ortodoxmezmur | Неотсортированное

Telegram-канал ortodoxmezmur - ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

134932

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . ዝማሬ ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Подписаться на канал

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

Code 9:- ይህንን ይመስላል
ለማዘዝ እና ለበለጠ መረጃ
📩 @kalSandy

📞 0965875219
📞 0922501999
📞 0913655116

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

Code 8:- ይህንን ይመስላል
ለማዘዝ እና ለበለጠ መረጃ
📩 @kalSandy

📞 0965875219
📞 0922501999
📞 0913655116

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

code 1 :- ሲታተም ይህንን ይመስላል።
ለማዘዝ እና ለበለጠ መረጃ
📩 @kalSandy

📞 0965875219
📞 0922501999
📞 0913655116

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

አሁን ONLINE ላይ ✅ ላላችሁ ብቻ መንፈሳዊ ጥያቄ ና መልስ ልንጀምር ነው ገብታችሁ ተሳተፉ
👇🏾በጥያቄ እና መልሱ
1⃣ ለወጣ 500 ብር ካርድ 💸
2⃣ ለወጣ 250 ብር ካርድ 💸
3⃣ ለወጣ 100 ብር ካርድ 💸

📍👉🏾 ዝግጁ ከሆናችሁ ብቻ 💸𝐒𝐓𝐀𝐑𝐓💸 የሚለውን ይጫኑት።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

አሁን ONLINE ላይ ✅ ላላችሁ ብቻ መንፈሳዊ ጥያቄ ና መልስ ልንጀምር ነው ገብታችሁ ተሳተፉ
👇🏾በጥያቄ እና መልሱ
1⃣ ለወጣ 500 ብር ካርድ 💸
2⃣ ለወጣ 250 ብር ካርድ 💸
3⃣ ለወጣ 100 ብር ካርድ 💸

📍👉🏾 ዝግጁ ከሆናችሁ ብቻ 💸𝐒𝐓𝐀𝐑𝐓💸 የሚለውን ይጫኑት።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​ታህሳስ 6
ቅድስት አርሴማ(ቅዳሴ ቤቷ)


✝እናታችን ቅድስት አርሴማን በምን እንመስላታለን? እርሷ በአድማስ ላይ ተቀምጦ እንደሚያበራ እንቁ ናትና ክብሯ ብዙ ነው። 

✝መድኃኒታችን ክርስቶስ በወንጌል እንዳለው "በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሠወር አይቻላትምና።"(ማቴ. ፭፥፲፩) የሰማዕቷ ሕይወት በፊታችን እንደ ብርሃን ተገልጦ ይታያል። ቅድስት አርሴማ እንደ ልጅ ወላጆቿን በመታዘዝ ደስ ያሰኘች ቡርክት ናት። ቅድስት አርሴማ ይህ ቀረሽ የማይሏት ውብ ናት።

ቅድስት አርሴማ ድንግል ናት። ቅድስት አርሴማ ባሕታዊት ጻድቅ ናት። ቅድስት አርሴማ ኃያል ሰማዕት ናት። ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ፦ አበው በትውፊት እንደ ነገሩን ቅዱሱ ጐርጐርዮስ የታላቋ ሰማዕት ቅድስት አርሴማ ትልቅ ወንድም ነው። በዜና ሰማዕታት ተጽፎ እንደሚገኘው በዚያ የመከራ ዘመን ቅዱስ ጐርጐርዮስ ሦስት ኃላፊነቶች ነበሩበት፦ ፩.ቅድስት አርሴማን ጨምሮ ደናግሉን ማጽናት ፪.ትምሕርተ ቤተ ክርስቲያንን በሚገባ ማጥናት ፫.የሚመጣውን መከራ ለመቀበል ራሱን ማዘጋጀት። ቅዱሱ ሦስቱንም ኃላፊነቶች በሚገባ በመወጣቱ ከራሱ አልፎ ለሌሎቹ አርአያ መሆን ቻለ። ያቺን ንጽሕት አርበኛ ቅድስት አርሴማንም አጽንቶ የደናግሉ መሪ አደረጋት። 

✝መከራው ገፍቶ እስከ መጣበት ጊዜ በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ ሆነው ይጸልዩ፣ ይጾሙ፣ ገዳማዊ ሥራንም ይሠሩ ነበር። ለዚህም ነው ቅድስት አርሴማና ቅዱስ ጐርጐርዮስን ጻድቃን የምንላቸው። በኋላ ግን ማኅደረ ሰይጣን ዲዮቅልጢያኖስ በመልኳ ተማርኮ ቅድስት አርሴማን ካላገባሁ በማለቱ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ድንግሏን አርሴማን ጨምሮ ክርስቲያኖችን ይዞ ወደ አርማንያ ተሰደደ። በአርማንያም በአንድ ገዳም ውስጥ ተደብቀው በጾምና በጸሎት ለጥቂት ጊዜ ቆዩ። ነገር ግን ረሃብ ፈጃቸው። የሚላስ የሚቀመስ ነገር በአካባቢው ባለ መኖሩ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ወደ ከተማ ለመውጣት ተገደደ። በዚያም በድርጣድስ ቤተ መንግሥት ውስጥ ባርነት ተቀጠረ። በሚያገኛት ገንዘብም ወገኖቹን ይረዳ ነበር። መከራው ግን አለቀቃቸውም።

ርጉም ዲዮቅልጢያኖስ ቅዱሳኑ ወደ አርማንያ መሔዳቸውን ስለ ሰማ ይዞ እንዲልክለት ድርጣድስን ላከው። ድርጣድስ ግን ቅድስት አርሴማን ባያት ጊዜ ከውበቷ የተነሳ መታገስ ባለመቻሉ "ካላገባሁሽ" አላት። ድንግሊቱ ግን "እኔ የክርስቶስ ሙሽራ ነኝ፤ አይሆንም።" አለችው። ሊያስፈራራት ሞከረ። ዓይኗ እያየ ደናግሉን ጨፈጨፋቸው። አልሳካልህ ቢለው በአደባባይ በግድ ሊያገባት ቢሞክር እጁን ጠምዝዛ በሰው ሁሉ ፊት መሬት ላይ ጣለችው። እጅግ ስላፈረ አስገረፋት፣ አሰቃያት፣ ዓይኗንም አወጣ። በመጨረሻም አንገቷን አስቆርጦ ከሰማዕታቱ ጋር ተራራ ላይ ጣላት። ከነገር ሁሉ በኋላ ድርጣድስና ባለሟሎቹ ለአደን በሔዱበት ርኩስ መንፈስ ወደ አውሬነት (እሪያነት) ቀየራቸው። 

✝የንጉሡ እንስሳ (አውሬ) መሆን በአርማንያ ታላቅ ድንጋጤን ፈጠረ። የንጉሡ እኅት ስታለቅስ በራእይ "ለእመ ኢያዕረግምዎ ለጐርጐርዮስ አልብክሙ ድኂን - ጐርጐርዮስን ከተቀበረበት ካላወጣችሁት አትድኑም።" አላቸው። ወዲያውም ቆፍረው አወጡት። ቅዱሱ እንደ ወጣ ዕረፍትን አልፈለገም።

ለአሥራ አምስት ዓመታት ቀባሪ አጥቶ የተበተነውን የቅድስት አርሴማንና የሰማዕታቱን አጽም ሰብስቦ በክብር አኖረው። ድርጣድስና ባለሟሎቹንም ወደ በርሃ ሒዶ ፈወሳቸው። የሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ አጽም በአሥራ አራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከሌሎች ሰማዕታት አጽም ጋር ኢትዮጵያ እንደ መጣ አባቶቻችን በትውፊት ነግረውናል። ለዚህም ነው ቡርክቷ እናታችን ከሌሎች ሃገራት ለይታ ለኢትዮጵያውያን ልዩ ፍቅር ያላት። 

✝በዋናው ገዳሟ (ወሎ /ኩላማሶ/ ስባ ውስጥ የሚገኝ ነው።) ጨምሮ ስሟ በተጠራበት ሁሉ ኃይልን ታደርጋለችና። ነገር ግን ወንድሞቼና እኅቶቼ በቅድስቷ እናታችን ስም የሚነግዱ ሥጋውያን ሰዎች በዝተዋልና እንጠንቀቅ። የሰማዕቷ ክብር ብዙ ነውና በሕልም ላይ ብቻ አንታመን። አባ እንጦንስ እንዳሉት "በሕልሙ የሚታመን ሰው ከንቱ ነውና።" (መዝ. ፸፭፥፭) በዚህ ዕለት ከሰማዕቷ ጋር የመንፈስ እናቷን ቅድስት አጋታን ልናስባት ይገባናል። ይህች እናት እመ ምኔት ስትሆን ቅድስት አርሴማን ታስተምራት፣ ታጸናት፣ ከጐኗም ትቆምላት ነበር። 

