ortodoxmezmur | Неотсортированное

Telegram-канал ortodoxmezmur - ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

134932

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . ዝማሬ ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Подписаться на канал

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

https://vm.tiktok.com/ZM6NbeFmb/

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​ኅዳር 27
ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሰማዕት


በዚህችም ቀን በንሑር ከሚባል አገር ቅዱስ ጢሞቴዎስ በሰማዕትነት አረፈ። ይህም ቅዱስ ከታናሽነቱ ጀምሮ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሁልጊዜ በጾም በጸሎት ተጠምዶ የሚኖር ነው ስሟ ሞራ የሚባል ሚስት አለችው እርሷም የአጎቱ ልጅ ናት በሥራዋ ሁሉ ደስ የምታሰኘው መልካም ሴት ናት።

እንደዚህም በፍቅርና በስምምነት ሲኖር ከከሀዲ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ የጣዖታት ቤቶች ይከፈቱ ዘንድ አብያተ ክርስቲያናት እንዲዘጉ ትእዛዝ ወጣ። ቅዱስ ጢሞቴዎስም ይህን ሰምቶ እጅግ ደስ አለው። እርሱ ስለ ክርስቶስ ፍቅር ደሙን ያፈስ ዘንድ ይህን ዘመን ይጠብቀው ነበርና ለሚስቱም ሊሠራው ያሰበውን ነገራት እርሷም የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን አለች።

ከዚህም በኋላ መንገዱን ያቀናለት ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ ጌታችንም በዚያች ሌሊት በሕልሙ ተገልጾለት ወዳጄ ጢሞቴዎስ ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን እነሆ ከጻድቃኖቼ ቁጥር ውስጥ ቆጥሬሃለሁ አሁንም ተነሣ ሚስትህንም ይዘህ ወደ ብህንሳ ከተማ ሒዳችሁ ጣዖታትን በሚያመልኩ ሁሉ ሕዝብ ፊት በስሜ ታመኑ አለው። በነቃ ጊዜም ለሚስቱ ነገራት እርሷም ይህንኑ የሚመስል ሕልሟን ነገረችው።

ከዚህም በኋላ ተነሥተው በአንድነት ሔዱ ወደ መኰንኑ ወደ ቊልቊልያኖስም ደረሱ መሰንቆና እንዚራ እያስመታ ለጣዖታቱ በዓልን ሲያከብር አገኙት ያንጊዜ ወታደሮቹ ይዘው በመኰንኑ ፊት አቆሙት ሚስቱም ተከተለችው መኰንኑም ለጣዖት መስገድን እያግባባ በርኅራኄ ቃል ተናገረው ቅዱሱ ግን እርሱንና የረከሰች ሃይማኖቱን ሰደበ ስለዚህም መኰንኑ ተቆጥቶ ከሚስቱ ጋር ወደ ወህኒ ቤት እንዲአስገቡት አዘዘ።

ከጥቂት ቀኖች በኋላም ከሚስቱ ጋር አውጥተው ደማቸው እንደ ውኃ እስቲፈስ በአለንጋዎች እንዲገረፉአቸው አዘዘ ያለ ርኅራኄም ገረፏቸው ሚስቱም በዚህ ሥቃይ ምስክርነቷን ፈጸመች።

ዳግመኛም ለጣዖታት መስገድን እሺ ይለው ዘንድ ቅዱስ ጢሞቴዎስን ማባበል ጀመረ እምቢ ባለውም ጊዜ የነዳጅ ድፍድፍ ሥጋውን ቀብተው ከእሳት ማንደጃ ውስጥ እንዲጨምሩት አዘዘ በጨመሩትም ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ወርዶ ከዚህ ቃጠሎ አዳነው ።

ከዚህም በኋላ ሁለተኛ ወደ ወህኒ ቤት መለሱት ተአምራትንም የሚያደርግ ሆነ በአንዲት ዕለትም በዚያ ሲጸልይ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደርሱ መጥቶ ቃል ኪዳንን ገባለት ሰላምታንም ሰጠው።

በማግሥቱም ከእሥር ቤት አውጥተው ወደ በንሑር ከተማ ወስደው ቅድስት ራሱን ቆረጡ ያን ጊዜ ንውጽውጽታ ሆነ አየርም መላእክትን ተመላች አማንያን ሰዎችም መጥተው ሥጋውን ወስደው በመልካም አገናነዝ ገንዘው ቀበሩት። የመከራውም ዘመን በአለፈ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ሠሩለት ሰኔ ሃያ ሰባት ቀንም አከበርዋት ሥጋውንም በውስጥዋ አኖሩ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ለሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ሼር አድርጉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​7. ሀ/ስብከቱ ለሐብትና ንብረት ቁጥጥር በሚል በወራዊ እና ዓመታዊ ክብረ በዓላት በተቆጣጣሪነት ወደ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት የሚልካቸው ልኡካን የገንዘብ እና የንብረት ገቢን አስመልክቶ አጠቃላይ ሪፖርት የማቅረብ ግዴታ ያለባቸው መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የሚላኩትም ልኡካን ምደባ እውቀትን፣ የሥራ ልምድንና ታማኝነትን መሠረት ያደረገ እንዲሆንና የሚከፈለውም አበል ከአጥቢያ እስከ ሀ/ስብከት ድረስ በቋሚ ሲኖዶስ በተወሰነው የአበል አከፋፈል መሠረት ብቻ ተፈጻሚ እንዲሆን፤

8. እስከ አሁን ድረስ ለዓመታዊ የሒሳብ ምርመራ የሚላኩ ልኡካን የሒሳብ እውቀት የሌላቸውን ሁሉ በጅምላ በመመደብ የሚፈጸመው ዓመታዊ የአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት የሒሳብ ምርመራና የኦዲት ሥራ አግባብነት የሌለውና በርካታ ክፍተቶች ያሉበት መሆኑ በጋራ ውይይቱ ስለተረጋገጠ ሀ/ስብከቱ የሒሳብ ሙያና ልምድ ባላቸው የጽ/ቤቱ ሠራተኞች የኦዲትና ቁጥጥር ሥራውን እንዲያከናውን ሆኖ የሒሳብ ባለሙያ እጥረት ካጋጠመው ከዋናው መሥሪያ ቤት የቁጥጥር መመሪያ አገልግሎት ከሚገኙ ኦዲተሮች ጋር በጣምራ ዓመታዊ የኦዲት ሥራው እንዲያከናውን፤

9. በጋራ የውይይት መድረኩ በተደረሰው ስምምነት መሠረት ልዩ ልዩ አስተዳደራዊ የሥራ በደል ደርሶባቸው አለአግባብ ከሥራ የታገዱ፣ በወቅታዊ ችግር ከሥራ የተፈናቀሉ የትግራይና ሌሎች አካባቢዎች ተወላጅ ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች ፣ ያለ ሥራ የተንሳፈፉና በሕገወጥ መንገድ ከደረጃ ዝቅ ያሉ እንዲሁም በአጥቢያ ደረጃ የተከሰቱ የሰበካ ጉባኤ ምርጫና ሌሎች የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎች በሙሉ ተጠቃለው በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተፈተውና ምላሽ አግኝተው ለዋናው መሥሪ ቤት ሪፖርት እንዲቀርብ፤

