሊሙም መስጊድ፣ ፕሮቴስታንቱም "ቸርች" እኛም ቤተ ክርስቲያን እንሔዳለን እንጂ ፈጣሪን ለማመስገን መስጊድ ወይም ቤተ ክርስቲያን በአንድነት አንሔድም።

አንድ የምንኾንበትንና የማንኾንበትን እንለይ እንጂ! በኢትዮጵያዊነት አንድ ነን፤ በባሕል እንተባበራለን፤ በልማት አንድ መኾን እንችላለን፤ እንኳን በሀገር በቤተ ዘመድም በሃይማኖት መለያየት ይገጥመናል፤ ዝምድናን ጨምሮ ግን ብዙ አንድ የሚያደርጉን ጉዳዮች አሉን። ኾኖም በሃይማኖት አንድ ካልኾንን ከእናቴም ጋር ለጸሎትና ለምስጋና አልቆምም።

እንኳን ከሙስሊምና ከፕሮቴስታንት ጋር ይቅርና በብሉይ ኪዳን በሃይማኖት አንድ ከነበርነው ከይሁዲውም ጋር ፈጣሪን ለማመስገን በአንድነት አንቆምም። የይሁዲው መሠረተ ሃይማኖት ( ሸማ፣ Creed) በእኛው ብሉይ ኪዳን ላይ ዘዳ.6÷4-9 ያለው ንባብ ነው። ይሁዲዎች ይህንን በእጃቸው ያሥሩታል (Teffilin)። በበራቸውም ይጽፉታል (Mezzuzah)። ንባቡ እኛም የምናምንበትና የምናነበው ነው። ነገር ግን ምንም ያኽል ብንወዳቸው ክርስቶስን ከማያምኑት ከይሁዲ እምነት (Judaism) ተከታዮች ጋር የሃይማኖት ኅብረት የለንም።

ወንጌላችንም ያዘናልና "ቢቻለንስ በእኛ በኩል ከሰው ኹሉ ጋር በሰላም መኖርና ሰላምን መከታተል" የክርስትና መርሐችን ነው። (ሮሜ 12÷18፣ ዕብ. 12÷14)። ኾኖም ፈጣሪን የምናመሰግንበት የሃይማኖት ኅብረት የሚኖረን ግን ከተጠመቁት ጋር ብቻ ነው።

#ይቀጥላል
#ሼር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#የናቁሽ_ሁሉ

የናቁሽ ሁሉ ወደእግሮችሽ ጫማ ይሰግዳሉ
የካዱሽ ሁሉ ይፀፀታሉ
እኛ ግን አንቺን እናከብራለን}2
እናታችነን ፅዮን አንልሻለን}

እናቴ እመቤቴ እኔም እልሻለው
ጌታዬ ባደራ የሰጠኝ አንቺን ነው
ከእግረ መስቀሉ ስር አንቺን አጊኝቻለው
ትውልድ ነኝና ብፅዕት እልሻለው

በድል ነሺዎች ዘንድ በፃድቃን ሰማዕታት
በቅዱሳኑ ና በትጉሃን መላዕክት
የሰለጠነ ነው ስምሽ በእግዚአብሔር ዘንድ
በፍጥረታት ሁሉ እጅግ የሚወደድ

እናቴ ማርያም ሆይ ካንቺ ጋር ምን አለኝ
ያልሽኝን እንዳልፈፅም የሚከለክለኝ
ብሏልና ልጅሽ በቤተ ዶኪማስ
ለምኝልን ድንግል እንባችን ይታበስ

የጌድዮን ፀምር ዳግማዊቷ ሰማይ
ሕይወትን ያስገኘሽ ወላዲተ ፀሐይ
የሕወትን መና ያገኘነው እኛ
ካንቺ ተወልዶ ነው የአለሙ እረኛ

ዘማሪት መብራት ድርብሣ (አብ-ሳላት)
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

📕 መጽሐፈ ጤፉት

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ቅዱስ መስቀል ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ በግሸን ደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም መቀመጡን እና ሌሎች ጥንታዊያን ታሪኮች የሚናገር መጽሐፍ ነው።

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

👥ከ133,000 በላይ ባለ ማህተቦች መእመናን ያሉበት ከ1500 በላይ አዳዲስ እና የዱሮ መዝሙሮች ከነግጥማቸው የምታገኙበትን ድንቅ ኦርቶዶክሳዊ የሆነውን ቻናል አሁንኑ ተቀላቀሉ📍
የመዝሙር ግጥሞች
👇🏽👇🏽👇🏽
https://t.me/joinchat/AAAAAE5K_dyT2-AYoTAW5A
https://t.me/joinchat/AAAAAE5K_dyT2-AYoTAW5A

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

💒ስለ ሀይማኖቴ ማወቅ ግዴታዬ ነው የሚል የማንኛውም ኦርቶዶክስ ሊቀላቀለው የሚገባ ቻናል። በቻናሉ ጥያቄ ይጠየቃል ምዕመኑም ይሳተፋል
ቻናሉን ለመቀላቀል ከስር ክፍት የሚለውን
መጫን በቂ ነው።

               ክፈት        ክፈት               
               ክፈት        ክፈት               
                                                   
ክፈት        ክፈት        ክፈት        ክፈት
ክፈት        ክፈት        ክፈት        ክፈት
                                                    
                                                   
                                                    
                                                    
                                                     
               ክፈት         ክፈት              
               ክፈት         ክፈት              .