✝ ረሃቧን፣ ጥሟን፣ ስደቷን፣ መከራዋንም ሁሉ አብራት ተሳትፋለች። በፍጻሜውም አብራት ተሰይፋለች። ይህች ዕለት ለቅድስት አርሴማና ለተከታዮቿ ሰማዕታት የፍልሰትና የቅዳሴ ቤት መታሰቢያ ናት። 

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ለወዳጅዎ ያጋሩ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የቅዳሴ ትምህርታችን ከ65-69
ተለማመዱት🙏🙏😍
መልካም አዳር

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የቅዳሴ ትምህርት ከክፍል 62-64
ተለማመዱት😍

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​ታኅሣሥ 5
ቅዱስ አባት አባ ገብረ ናዝራዊ

ታኅሣሥ አምስት በዚህችም ቀን ለእግዚአብሔር ሕግ የሚቀና ገድለኛ የሆነ ንጹሕ ድንግል ቅዱስ አባት አባ ገብረ ናዝራዊ አረፈ። የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ በወገን የከበሩ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ናቸው አባቱም የቤተ ክርስቲያንን ሕጓንና ሥርዓቷን የሚጠብቅ ካህን ነው እናቱም ፈጣሪዋን የምትወድ ደግ ሴት ናት።

ይህም ቅዱስ በተወለደ ጊዜ በዕውቀት እግዚአብሔርን በመፍራት በመማር አደገ ከዚህም በኋላ ዲቁናን በተሾመ ጊዜ የብሉይና የሐዲስ መጻሕፍትን የሚያነብ ሆነ። በኦሪትም ውስጥ የሰንበትን ቀን የሻረና ሥራ የሠራባት በሞት ይቀጣ የሚል አገኘ ከወንጌልም ውስጥ እንዲህ የሚል አገኘ ከእነዚህ ትእዛዛት ታንሳለች ብሎ የሚያስተምር አንዲቱን የሻረ ለሰውም እንዲህ ብሎ የሚያስተምር በመንግሥተ ሰማያት የተለየ ይሆናል የምያደርግ እና የምያስተምር ግን እርሱ በመንግስተ ሰማይ ታላቅ ይሆናል ዳግመኛም መድኃኒታችን አባትና እናቱን ያልተወ ሰውነቱንም ለመከራ አሳልፎ ያልጣላት ሊያገለግለኝ ደቀ መዝሙሬም ሊሆነኝ አይችልም ያለውን አስተዋለ።

ከዚህም በኋላ ወደ አቡነ ጎርጎርዮስ ሔደ እርሱም ጽጋጃ በሚባል ገዳም የአቡነ አኖሬዎስ ገዳም የአቡነ አኖሬዎስ ልጅ ነው ከዚያም መነኵሶ በጾም በጸሎት በስግደት እየተጋ ኖረ። ከዚህም በኋላ ቅስና ተሾመ ከዚያም ወደ ትግራይ አገር ሔዶ ከአባ ያዕቆብ ጋር ተገናኝቶ በቅዱሳት መጻሕፍት ቃሎች ተነጋገሩ።

ከዚህም በኋላ ሀሳቡን ገለጠለት አባ ያዕቆብም እንዴት ይቻላል አለው አባ ገብረ ናዝራዊም እግዚአብሔር ይረዳኛል አለ። ከአባ ያዕቆብም ጎልት ተቀብሎ እርስ በርሳቸው በእግዚአብሔር ፈቃድ ተለያዩ። ከዚህም በኋላ ተስፋፍቶ ገዳምን ሠራ ብዙ ሰዎችም ወደርሱ ተሰብስበው መነኰሳትን ሆኑ ስለሰንበታትና በዓላትም አከባበር እንደሚገባ ሥርዓትን ሠራ። ለመነኰሳትም ከመድኃኒታችን ከልደቱና ከጥምቀቱ በዓል ከሰንበታትና ከበዓለ ሃምሳ በቀር በየሰሞኑ ሁሉ እስከ ማታ ያለማቋረጥ መጾም እንደሚገባቸው ሥርዓትን ሠራ። ዳግመኛም የሌላውን ገንዘብ እንዳይነኩ፣ እንዳይረግሙ፣ በሕያው እግዚአብሔርም ስም እንዳይምሉም ለልጆቹ ይህን ሁሉ ያስተምራቸው ነበር።

ለእርሱ ግን ለሚጸልየው ጸሎት ልክ የለውም ነቢይ ዳዊት እግዚአብሔርን ሁልጊዜ አመሰግነዋለሁ። ምስጋናውም ዘወትር በአፌ ውስጥ አለ ያለውን አስቦ ዳግመኛም ትእዛዝህን በማሰብ እጫወታለሁ ሕግህን እሻለሁ ትእዛዞችህንም አስተምራለሁ ቃልህንም አልረሳም ያለውን አስቦ።

ዳግመኛም ከሰባውና ደም ካለው ጣዕም ካላቸውም መብሎች ሁሉ ይከለከላል የጌታውን መከራ ለነፍሱ ያሳስባታልና ዕንባው ያለ ማቋረጥ ይፈስ ነበር ያለማቋረጥም ይሰግዳል ያመሰግናልም እንግዳና መጻተኛውን ይቀበላል በጽዮን ዘር በኢየሩሳሌም ቤቶች ያሉት ብፁዕ ነው ያለውን የነቢይ ቃል አስቦ ድኆችንና ችግረኞችን ይጉበኛቸዋል ።

ለዚህም አባት ትሩፋቱ ብዙ ነው ደጋግ ተአምራትንም በማድረግ በሰው ልቡናም ተሠውሮ ያለውን በማወቅ ብዙ የተለያዩ ሀብቶች ተሰጥተውታል ለልጆቹም የቀናች ሃይማኖትን አስተማራቸው በእርሷም እንዲጸኑ አዘዛቸው ከዚህም በኃላ በሸመገለ ጊዜ እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ።

ለሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ሼር አድርጉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​ታኅሣሥ 3

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ሦስት በዚህች ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ነው፣ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ፋኑኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው፣ የጻድቁ አቡነ ዜና ማርቆስ ዕረፍታቸው ነው።

በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም

ታኅሣሥ ሦስት በዚህች ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሦስት ዓመት ሲሆናት ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ነው ። እርሷ ለእግዚአብሔር የስእለት ልጅ ነበረችና።

እናቷ ቅድስት ሐና ልጅ የሌላት ስለሆነች በቤተ እግዚአብሔር ውስጥ ከሴቶች ተለይታ ርቃ ትኖር ነበር ሽማግሌ ከሆነ ከኢያቄም ከባሏ ጋርም እጅግ የምታዝን ሆነች ። እግዚአብሔርም ኀዘናቸውን ሰማ ቅድስት ሐናም እንዲህ ብላ ለእግዚአብሔር ተሳለች የሰጠህኝን ፍሬ ለእግዚአብሔር አገልጋይ አደርገዋለሁ ።

ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያምንም በወለደቻት ጊዜ ሦስት ዓመት በቤቷ ውስጥ አሳደገቻት ከዚህም በኋላ ከደናግል ጋር ትኖር ዘንድ ወደ ቤተ መቅደስ ወሰደቻት በቤተ መቅደስም ምግቧን ከመላእክት እጅ እየተቀበለች ዐሥራ ሁለት ዓመት ኖረች ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ዓለም መጥቶ ከእርሷ ሥጋን እስከ ነሣ ድረስ።

ከሴቶች ሁሉ የተመረጠች ይቺ ናት በቤተ መቅደስም በመኖር ዐሥራ ሁለት ዓመት ሲፈጸምላት እርሷ ለእግዚአብሔር የተሰጠች የስዕለት ልጅ ናትና ለሚጠብቃት ይሰጧት ዘንድ ካህናት እርስበርሳቸው ተማከሩ በሴቶች ላይ የሚደርስ በርሷ ላይም ይደርስባታል ብለው ስለፈሩ በቤተ መቅደስ ውስጥ ይተዋት ዘንድ ለእርሱ ትክክል መስሎ አልታያቸውም ስለዚህም ሊጠብቃት ለሚገባው በእርሷ ላይ እጮኛ ሊአኖሩ ወደዱ።

ከዚህም አስቀድሞ ሊቀ ካህናት ዘካርያስ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ልጄ ማርያም ሆይ አንቺ እንዳደግሽና ለአካለ መጠን እንደደረስሽ ዕወቂ ልትታጪ ትወጃለሽን እግዚአብሔርን የሚፈራ መልካም የሆነ የተባረከ ጐልማሳ እንፈልግልሽን ወይም በሕይወትሽ ዘመን ሁሉ በቤተ መቅደስ ተቀምጠሽ እግዚአብሔርን ልታገለግዪው የምትሺ ከሆነ በሴቶች ላይ የሚደርሰው በሚደርስብሽ ወራት ወደ ቤተ መቅደስ ደጅ ከመግባት ትጠበቂ ዘንድ በኦሪቱ የተጸፈውን የርግማን ሥርዓት በአንቺ ላይ እንሠራለን አላት ።

ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያምም እነሆ እኔ የእግዚአብሔር አገልጋዩ በፊታችሁ ነኝ አባትና እናት የሉኝም ስሙ ቡሩክ ምስጉን ከሆነ ከእግዚአብሔር በታች በእናትና አባት ፈንታ እናንት ናችሁና የእግዚአብሔርን ትእዛዝ እንደምታውቁ አድርጉ ብላ መለሰች።

ካህናቱና ማኅበሩም ሁሉ ዘካርያስን ወደ ቤተ መቅደስ ገብተህ ስለዚች ብላቴና ማርያም ወደ እግዚአብሔር ጸልይ አሉት ዘካርያስም ገብቶ ሲጸልይ በዚያን ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጠለትና እንዲህ አለው። ዘካርያስ ሆይ ወጥተህ ከዳዊት ወገን ሚስቶቻቸው የሞቱባቸውን ሁሉ ወንዶች ሰብስብ የየአንዳንዱንም በትር ከስሙ ጋር ውሰድ ወደ ቤተ መቅደስም በምሽት አግብተህ ወደ እግዚአብሔር ጸልይበት በነጋ ጊዜም በትሮቻቸውን አውጣ እግዚአብሔርም በበትሩ ላይ ምልክት ለገለጠልህ ለዚያ ሰው ማርያምን ተቀብሎ ሊጠብቃት ይገባዋል።

ካህኑ ዘካርያስም ወጥቶ አንድነት ለተሰበሰቡት ሕዝብ የእግዚአብሔር መልአክ የነገረውን ነገራቸው በዚያንም ጊዜ ከዳዊት ወገን ጐልማሳም ቢሆን ሽማግሌም ቢሆን ሚስቱ የሞተችበት ሁሉ በኢየሩሳሌም ወደአለ ቤተ መቅደስ ይሒድ እያሉ ዓዋጅን ዙረው የሚናገሩ በእስራኤል አገር ሁሉ ላከ ።

ከዳዊት ወገን የሆነ ጠራቢው ዮሴፍም በሰማ ጊዜ በትሩን ይዞ ከናዝሬት ወደ ኢየሩሳሌም ሔደ ካህኑ ዘካርያስም የሁሉንም በትሮች ተቀብሎ ስማቸውን በላያቸው ጻፈ ቁጥራቸውም አንድ ሽህ ዘጠኝ መቶ ሰማንያ አምስት ሆነ ዘካርያስም በትሮችን ወደ ቤተ መቅደስ አስገብቶ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ እንዲሁም ሰዎች ሁሉ ከቤተ መቅደስ ውጭ ቁመው ይጸልዩ ነበር ዘካርያስም ጸሎቱን በፈፀመ ጊዜ ለየአንዳንዱ በትራቸውን አውጥቶ ሰጠ ጠራቢው ዮሴፍም በትሩን ሊቀበል በቀረበ ጊዜ ከእርሷ ነጭ ርግብ የመሰለች ተገለጠች እየበረረችም ሒዳ በጠራቢው ዮሴፍ ራስ ላይ ተቀመጠች ካህናቱና ሕዝቡ ሁሉ አይተው እጅግ አደነቁ ምስጉን የሆነ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት።

ዘካርያስም ዮሴፍን ዮሴፍ ሆይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ እንደ ተናገረ ድንግል ማርያምን ወደ ቤትህ ወስደህ ጠብቃት አለው ዮሴፍም ቅድስት ድንግል ማርያምን ከካህናት እጅ ተቀበላት በእርሱም ዘንድ ኖረች ። ከዚህም በኋላ የመላእክት አለቃ ገብርኤል ስለ እግዚአብሔር ልጅ ከእርሷ ሰው ሁኖ ስለመወለዱ በዮሴፍ ቤት አበሠራት።

ለሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ሼር አድርጉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

የቅዳሴ ትምህርታችን ከክፍል 59-61

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​ኅዳር 28
ቅዱስ አባ ሊቃኖስ


በዚችም ቀን በኢትዮጵያ ምድር በደብረ ቊንጽል ተጋድሏቸውን የፈጸሙ አባ ሊቃኖስ ተሰወሩ።

አቡነ ሊቃኖስ ከዘጠኙ ቅዱሳን ውስጥ አቡነ ሊቃኖስ ለየት የሚሉበት ነገር ቢኖር ዓሥሩም የእጆቻቸውና የእግሮቻቸው ጣቶች እንደፋና ያበሩ ነበር፡፡ ይህንንም ገድለ አቡነ አረጋዊ "ቆመው ጸሎት በሚጸልዩበት ጊዜ ዓሥሩ የእጆቻቸው ጣቶችና ዓሥሩ የእግሮቻቸው ጣቶች እንደፋና የሚያበሩበትና እንደመብረቅ የሚብለጨልጩበት ጊዜ አለ" በማለት ይገልጸዋል፡፡ በሥዕላቸውም ላይ ይህንኑ ለማሳየት አባቶቻችን የራሳቸውን ጥበብ ተጠቅመዋል፡፡

የአቡነ ሊቃኖስ ገዳማቸው በደብረ ቁናጽል አክሱም ከአባ ጰንጠሌዎን ገዳም አቅራቢያ ይገኛል፡፡ ጻድቁ ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ያደረጉ ነበር፡፡ መላእክትም ዘወትር ባለመለየት ይጎበኙዋቸው ነበር፡፡ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም ዘወትር እየተገለጠላቸው ይባርካቸውና ቃልኪዳን ይሰጣቸው ነበር፡፡

በጸሎታቸውም አጋንንትን አውጥተዋል፣ ድውያንን ፈውሰዋል፣ ዕውራንን አብርተዋል፣ ሙታንን አንሥተዋል፡፡ ስለዘጠኙ ቅዱሳን ሐዋርያዊ አገልግሎት ከአቡነ አረጋዊ ገድል ጋር ጥቅምት 14 በስፋት ስለተጻፈ ከዚያ ላይ ይመለከቷል፡፡

ከተስዓቱ ቅዱሳን ውስጥ አራቱ ሞትን ሳያዩ ተሰውረዋል፡፡ አቡነ አረጋዊ ጥቅምት 14 ቀን ተሰወሩ፡፡ አቡ ገሪማ ሰኔ 17 ቀን፣ አቡነ አፍጼ ግንቦት 29 ቀን፣ አቡነ ሊቃኖስ ህዳር 28 ቀን ተሰወሩ፡፡

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ለሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ሼር አድርጉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እነዚህን ውብ ቲሸርቶች ተመልከቱ!

በ2016 ዓ.ም በጥምቀት ቀን መላው ሃገሪቱን ያጥለቀልቁታል ከተባሉት እና በብዙዎች ከተወደዱት ቲሸርቶች መካከል እነዚህ ጥቂቶቹ ናቸው።

ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በእነዚህ ክፍለ ሃገር ላላችሁ
👉 ጅማ 👉 ሊሙ
👉 አዳማ 👉 ዝዋይ (ባቱ)
👉 ቦንጋ 👉 ወሊሶ
👉 አሰላ 👉 ሃዋሳ
👉 ሻሸመኔ 👉 ሆለታ
👉 አንቦ 👉 ሆሳዕና
👉 ወላይታ ሶዶ 👉 ድሬድዋ
👉 ሀረር 👉 ጂግጂጋ
👉 ወልቂጤ 👉 ደብረ ብርሃን
👉 ዲላ

ከኛ ተረክባችሁ ማከፋፈልበማህበርም ሆነ በግል ማዘዝ ከፈለጋችሁ ከላይ በተጠቀሱት ቦታዎች በሙሉ ያሉበት ድረስ የምናደርስ ይሆናል።

ሌሎቹንም በኦርቶዶክሳዊ ዲዛይነሮች ተውበው የተሰሩ የጥምቀት ቲሸርቶችን ለማየት እና ለማዘዝ የስር ያለውን የቴሌግራም ሊንክ ይጠቀሙ።
👉 /channel/KABAPrint
👉 /channel/KABAPrint

ማሳሰቢያ - በምታዙበት ወቅት ለምትከፍሉት የቀብድ ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ሀላፊነቱን እኛ እንወስዳለን። አንዳንድ ጥያቄዎች እየደረሱን ስለሆነ ነው።

በብዛት ማዘዝ የምትፈልጉ ቀደም ብላችሁ ብታዙን መልካም ነው ቀኑ እየደረሰ ሲመጣ ትዕዛዝ በጣም ስለሚበዛብን ቀደም ብለው ይዘዙን።