10.ከሀ/ስብከቱ መተዳደሪያ ደንብ እስከ የበላይ ሕግ የሆነው ሕገ ቤተ ክርስቲያን ድረስ ጥብቅ አስተዳዳሪ የሚል የሥራ መደብ በሌለበት ሁኔታ ሀ/ስብከቱ በእራሱ ፍላጎት ስያሜውን ፈጥሮ በርካታ አስተዳዳሪዎች ያለ ሥራ መደብ ተንሳፈው እያለ ከአሥራ ሁለት ያላነሱ አብያተ ክርስቲያናት ጥብቅ በሚል አስተዳዳሪ እየተመሩ መሆናቸውን በመረጃ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ስለሆነም በቀጣይ ከመዋቅር ውጭ በሆነ ስያሜ በየትኛውም አብያተ ክርስቲያናት ጥብቅ አስተዳዳሪ እንዳይመደብ እንዲደረግና አሁን በጥብቅ አስተዳደር በሚል ክፍት በሆኑ አብያተ ክርስቲያናት ላይ መተዳደሪያ ደንቡ ተጠብቆ ያለ ሥራ የተንሳፈፉና በአቤቱታ ላይ የሚገኙት አስተዳዳሪዎች ምደባ ተጠንቶ እንዲቀርብ፡፡

11. ለሀ/ስብከቱ መልካም አስተዳደር ችግር እንደ ዋና መንስኤ የሆኑት በክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት እና በአጥቢያ ደረጃ የሚፈጸሙ ቅጥር፣ ዝውውርና እግድ በሙሉ እንዲቆም፤

12. ከክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት እስከ ሀ/ስብከት በውይይቱ ተሳታፊ የሆኑ የሥራ ኃላፊዎች ለሀ/ስብከቱ መተዳዳሪያ ደንብ ተፈጻሚነትና ስለ መልካም አስተዳደር ችግሮች አፈታት እስከታች አስፈጻሚ አካል ደረስ ግንዛቤ ይፈጠርልን በማለት በአጽንኦት ባሳሰቡት መሠረት ከሀ/ስብከት አስከ አጥቢያ ድረስ ላሉት የቤተ ክርስቲያናችን አገልጋችና የቢሮ ሰራተኞች እንዲሁም ለሰበካ ጉባኤ ሥራ አስፈጻሚ አባላት በቀጣይ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ጽ/ቤት በኩል በአጭር ጊዜ ውስጥ የግንዛቤ ማስጨበጫ የውይይት መድረክ እንዲዘጋጅ፤

13. የሀ/ስብከቱ ማኅበራዊ ሚዲያ የተቋቋመበት መሠረታዊ ዓላማ ከሀ/ስብከት እስከ አጥቢያ ያሉትን የዕለት ተዕለት ሐዋርያዊና አስተዳደራዊ ክንውኖችን ለምዕመናን ተደራሽ ለማድረግ መሆኑ አጠያያቂ አይደለም፤ ይሁን እንጂ ማኅበራዊ ሚድያው ከቋቋመበት ዓላማ ውጪ የሀ/ስብከቱን የመልካም አስተዳደር ችግር በጋራ ውይይት ለመፍታት የተደረገውን የምክክር መድረክ በተሳሳተ መድረክ በመዘገብ የተዛባ መረጃ ለሕዝብ እንዲደርስ በማድረግ የፈጸመው ሕገወጥ ተግባር ጉባኤውን በእጅጉ ያሳዘነ አድራጎት ሲሆን ዋናው መሥሪያ ቤት ባደረገው ማጣራትም በድረገጹ ላይ የማይመለከታቸው ግለሰቦች ጭምር የራሳቸውን ፍላጎት የሚለጥፉበት አጋጣሚዎችም እንዳሉ መረጃዎች ቀርበዋል፡፡ ስለሆነም እንዲህ ዓይነቱ ሕገ ወጥ አድራጎት እንዳይደገም ሆኖ በቀጣይ ከሚዲያ ዋና ክፍል ኃላፊውና ከሚመለከታቸው የክፍሉ ሠራተኞች በስተቀር የትኛውም አካል የራሱን ፍላጎትና የተዛባ መረጃ እንዳይለጥፍ በሀ/ስብከቱ በኩል ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል እንዲደረግ ሲል ጉባኤው በሙሉ ድምጽ ወስኖ የዕለቱን ስብሰባ በብፁዕ አባታችን ጸሎትና ቡራኬ አጠናቋል፡፡

ትእዛዝ
1ኛ. የአስተዳደር ጉባኤው የውሳኔ ቃለ ጉባኤ በመሸኛ ደብዳቤ ለሀ/ስብከቱ ይላክ፤
2ኛ. የቅሬታ አቅራቢ ባለጉዳዮች ስም ዝርዝር ከመሸኛ ደብዳቤ ጋር ለሀ/ስብከቱ ይላክ፤
3ኛ. ይህ ውሳኔ በአግባቡ ስለመፈጸሙና አለመፈጸሙ የጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደር ምምሪያ ፤የሕግ አገልግሎት መምሪያና የቁጥጥር አገልግሎት መምሪያ እየተከታተሉ ሪፖርት እንዲያደርጉ፤

ምንጭ: የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እግዚአብሔር ሰዶም እና ገሞራን እንዳያጠፋ የለመነው ጻድቅ አባት ማን ይባላል?

ቀድሞ የመለሰ ሽልማት አለው!

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የተፈጸመውን ጥቃት በማስመልከት ከኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የተሰጠ መግለጫ ፤


"ወዳጆች ሆይ፥ በእናንተ መካከል እንደ እሳት ሊፈትናችሁ ስለሚሆነው መከራ ድንቅ ነገር እንደ መጣባችሁ አትደነቁ፤ ነገር ግን ክብሩ ሲገለጥ ደግሞ ሐሤት እያደረጋችሁ ደስ እንዲላችሁ፥ በክርስቶስ መከራ በምትካፈሉበት ልክ ደስ ይበላችሁ።" 1ኛ ጴጥርስ 4፥12:13

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ  አሜን       

በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት በጥብቅ እናወግዛለን፤ የጸጥታ ተቋማትም ጥቃቱን እንዲከላለሉ እንጠይቃለን።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአርሲ ዞን በሹርካ ወረዳ ሶሌ ሚካኤል፣ በዲገሎ ማርያም፣ በሮቤ እንደቶ ደብረ ምጥማቅ ማርያም አብያተክርስቲያናት ላይ በተለያዩ ጊዜያት 36 ኦርቶዶክሳዊያን በደረሰባቸው ጥቃት ሕይወታቸውን ማጣታቸውን ሀገረ ስብከቱ ባደረሰን መረጃ ለማወቅ ችለናል።

በዚሁ ጥቃት በሶሌ ዲገሉ እና ጢጆ ለቡ በተባሉ ቀበሌዎች 28 ኦርቶዶክሳዊያን ከየቤታቸው ተለቅመው የተገደሉ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥም 7ቱ ሴቶችና 21ዱ ወንዶች መሆናቸው ታውቋል። በዚህ ጥቃትም እድሜያቸው ከሰባ ዓመት አዛውንት እስከ ሃያ ስምንት ቀን ጨቅላ ሕጻናት ይገኙበታል። በዛሬው ዕለት ደግሞ በዲገሉ ማርያም ቤተ ክርስቲያን 5 ኦርቶዶክሳዊያን ከመገደላቸው በተጨማሪ የሦስት ኦርቶዶክሳውያን ቤት ደግሞ ተቃጥሏል። 

ከዚህ ቀደም በሮቤ አንዲቶ ደብረ ምጥማቅ ማርያም ቤተክርስቲያን በዓለ ማርያምን አክብረው ወደ ቤታቸው በመመለስ ላይ የነበሩ ሦስት ኦርቶዶክሳዊያን ጨለማን ተገን ባደረጉ ነፍሰ ገዳዮች መገደላቸው ይታወሳል።

የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች ከመንግሥት የጸጥታ አካላት ጋር በተደጋጋሚና ሆን ተብሎ በሚፈጸመው የኦርቶዶክሳዊያን ጥቃት ዙሪያ በጋራ እየሠሩ የሚገኙ ሲሆን በዚህ ዐይነት የጥቃት ተግባር ላይ ተሰማርተው የሚገኙ አንዳንድ አካላት ላይ በመንግሥት በኩል የማያዳግም ርምጃ እንደተወሰደባቸው ሀገረ ስብከቱ  በላከው ሪፖርት አረጋግጠዋል።