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

አዲስ በ live ብቻ የሚሰጠውን የ tiktok እና YouTube ይቀላቀሉ።

የስነልቦና ባለሞያ Bini Girmachew

እሁድ ከምሽቱ  ከ3 እስከ 4 ሰዓት  በtik tok Live ትምህርት የምታገኙበት

tiktok.com/@begood2716


በYouTube  ደሞ እሮብ ከቀኑ 11-12 Live የምንገባበት ቻናል ነው SUBSCRIBE በማድረግ የተለቀቁትን ትምህርቶች በመመልከት ይጠብቁን


biniGirmachew27" rel="nofollow">https://www.youtube.com/@biniGirmachew27

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የብፁዕ አቡነ ሰላማ ሥርዓተ ቀብር እሁድ መስከረም ፳ ቀን ፳፻፲፮ዓ.ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማል።
*******
*

መስከረም ፲፰ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም ያረፉት የብፁዕ አቡነ ሰላማን የቀብር ሥነሥርዓት በማስመልከት ቋሚ ሲኖዶስ ከቀትር በፊት አስቸኳይ ስብሰባ በማድረግ ባሳለፈው ውሳኔ መሠረት እሁድ መስከረም ፳ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም ከቅዳሴ በኋላ የብፁዕነታቸው ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንዲፈጸም ውሳኔ አስተላልፏል።

በዚህም መሠረት ነገ ቅዳሜ መስከረም ፲፱ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም ከቀኑ ፱ ሰዓት ላይየብፁዕነታቸው ክቡር አስከሬን ከሃሌ ሉያ ሆስፒታል በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ በአበው ቆሞሳትና በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ጸሎት ከተደረገበት በኋላ ወደ መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ጉዞ በማድረግ ሥርዓተ ጸሎት ተደርሶ ሌሊቱን ሙሉ ጸሎተ ፍትሐትና ሥርዓተ ማኅሌት ሲደረግበት ያድራል።

በማግስቱ እሁድ መስከረም ፳ ቀን ፳፻፲፮ዓ.ም ጠዋት ሥርዓተ ቅዳሴው በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ከተካሔደ በኋላ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ አበው መነኮሳት፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የየመምሪያ ኃላፊዎች ፣የአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችና ወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው ታጅበው ወደ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ገዳም በእግር ጉዞ ይደረጋል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት #የብፁዕ_አቡነ_ሰላማ የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም እና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የበላይ ጠባቂ ሊቀጳጳስ ዕረፍትን በማስመልከት ያስተላለፉት አባታዊ የሐዘን መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

«መኑ ሰብእ ዘየሐዩ ወኢይሬእያ ለሞት:–ሕያው ሆኖ የሚኖር ሞትንስ የማያይ ማን ነው?»
መዝሙር ፹፱፥፵፰

የትህትና፣ የጸሎት ሕይወት እና የመልካምነት ምሳሌ የነበሩት #ብፁዕ_አባ_ሰላማ ሊቀ ጳጳስ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን የሰማነው በታላቅ ሐዘን ነው።

ያለንበትን ፈተና የበዛበት ዘመን በጸሎት የሚያሻግሩ አባቶችን ማጣት  ቤተ ክርስቲያንን የሚጎዳ ቢሆንም በቅዱስ መጽሐፍ ሞትን ሳያይ ሕያው ሆኖ መኖር የሚችል ማን ነው? እንደተባለ ሰው በምድር ላይ የሚኖርበት ዘመን በእግዚአብሔር ዘንድ የተቆጠረ እና የተለካ በመሆኑ ብፁዕነታቸው  ሃይማኖትን ጠብቀውና መልካሙን ገድል ፈጽመው  ወደ መንግሥተ እግዚአብሔር  በክብር ተሸጋግረዋል።

ብፁዕነታቸው በዕረፍተ ሥጋ ከእኛ በመለየታቸው ጥልቅ ሐዘን ቢሰማንም በሰማይ የሚጠብቃቸውን ክብር እያሰብን እንጽናናለን።

የብፁዕነታቸውን ነፍስ በቅዱሳን ጻድቃን ሰማዕታት አጠገብ ያሳርፍልን!
ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን እና ለመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸውም መጽናናትን ያድልልን!
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ ይቀድስ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
አሜን!!


አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
መስከረም 18 ቀን 2016 ዓመተ ምሕረት
ዋሽንግተን ዲሲ አሜሪካ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ምን አይነት ስርዓተ ቢስነት ነው?
ምን አይነት ጨለምተኝነት ነው?

ቅድስት ቤተክርስቲያን የራሷ የዜማ ንዋየ ቅድሳት አሏት። ብሄርተኝነታችሁን ወደ ቤተክርስቲያን ይዛችሁ አትግቡ።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​#ቃል_ኪዳንዋ

ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይድረሰውና ጌታችን ምድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰማዕቷ ለትውልድ የሚተላለፍ የዘላለም ቃል ኪዳን ገብቶላታል፡፡

መታሰብያዋን ያደረገ ስሟን የጠራ፣ በስሟ ቤተ ክርስትያን የሠራ፣ የተራበውን በስሟ ያበላ፣ የተጠማውን በስሟ ያጠጣ፣ የገድሏን መጽሐፍ የጻፈውን፣ ያጻፈውን፣ ያነበበውን፣ የተረጎመውን፣ ሰምቶም በልቡ ያኖረውን፣ የልቡን መሻት እንደሚፈጽምለት እና በመንግስተ ሰማያት እንደ እርሷ የክብር አክሊል እንደሚያቀዳጀው፤ ሥዕሏን አሥሎ በክብር በቤቱ አስቀምጦ ሽቶ እየረጨ ቢጸልይበት ጸሎቱ እንደሚሰማና ልብን የሚመስጥ ጣፋጭ የሆነ መዓዛ እንደሚያሸተው፣ ወንድ ልጁንና ሴት ልጁን በስሟ የሰየመ በመንግስተ ሰማያት የበለጠና የከበረ ስም እንደሚሰጣቸው፣ ዕጣን፣ ስንዴና መብራትን፣ ልብሰ ተክህኖ፣ መጋረጃ ቢሰጥ በሞቱ ቀን የብርሃን ልብስ እንደሚለብስ፣ ያለ ወቀሳ ያለከሳ ባህረ ሲኦልን ተሻግሮ መንግስቱን እንደሚወርስ ቃል ኪዳን ገብቶላታል፡፡