   ለበለጠ መረጃ
👉 0965875219
👉 0922501999
👉 0913655116

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​ኅዳር 26

ቅዱስ አቡነ ኢየሱስ ሞዓ ዘሐይቅ

ኅዳር ሃያ ስድስት በዚህች ዕለት አቡነ ኢየሱስ ሞዓ ዘሐይቅ እረፍታቸው ነው። በጐንደር ክፍለ ሀገር ስማዳ ወረዳ ዳህና ሚካኤል በተባለው ቦታ ከአባታቸው ከዘክርስቶስና ከእናታቸው ከእግዚእ ክብራ በ1210 ዓ.ም ነው ተወለዱ። ዕድሜያቸው 3ዐ ዓመት እስከሚደርስ ከቤተሰቦቻቸው ትምህርተ ሃይማኖትንና ግብረ ገብን ሲማሩ ከቆዩ በኋላ በ124ዐ ዓ.ም ይኼንን ዓለም በመተው ወደ ደብረ ዳሞ ገዳም ገቡ። በደብረ ዳሞ ገዳም መነኰሳቱን እየረዱ፣ ትምህርተ ቤተ ክርስቲያንን እያጠኑ፣ ትምህርተ ቅዱሳት መጻሕፍትን እየገለበጡ ለሰባት ዓመታት ከቆዩ በኋላ የደብረ ዳሞ 3ኛ አበ ምኔት ከሆኑት ከአባ ዮሐኒ ምንኩስናን ተቀበሉ (1247 ዓ.ም.)።

አንድ ቀን ሌሊት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ወደርሳቸው መጥቶ (ገድልህና ትሩፋትህ በዓለም ሕዝብ ሁሉ ትተህ የስምህ መክበርያ ወደሆነው ሐይቅ ወደ ተባለው ሥፍራ ሂድ) አላቸው። አባታችን "ቦታውን እንዴት ዐውቀዋለሁ" በማለት ቢጠይቁት "ተነሥ። ጉዞህን ጀምር ቦታውን እኔ አሳይሃለሁ" አላቸው። አባ ኢየሱስ ሞዓ በመልአኩ እንደታዘዙት ከበአታቸው ተነሥተው ተከተሉት። የብዙ ወራት መንገድ የሆነው ጐዳናም በስድስት ሰዓት አለቀላቸው።

በዚያን ወቅት ከሐይቅ ገዳም በስተ ሰሜን ወደነበረው ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን ደረሱ። ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ከመግባታቸውም በፊት ለ6 ወራት ያህል በጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን አገልግለዋል። ያገለግሉበት በነበረው ቤተ ክርስቲያን ቀን ቀን ሕዝቡን ሲያስተምሩ በመዋል ሲመሽ ወደ ሐይቁ በመግባት ሲጸልዩ ያድሩ ነበር። በሐይቅ እስጢፋኖስና በዙርያው ለነበሩ አበውም ማታ ማታ አንድ ብርሃን ወደ ሐይቁ ሲገባ ጠዋት ጠዋትም ሲወጣ ይታያቸው እንደነበር ዛሬ በገዳማቸው የሚገኘው ገድለ ኢየሱስ ሞዓ ያስረዳል።

በመጨረሻም በገዳሙ አባቶች ልመናና በልዑል እግዚአብሔር ትዕዛዝ ወደ ሐይቅ ገዳም ገብተው አበምኔት ሆኑ። ሐይቅ እስጢፋኖስ ማለት ከደሴ 30 ኪሎ ሜትር ርቆ የሚገኝ ሲሆን የመሰረቱት ካልዕ ሰላማ የተባሉ ግብጻዊ ጻድቅ ናቸው፤ ገዳሙን ከሰሩ በኃላ የማንን ታቦት እናስገባ ብለው ሲያስቡ ቶራ የምትባል እንስሳ ጭነት ተጭና ከመካከላቸው ተገኘች፤ ጭነቱን አውርደው ቢያዩት በሐር ጨርቅ የተጠቀለለ ሁለት ታቦት አገኙ አንዱ የእስጢፋኖስ አንዱ የጊዮርጊስ " ይህንን ታቦት በእየሩሳሌም የሚኖሩ የተሰወሩ ቅዱሳን ከእግዚያብሔር ታዘው የላኩት ነው" የሚል ጽሑፍም አገኙ ይላል። ይህ ከሆነ ከ 400 ዘመን በኃላ ነው አባ እየሱስ ሞኣ ወደዚህ ቦታ የመጡት ለ 52 ዓመት ቀን ቀን መንፈሳዊ ስራቸውን ይሰራሉ ሌሊት ሌሊት ሐይቁ ውስጥ ቆመው ሲጸልዩ ያድራሉ።

አባ ኢየሱስ ሞዓ በሐይቅ እስጢፋኖስ በአበምኔትነት በቆዩባቸው 45 ዓመታት ከየገዳማቱ ቅዱሳን መጻሕፍትን በመገልበጥና በማስገልበጥ ብሎም በማሰባሰብ የመጀመርያው ዘመናዊ የቤተ ክርስቲያን ቤተ መጻሕፍት በሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም እንዲቋቋም አድርገዋል። በዚሁ ገዳም ውስጥም የመጀመርያውን የቤተ ክርስቲያን ቋሚ ትምህርት ቤት በማቋቋም 8ዐዐ መነኮሳትን በትምህርተ ሃይማኖት አሠልጥነው በንቡረ ዕድነት ማዕረግ በመላ ሀገሪቱ እንዲሠማሩ አድርገዋቸዋል።

ከተማሪዎቻቸውም መካከል አቡነ ተክለ ሃይማኖት (ዘደብረ ሊባኖስ)፣ አባ ተክለሃይማኖት ያመነኮሱ አባት ናቸው። አባ ኂሩተ አምላክ (ዘጣና ሐይቅ)፣ አባ ጊዮርጊስ (ዘጋሥጫ)፣ አባ ዘኢየሱስ፣ አባ በጸሎተ ሚካኤል፣ አባ አሮን (ዘደብረ ዳሬት) ጥቂቶች ናቸው። አፄ ይኩኖ አምላክንም በትምህርተ ሃይማኖት ያነፁት እርሳቸው ናቸው።

እንደዚህ ነው የመነኮሳት አባት እንጦንስ ነው እንጦንስ መቃርስን ወለደ መቃርስ ጳኩሚስን ጳኩሚስ አቡነ አረጋዊን አቡነ አረጋዊ አባ ዮሐኒን አባ ዮሐኒ የሐይቁን አባ እየሱስ ሞአን ወለዱ አባ ኢየሱስ ሞዓ ደግሞ ተክለሃይማኖትን ወለዱ።

በዮዲት ጉዲት ተጐድታ የነበረችው ሀገራችን ዳግም የወንጌሉ ብርሃን እንዲበራባት ሊቃውንት እንዲይነጥፉባት፣ ቅዱሳት መጻሕፍት እንዳይቆነጻጸሉ፣ መነኮሳት አባቶች ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ወርደው ገዳማትን እንዲያስፋፉ ያደረጉት አባ ኢየሱስ ሞዓ ናቸው። በተለይም የሐይቅ እስጢፋኖስ ያፈራቸው 8ዐዐ ሊቃውንት በመላዋ ሀገሪቱ በመሠማራታቸው ዛሬ የምናያቸውን አብዛኞቹን ገዳማትና ቅዱሳት መጻሕፍት አቆይተውናል።

አባታችን አባ ኢየሱስ ሞዓ ለ45 ዓመታት ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ከቆዩ በኋላ ኅዳር 26/1292 ዓ.ም በዕለተ እሑድ በ82 ዓመታቸው ዐረፉ። በዚያች ዕለትም በቦታው የታየው ብርሃን ሀገሪቱን መልቷት እንደነበረ ገድላቸው ይመሠክራል።

ለሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ሼር አድርጉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ቤት መፍትሔ ሊሰጥባቸው ይገባል ያላቸውን በ13 ነጥቦች የተዘረዘሩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በሀገረ ስብከቱ በኩል መፍትሔ እንዲሰጣቸው ውሳኔ አስተላለፈ።