ይህ ዐይነት ሃይማኖት ተኮር ጥቃት በምእመናን ላይ መድረሱ አግባብነት የሌለውና እምነትን በነጻነት የማራመድ መንግስታዊ መብትን የሚጥስ በመሆኑ መሰል  ሕገ ወጥ ጥቃትን ለመከላከልና  ሁሉም የሃይማኖት ተቋማት መብቶቻቸውን ተቋማዊ በሆነ መንገድ ማስከበር እንዲችሉ  ያቋቋሙት የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ድርጊቱን በማውገዝ ችግሩ ከመሠረቱ እንዲፈታ ከሚመለከታቸው የመንግሥት ኃላፊዎች ጋር በመነጋገር መፍትሔ መፈለግ ሲገባው በዝምታ በማለፉ ቤተክርስቲያን ከፍተኛ ቅሬታ ተሰምቷታል።

ይህ ዐይነቱ ኦርቶዶክሳዊያን ላይ ያነጣጠረ ግድያ እንዲቆምና የወንጀሉ ፈጻሚዎችም ለፍርድ እንዲቀርቡ በሀገረ ስብከቱ በኩል እየተደረገ ያለው ጥረት እንደተጠበቀ ሆኖ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤትም በድርጊቱ እጅጉን ማዘኑን እየገለጸ ጉዳዩን  ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር  በመሆን የሚከታተለው መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን።

በሌሎች ስፍራዎች የሚያጋጥሙ ተመሳሳይ ጥቃቶችን በእንጭጩ ለመቅጨትና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በመነጋገር መፍትሔ ማበጀት ይቻል ዘንድ አህጉረ ስብከት ችግሮች በሚያጋጥሙ ወቅት ሪፖርት እንዲልኩ ቀደም ሲል በደብዳቤ በተላከላቸው የስልክና ዘመናዊ የመገናኛ ዘዴዎች አማካኝነት በፍጥነት በማሳወቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እያሳሰብንና ለሞቱት ኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ሁሉ ልዑል እግዚአብሔር መንግሥተ ሰማያትን እንዲያወርስልን በመጸለይ የፌዴራልም ሆነ የክልል መንግሥታት የሚደርሱ ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች እንዲቆሙና መሰል ጥቃት እንዳይፈጸም ለኦርቶዶክሳዊያን ወገኖቻችን ከለላ እንዲሰጡልን እንጠይቃለን።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት

ምንጭ: የኢኦተቤ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ላስታውሳችሁ!

ቻሌንጃችን ነገም ይቀጥላል! ቻሌንጅ ሁለት የምንለቀውን የቅዱሳን ህይወት ወይም የዕለቱን በዓል ከትምህርት ወይም ከስራ በፊት ማንበብ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

✝ መስቀሉን ስትነኩት የሚወስዳችሁ ቻናሎች ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶችን የሚያስተምር ጠቃሚ ቻናሎች ስለሆኑ መስቀሉን  ይጫኑ Join ይበሏቸው
/Start


                 🔳🔳
                 🔳🔳
        🔳🔳🔳🔳🔳🔳
        🔳🔳🔳🔳🔳🔳
                 🔳🔳
                 🔳🔳
                 🔳🔳
                 🔳🔳


         ✝መስቀሉ አርማችን ነው።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🌺 ሰላም፡ለኵልክሙ። እነሆ ግእዝን በአንድ ወር ኮርሳችን በአዲስ መልኩ ለመጀመር በ10ኛው ዙር ትምህርት መርሐ-ግብር ተመልሷል።

📜 በመሆኑም ለጀማሪዎች የግእዝ ቋንቋን ቀለል ባለና ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅታችንን አጠናቀናል ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመመዝገብ ጥንታዊና ውዱ ቋንቋችንን እናጥና ፥ ዕንወቅ።

📖 ትምህርቱን ከ14 ዓመት ዕድሜ በላይ የሆነ ማንኛውም ሰው፤ ስልክ ወይም ላፕቶፕ ወዴስክቶፕ በመጠቀም መማር ይቻላል።

✅ ለመመዝገብ በዚህ ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር በመላክ ግሩፖችን መቀላቀል ነው ✅
@Geez202
@Geez202
@Geez202 👈
                

⛳️ ለበለጠ መረጃ በ @Geez202 ውስጥ ይደርስዎታል ወይም ከታች በተቀመጠው ደውለው ያግኙን። ሠናይ፡ጊዜ።

🗣 ለሌሎችም ሼር በማድረግ እንድናዳርስ በአክብሮት እንጠይቃለን
🌺 መሠረተ፡ግእዝ 🌺
@MesereteGeez - 0977682046

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን!!

34,000+ MEMBER በጥቂት ወራት ያፈራው   
              👇👇👇
👉🏾 @BINIGIRMACHEW 👈🏾
       ☝️JOIN NOW☝️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ሶበ ተዘከርናሃ ለጽዮን

ሶበ ተዘከርናሃ ለጽዮን 
ሶበ ተዘከርናሃ ለጽዮን
ውስተ አፍላገ ባቢሎን
ህየ ነበርነ ወበከይነ
እንዚራቲነ ሰቀልነ ውስተ ኲሓቲሃ

ባሰብናት ጊዜ ጽዮንን
ባሰብናት ጊዜ ጽዮንን
በባቢሎን ወንዞች አጠገብ
ተቀምጠን አለቀስን
መሰንቆአችንን ሰቀልን በዛፎቿ ላይ
አዝ
ፅኑ መከራን ተቀበልን ተጨነቅን በፈተና
የደዌ ሞት በላያችን እንደዝናብ ወርዷልና
አሕዛብም ዘበቱብን እንዲህ ብለው በየተራ
ዘምሩለት ለአምላካችሁ ቢያድናችሁ ከመከራ

እግዚአብሔር ጽዮንን በመንግስቱ መርጧታል እና
ማደሪያው ትሆነው ዘንድ ወዷታል እና
ጽዮን ሆይ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
ጽዮን ሆይ እናታችን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
አንቺን ብንረሳ ቀኛችን ትርሳን
አዝ
የማረኩን በጦራቸው በኃይላቸው የተመኩ
በጽዮን ደጅ ያለፍርሃት የጽዮንን ክብሯን ነኩ
ይህን ያየ ከላይ ሆኖ በደመና ተሸፍኖ
ባቢሎንን አሻገረ የማረኩንን በትኖ

እግዚአብሔር ጽዮንን በመንግስቱ መርጧታል እና
ማደሪያው ትሆነው ዘንድ ወዷታል እና
ጽዮን ሆይ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
ጽዮን ሆይ እናታችን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
አንቺን ብንረሳ ቀኛችን ትርሳን
አዝ
ስጋችንን ሊገንዘን የሞት ጥላ ቢያጠላም
እናልፋለን ሁሉን ባንቺ
የአምላክ እናት ድንግል ማርያም
ቅድስት ሆይ ከባረክሽን
እንድናለን ከደዌያችን
ለስጋና ለነብሳችን መድኃኒት ነሽ እናታችን

እግዚአብሔር ጽዮንን በመንግስቱ መርጧታልና
ማደሪያው ትሆነው ዘንድ ወዷታልና
ጽዮን ሆይ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
ጽዮን ሆይ እናታችን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
አንቺን ብንረሳ ቀኛችን ትርሳን

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​እንኳን ለጽዮን "ማርያም ማሕደረ አምላክ" እና ለቅዱሳኑ "ጐርጐርዮስ ወዮሐንስ" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ

"ጽዮን ማርያም"