፨ ሰማዕቷን ከሌሎች ቅዱሳን ልዩ የሚያደርጋት ታሪክ ፨

በግብጽ አገር አርባ ዓመታት የነገሠ ባለ 12 ክንፉ ብጹአዊ አቡነ ሙሴ የሚባሉ ታላቅ ጻድቅ አሉ፡፡ እኝህ ጻድቅ ከንግስና ወደ ምንኩስና የተሸጋገሩ መንፈሳዊ አርበኛ ናቸው፡፡

ታድያ እኝህ ጻድቅ የቅዱሳን፣ የሰማዕታትን ዓጽም እሰበሰቡ ደግላቸውን እያጻፉ፣ ቤተ ክርስትያን በመስራት፣ ታቦታቸውን በማክበር፣ በበዓላቸውም ቀን ይቀድሱ ነበር፡፡

ከእለታት አንድ ቀን ታቦት ለማሰናዳት፣ ሜሮን ለመቀባት ወደ ቤተ መቅደስ በገቡ ጊዜ በወርቅ የተለበጠ እና በላዩ በሮማይስጥና በጽርዕ ቋንቋ የብጽዕት ቅድስት አርሴማ ስም የተጻፈበት አንድ ጽላት ያገኛሉ፡፡ ያን ጊዜ የቅዱሳንን ስማቸውን አሰቡ፡፡ የገድላቸውንም ዜና መረመሩ፡፡ ግን የቅድስት አርሴማን ግድልና የሞቷን ዜና አላገኙም። ስለዚህም ነገር በምን ዘመን ሰማዕት እንደሆነች እና የሰማዕትነቷን ሥራ ያስረዳቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር በጸሎት አመለከቱ፡፡

ያን ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ለአቡነ ሙሴ ተገልጦ ‹‹ብጽአዊ ሙሴ ሆይ የብጽእት አርሴማን ሥራ እነግርህ ዘንድ ስማ፡፡ ይህቺ ሰማዕት ገና አልተጸነሰችም፣ አልተወለደችም፤ በወርቅ ዓምድ በሕይወት መጽሐፍ ስሟ ተጽፏል እንጂ፡፡ ነብዩ በመጽሐፍ ውስጥ ሁሉ ይጻፋል እንዳለ እርሷም በኋለኛው ዘመን ሰማዕት ትሆናለች፤ በዓለም ዳርቻ ሁሉ የገድሏ ዜና ይታወቃል፡፡

ተአምሯ የሚነገረው በኢትዮጲያ ነው፡፡ ስለዚህ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የብጽዕት ቅድስት አርሴማን የስም መታሰብያ መጥራት አትተው፡፡ ጽላትዋም ከአንተ ጋር ይኑር፡፡ የመቅደስዋም ህንጻ በህንጻህ ቦታ ጎን ይኑር፡፡ ስምህ በተጠራበትም የስሟ መታሰብያ ይጠራል›› ብሎ መልአኩ ወደ ላከው እግዚአብሔር ተመለሰ፡፡

አቡነ ሙሴም የእግዚአብሔር መልአክ እንዳዘዛቸው አደረጉ፡፡ ሰማዕቷም ገና ሳትወለድ በፊት እንደ እመቤታችን በእግዚአብሔር ህሌና ታስባ ትኖር ነበር፡፡ እኛም እንደ እንደ ጻድቁ አቡነ ሙሴ በሰማዕቷ ጸሎት እና ቃል ኪዳን ልንጠቀምባት ይገባል፡፡

ተወዳጆች ሆይ ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹እንግዲህ ምን እላለሁ? ስለ ጌዴዮንና ስለ ባርቅ ስለ ሶምሶም ስለ ዮፍታሔ ስለ ዳዊትና ስለ ሳሙኤልም ስለ ነብያትም እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛልና›› ነው ያለው፡፡ /ዕብ 11÷32/ እኔም ስለ እዚች ድንቅ ብርቅ እና ከወርቅ በላይ የከበረች ከአልማዝም በላይ የተወደደች ስለ ሰማዕቷ ለመተረክ ጊዜ ስለማይበቃን እዚህ ላይ ይብቃን፡፡

የሰማዕቷ የቅድስት አርሴማ ጸሎት፣በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡

በሰማዕቷ በቅድስት አርሴማ ስም ‹‹ሼር›› አድርገው ለወዳጆ ይዘክሩ፡፡

መስከረም 29/1/12 ዓ.ም
አዲስ አበባ

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ይሄንን የቅዳሴ ትምህርት ምዕመናን ተለማመዱት ቅዳሴ መማር ለምትፈልጉ ኦርቶዶክሳዊያን የተዘጋጀ ነው።

ለምታውቋቸው ኦርቶዶክሳዊያን እህት ወንድሞቻችሁ የዝማሬ ዳዊትን ቻናል ሊንክ ላኩላቸው።ከእኛ ጋር በሕብረት ሆነው ቅዳሴውን ይማሩ እና እኩል ያስቀድሱ ዘንድ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

💒ስለ ሀይማኖቴ ማወቅ ግዴታዬ ነው የሚል የማንኛውም ኦርቶዶክስ ሊቀላቀለው የሚገባ ቻናል። በቻናሉ ጥያቄ ይጠየቃል ምዕመኑም ይሳተፋል
ቻናሉን ለመቀላቀል ከስር ክፍት የሚለውን
መጫን በቂ ነው።

               ክፈት        ክፈት               
               ክፈት        ክፈት               
                                                   
ክፈት        ክፈት        ክፈት        ክፈት
ክፈት        ክፈት        ክፈት        ክፈት
                                                    
                                                   
                                                    
                                                    
                                                     
               ክፈት         ክፈት              
               ክፈት         ክፈት              .