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጋር ባደረገው ውይይት በሀገረ ስብከቱ በኩል የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በተመለከተ በተደረገው የጋራ ውይይት በሀገረ ስብከቱ የሚስተዋሉትን ዋናዋና ችግሮች መቅረፍ ይቻል ዘንድ በጠቅላይ ቤተክህነት በኩል ተለይተው የሚታወቁት ዋናዋና ነጥቦች ለሀገረ ስብከቱ እንዲደርሰው ተደርጎ መፍትሔ እንዲሰጥበት የአዲስአበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሔኖክ በጉባኤው ወቅት በሰጡት ማጠቃለያ ሀሳብ ላይ በገለጹት መሰረት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ ኅዳር 24ቀን2016ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ ሀገረ ስብከቱ በኩል በአፋጣኝ ምላሽ ሊያገኙ ይገባቸዋል ያላቸውን
13 ነጥቦችን በመለየት ለሀገረ ስብከቱ እንዲደርሰውና ከበዛ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለተጠቀሱት የመልካም አስተዳደር ችግሮች ምላሽ እንዲሰጥና የውሳኔውን መፈጸም አለመፈጸም በተመለከተም ተከታትለው የሚያስፈጽሙ ሦስት የመምሪያ ኃላፊዎችን መድቧል።

የጠቅላይ ቤተክህነቱ ዋና ዓላማ ሕግ፣ደንብና መመሪያ ተከብሮ ስራ እንዲሰራ ፣ፍትሕና ርትዕ እንዲነግስ፣
ተጠያቂነትና ግልጽነትን የተከተለ ተቋማዊ አሰራር እንዲሰፍን ለማድረግ እንደሆነ ከመግለጽ ጋር የሚከሉት ዋና ዋና ነጥቦች በሥራ ላይ እንዲውሉ ሲል ልዩነት በሌለው ድምጽ ወስኗል።

የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን አስመልክቶ በጋራ የውይይት መድረክ ችግሮችን በመለየት በውይይት በመፈተሸ በጋራ የመፍትሔ አቅጣጫ ለማስቀመጥ እንዲቻል አስቀድሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደር ጉባኤ ኅዳር 4 ቀን 2016 ዓ.ም በወሰነው መሠረት ኅዳር 18 ቀን 2016 ዓ.ም ባደረገው የጋራ የውይይት መድረክ እንደ ችግር ተለይተው በቀረቡ ዋና ዋና ነጥቦች ላይ ተመሥርቶ በቀረበው የቃለ ጉባኤ ዘገባ ላይ ተወያይቶ ለመወሰን የተደረገ ስብሰባ ነው፡፡

በመሆኑም ጉባኤው ኅዳር 18 ቀን 2016 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ከክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት የሥራ ኃላፊዎች ጋር የተደረገውን የጋር የውይይት መድረክ አስመልክቶ ከቃለ ጉባኤ ጸሐፊዎች የቀረበውን የቃለ ጉባኤ ዘገባ በንባብ ካዳመጠ በኋላ የችግሩ መንስዔ ናቸው በማለት የተለዩ ዋና ዋና ነጥቦች፦

1.በሀ/ስብከቱ ረጅም ዘመናት ሲንከባለል የመጣ የመልካም አስተዳደር ችግር መኖሩ የሚታወቅ ቢሆንም በአሁኑም ሰዓት የበለጠ ተባብሶ የቀጠለ መሆኑን፤

2 የመልከም አስተዳደር ችግርሩ መንስዔ የሕጎችና የደንቦች ጥሰት፤በእቅድና በጸደቀ በጀት ላይ ተመስርቶ ያለመሥራት ውጤት መሆኑን፤

3. መተዳደሪያ ደንቡ ተጥሶ በፍላጎት ላይ ያልተመሠረተ ቅጥርና የሠራተኞች መብትን ያላከበረ የዝውውር ምደባ ውጤት መሆኑን፤

4.የሐብትና የገንዘብ ቁጥጥር ሥራው ደካማ መሆኑ፤

5.ከበላይ መስሪያ ቤት ጋር ተናቦ ያለመሥራትና መሰል ችግሮች ያስከተለው ውጤት መሆኑን ከጋራ ስብሰባውና ከዘገባ ሪፖርቱ ለአስተዳደር ጉባኤው ግንዛቤ በመውሰድና በውይይት የተለዩትን ዋና ዋና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን አስመልክቶ የሀስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በማጠቃለያ በሰጡት ሐሳብ ላይ የመልካም አስተዳደር ችግሮቹ ተለይተውና ተቆጥረው ይሰጡን ለመፍታት ዝግጁ ነን በማለት በገቡት ቃል መሠረት አስተዳደር ጉባኤው በችግሮቹ ላይ በሰፊው ተወያይቶ የሚከተለውን ውሳኔ ወስኗል፡፡

ው ሳ ኔ
አስተዳደር ጉባኤው ከፍ ብሎ በጋራ የውይይት መድረኩ በዝርዝር የተቀመጡትን ዋና ዋና የችግር መንስኤዎችን በመለየት በሀ/ስብከቱ የተሸለ የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት መልካም አስተዳደር ማስፈን ይቻል ዘንድ ፡-

1.በሀ/ስብከቱ መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ  ንኡስ ቁጥር  የህግ ድንጋጌ መሠረት ሀ/ስብከቱ ዓመታዊ እቅዱንና በጀቱን አጥንቶና በጉባኤ ወስኖ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት አቅርቦ በማጸደቅ ተግባራዊ ያደርጋል በሚል የተደነገገ ቢሆንም እስከአሁን ድረስ ወደ ዋናው መሥሪያ ቤት ቀርቦ የጸደቀ በጀት ባለመኖሩ ሀ/ስብከቱ ዓመታዊ ዕቅዱንና በጀቱን በአስቸኳይ በጉባኤ ወስኖ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት አቅርቦ በማጸደቅ ተግባራዊ እንዲያደር፤

2.ሀ/ስብከቱ የሰው ኃይል እጥረት ሳይሆን ያለውን የሰው ኃይል ከሥራው ጋር በማጣጣም ሥራና ሠራተኛን በማገናኘት የማሠራት ችግር መሆኑን ጉባኤው ተረድቷል በመሆኑም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ግንቦት 18 ቀን 2014 ዓ.ም ቋሚ ሲኖዶስ ጥር 27 ቀን 2014 ዓ.ም. ፣ መስከረም 27 ቀን 2015 ዓ.ም እና ጥቅምት 30 ቀን 2016 ዓ.ም. በወሰነው መሠረት ለሥራው ሲባል መተዳደሪያ ደንቡ ተጠብቆ ከሚደረግ የውስጥ ዝውውርና ሽግሽግ በስተቀር ይህ ውሳኔ ከተወሰነበት ቀን ጀምሮ ምንም ዓይነት ቅጥር እንዳይፈጸም፤

3.ሽልማትና ልዩ ልዩ ስጦታዎችን በተመለከተ አንድ ሰው ሊሸለም የሚችለው ዕለት ተዕለት እንዲያከናውን ከተሰጠው የሥራ ተልዕኮ በላይ ለተቋሙ እድገትና ለተሻለ አሠራር በእራሱ ተነሳሽነት ላከናወናቸው ተጨማሪ የሥራ አፈጻጸም የተለየ ብልጫ እንዳስመዘገበ ሲታመን ለበለጠ ሥራ ለማነሳሳትና ለሌሎቹ ምሳሌ መሆኑ የታመነ ነው፤ ነገር ግን እውነታው ይህ ሆኖ እያለ ከሀ/ስብከት እስከ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያን ድረስ እየተፈጸመ ያለው ሽልማት ግን ለብዙ ትችትና የሐብት ብክነት የተጋለጠ በመሆኑ ሽልማት መስጠት አስፈላጊነቱ ሲታመንበት የሥራ አፈጻጸምንና የአገልግሎት ትጋትን መሠረት አድርጎ እንዲከናወን እንዲደረግና ከነዚህ መመዘኛ መሥፈርት ውጪ ያሉ ሽልማቶች እንዲቆም፤

4. የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እስከአሁን ሲያደርገው እንደቆየው ሁሉ ሒሳቡን በውጭ ኦዲተር ለማስመርመር በያዘው እቅድ መሠረት ኦዲተሮችን አወዳድሮ ሥራውን ለማስጀመር ዝግጅቱን ያጠቃለለ ሲሆን ሀ/ስብከቱም በአስቸኳይ እስከ ክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ድረስ የሚገኙትን ሒሳቦች በገለልተኛ የውጭ ኦዲተር አስመርምሮ ለጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ሪፖርት እንዲያቀርብ፤

5. በክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ደረጃ ለፐርሰንት መሰብሰቢያ በሚል የተከፈቱ የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች እስከ አሁን ድረስ በሀ/ስብከቱና በክፍለ ከተማው ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ ጣምራ ፊርማ ሲንቀሳቀስ የቆየ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ከሁለቱ ፈራሚዎች በተጨማሪ የሀ/ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ተጨምረው በሦስት ጣምራ ፊርማ ብቻ እንዲንቀሳቀስና ከፐርሰንቱ የሚገኘው የባንክ ወለድም ተጠቃሎ ወደ ሀ/ስብከቱ የባንክ ሒሳብ ፈሰስ እንዲደረግ፤

6. ከአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ጀምሮ እስከ ሀ/ስብከቱ ጽ/ቤት ድረስ መስተንግዶ በሚል ሽፋን ከፍተኛ የሆነ የገንዘብ ብክነት እየደረሰ እንደሚገኝ ጉባኤው በጋራ ውይይቱ ከተነሱ ሐሳቦች ተገንዝቧል፤ ስለሆነም አስቀድሞ በእቅድ ላይ ተመሥርቶ ከጸደቀ የእህል ውሃ መስተንግዶ በጀት ውጭ ምንም ዓይነት የመስተንግዶ ወጪ እንዳይደረግ፤

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

code 6 :- ይህንን ይመስላል
ለማዘዝ እና ለበለጠ መረጃ
📩 @kalSandy

📞 0965875219
📞 0922501999
📞 0913655116

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

code 3 :- ይህንን ይመስላል 🙏
ለማዘዝ እና ለበለጠ መረጃ
📩 @kalSandy

📞 0965875219
📞 0922501999
📞 0913655116

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ተመልከቱ ሕትመቱ ላይ ውበቱን!!!