"ጽዮን" ማለት "ጸወን - አምባ - መጠጊያ" ማለት ነው:: አንድም በምሥጢሩ "ማሕደረ አምላክ" ማለት ነው:: ጽዮን የሚለው ስም በቁሙ ለቅዱስ ዳዊት ተራራና ለኪዳኑ ጽላት ሲያገለግል በትንቢታዊ ምሥጢሩ ግን ለድንግል ማርያም: ለቤተ ክርስቲያንና ለዘለዓለማዊት ርስት ያገለግላል::

እግዚአብሔር ከዘመነ አበው በሁዋላ በጊዜው ለእሥራኤላውያን ክብር: ሞገስ: አምባ የምትሆናቸውን ታቦተ ጽዮንን በቅዱስ ሙሴ አማካኝነት ሰጥቷቸዋል:: (ዘጸ. 31:18) ከዚያም ለ500 ዓመታት ከእነሱ ጋር በመሆኗ በፈጣሪና በእነሱ መካከል ድልድይ ሆና ኖራለች::

ከዚያም ባለቤቱ ሲፈቅድ በዘመነ ሳባ: በቀዳማዊ ምኒልክ (እብነ መለክ-እብነ ሐኪም) አማካኝነት ወደ ኢትዮዽያ መጥታለች:: እነሆ በሃገራችን የ3ሺ ዓመት ቆይታዋን ልትደፍን የቀራት ጥቂት ዓመታት ብቻ ናቸው:: ጌታ እንደ ፈቀደ ቅዱስ መስቀሉንና ታቦተ ጽዮንን ይዘን ይሔው በቸርነቱ እንኖራለን::

ያም ሆኖ ታቦተ ጽዮንን መስረቅ የሚፈልጉ ብዙ ቀሳጢዎች እንዳሉ እናውቃለን:: ግን አንጨነቅም:: ምክንያቱም የመጣችውም: የምትጠበቀውም በፈቃደ እግዚአብሔር ነውና እንጸልያለን እንጂ አንጨነቅም:: በተለያየ ወሬም ራሳችንን አናማጥንም:: ባለቤቱ እንድትሔድ ከፈቀደ ደግሞ ማንም ጉልበተኛ አያስቀራትም::

ታቦተ ጽዮን ብዙ ጊዜ "ጽላተ ኪዳን: ታቦተ ሕጉ" እየተባለች ትጠራለች:: "ጽሌ" ማለት "ሰሌዳ" እንደ ማለት ሲሆን "ጽላት" ደግሞ በብዙ ቁጥር ነው:: "ኪዳን" ደግሞ በፈጣሪና በሰው ልጆች መካከል ያለ "ውል - ስምምነት" ነው::

"ታቦት" ማለት "ማሕደር-ማደሪያ" እንደ ማለት ነው:: ሕጉ የተጻፈባቸውን ሰላድው "ጽላት" ስንላቸው የጽላቱ ማደሪያ ደግሞ "ታቦት" ይባላል:: ጽላት (ታቦትን) ያመጣ ፈጣሪ ነው:: በሐዲስ ኪዳንም ምሥጢርና ሐተታ ቢኖረውም 2 ቦታ ላይ ስለ ታቦት ተጠቅሶ እናገኛለን:: (2ቆሮ. 6:16, ራዕይ. 11:19)

#በመጨረሻም_ኅዳር_21 ቀን ጽዮን ማርያምን የምናከብርባቸውን ምክንያቶች እንመለከታለን:: በዚህች ቀን:-

1. ታቦተ ጽዮን (ጽላተ ኪዳን) ለሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ መሰጠቷን እናስባለን:: ይሕ ሲሆንም ቅዱስ ሙሴ 40 መዓልት: 40 ሌሊት ጾሞ እንደ ተቀበለ ሳንዘነጋ ማለት ነው:: (ዘጸ. 31:18, ዘዳ. 9:19)

2. በዘመነ ኤሊ ሊቀ ካህናት ታቦተ ጽዮን በታሪኩዋ ለመጀመሪያ ጊዜ በአሕዛብ (ኢሎፍላውያን) እጅ ተማርካለች:: ግን ደግሞ ዳጐንን ቀጥቅጣዋለች:: (1ሳሙ. 5:1)

3. በዘመነ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በአሚናዳብ ሠረገላ ሁና: ከአቢዳራ ቤት ስትመጣ ቅዱሱ ንጉሥ በታላቅ ሐሴት በፊቷ ዘመረ: አገለገለ:: ምድራዊ ክብሩን እስኪረሳ ድረስ ለታቦተ አምላክ ተቀኘላት:: በዚህም ሜልኮል ንቃው ማሕጸኗ ተዘግቷል:: (1ዜና. 15:25) ሊቃውንትም "ድንግል እመቤታችን ማርያም በትንቢት መነጽር ተመልክቷል" ብለውናል::

"ሰላም ለኪ ማርያም እምነ::
ዘሰመይናኪ ጸወነ::
ሶበ እምርሑቅ ርእየ ዘጽላሎትኪ ስነ::
ለቢሶ ዳዊት ልብሰ ክብር ዘየኀይድ ዓይነ::
ቅድመ ታቦተ ሕግ ኀለየ ወዓዲ ዘፈነ::" እንዲል:: (አርኬ ዘኅዳር 21)

4. በዘመነ ንጉሥ ሰሎሞን (መፍቀሬ ጥበብ) ግሩም የሆነ ቤተ መቅደስ ተሰርቶላት ስትገባ ታላቅ ሐሴት ተደርጉዋል:: እግዚአብሔርም በደመና ወርዶ ንጉሡን አነጋግሯል:: (2ዜና. 5:1, 1ነገ. 8:1)

5. በዚያው ዘመንም በፈጣሪ ፈቃድ ንጉሥ ምኒልክ ቀዳማዊ (ዕብነ ሐኪም) ታቦተ ጽዮንን ይዞ ወደ ኢትዮዽያ ገብቷል::

6. በዘመነ አፄ ባዜን (በ4 ዓ/ም አካባቢ) አማናዊት ጽዮን ድንግል ማርያም ወደ አክሱም ጽዮን በስደት መጥታ ገብታለች:: በዚህ ጊዜም 2ቱ ጽዮኖች ሲገናኙ ታላቅ ብርሃን አክሱምን ውጧታል::

7. በ4ኛው መቶ ክ/ዘመንም ነገሥት ጻድቃን አብርሐ ወአጽብሐ 12 መቅደሶች ያሏትን ግሩም ቤተ ክርስቲያን ለእመ ብርሃን ሠርተው በዚሁ ቀን በጌታችን ተቀድሷል::

8. በተጨማሪም በየጊዜው: ማለትም በዮዲት ጉዲትና በግራኝ አማካኝነት ስትፈርስ ወደ ዝዋይ ትሰደድ ነበር:: ተመልሳ ስትታነጽም ቅዳሴ ቤቷ የሚከበረው ኅዳር 21 ቀን ነው:: በእነዚህና በሌሎች ምክንያቶች ይህ በዓል ልዩ ነው::

" አማናዊት ጽዮን እመ ብርሃን ድንግል ማርያምን እንዲህ እንላታለን "

"ቅድስት" የሚለው ቃል ለሁሉም ቅዱሳት እናቶች ቢሰጥም ቅሉ ለድንግል ማርያም ሲሰጥ ግን ትርጉሙ ይለያል:: እርሷ "ቅድስተ ቅዱሳን: ንጽሕተ ንጹሐን: ቡርክት እምቡሩካን: ኅሪት እምኅሩያን" ናትና::

ከሰው ልጆችም ሁሉ ትበልጣለች:: ይቅርና የሰው ልጅን ንጹሐን መላእክትንም በንጽሕናና በቅድስና ትበልጣቸዋለች:: እርሷ እመ ብርሃን: የአምላክ እናቱ: የሰውነታችን መመኪያ ናትና::

#እመቤታችንን "ቅድስት" ስንል "ጽንዕት: ንጽሕት: ክብርት: ልዩ" ማለታችን ነው::