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የቅዳሴ ትምህርታችንን እንቀጥላለን ለምዕመናን ብቻ። ተለማመዱት👉👉👉

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ሰውም ሲኖርም ሲሞትም ፈጣሪውን ማስደሰት አለበት እንጅ ያለ ፍሬ ንስሓ መሞት የለበትም፤ "ግበሩኬ እንከ ፍሬ ሠናየ ዘይደልወክሙ ለንስሓ፤ እንግዲህስ ለንስሓ የሚገባ ፍሬ አድርጉ እንዲል፡፡ (ማቴ.፫፥፰)
 
ወርኃ ጽጌ የእናታችንን ስደት ከተወደደው ልጇ ጋር የምናስብበት ነው። በተለይም ማሕሌተ ጽጌ በተባለው ድርሰት ሊቁ አባ ጽጌ ድንግል እርሷን በአበባ ጌታችንን በፍሬ፣ እርሷን በፍሬ ጌታን በአበባ እየመለሰ ብሉይን ከሐዲስ አጣጥሞ የተናገረው ምሥጢር ድንቅ ነው። ክርስቶስን በአበባ ሲመስለው ነቢዩ ኢሳይያስ በትንቢቱ ቅዱስ ያሬድ በድጓው "ትወፅእ በትር እም ሥርወ እሴይ ወየዐርግ ጽጌ እም ጉንዱ" በማለት ድንግል ማርያምን በጉንድ ክርስቶስን በጽጌ መስሎ ይናገራል። እርሷን በአበባ ሲመስልም ከአበባ ፍሬ እንዲገኝ ፍሬ ሕይወት ፍሬ መድኃኒት ክርስቶስ ከእርሷ እንደሚገኝ ለማመልከት ነው። (ኢሳ.፲፩፥፩)
 
ከማሕሌተ ጽጌ አንድ ማሳያ አቅርበን ክርስቶስ ለምን ተሰደደ የሚለውን እንመልከት፤ “በጌጋየ አዳም ወሔዋን ሱራፊ ዘዐፀዋ፣ እንበለ ጽጌኪ መኑ ለአንቀጸ ገነት ዘአርኀዋ፣ ተፈሥሒ ድንግል መያጢተ አዳም እምጼዋ፣በተአምርኪ ውስተ ምድረ ጽጌ አቲዋ፣ ከመ ጣዕዋ አንፈርዓፀት ሔዋ፤በአዳምና በሔዋን በደል ሱራፊ የዘጋውን የገነትን በር ከጽጌ ልጅሽ በቀር ማን ከፈተው? አዳምን ከምርኮ የመለስሽው ድንግል! ደስ ይበልሽ  በተአምርሽ ወደ አበባይቱ ምድር ገብታለችና ሔዋን እንደ እንቦሳ ዘለለች።” ሊቁ በዚች ክፍል ብቻ ሐዲስን ከብሉይ እንዴት እንዳገናኘው ልብ ይሏል።
 
በሰውነቱ መሰደድ፣ መራብ፣ መጠማትን ገንዘብ ያደረገው ክርስቶስ እንደ አምላክነቱ ማንም በማይቀርበው ብርሃን የሚኖር ነቢዩ ዕንባቆም እንደተናገረው “እግዚአብሔር ከቴማን፥ ቅዱሱም ከፋራን ተራራ ይመጣል። ክብሩ ሰማያትን ከድኖአል፥ ምስጋናውም ምድርን ሞልቶአል። ጸዳሉም እንደ ብርሃን ነው፤ ጨረር ከእጁ ወጥቶአል፤ ኃይሉም በዚያ ተሰውሯል። ቸነፈር በፊቱ ይሄዳል፥ የእሳትም ነበልባል ከእግሩ ይወጣል። ቆመ፥ ምድርንም አወካት ተመለከተ፥ አሕዛብንም አናወጠ፤ የዘለዓለምም ተራሮች ተቀጠቀጡ፥ የዘለዓለምም ኮረብቶች ቀለጡ፤ መንገዱ ከዘለዓለም ነው” (ዕን ፫፥፴፮)  በማለት የገለጸው አምላክ ለምን ተሰደደ ቢሉ፡-
 
ለካሣ፦ የመጀመርያውን ሰው አዳምን በበደሉ ምክንያት ከገነት አስወጥቶት ነበርና ካሣ ይሆነው ዘንድ ዳግማዊ አዳም ክርስቶስም ተሰደደ። በገድለ አዳም ተመዝግቦ እንደምናገኘው አዳም ገነት ከወጣ በኋላ ተራበ ተጠማ ክርስቶስም በግብጽ ምድር ተራበ ተጠማ፣ አዳም ከገነት ሲወጣ ከሔዋን በቀር አብሮት ማንም አልነበረም፤ ዳግማዊ አዳም ክርስቶስም ከዳግማዊት ሔዋን ከድንግል ማርያም በቀር ማንም አልነበረውም፤ “ብክዩ ኅዙናን ኀልየክሙ ስደታ፣ ወላህዉ ፍሡሓን ተዘኪረክሙ ብዝኀ ሠናይታ፣ ማርያም ተዓይል ከመ ዖፍ ውስተ አድባረ ግብጽ ባሕቲታ፣ ተአወዩ በኀጢኦታ ሀገረ አቡሃ ኤፍራታ፤ እናንተ ኀዘንተኞች የእመቤታችንን ስደቷን አስባችሁ አልቅሱ፣ እናንተ ደስተኞች የቸርነቷን  ብዛት አስባችሁ አልቅሱ። ድንግል ማርያም እንደ ወፍ በግብፅ ተራራዎች ብቻዋን ትዞራለች የአባቷ የኢያቄም ሀገር የምትሆን ኤፍራታን አጥታ ታለቅሳለችና እናተ ኀዘንተኞች አልቅሱ።” እንዲል (ሰቆቃወ ድንግል)
 