ጥራት እና ውበት መገለጫችን ነው። እንደምታዩት በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ በጣም የተዋቡ ቲሸርቶችን ለማህበራት፣ ለግለሰብ፣ ከኛ ተረክበው ለሚያከፋፍሉ፣ ለሰፈር ወጣቶች፣ ለቤተክርስቲያን ከአዲስአበባ ጀምሮ ወደ ተለያየ ቦታ እያከፋፈልን እንገኛለን።

በተለይም በብዛት ተረክባችሁ ለምታከፋፍሉለምትሸጡ በሙሉ በጣም አስገራሚ ቅናሽ አቅርበንላቹኀል።

እንደምትመለከቱት ዲዛይናችን እና ሕትመታችን ልዩነት የለውም። በዓይናቹ ምታዩትን በእጃቹ ትወስዳላቹ።

"ትዕዛዝ በጣም ስለሚበዛብን ቀኑ ደርሶ ከመዋከብ ቀደም ብለው ቢያዙን መልካም ነው።"

ተጨማሪ ዲዛይኖችን ለመመልከት
👉 /channel/KABAPrint
👉 /channel/KABAPrint

ለማዘዝ እና ለበለጠ መረጃ
📩 @kalSandy

📞 0965875219
📞 0922501999
📞 0913655116

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🤴ቅዱስ ዳዊት ለልጁ ጠቢቡ ሰሎሞንን ልጄ ሆይ ሰው ኹን ከሰውም ሰው ኹን አለው
መጽሐፈ ነገሥት ፩ኛ 2፥3

ቅዱስ ዳዊት ሰው ኹን ማለቱ ምን ማለቱ ነው?🤔
ሰው ከሰውም ሰው ለመሆን ምን ማድረግ አለብን?😨
ሰው የመሆን ጥቅም እና ጉዳቱ ምነው ?
ፈጣሪ ለምን ከፍጥረታት ልዩ አድርጎ ፈጠረን?
እስቲ ይህን ቻናል በመቀላቀል የተለያዩ ሰለ ሰው ስለመሆን ያለንን ዕውቀት እናሳድገው።

ሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን
                 👇👇👇
/channel/+3zD2O5b66OtlMTFk
/channel/+3zD2O5b66OtlMTFk

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ከ94,000member በላይ ባለው ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍ ቻናል የኦርቶዶክስ መጽሐፍ በPDF ያንብቡ።

❣📚❣
1, እመጓ
2, ዝጎራ
3, መርበብት
4, ዴርቶጋዳ
5, ዮራቶራድ
6, ዣንቶዣራ
7,መጽሐፈ ሄኖክ
8, ቤተክርስቲያንህን እወቅ እንዳትሆን መናፍቅ
9, ፍኖተ አእምሮ
9, አዳም እና ጥበቡ
10, ዝክረ መስቀል
11, ሰይፈ ሥላሴ
12, ፍትሐ ነገስት
13, መጽሐፈ መነኮሳት
14, ከአክራሪ እስልምና ወደ ክርስትና
16, ህግጋተ ወንጌል
17, ነገረ ማርያም በጥንታዊቷ ቤተከርስቲያን
18, ድርሳነ ሚካኤል ወ ገብርኤል
19, ውዳሴ ማርያም በግእዝ
20, ግድለ ተክለሃይማኖት
21, ገድለ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሰጫ
22, የወጣቶች ህይወት
23, መጽሐፈ ገድለ ሐዋርያት
24, ኦርቶዶክስ መልስ አላት
25, የዋልድባ ገዳም ታሪክ
26, መጽሐፈ አክሲማሮስ
27, 14ቱ ፍሬ ቅዳሴያት ከነ አንድምታው
28, መልክዓ መለኮት
29, መጽሐፈ አሚን ወ ሥርዓት
30, ሰባቱ ምስጢራተ ቤተከርስቲያን
31, ሐይማኖተ አበው
32, ራዕየ ማርያም
34, የመናኝ ጉዞ



📚📚📚የቱን ኦርቶዶክሳዊ መፅሀፍ ማንበብ ይፈልጋሉ የሚፈልጉትን መፅሀፍ በመንካት ያንብቡ መልካም ንባብ📖

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

⏰ከ60 second በኋላ ሰለሚጠፋ አሁኑኑ JOIN✅ በማድረግ ተቀላቀሉ በቴሌግራም ኦርቶዶክሳዊያን በርካታ ምእመናን ያለው ቻናል ነው ይወዱታል።

ይ🀄️ላ🀄️ሉን
❤️👇🏽👇🏽👇🏽❤️
/channel/addlist/ixbE7pBtBZRmMzQ0

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

መጽሐፉ ለጠፋባችሁ ድጋሜ ይኸው ተልኳል።

በእዚህ መከታተል ትችላላችሁ። እባካችሁ
እህት ወንድሞቻችንን ወደ እዚህ ቻናል አስገቧቸው ይቀላቀሉን።

ቅዳሴ ሁላችንም ኦርቶዶክሳዊያን እንቀጥል እንማማር

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ተመልከቱ ሕትመቱ ላይ ውበቱን!!!

ጥራት እና ውበት መገለጫችን ነው። እንደምታዩት በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ በጣም የተዋቡ ቲሸርቶችን ለማህበራት፣ ለግለሰብ፣ ከኛ ተረክበው ለሚያከፋፍሉ፣ ለሰፈር ወጣቶች፣ ለቤተክርስቲያን ከአዲስአበባ ጀምሮ ወደ ተለያየ ቦታ እያከፋፈልን እንገኛለን።

በተለይም በብዛት ተረክባችሁ ለምታከፋፍሉለምትሸጡ በሙሉ በጣም አስገራሚ ቅናሽ አቅርበንላቹኀል።

እንደምትመለከቱት ዲዛይናችን እና ሕትመታችን ልዩነት የለውም። በዓይናቹ ምታዩትን በእጃቹ ትወስዳላቹ።

"ትዕዛዝ በጣም ስለሚበዛብን ቀኑ ደርሶ ከመዋከብ ቀደም ብለው ቢያዙን መልካም ነው።"

ተጨማሪ ዲዛይኖችን ለመመልከት
👉 /channel/KABAPrint
👉 /channel/KABAPrint

ለማዘዝ እና ለበለጠ መረጃ
📩 @kalSandy

📞 0965875219
📞 0922501999
📞 0913655116

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እነዚህን ውብ ቲሸርቶች ተመልከቱ!

በ2016 ዓ.ም በጥምቀት ቀን መላው ሃገሪቱን ያጥለቀልቁታል ከተባሉት እና በብዙዎች ከተወደዱት ቲሸርቶች መካከል እነዚህ ጥቂቶቹ ናቸው።

ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በእነዚህ ክፍለ ሃገር ላላችሁ
👉 ጅማ 👉 ሊሙ
👉 አዳማ 👉 ዝዋይ (ባቱ)
👉 ቦንጋ 👉 ወሊሶ
👉 አሰላ 👉 ሃዋሳ
👉 ሻሸመኔ 👉 ሆለታ
👉 አንቦ 👉 ሆሳዕና
👉 ወላይታ ሶዶ 👉 ድሬድዋ
👉 ሀረር 👉 ጂግጂጋ
👉 ወልቂጤ 👉 ደብረ ብርሃን
👉 ዲላ

ከኛ ተረክባችሁ ማከፋፈልበማህበርም ሆነ በግል ማዘዝ ከፈለጋችሁ ከላይ በተጠቀሱት ቦታዎች በሙሉ ያሉበት ድረስ የምናደርስ ይሆናል።

ሌሎቹንም በኦርቶዶክሳዊ ዲዛይነሮች ተውበው የተሰሩ የጥምቀት ቲሸርቶችን ለማየት እና ለማዘዝ የስር ያለውን የቴሌግራም ሊንክ ይጠቀሙ።
👉 /channel/KABAPrint
👉 /channel/KABAPrint

ማሳሰቢያ - በምታዙበት ወቅት ለምትከፍሉት የቀብድ ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ሀላፊነቱን እኛ እንወስዳለን። አንዳንድ ጥያቄዎች እየደረሱን ስለሆነ ነው።

በብዛት ማዘዝ የምትፈልጉ ቀደም ብላችሁ ብታዙን መልካም ነው ቀኑ እየደረሰ ሲመጣ ትዕዛዝ በጣም ስለሚበዛብን ቀደም ብለው ይዘዙን።

   ለበለጠ መረጃ
📩 @kalSandy

👉 0965875219
👉 0922501999
👉 0913655116

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እነዚህን ውብ ቲሸርቶች ተመልከቱ!