1. "ንጽሕት" ትባላለች:: ሌሎች ቅዱሳን ቢነጹ ከገቢር: ከነቢብ ኃጢአት ነው እንጂ ከኃልዮ ኃጢአት አይደለም:: እርሷ ግን ከነቢብ: ከገቢር: ከኃልዮ ንጽሕት ናት::

"ለመኑ ተውኅቦ ተደንግሎ ኅሊና: ለመላእክትሂ ኢተክህሎሙ-ኃጢአትን ከማሰብ መጠበቅ ከሰው ልጆች ለማን ተሰጠው: ይህስ ለመላእክትም አልተቻላቸውም" እንዲል:: (ተአምረ ማርያም)

2. "ጽንዕት" እንላታለን:: ሴቶች ቢጸኑ ለጊዜው ነው እንጂ በሁዋላ በጊዜው ተፈትሆ አለባቸው:: እመቤታችን ግን ቅድመ ጸኒስ: ጊዜ ጸኒስ: ድኅረ ጸኒስ: ቅድመ ወሊድ: ጊዜ ወሊድ: ድኅረ ወሊድ ድንግል ናትና::

¤ "ጽንዕት በድንግልና አልባቲ ሙስና" እንዳላት:: (ቅዱስ ያሬድ)
¤ ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስም "ወትረ ድንግል ማርያም-ማርያም ዘለዓለማዊት ድንግል ናት" እንዳለ:: (መጽሐፈ ቅዳሴ)

3. ድንግልን "ክብርት" እንላታለን:: ሌሎች ሴቶች ቢከብሩ ጻድቃን ሰማዕታትን: ነቢያት ሐዋርያትን ወልደው ነው:: እመቤታችንን ግን የምናከብራት "ወላዲተ አምላክ-የአምላክ እናቱ" ብለን ነውና::

4. እመቤታችንን "ልዩ" እንላታለን:: ከእርሷ በቀር እናት ሁና ድንግል: እመቤት ሁና አገልጋይ የሆነች: በድንግልና ወልዳ ወተትን (ሐሊበ ድንግልናዌን) ያስገኘች ሌላ ሴት የለችምና::

#ሼር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🌺 ሰላም፡ለኵልክሙ። እነሆ ግእዝን በአንድ ወር ኮርሳችን በአዲስ መልኩ ለመጀመር በ10ኛው ዙር ትምህርት መርሐ-ግብር ተመልሷል።

📜 በመሆኑም ለጀማሪዎች የግእዝ ቋንቋን ቀለል ባለና ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅታችንን አጠናቀናል ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመመዝገብ ጥንታዊና ውዱ ቋንቋችንን እናጥና ፥ ዕንወቅ።

📖 ትምህርቱን ከ14 ዓመት ዕድሜ በላይ የሆነ ማንኛውም ሰው፤ ስልክ ወይም ላፕቶፕ ወዴስክቶፕ በመጠቀም መማር ይቻላል።

✅ ለመመዝገብ በዚህ ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር በመላክ ግሩፖችን መቀላቀል ነው ✅
@Geez202
@Geez202
@Geez202 👈
                

⛳️ ለበለጠ መረጃ በ @Geez202 ውስጥ ይደርስዎታል ወይም ከታች በተቀመጠው ደውለው ያግኙን። ሠናይ፡ጊዜ።

🗣 ለሌሎችም ሼር በማድረግ እንድናዳርስ በአክብሮት እንጠይቃለን
🌺 መሠረተ፡ግእዝ 🌺
@MesereteGeez - 0977682046

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

አብሰራ ገብርኤል

አብሰራ ገብርኤል ለማርያም
ወይቤላ /2/ ትወልዲ ወልድ
ሚካኤል መላዕክ በክነፍ ፆራ
መንጦላዕት ደመና ሰወራ
ንፅህት በድንግልና አልባቲ ሙስና 
ተወልደ ወልድ እምኔሐ
         
ገብርኤል ማርያምን አበሰራት አበሰራት
ወንድ ልጅም ትወልጃለሺ አላት
ሚካኤል መላዕክ  በክንፋ ከለላት
የሰማይ መጋረጃውን ሸፈናት
ንፅህት ናትና በድንግልና /2/
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልናለችና
አዝ
አዳም በጥፋቱ ከገነት ሲባረር
በሚካኤል ክንፎች ቀድሞ አይቶሽ ነበር
ሔዋንን ሲጠራት ሕይወቴ ነሽ አላት
እንደሚድን አውቆ ድንግል በአንች ምክንያት

ንፅህት ናትና በድንግልና /2/
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልናለችና
አዝ
እግዚአብሔር የላከው የከበረው መላዕክ
ድንግል ሆይ ለክብርሽ ዐየን ሲንበረከክ
በፍቅር በትህትና በፍፁም ሰላምታ
የጌታ ሰው መሆን የነገረሽ በደስታ

ንፅህት ናትና በድንግልና /2/
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልናለችና
አዝ
ደስተኛዬቷ ሆይ ደስ ይበልሽ ድንግል
የአብ ቃል ክርስቶስ ሥጋሽን ይለብሳል
አንቺም ትይዋለሽ ስሙን ኢየሱስ
መድኋኒት ነውና ለሥጋ ወነፍስ

ንፅህት ናትና በድንግልና /2/
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልናለችና
አዝ
አንደ ኒቆዲሞስ ሳትከራከሪ
አንደ ዘኬርያስ ሳትጠራጠሪ
ይሁነኒ ብለሽ ቃልን ተቀበልሽ
ከፍጥረት ማነው አንቺ የሚመስልሽ

ንፅህት ናትና በድንግልና /2/
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልናለችና

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በ2016 ዓ.ም በጥምቀት ቀን መላው ሃገሪቱን ያጥለቀልቁታል ከተባሉት እና በብዙዎች ከተወደደው ቲሸርቶች መካከል አንዱ ይህ ነው።

ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በእነዚህ ክፍለ ሃገር ላላችሁ
👉 ጅማ
👉 ሊሙ
👉 አዳማ
👉 ዝዋይ (ባቱ)
👉 ቦንጋ
👉 ወሊሶ
👉 አሰላ
👉 ሃዋሳ
👉 ሻሸመኔ
👉 ሆለታ
👉 አንቦ
👉 ሆሳዕና
👉 ወላይታ ሶዶ
👉 ድሬድዋ
👉 ሀረር
👉 ጂግጂጋ
👉 ወልቂጤ
👉 ደብረ ብርሃን
👉 ወሊሶ

ከኛ ተረክባችሁ ማከፋፈልበማህበርም ሆነ በግል ማዘዝ ከፈለጋችሁ ከላይ በተጠቀሱት ቦታዎች በሙሉ ያሉበት ድረስ የምናደርስ ይሆናል።

ሌሎቹንም በኦርቶዶክሳዊ ዲዛይነሮች ተውበው የተሰሩ የጥምቀት ቲሸርቶችን ለማየት እና ለማዘዝ የስር ያለውን የቴሌግራም ሊንክ ይጠቀሙ።
👉 /channel/KABAPrint
👉 /channel/KABAPrint

ማሳሰቢያ - በምታዙበት ወቅት ለምትከፍሉት የቀብድ ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ሀላፊነቱን እኛ(ዝማሬ ዳዊት) እንወስዳለን። አንዳንድ ጥያቄዎች እየደረሱን ስለሆነ ነው።

   ለበለጠ መረጃ
👉 0965875219
👉 0922501999
👉 0913655116

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን፡፡ ✞✞✞

ቅዱስ ፊልዾስ ሐዋርያ

እንደ አባቶቻችን ትርጉም 'ፊልዾስ' ማለት መፍቀሬ አኃው ወንድሞችን የሚወድ' ማለት ሲሆን ከ12ቱ ቅዱሳን ሐዋርያት አንዱ ነው:: (ማቴ. 10:3) በዚህ ስም የሚጠራ ሐዋርያ ከ72ቱ አርድእት ውስጥ ነበር:: እርሱም ጃንደረባውን ባኮስን ያጠመቀው ነው።