ስደትን ለሰማዕታት ለመባረክ፦ ሰማዕትነት እሳት፣ ስለት ብቻ መቀበል አይደለም ሀገር ጥሎ መሰደድም ሰማዕትነት ነውና። በመዋዕለ ስብከቱ  “በአንዲቱ ከተማም መከራ ቢያሳዩአችሁ ወደ ሌላይቱ ሽሹ” ብሎ የሚያመጣው ነውና። (ማቴ.፲፥፳፫) የስደተኞች ተስፋ ክርስቶስ ገና በእናቱ እቅፍ ሳለ ስደትን ባረከው። “ኢየሱስ ስዱድ ተስፋሆሙ ለስዱዳን ኢየሱስ ግፉዕ ምስካየ ግፉዓን፤ኢየሱስ በመሰደዱ የስደተኞች ተስፋ፣ በመገፋቱ የግፉዓን መጠጊያ ሆነ” እንዳለ ሊቁ (ሰቆቃወ ድንግል) ለዚህም ነው ዛሬ ቅዱሳን ፍቅሩ አገብሮቸው ከዘመድ ባዳ ከሀገር ምድረ በዳ አሰኝቶ በዱር በጫካ ከአራዊትና ከእንስሳት ጋር እየታገሉ መኖርን የሚመርጡት።
 
ቅድስት ድንግል ማርያም ከተወደደው ልጇ ጋር በስደት ሳለች ያጋጠማትን መከራዎች ከሰቆቃወ ድንግል አንዲትን ቃል አንሥተን እንመልከት። ገና የዐሥራ አምስት ዓመት ብላቴና ሳለች ሕፃን ታቅፋ መሰደዷን ተመልክቶ “ምዕረ በዘባንኪ ወምዕረ በገቦኪ ማርያም ብዙኀ በሐዚ ለሕፃን ደከምኪ ሶበኑ የሐውር  በእግሩ ከመ ትጹሪዮ ይበኪ” በማለት አንድ ጊዜ በጀርባዋ አንድ ጊዜ በጎኗ እያለች ልጅ አዝላ በግብጽ በርኃ ስትንከራተት የሚዘክራት ሰው አጥታ ይልቁንም የልጇን የወርቅ ጫማ ሲወስዱባት ምርር ብላ ስታለቅስ፣ ክርስቶስን ታቅፋ ይዛ ዓይኑን እየተመለከተች ስታልቅስ ልብ በሉ። ሊቁ ይህን ተመልክቶ እናንተ የገሊላ ሰዎች እንቦሳይቱ ማርያም ወዴት ሔደች በለቅሶ እከተላት ዘንድ  መንገዷን ነገሩኝ በማለት ይማጸናል። (ሰቆቃወ ድንግል)
 
ዛሬም ሊቃውንቱ ስደቷን እያሰቡ ሌሊቱን በማሕሌት ወደ ግብጽ እየወረዱ ያድራሉ። የቤተ ክርስቲያን ልጆች አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ! በእውኑ ዛሬስ ድንግል ማርያም ከስደት ተመልሳለችን? በልባችን ላይ ያነገስነው ሄሮድስን ወይስ ክርስቶስን? የቤተ ክርስቲያን ልጆች ዛሬም ድንግል ማርያም ተመልሳ የምታርፍበት የንጹሕ ልቡና ሀገር ያስፈልጋልና ማረፊያ ለመሆን እንዘጋጀ፡፡ ቅድስት ድንግል ወደ ሀገሯ ስትመለስ ከናዝሬት መልካም ሰው ይወጣልን የተባለላት ናዝሬት የተወደደ የተመሰገነ ክርስቶስን አስገኘች። ይህን ሳስብ ዛሬ የእኛ ሀገርም ድንግል ከስደት ከመመለሷ በፊት ያለችዋ ናዝሬት ትመስለኛለች፤ መልካም ሰው ደግ ሰው የለባትምና። "አድኅነኒ እግዚኦ እስመ ኀልቀ ኄር ወውኅደ ሃይማኖት እም እጓለ መሕያው፤ አቤቱ ደግ ሰው አልቋልና አድነኝ ከሰው ልጆችም መተማመን ጠፍቶአልና” እንዳለ ነቢዩ ዳዊት (መዝ.፲፩፥፩)
 
በመጨረሻም በየቀኑ የምትሰደደውን ድንግል ዓመት ጠብቀን ስደቷን ከምናስብ አሳዳጁን ሄሮድስን አስወግደን ዘወትር ሕፃኑንና እናቱን በልባችን ጽላት አንግሠን እንድንኖር አምላካችን ይርዳን።የልባችን ንጉሥ ክርስቶስ ሲሰደድ አብራ ትሰደዳለችና። ድንግል ሆይ "እስከ ማእዜኑ ትሄልዊ በምድረ ነኪር ሀገረኪ ገሊላ እትዊ፤ እስከመቼ ድረስ በባዕድ ሀገር ትኖሪአለሽ? ወደ ሀገርሽ ገሊላ ተመለሽ።” የሰላም መገኛ ሰላማዊት ርግብ ሱላማጢስ ሆይ፥ ሰላምን ትሰጭን ዘንድ ወደ ዐሥራት ሀገርሽ ገሊላ ኢትዮጵያ ተመለሽ።
 
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​#በተለይ_ለኦርቶዶክሳውያን

አምልኮ/ምስጋና/ ማለት ክርስቶስ ራስ ለኾነላት ቤተ ክርስቲያን ለተባለችው አንዲት አካል ብልት ለመኾን የምንጋደልበት ሰማያዊ ሥርዓት ነው። ኦርቶዶክሳውያን በአምልኮ ጊዜ እርስ በእርሳችን ብቻ ሳይኾን ከመላእክትም ጋር ረቂቅ አንድነት አለን። "በሰላም ማሠሪያ (ይህን) የመንፈስ አንድነት ለመጠበቅ እንድንተጋም" ታዘናል። (ኤፌ.4÷3)።