በ2016 ዓ.ም በጥምቀት ቀን መላው ሃገሪቱን ያጥለቀልቁታል ከተባሉት እና በብዙዎች ከተወደዱት ቲሸርቶች መካከል እነዚህ ጥቂቶቹ ናቸው።

ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በእነዚህ ክፍለ ሃገር ላላችሁ
👉 ጅማ 👉 ሊሙ
👉 አዳማ 👉 ዝዋይ (ባቱ)
👉 ቦንጋ 👉 ወሊሶ
👉 አሰላ 👉 ሃዋሳ
👉 ሻሸመኔ 👉 ሆለታ
👉 አንቦ 👉 ሆሳዕና
👉 ወላይታ ሶዶ 👉 ድሬድዋ
👉 ሀረር 👉 ጂግጂጋ
👉 ወልቂጤ 👉 ደብረ ብርሃን
👉 ዲላ

ከኛ ተረክባችሁ ማከፋፈልበማህበርም ሆነ በግል ማዘዝ ከፈለጋችሁ ከላይ በተጠቀሱት ቦታዎች በሙሉ ያሉበት ድረስ የምናደርስ ይሆናል።

ሌሎቹንም በኦርቶዶክሳዊ ዲዛይነሮች ተውበው የተሰሩ የጥምቀት ቲሸርቶችን ለማየት እና ለማዘዝ የስር ያለውን የቴሌግራም ሊንክ ይጠቀሙ።
👉 /channel/KABAPrint
👉 /channel/KABAPrint

ማሳሰቢያ - በምታዙበት ወቅት ለምትከፍሉት የቀብድ ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ሀላፊነቱን እኛ እንወስዳለን። አንዳንድ ጥያቄዎች እየደረሱን ስለሆነ ነው።

በብዛት ማዘዝ የምትፈልጉ ቀደም ብላችሁ ብታዙን መልካም ነው ቀኑ እየደረሰ ሲመጣ ትዕዛዝ በጣም ስለሚበዛብን ቀደም ብለው ይዘዙን።

   ለበለጠ መረጃ
👉 0965875219
👉 0922501999
👉 0913655116

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​ጴጥሮስን ለታላቅ ንስሓ የቀሰቀሰው የዶሮ ጩኸት ነበር ... ‹የዶሮ ጩኸት ጴጥሮስን ለንስሓ አበቃው› የሚለው ታሪክ ከዶሮ ጩኸት አልፎ እልፍ ሰባኪያን ‹ንስሓ ግቡ› እያሉ ሲጮኹ እየሰማን ምንም ለማይመስለን ለእኛ ለልበ ደንዳኖቹ መልእክቱ ምን ይሆን? የዶሮዎቹን ጩኸት ሰምቶ በመመለስ ፈንታ የዶሮዎቹን የአጯጯህ ስልት እያወዳደርን ሰባኪያን ለምናማርጥ ለእኛ መልእክቱ በእርግጥ ምን ይሆን?

በእርግጥ የዶሮውም እድል የሚያስቀና ነው፡፡ አንድ ጊዜ ጮኾ የወደቀውን ጴጥሮስ እንዲነሣ መቀስቀስ መቻሉ የታደለ ሰባኪ ያደርገዋል፡፡ ብዙ ጊዜ ስንጮኽ ውለን አንድ ሰው ለንስሓ ማብቃት ላልቻልን ሰባኪያን ይህ ዶሮ ምንኛ የሚያስቀና ነው? ለነገሩ በልማዱ ዶሮ ጮኾ ሌሎቹን ከማስነሣቱ በፊት እሱ ተነሥቶ ክንፉን እያርገበገበ ከፍ ከፍ ይላል፡፡ እኛ ግን ራሳችን በኃጢአት ተኝተን ሌላውን ለንስሓ ለመቀስቀስ የምንሞክር እንቅልፋም ዶሮዎች ስለሆንን በጩኸታችን የረበሽነው እንጂ የቀሰቀስነው ሰው የለም፡፡

(ከዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ - ሕማማት መጽሐፍ የተወሰደ)
ለሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ሼር አድርጉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

https://vm.tiktok.com/ZM6NbeFmb/

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​ኅዳር 27
ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሰማዕት


በዚህችም ቀን በንሑር ከሚባል አገር ቅዱስ ጢሞቴዎስ በሰማዕትነት አረፈ። ይህም ቅዱስ ከታናሽነቱ ጀምሮ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሁልጊዜ በጾም በጸሎት ተጠምዶ የሚኖር ነው ስሟ ሞራ የሚባል ሚስት አለችው እርሷም የአጎቱ ልጅ ናት በሥራዋ ሁሉ ደስ የምታሰኘው መልካም ሴት ናት።

እንደዚህም በፍቅርና በስምምነት ሲኖር ከከሀዲ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ የጣዖታት ቤቶች ይከፈቱ ዘንድ አብያተ ክርስቲያናት እንዲዘጉ ትእዛዝ ወጣ። ቅዱስ ጢሞቴዎስም ይህን ሰምቶ እጅግ ደስ አለው። እርሱ ስለ ክርስቶስ ፍቅር ደሙን ያፈስ ዘንድ ይህን ዘመን ይጠብቀው ነበርና ለሚስቱም ሊሠራው ያሰበውን ነገራት እርሷም የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን አለች።

ከዚህም በኋላ መንገዱን ያቀናለት ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ ጌታችንም በዚያች ሌሊት በሕልሙ ተገልጾለት ወዳጄ ጢሞቴዎስ ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን እነሆ ከጻድቃኖቼ ቁጥር ውስጥ ቆጥሬሃለሁ አሁንም ተነሣ ሚስትህንም ይዘህ ወደ ብህንሳ ከተማ ሒዳችሁ ጣዖታትን በሚያመልኩ ሁሉ ሕዝብ ፊት በስሜ ታመኑ አለው። በነቃ ጊዜም ለሚስቱ ነገራት እርሷም ይህንኑ የሚመስል ሕልሟን ነገረችው።

ከዚህም በኋላ ተነሥተው በአንድነት ሔዱ ወደ መኰንኑ ወደ ቊልቊልያኖስም ደረሱ መሰንቆና እንዚራ እያስመታ ለጣዖታቱ በዓልን ሲያከብር አገኙት ያንጊዜ ወታደሮቹ ይዘው በመኰንኑ ፊት አቆሙት ሚስቱም ተከተለችው መኰንኑም ለጣዖት መስገድን እያግባባ በርኅራኄ ቃል ተናገረው ቅዱሱ ግን እርሱንና የረከሰች ሃይማኖቱን ሰደበ ስለዚህም መኰንኑ ተቆጥቶ ከሚስቱ ጋር ወደ ወህኒ ቤት እንዲአስገቡት አዘዘ።

ከጥቂት ቀኖች በኋላም ከሚስቱ ጋር አውጥተው ደማቸው እንደ ውኃ እስቲፈስ በአለንጋዎች እንዲገረፉአቸው አዘዘ ያለ ርኅራኄም ገረፏቸው ሚስቱም በዚህ ሥቃይ ምስክርነቷን ፈጸመች።

ዳግመኛም ለጣዖታት መስገድን እሺ ይለው ዘንድ ቅዱስ ጢሞቴዎስን ማባበል ጀመረ እምቢ ባለውም ጊዜ የነዳጅ ድፍድፍ ሥጋውን ቀብተው ከእሳት ማንደጃ ውስጥ እንዲጨምሩት አዘዘ በጨመሩትም ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ወርዶ ከዚህ ቃጠሎ አዳነው ።

ከዚህም በኋላ ሁለተኛ ወደ ወህኒ ቤት መለሱት ተአምራትንም የሚያደርግ ሆነ በአንዲት ዕለትም በዚያ ሲጸልይ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደርሱ መጥቶ ቃል ኪዳንን ገባለት ሰላምታንም ሰጠው።