አንዳንዴ የ2ቱ ታሪክ ሲቀላቀል እንሰማለን:: ለሁሉም ይህኛው ቅዱስ ፊልዾስ ቁጥሩ ከ12ቱ ሐዋርያት ሆኖ ምሑራነ ኦሪት ከሚባሉትም አንዱ ነበር:: በወቅቱ ገማልያል የሚሉት ክቡርና ምሑረ ኦሪት በርካታ ምሑራነ ኦሪትን አፍርቶ ነበር::

እንደ ምሳሌም ቅዱሳኑን "ዻውሎስን: ኒቆዲሞስን: ናትናኤልን: እስጢፋኖስንና የዛሬውን ሐዋርያ ቅዱስ ፊልዾስን" መጥቀስ እንችላለን:: ቅዱስ ፊልዾስ ነገዱ ከእሥራኤል ሲሆን ተወልዶ ያደገው በቤተ ሳይዳ ነው:: ኦሪትን ተምሮ በመንገድ ዳር ቁጭ ብሎ 'መሲሕ ቀረ' እያለ ሲተክዝ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እርሱ ደረሰ::

ትክ ብሎ አይቶት "ተከተለኝ" አለው:: (ዮሐ. 1:44) ቅዱስ ፊልዾስም ያለ ማመንታት: ሁሉን ትቶ በመንኖ ጥሪት ተከተለው:: በዚህ ዓይነት ጥሪ መድኃኒታችን ቅዱስ ማቴዎስንም ጠርቶታል:: (ማቴ. 9:9) ቅዱስ ፊልዾስ ጌታን ከተከተለ በሁዋላ ሥራ አልፈታም። ወዲያውኑ ሒዶ ለናትናኤል (ቀናተኛው ስምዖን) ሰበከለት እንጂ።

"ሙሴ በኦሪት: ነቢያትም የተነበዩለትን መሲሕን አግኝቸዋለሁ" አለው:: ይሕ አነጋገሩም ምሑረ ኦሪት እንደ ነበር በእርግጥ ያሳያል:: (ዮሐ. 1:46) ቅዱስ ናትናኤልም ምሑር ነውና "ከናዝሬት ደግ እንዴት ይወጣል?" ቢለው ቅዱስ ፊልዾስም መልሶ "ነዐ ትርአይ-ታይ ዘንድ ና" አለው::

ናትናኤልም ሒዶ በጌታ አመነ:: ቅዱስ ፊልዾስ አገልጋይ እንደ መሆኑ መጠን በዮሐንስ ወንጌል ተደጋግሞ ስሙ ተጠቅሷል:: በተለይ ደግሞ ጌታ የ5 ገበያ ሕዝብን አበርክቶ ሲመግብ አስቀድሞ ጥያቄ ቀርቦለት ነበር:: እርሱ ግን "ጌታ ሆይ! የ200 ዲናር እንጀራ ብንገዛም አንዘልቀውም" ብሎ ነበር::

በሁዋላ ግን የጌታን ድንቅ ተአምር ተመለከተ:: (ዮሐ. 6:5) በተለይ ደግሞ በሐዋርያት አበው መካከል ለጌታ እንደ እንደራሴ ሆኖ ያገለግል እንደ ነበርም ተጠቅሷል:: ሰዎች ጌታን ማግኘት ሲፈልጉ እሱና እንድርያስን ያናግሩ ነበር:: (ዮሐ. 12:20) አንድ ጊዜ ግን እስካሁን ሊቃውንትን የምታስደምም ጥያቄ ጠይቆ ነበር::

አጠያየቁ ደግሞ ፍጹም የዋሕ እንደ ሆነ ያሳያል:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ባሕርይ አባቱ አብ እየነገራቸው ሳለ ቅዱስ ፊልዾስ ከመካከል ተነስቶ "እግዚኦ አርእነሁ ለአብ ወየአክለነ": ልክ ወልድን በዐይኑ እንዳየ ሁሉ አብን ሊያይ ቸኩሎ "አቤቱ ስለ አብ የሰማነው ይበቃልና አሳየን" ብሎታል:: (ዮሐ. 14:8)

ጌታችን ግን "ዘርእየ ኪያየ ርዕዮ ለአብ-እኔን ያየ አብን አይቷል" (ዮሐ.14:9) ብሎ ምሥጢረ ባሕርዩን: አንድነቱን ሦስትነቱን አስረድቶታል:: ቅዱስ ፊልዾስም ጌታን እስከ ሕማሙ አገልግሎ: ቅድስት ትንሳኤውን አይቶ: ለ40 ቀናት መጽሐፈ ኪዳንን: ትምሕርተ ኅቡዓትን ተምሮ: ቅዱስ መንፈሱን ከ72 ልሳን ጋር ነስቶ ለስብከተ ወንጌል ወጥቷል::

ቅዱሳን ሐዋርያት ዓለምን በእጣ ሲካፈሉ ለእርሱ አፍራቅያ (አፍሪካ) ደርሳዋለች:: ስለዚህም በምድረ አፍሪካ ወንጌልን ከሰበኩ ሐዋርያት አንዱ ነው:: በአፍራቅያና በቀድሞው የኃምስቱ አሕጉር ግዛት ድንቅ ድንቅ ተአምራትን አድርጐ ብዙዎችን ወደ መንጋው (ወደ ክርስትና በረት) ቀላቀለ::

ለበርካታ ዓመታትም በተለያዩ የዓለም ክፍሎች እየተዘዋወረ ወንጌልን ሲሰብክ: ብርሃነ ክርስቶስን ሲያበራ: ነፍሳትንም ሲማርክ ቆየ:: ገድለ ሐዋርያት እንደሚለው የቅዱስ ፊልዾስ ፍጻሜው በሰማዕትነት እንደ ሆነ ቢታወቅም የትኛው ሃገር ውስጥ እንደ ሆነ መለየት አልተቻለም::

ዜናው ግን እንዲህ ነው:- በአንዲት ሃገር ውስጥ ገብቶ ሰበከ:: ብዙዎችንም አሳመነ:: ያላመኑት ግን ይዘው አሰቃዩት: ገረፉት:: "በክርስቶስ እመኑ እባካችሁ!" እያለ እየለመናቸው ዘቅዝቀው ሰቅለው ገደሉት::

ከዚያም በእሳት እናቃጥላለን ሲሉ ቅዱስ መልአክ ከእጃቸው ነጥቆ ወደ ኢየሩሳሌም ወሰደው:: በዚህ የደነገጡት ገዳዮቹ ለ3 ቀናት ጾሙ: ተማለሉ:: በዚህ ምክንያት የቅዱሱ ሥጋ ተመልሶላቸው: ገንዘው ቀብረውት በክርስቶስ አምነዋል::

አምላከ ቅዱሳን ስለ ወዳጆቹ ሲል ቸርነቱን: ምሕረቱን ይላክልን። ከበረከታቸውም ይክፈለን።

ለሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ሼር አድርጉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እነዚህን ውብ ቲሸርቶች ተመልከቱ!