ወደዚህ ሰማያዊ ኅብረት ይመጡ ዘንድም ለዓለም ኹሉ እንደ ሐዋርያቱ እንጮኃለን፤ "ወደ ክርስቶስ ኅብረት በሃይማኖት ኑ" እንላለን። "እናንተ ደግሞ ከእኛ ጋር ኅብረት እንዲኖራችሁ ያየነውንና የሰማነውን ለእናንተ ደግሞ እናወራላችኋለን። ኅብረታችንም ከአባት ጋር ከልጁም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ነው " እንዲል ሐዋርያው።
(1ኛ ዮሐ. 1÷3)።

ይህን በማድረግ ፈንታ ግን በማይመች አካሔድ ከማያምኑ ጋር መሰለፍ በሃይማኖታችን አይፈቀድም። ስለዚህ ማንም ኦርቶዶክሳዊ በሌላ ማኅበረሰባዊ ጉዳይ እንጂ በሃይማኖት ከማያምኑ ጋር ቢተባበር ራሱን ለካህን ያሳይ፣ በንስሐ ይመለስ።

ወንጌላችንም የሚለው የሚከተለውን ነው:-

"ከማያምኑ ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመዱ፤ ጽድቅ ከዓመፅ ጋር ምን ተካፋይነት አለውና? ብርሃንም ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው? ክርስቶስስ ከቤልሆር ጋር ምን መስማማት አለው? ወይስ የሚያምን ከማያምን ጋር ምን ክፍል አለው?" (2ኛ ቆሮ. 6÷14-15)።

እኔም እላለሁ - ኦርቶዶክሳዊ ከኢሬቻ/ዋቄፈና ጋር ምን ኅብረት አለው?

+ የኢሬቻና የኢኩሜኒዝም አካሔድ መመሳሰል - ሌላው ሥጋት?

የዓለማዊነት (Secularism) አቀንቃኞች ከፖለቲካ ዲሞክራሲን ፣ ከምጣኔ ሀብት የነፃ ገበያ ኢኮኖሚን ፣ ከሃይማኖት ፕሮቴስታንቲዝምን ይመርጣሉ፣ ይደግፋሉ። እነዚህ ሦስቱም በዓለማዊነት አቀንቃኞች መደገፋቸው: ለአንድ ማኅበረሰብ በኹሉም መልክ ለዘብተኝነትን ( Liberalism) ስለሚያለማምዱ ነው። አንድ ማኅበረሰብእ ለዘብተኛ ከኾነ ደግሞ ቸልተኝነቱ ይጨምርና ኹሉን ችላ በማለት በእነርሱ ቁጥጥር ሥር ለመዋል ምቹ ይኾናል። ስለዚህ ለዚህ አካሔድ ወግ አጥባቂ (Conservative) ኾነው የሚያስቸግሯቸው ኦርቶዶክሶች ኹሉ (Orthodox Christians, Orthodox Jews, Orthodox Muslims) ጥርስ ውስጥ የገቡ ናቸው። በተለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የመሰሉ በሥርዓትና በዜማ የደመቁ አብያተ ክርስቲያናትን ለዘብተኛ ለማድረግ በተሐድሶ እንቅስቃሴና በተለያዩ መንግሥታዊ ተጽዕኖዎችም ጭምር እንዲጎዱ ተደርጓል።

ለዚህ ለዓለማዊነት እንቅስቃሴ የተሸረበው ሌላው ሴራ ደግሞ (ምንም እንኳን ጠቃሚ ጎን ቢኖረውም) የኢኩሜኒዝም (Ecumenism) እንቅስቃሴ ነው። ይህን እንቅስቃሴ በቅርቡ እነ ዶክተር ወዳጄነህን የመሳሰሉት እንደሚከተሉት በግልጽ አስረድተው ነበር። በዚሁ እንቅስቃሴ ስም የሚንቀሳቀሱት አንዳንዶች ታዲያ "ከኹሉም ሃይማኖት ጥሩ ጥሩውን ፣ የጋራውን እንውሰድ" በሚል መርሕ ሌላ ዓይነት ፕሮቴስታንቲዝምን ይዘውና ሃይማኖትን በልካቸው አበጅተው ብቅ ብለዋል። ይህንን የሚደግፉት በዋናነት ግላዊነትን የሚያበረታቱት ፕሮቴስታንቶችና ዓለማውያን ናቸው።

ኢሬቻም የዚሁ ኮፒ እየኾነ ነው። በኦሮሞ ፕሮቴስታንቶችና በፕሮቴስታንታዊው ኦዲፒ ከሞላ ጎደል ካለ ምንም ማንገራገር ይደገፋል። ኢኩሜኒዝም በክርስትና ስም የሚንቀሳቀሱትን ማዕከል ያደረገ ቢሆንም፣ ኢሬቻ/ዋቄፈና ደግሞ ሙስሊሙንም፣ ኦርቶዶክሱንም ፣ ፕሮቴስታንቱንም ማዕከል አድርጓል። ይህም በተለይ ኦርቶዶክሱን በኦሮሙማ ስም ከኦርቶዶክሳዊነት ለማለዘብ የተነደፈ ሴራ ይመስላል።

"ምን ችግር አለው?" የሚል ለዘብተኛ ኦርቶዶክስ ደግሞ በስም እንጂ በግብር የቤተ ክርስቲያን ሊኾን አይችልም። ስለዚህ በተለይ የኦሮሞ ኦርቶዶክሳውያን ትልቅ አስተዋይነትን የሚጠይቅ ጊዜ ላይ እንዳላችሁ ልትገነዘቡት ይገባል። ከኦርቶዶክሳዊነትና በተወዳጅ ባሕል ስም ከመጣ ሌላ እምነት መካከል ያላችሁ የምትወስኑበት ጊዜ እንደኾነ ይሰማኛል።

ኹለቱንም መኾን አይቻልም። ወይ ከጊዜ በኋላ በቅርቡ የሚበርደውን የወቅቱን ሞቅታ መምረጥ ወይም ደግሞ ካለችበት ከፍታ ላይ ሳትወርድ ለዘመናት የኖረችውን ተዋሕዶን መምረጥ ያሻል።

እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያናችንንና ምዕመኖቿን፣ ሀገራችንንና ዜጎችን ይጠብቅልን። አሜን።

hilinabzehohite@gmail.com
©ዘሕሊና

#ሼር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#ድንግል_ማርያም_ብዬ

ድንግል ማርያም ብዬ
ስማጸን በስምሽ (፪)
በቅድመ እግዚአብሔር
ልመናዬን አድርሽ (፪)

እኔ ደካማ ነኝ ኃጢአቴ የበዛ
እኔ ጎስቋላ ነኝ በደሌ የበዛ
ጊዜዬን ያባከንኩ በዋዛ ፈዛዛ
ጊዜዬን ያሳለፍኩ በከንቱ በዋዛ

እመብርሃን ስልሽ ፈጥነሽ ድረሽልኝ(፪)
ልመናዬን ሰምተሽ ቆመሽ ለምኝልኝ
ኃጢአቴ ቢበዛም ይዣለሁ አንቺን(፪)
አስምረሻልና በላዒ ሰብን
#አዝ
አንገት የሚያስደፋ በዝቶብኝ ኃጢአቴ
ምልጃሽን ፈለኩኝ ድንግል ሆይ እናቴ
ያን ክፉ ጨለማ እንዳላይ አደራ(፪)
ድንግል ሆይ ከልይኝ ከዲያብሎስ ጭፍራ
#አዝ
እመብርሃን እያልኩ ቆሜ ከደጅሽ
በብርሃን እጆችሽ እንባዬን አብሽ
ዓለም አታላይ ነች ወደሷ ተሳብኩኝ
ታማልጂኝ ብዬ አንቺኑ ተራብኩኝ

ሊቀ መዘምራን
ኪነጥበብ ወልደቂርቆስ

"ጻድቃን እኔን ይጠብቃሉ"
መዝ፻፵፩፥፯

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

#ተአብዮ_ነብሴ

ተአብዮ ነብሴ ለእግዚአብሔር (3)
ሰአሊለነ ማርያም (2)
ሀበወልድክሂር መዳሕኔዓለም

የአብ ሙሽራ ነሽ የወልድም እናቱ
ለመንፈስ ቅዱስ ነሽ ፅራሃዊቱ
በፊትሽ ሰገዱ ቅዱሳን መላእክት

ለምኝልን ማርያም (2)
ከቸሩ ልጅሽ ከመድሐኒአለም

ከዋክብት ብርሃናት ሳይታይ ደመና
ታስበሽ ኖረሻል በአምላክ ህሊና
ገብርኤል ነገረሽ የክብርሽን ዜና

ለምኝልን ማርያም (2)
ከቸሩ ልጅሽ ከመድሐኒአለም

የወርቅ ታቦት ነሽ በሰማይ ያለሽ
የፅድቅ ንግስት ነሽ የተመሰገንሽ
በእናትነትሽ ተመካ ልብሽ

ለምኝልን ማርያም (2)
ከቸሩ ልጅሽ ከመድሐኒአለም

የአለሙን ጌታ በእቅፍሽ አየነው
በመሀፀንሽ አድሮ ቃል ስጋ የሆነው
እግዚአብሔር ስላንቺ ምስጋናው ብዙ ነው

ለምኝልን ማርያም (2)
ከቸሩ ልጅሽ ከመድሐኒአለም

የዳዊት ልጅ ማርያም ትምክህታችን
የአማኑኤል እናት መሰብሰቢያችን
የእግዚአብሔር ከተማ መማፀኛችን

ለምኝልን ማርያም (2)
ከቸሩ ልጅሽ ከመድሐኒአለም

ድንግል በክሊሄም በነፍስም በስጋ
ጎዶሎ ይምላል አንቺን የተጠጋ
ክርስቶስ ወልደሽ ክሳችን ተዘጋ

ለምኝልን ማርያም (2)
ከቸሩ ልጅሽ ከመድሐኒአለም

በፊትሽ ልማፀን ቆምኩኝ ከደጅሽ
ልመናዬ ሁሉ ይግባ ከጆሮሽ
ለሚጠራሽማ ማርያም ቅርብ ነሽ

ለምኝልን ማርያም (2)
ከቸሩ ልጅሽ ከመድሐኒአለም
ሰአሊለነ ማርያም (2)
ሀበወልድክሂር መዳሕኒአለም

ዘማሪ ገ/ዮሐነስ ገ/ጻድቅ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​እንኳን ለግሼን ደብረ ከርቤ: ለብዙኃን ማርያምና ለቅዱሳኑ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

#ግሼን_ደብረ_ከርቤ

ሃገራችን ኢትዮጵያ ሃገረ እግዚአብሔር መሆኗን ታላቁ ቅዱስ መጽሐፍ ይመሰክራል። (መዝ. 67, አሞጽ. 9:7) ሕዝቦቿም የድንግል ማርያምና የቅዱሳን አሥራት ናቸው። የኢትዮዽያውያንን ያህል ድንግል ማርያምን የሚወድ ለቅዱስ መስቀሉ ክብርን የሚሰጥ ቅዱሳንንም የሚዘክር ያለ አይመስለኝም። "እመ ብርሃንም ፈጽማ ትወደናለች። ለዚህ ደግሞ ቅንጣት ታህል አንጠራጠርም።"

ለዓለም እስከ አሁን ድረስ የሁለቱ (የታቦተ ጽዮንና የቅዱስ ዕፀ መስቀሉ) መገኛ እንቆቅልሽ ነው። ለእኛ ግን ሁለቱም ያሉት በቤታችን ውስጥ ነውና እንመሠክራለን። ክብር ለቀደምት አበው ይድረሳቸውና አስፈላጊውን መንፈሳዊና ሥጋዊ ዋጋ ከፍለው ታቦተ ጽዮንን እና ቅዱስ ዕፀ መስቀሉን አምጥተውልናል።