በማግሥቱም ከእሥር ቤት አውጥተው ወደ በንሑር ከተማ ወስደው ቅድስት ራሱን ቆረጡ ያን ጊዜ ንውጽውጽታ ሆነ አየርም መላእክትን ተመላች አማንያን ሰዎችም መጥተው ሥጋውን ወስደው በመልካም አገናነዝ ገንዘው ቀበሩት። የመከራውም ዘመን በአለፈ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ሠሩለት ሰኔ ሃያ ሰባት ቀንም አከበርዋት ሥጋውንም በውስጥዋ አኖሩ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ለሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ሼር አድርጉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​7. ሀ/ስብከቱ ለሐብትና ንብረት ቁጥጥር በሚል በወራዊ እና ዓመታዊ ክብረ በዓላት በተቆጣጣሪነት ወደ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት የሚልካቸው ልኡካን የገንዘብ እና የንብረት ገቢን አስመልክቶ አጠቃላይ ሪፖርት የማቅረብ ግዴታ ያለባቸው መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የሚላኩትም ልኡካን ምደባ እውቀትን፣ የሥራ ልምድንና ታማኝነትን መሠረት ያደረገ እንዲሆንና የሚከፈለውም አበል ከአጥቢያ እስከ ሀ/ስብከት ድረስ በቋሚ ሲኖዶስ በተወሰነው የአበል አከፋፈል መሠረት ብቻ ተፈጻሚ እንዲሆን፤

8. እስከ አሁን ድረስ ለዓመታዊ የሒሳብ ምርመራ የሚላኩ ልኡካን የሒሳብ እውቀት የሌላቸውን ሁሉ በጅምላ በመመደብ የሚፈጸመው ዓመታዊ የአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት የሒሳብ ምርመራና የኦዲት ሥራ አግባብነት የሌለውና በርካታ ክፍተቶች ያሉበት መሆኑ በጋራ ውይይቱ ስለተረጋገጠ ሀ/ስብከቱ የሒሳብ ሙያና ልምድ ባላቸው የጽ/ቤቱ ሠራተኞች የኦዲትና ቁጥጥር ሥራውን እንዲያከናውን ሆኖ የሒሳብ ባለሙያ እጥረት ካጋጠመው ከዋናው መሥሪያ ቤት የቁጥጥር መመሪያ አገልግሎት ከሚገኙ ኦዲተሮች ጋር በጣምራ ዓመታዊ የኦዲት ሥራው እንዲያከናውን፤

9. በጋራ የውይይት መድረኩ በተደረሰው ስምምነት መሠረት ልዩ ልዩ አስተዳደራዊ የሥራ በደል ደርሶባቸው አለአግባብ ከሥራ የታገዱ፣ በወቅታዊ ችግር ከሥራ የተፈናቀሉ የትግራይና ሌሎች አካባቢዎች ተወላጅ ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች ፣ ያለ ሥራ የተንሳፈፉና በሕገወጥ መንገድ ከደረጃ ዝቅ ያሉ እንዲሁም በአጥቢያ ደረጃ የተከሰቱ የሰበካ ጉባኤ ምርጫና ሌሎች የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎች በሙሉ ተጠቃለው በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተፈተውና ምላሽ አግኝተው ለዋናው መሥሪ ቤት ሪፖርት እንዲቀርብ፤

10.ከሀ/ስብከቱ መተዳደሪያ ደንብ እስከ የበላይ ሕግ የሆነው ሕገ ቤተ ክርስቲያን ድረስ ጥብቅ አስተዳዳሪ የሚል የሥራ መደብ በሌለበት ሁኔታ ሀ/ስብከቱ በእራሱ ፍላጎት ስያሜውን ፈጥሮ በርካታ አስተዳዳሪዎች ያለ ሥራ መደብ ተንሳፈው እያለ ከአሥራ ሁለት ያላነሱ አብያተ ክርስቲያናት ጥብቅ በሚል አስተዳዳሪ እየተመሩ መሆናቸውን በመረጃ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ስለሆነም በቀጣይ ከመዋቅር ውጭ በሆነ ስያሜ በየትኛውም አብያተ ክርስቲያናት ጥብቅ አስተዳዳሪ እንዳይመደብ እንዲደረግና አሁን በጥብቅ አስተዳደር በሚል ክፍት በሆኑ አብያተ ክርስቲያናት ላይ መተዳደሪያ ደንቡ ተጠብቆ ያለ ሥራ የተንሳፈፉና በአቤቱታ ላይ የሚገኙት አስተዳዳሪዎች ምደባ ተጠንቶ እንዲቀርብ፡፡

11. ለሀ/ስብከቱ መልካም አስተዳደር ችግር እንደ ዋና መንስኤ የሆኑት በክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት እና በአጥቢያ ደረጃ የሚፈጸሙ ቅጥር፣ ዝውውርና እግድ በሙሉ እንዲቆም፤

12. ከክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት እስከ ሀ/ስብከት በውይይቱ ተሳታፊ የሆኑ የሥራ ኃላፊዎች ለሀ/ስብከቱ መተዳዳሪያ ደንብ ተፈጻሚነትና ስለ መልካም አስተዳደር ችግሮች አፈታት እስከታች አስፈጻሚ አካል ደረስ ግንዛቤ ይፈጠርልን በማለት በአጽንኦት ባሳሰቡት መሠረት ከሀ/ስብከት አስከ አጥቢያ ድረስ ላሉት የቤተ ክርስቲያናችን አገልጋችና የቢሮ ሰራተኞች እንዲሁም ለሰበካ ጉባኤ ሥራ አስፈጻሚ አባላት በቀጣይ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ጽ/ቤት በኩል በአጭር ጊዜ ውስጥ የግንዛቤ ማስጨበጫ የውይይት መድረክ እንዲዘጋጅ፤

13. የሀ/ስብከቱ ማኅበራዊ ሚዲያ የተቋቋመበት መሠረታዊ ዓላማ ከሀ/ስብከት እስከ አጥቢያ ያሉትን የዕለት ተዕለት ሐዋርያዊና አስተዳደራዊ ክንውኖችን ለምዕመናን ተደራሽ ለማድረግ መሆኑ አጠያያቂ አይደለም፤ ይሁን እንጂ ማኅበራዊ ሚድያው ከቋቋመበት ዓላማ ውጪ የሀ/ስብከቱን የመልካም አስተዳደር ችግር በጋራ ውይይት ለመፍታት የተደረገውን የምክክር መድረክ በተሳሳተ መድረክ በመዘገብ የተዛባ መረጃ ለሕዝብ እንዲደርስ በማድረግ የፈጸመው ሕገወጥ ተግባር ጉባኤውን በእጅጉ ያሳዘነ አድራጎት ሲሆን ዋናው መሥሪያ ቤት ባደረገው ማጣራትም በድረገጹ ላይ የማይመለከታቸው ግለሰቦች ጭምር የራሳቸውን ፍላጎት የሚለጥፉበት አጋጣሚዎችም እንዳሉ መረጃዎች ቀርበዋል፡፡ ስለሆነም እንዲህ ዓይነቱ ሕገ ወጥ አድራጎት እንዳይደገም ሆኖ በቀጣይ ከሚዲያ ዋና ክፍል ኃላፊውና ከሚመለከታቸው የክፍሉ ሠራተኞች በስተቀር የትኛውም አካል የራሱን ፍላጎትና የተዛባ መረጃ እንዳይለጥፍ በሀ/ስብከቱ በኩል ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል እንዲደረግ ሲል ጉባኤው በሙሉ ድምጽ ወስኖ የዕለቱን ስብሰባ በብፁዕ አባታችን ጸሎትና ቡራኬ አጠናቋል፡፡

ትእዛዝ
1ኛ. የአስተዳደር ጉባኤው የውሳኔ ቃለ ጉባኤ በመሸኛ ደብዳቤ ለሀ/ስብከቱ ይላክ፤
2ኛ. የቅሬታ አቅራቢ ባለጉዳዮች ስም ዝርዝር ከመሸኛ ደብዳቤ ጋር ለሀ/ስብከቱ ይላክ፤
3ኛ. ይህ ውሳኔ በአግባቡ ስለመፈጸሙና አለመፈጸሙ የጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደር ምምሪያ ፤የሕግ አገልግሎት መምሪያና የቁጥጥር አገልግሎት መምሪያ እየተከታተሉ ሪፖርት እንዲያደርጉ፤

ምንጭ: የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እግዚአብሔር ሰዶም እና ገሞራን እንዳያጠፋ የለመነው ጻድቅ አባት ማን ይባላል?

ቀድሞ የመለሰ ሽልማት አለው!

Читать полностью…
Подписаться на канал