በ2016 ዓ.ም በጥምቀት ቀን መላው ሃገሪቱን ያጥለቀልቁታል ከተባሉት እና በብዙዎች ከተወደዱት ቲሸርቶች መካከል እነዚህ ጥቂቶቹ ናቸው።

ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በእነዚህ ክፍለ ሃገር ላላችሁ
👉 ጅማ 👉 ሊሙ
👉 አዳማ 👉 ዝዋይ (ባቱ)
👉 ቦንጋ 👉 ወሊሶ
👉 አሰላ 👉 ሃዋሳ
👉 ሻሸመኔ 👉 ሆለታ
👉 አንቦ 👉 ሆሳዕና
👉 ወላይታ ሶዶ 👉 ድሬድዋ
👉 ሀረር 👉 ጂግጂጋ
👉 ወልቂጤ 👉 ደብረ ብርሃን
👉 ዲላ

ከኛ ተረክባችሁ ማከፋፈልበማህበርም ሆነ በግል ማዘዝ ከፈለጋችሁ ከላይ በተጠቀሱት ቦታዎች በሙሉ ያሉበት ድረስ የምናደርስ ይሆናል።

ሌሎቹንም በኦርቶዶክሳዊ ዲዛይነሮች ተውበው የተሰሩ የጥምቀት ቲሸርቶችን ለማየት እና ለማዘዝ የስር ያለውን የቴሌግራም ሊንክ ይጠቀሙ።
👉 /channel/KABAPrint
👉 /channel/KABAPrint

ማሳሰቢያ - በምታዙበት ወቅት ለምትከፍሉት የቀብድ ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ሀላፊነቱን እኛ እንወስዳለን። አንዳንድ ጥያቄዎች እየደረሱን ስለሆነ ነው።

በብዛት ማዘዝ የምትፈልጉ ቀደም ብላችሁ ብታዙን መልካም ነው ቀኑ እየደረሰ ሲመጣ ትዕዛዝ በጣም ስለሚበዛብን ቀደም ብለው ይዘዙን።

   ለበለጠ መረጃ
👉 0965875219
👉 0922501999
👉 0913655116

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​ኅዳር 26

ቅዱስ አቡነ ኢየሱስ ሞዓ ዘሐይቅ

ኅዳር ሃያ ስድስት በዚህች ዕለት አቡነ ኢየሱስ ሞዓ ዘሐይቅ እረፍታቸው ነው። በጐንደር ክፍለ ሀገር ስማዳ ወረዳ ዳህና ሚካኤል በተባለው ቦታ ከአባታቸው ከዘክርስቶስና ከእናታቸው ከእግዚእ ክብራ በ1210 ዓ.ም ነው ተወለዱ። ዕድሜያቸው 3ዐ ዓመት እስከሚደርስ ከቤተሰቦቻቸው ትምህርተ ሃይማኖትንና ግብረ ገብን ሲማሩ ከቆዩ በኋላ በ124ዐ ዓ.ም ይኼንን ዓለም በመተው ወደ ደብረ ዳሞ ገዳም ገቡ። በደብረ ዳሞ ገዳም መነኰሳቱን እየረዱ፣ ትምህርተ ቤተ ክርስቲያንን እያጠኑ፣ ትምህርተ ቅዱሳት መጻሕፍትን እየገለበጡ ለሰባት ዓመታት ከቆዩ በኋላ የደብረ ዳሞ 3ኛ አበ ምኔት ከሆኑት ከአባ ዮሐኒ ምንኩስናን ተቀበሉ (1247 ዓ.ም.)።

አንድ ቀን ሌሊት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ወደርሳቸው መጥቶ (ገድልህና ትሩፋትህ በዓለም ሕዝብ ሁሉ ትተህ የስምህ መክበርያ ወደሆነው ሐይቅ ወደ ተባለው ሥፍራ ሂድ) አላቸው። አባታችን "ቦታውን እንዴት ዐውቀዋለሁ" በማለት ቢጠይቁት "ተነሥ። ጉዞህን ጀምር ቦታውን እኔ አሳይሃለሁ" አላቸው። አባ ኢየሱስ ሞዓ በመልአኩ እንደታዘዙት ከበአታቸው ተነሥተው ተከተሉት። የብዙ ወራት መንገድ የሆነው ጐዳናም በስድስት ሰዓት አለቀላቸው።

በዚያን ወቅት ከሐይቅ ገዳም በስተ ሰሜን ወደነበረው ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን ደረሱ። ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ከመግባታቸውም በፊት ለ6 ወራት ያህል በጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን አገልግለዋል። ያገለግሉበት በነበረው ቤተ ክርስቲያን ቀን ቀን ሕዝቡን ሲያስተምሩ በመዋል ሲመሽ ወደ ሐይቁ በመግባት ሲጸልዩ ያድሩ ነበር። በሐይቅ እስጢፋኖስና በዙርያው ለነበሩ አበውም ማታ ማታ አንድ ብርሃን ወደ ሐይቁ ሲገባ ጠዋት ጠዋትም ሲወጣ ይታያቸው እንደነበር ዛሬ በገዳማቸው የሚገኘው ገድለ ኢየሱስ ሞዓ ያስረዳል።

በመጨረሻም በገዳሙ አባቶች ልመናና በልዑል እግዚአብሔር ትዕዛዝ ወደ ሐይቅ ገዳም ገብተው አበምኔት ሆኑ። ሐይቅ እስጢፋኖስ ማለት ከደሴ 30 ኪሎ ሜትር ርቆ የሚገኝ ሲሆን የመሰረቱት ካልዕ ሰላማ የተባሉ ግብጻዊ ጻድቅ ናቸው፤ ገዳሙን ከሰሩ በኃላ የማንን ታቦት እናስገባ ብለው ሲያስቡ ቶራ የምትባል እንስሳ ጭነት ተጭና ከመካከላቸው ተገኘች፤ ጭነቱን አውርደው ቢያዩት በሐር ጨርቅ የተጠቀለለ ሁለት ታቦት አገኙ አንዱ የእስጢፋኖስ አንዱ የጊዮርጊስ " ይህንን ታቦት በእየሩሳሌም የሚኖሩ የተሰወሩ ቅዱሳን ከእግዚያብሔር ታዘው የላኩት ነው" የሚል ጽሑፍም አገኙ ይላል። ይህ ከሆነ ከ 400 ዘመን በኃላ ነው አባ እየሱስ ሞኣ ወደዚህ ቦታ የመጡት ለ 52 ዓመት ቀን ቀን መንፈሳዊ ስራቸውን ይሰራሉ ሌሊት ሌሊት ሐይቁ ውስጥ ቆመው ሲጸልዩ ያድራሉ።

አባ ኢየሱስ ሞዓ በሐይቅ እስጢፋኖስ በአበምኔትነት በቆዩባቸው 45 ዓመታት ከየገዳማቱ ቅዱሳን መጻሕፍትን በመገልበጥና በማስገልበጥ ብሎም በማሰባሰብ የመጀመርያው ዘመናዊ የቤተ ክርስቲያን ቤተ መጻሕፍት በሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም እንዲቋቋም አድርገዋል። በዚሁ ገዳም ውስጥም የመጀመርያውን የቤተ ክርስቲያን ቋሚ ትምህርት ቤት በማቋቋም 8ዐዐ መነኮሳትን በትምህርተ ሃይማኖት አሠልጥነው በንቡረ ዕድነት ማዕረግ በመላ ሀገሪቱ እንዲሠማሩ አድርገዋቸዋል።

ከተማሪዎቻቸውም መካከል አቡነ ተክለ ሃይማኖት (ዘደብረ ሊባኖስ)፣ አባ ተክለሃይማኖት ያመነኮሱ አባት ናቸው። አባ ኂሩተ አምላክ (ዘጣና ሐይቅ)፣ አባ ጊዮርጊስ (ዘጋሥጫ)፣ አባ ዘኢየሱስ፣ አባ በጸሎተ ሚካኤል፣ አባ አሮን (ዘደብረ ዳሬት) ጥቂቶች ናቸው። አፄ ይኩኖ አምላክንም በትምህርተ ሃይማኖት ያነፁት እርሳቸው ናቸው።