በዚህች ዕለትም የጌታችንና የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በደብረ ከርቤ ግሼን ማረፉን አስበን በዓልን እናከብራለን። ይኸውም ደጉ አፄ ዳዊት በሠይፈ አርዕድ የተጀመረውን ጥረት ቀጥለው በኃይለ እግዚአብሔር አሕዛብን አስደንግጠው እመ ብርሃንንም በጸሎት ጠየቁ።

የአምላክ እናትም ረድታቸው ቅዱስ ዕፀ መስቀሉን ከኩርዓተ ርዕሡ ወንጌላዊ ቅዱስ ሉቃስ ከሳላት ምስለ ፍቁር ወልዳ እና ከብዙ ንዋያተ ቅዱሳት ጋር ተላከላቸው። እርሳቸው መስከረም 10 ቀን መስቀሉን ተቀብለው በዓሉን በተድላ አክብረው በመንገድ በ1396 ዓ/ም ዐርፈዋል።

አፄ ዳዊት ካረፉ በኋላ ቅዱስ መስቀሉ ለ30 ዓመታት ተቀምጧል። አፄ ዘርዓ ያዕቆብ እስከ ነገሠበት 1426 ዓ/ም ድረስም ከ6 በላይ ነገሥታት አልፈዋል።

አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ከነገሠ ከጥቂት ዓመታት በኋላ ለቅዱስ መስቀሉ በመካነ ንግሡ ደብረ ብርሃን ቤተ ክርስቲያንን ለማነጽ ሲያስብ ጌታችን በራዕይ "አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል" አለው። ከዚህ ቀን ጀምሮ ደጉ ንጉሥ የመካነ መስቀሉን ቦታ ይፈልግ ዘንድ ከሠራዊቱ ጋር ብዙ ደክሟል።

በመጨረሻም በነገሠ በ10 ዓመታት ግሼንን አምባሰል (ወሎ) ውስጥ አግኝቷት ሐሴትን አድርጓል። ቦታዋ በሥላሴ ፈቃድ በትእምርተ መስቀል የተፈጠረች ናትና እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያንን አንጾ መስቀሉን በብረት በመዳብ በናስ በብር በወርቅ ለብጦ ዐፈር እንዳይነካውም አድርጐ አኑሮታል።

በቦታውም ተአምራት ተደርገዋል። ጻድቁ ዘርዓ ያዕቆብም 'ጤፉት' የሚባል መጽሐፍን ጽፎ እዚያው አኑሮታል። መጽሐፉ እንደሚለው በሃገራችን ያለው ግማደ መስቀሉ (የቀኝ እጁ) ብቻ ሳይሆን ሙሉው ዕፀ መስቀል ነው። ይህ የተደረገውም መስከረም 21 ቀን ነው።

#ሼር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

📚ድርሳነ ቅዱስ ገብርኤል
📚መልክዓ ቅዱስ ገብርኤል

የየበዓሉን ድርሳናት መልክዓት የቅዱሳን ታሪክ የምታገኙበትን ቻናል ተቀላቀሉ ከ70,000+ ኦርቶዶክሳዊያን አሉበት ከ350 በላይ pdf መጽሐፍ አሉ።

                👇👇👇
/channel/+7Itsth8QSrY2Y2Q0

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

📚ድርሳነ ቅዱስ ገብርኤል
📚መልክዓ ቅዱስ ገብርኤል

የየበዓሉን ድርሳናት መልክዓት የቅዱሳን ታሪክ የምታገኙበትን ቻናል ተቀላቀሉ ከ70,000+ ኦርቶዶክሳዊያን አሉበት ከ350 በላይ pdf መጽሐፍ አሉ።

                👇👇👇
/channel/+7Itsth8QSrY2Y2Q0

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በካቴድራሉም ለብፁዕነታቸው የሚመጥን ሥርዓተ ጸሎት ተደርጎ የሕይወት ታሪካቸው ተነቦ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የማጽናኛ ቃለ ምዕዳን ተላልፎ ሲያበቃ ሥርዓተ ቀብሩ የሚፈጸም ይሆናል።

በሥርዓተ ጸሎቱ ላይ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ዶ/ር የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒዩወርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ይገኛሉ።

የብፁዕነታቸው ጸሎትና ቢራኬ ይደርብን

ምንጭ:EOTC public relations

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሰላማ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፍ የተሰማትን ሐዘን ገለጸች።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።


ጸሎ
ተኛው፣ ደጉ፣ ርህሩሁና ታጋሹ አረጋዊው አባት ብፁዕ አቡነ ሰላማ መስከረም ፲፰ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። ብፁዕ አባታችን ባደረባቸው ህመም ምክንያት በአዲስ አበባ ሀሌሉያ ሆስፒታል በህክምና ላይ እንዳሉ ነው ከዚህ ዓለም ድካም ያረፉት።

የብፁዕነታቸውን ሽኝት መርሐ ግብር በተመለከተ በቋሚ ሲኖዶስ እንደተወሰነ ዝርዝሩን  የምናሳውቅ ይሆናል።

  የብፁዕነታቸው በረከት ይደርብን

ምንጭ: የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

👳‍♂የርዕሰ ሊቃውንት መጋቤ ብሉይ ወሐዲስ አባ ገብረኪዳን ትምህርቶች⛪️

ድንቅ፣ኃያል፣ርትዕት፣ጥንታዊት የሆነች የኦርቶዶክስን ሃይማኖት ከሚሰብኩ እናም ዕንቁ ከሚባሉት መካከል ቀዳሚው አባት ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳንን ትምህርት የሚያገኙት ብቸኛው ቻናል ነው ይግቡ።

👇🏽👇🏽👇🏽
@abagebrekidan
@abagebrekidan
@abagebrekidan

Читать полностью…
Подписаться на канал