እንደዚህ ነው የመነኮሳት አባት እንጦንስ ነው እንጦንስ መቃርስን ወለደ መቃርስ ጳኩሚስን ጳኩሚስ አቡነ አረጋዊን አቡነ አረጋዊ አባ ዮሐኒን አባ ዮሐኒ የሐይቁን አባ እየሱስ ሞአን ወለዱ አባ ኢየሱስ ሞዓ ደግሞ ተክለሃይማኖትን ወለዱ።

በዮዲት ጉዲት ተጐድታ የነበረችው ሀገራችን ዳግም የወንጌሉ ብርሃን እንዲበራባት ሊቃውንት እንዲይነጥፉባት፣ ቅዱሳት መጻሕፍት እንዳይቆነጻጸሉ፣ መነኮሳት አባቶች ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ወርደው ገዳማትን እንዲያስፋፉ ያደረጉት አባ ኢየሱስ ሞዓ ናቸው። በተለይም የሐይቅ እስጢፋኖስ ያፈራቸው 8ዐዐ ሊቃውንት በመላዋ ሀገሪቱ በመሠማራታቸው ዛሬ የምናያቸውን አብዛኞቹን ገዳማትና ቅዱሳት መጻሕፍት አቆይተውናል።

አባታችን አባ ኢየሱስ ሞዓ ለ45 ዓመታት ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ከቆዩ በኋላ ኅዳር 26/1292 ዓ.ም በዕለተ እሑድ በ82 ዓመታቸው ዐረፉ። በዚያች ዕለትም በቦታው የታየው ብርሃን ሀገሪቱን መልቷት እንደነበረ ገድላቸው ይመሠክራል።

ለሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ሼር አድርጉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ቤት መፍትሔ ሊሰጥባቸው ይገባል ያላቸውን በ13 ነጥቦች የተዘረዘሩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በሀገረ ስብከቱ በኩል መፍትሔ እንዲሰጣቸው ውሳኔ አስተላለፈ።


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጋር ባደረገው ውይይት በሀገረ ስብከቱ በኩል የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በተመለከተ በተደረገው የጋራ ውይይት በሀገረ ስብከቱ የሚስተዋሉትን ዋናዋና ችግሮች መቅረፍ ይቻል ዘንድ በጠቅላይ ቤተክህነት በኩል ተለይተው የሚታወቁት ዋናዋና ነጥቦች ለሀገረ ስብከቱ እንዲደርሰው ተደርጎ መፍትሔ እንዲሰጥበት የአዲስአበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሔኖክ በጉባኤው ወቅት በሰጡት ማጠቃለያ ሀሳብ ላይ በገለጹት መሰረት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ ኅዳር 24ቀን2016ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ ሀገረ ስብከቱ በኩል በአፋጣኝ ምላሽ ሊያገኙ ይገባቸዋል ያላቸውን
13 ነጥቦችን በመለየት ለሀገረ ስብከቱ እንዲደርሰውና ከበዛ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለተጠቀሱት የመልካም አስተዳደር ችግሮች ምላሽ እንዲሰጥና የውሳኔውን መፈጸም አለመፈጸም በተመለከተም ተከታትለው የሚያስፈጽሙ ሦስት የመምሪያ ኃላፊዎችን መድቧል።

የጠቅላይ ቤተክህነቱ ዋና ዓላማ ሕግ፣ደንብና መመሪያ ተከብሮ ስራ እንዲሰራ ፣ፍትሕና ርትዕ እንዲነግስ፣
ተጠያቂነትና ግልጽነትን የተከተለ ተቋማዊ አሰራር እንዲሰፍን ለማድረግ እንደሆነ ከመግለጽ ጋር የሚከሉት ዋና ዋና ነጥቦች በሥራ ላይ እንዲውሉ ሲል ልዩነት በሌለው ድምጽ ወስኗል።

የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን አስመልክቶ በጋራ የውይይት መድረክ ችግሮችን በመለየት በውይይት በመፈተሸ በጋራ የመፍትሔ አቅጣጫ ለማስቀመጥ እንዲቻል አስቀድሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደር ጉባኤ ኅዳር 4 ቀን 2016 ዓ.ም በወሰነው መሠረት ኅዳር 18 ቀን 2016 ዓ.ም ባደረገው የጋራ የውይይት መድረክ እንደ ችግር ተለይተው በቀረቡ ዋና ዋና ነጥቦች ላይ ተመሥርቶ በቀረበው የቃለ ጉባኤ ዘገባ ላይ ተወያይቶ ለመወሰን የተደረገ ስብሰባ ነው፡፡

በመሆኑም ጉባኤው ኅዳር 18 ቀን 2016 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ከክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት የሥራ ኃላፊዎች ጋር የተደረገውን የጋር የውይይት መድረክ አስመልክቶ ከቃለ ጉባኤ ጸሐፊዎች የቀረበውን የቃለ ጉባኤ ዘገባ በንባብ ካዳመጠ በኋላ የችግሩ መንስዔ ናቸው በማለት የተለዩ ዋና ዋና ነጥቦች፦

1.በሀ/ስብከቱ ረጅም ዘመናት ሲንከባለል የመጣ የመልካም አስተዳደር ችግር መኖሩ የሚታወቅ ቢሆንም በአሁኑም ሰዓት የበለጠ ተባብሶ የቀጠለ መሆኑን፤

2 የመልከም አስተዳደር ችግርሩ መንስዔ የሕጎችና የደንቦች ጥሰት፤በእቅድና በጸደቀ በጀት ላይ ተመስርቶ ያለመሥራት ውጤት መሆኑን፤

3. መተዳደሪያ ደንቡ ተጥሶ በፍላጎት ላይ ያልተመሠረተ ቅጥርና የሠራተኞች መብትን ያላከበረ የዝውውር ምደባ ውጤት መሆኑን፤

4.የሐብትና የገንዘብ ቁጥጥር ሥራው ደካማ መሆኑ፤

5.ከበላይ መስሪያ ቤት ጋር ተናቦ ያለመሥራትና መሰል ችግሮች ያስከተለው ውጤት መሆኑን ከጋራ ስብሰባውና ከዘገባ ሪፖርቱ ለአስተዳደር ጉባኤው ግንዛቤ በመውሰድና በውይይት የተለዩትን ዋና ዋና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን አስመልክቶ የሀስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በማጠቃለያ በሰጡት ሐሳብ ላይ የመልካም አስተዳደር ችግሮቹ ተለይተውና ተቆጥረው ይሰጡን ለመፍታት ዝግጁ ነን በማለት በገቡት ቃል መሠረት አስተዳደር ጉባኤው በችግሮቹ ላይ በሰፊው ተወያይቶ የሚከተለውን ውሳኔ ወስኗል፡፡

ው ሳ ኔ
አስተዳደር ጉባኤው ከፍ ብሎ በጋራ የውይይት መድረኩ በዝርዝር የተቀመጡትን ዋና ዋና የችግር መንስኤዎችን በመለየት በሀ/ስብከቱ የተሸለ የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት መልካም አስተዳደር ማስፈን ይቻል ዘንድ ፡-

1.በሀ/ስብከቱ መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ  ንኡስ ቁጥር  የህግ ድንጋጌ መሠረት ሀ/ስብከቱ ዓመታዊ እቅዱንና በጀቱን አጥንቶና በጉባኤ ወስኖ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት አቅርቦ በማጸደቅ ተግባራዊ ያደርጋል በሚል የተደነገገ ቢሆንም እስከአሁን ድረስ ወደ ዋናው መሥሪያ ቤት ቀርቦ የጸደቀ በጀት ባለመኖሩ ሀ/ስብከቱ ዓመታዊ ዕቅዱንና በጀቱን በአስቸኳይ በጉባኤ ወስኖ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት አቅርቦ በማጸደቅ ተግባራዊ እንዲያደር፤

2.ሀ/ስብከቱ የሰው ኃይል እጥረት ሳይሆን ያለውን የሰው ኃይል ከሥራው ጋር በማጣጣም ሥራና ሠራተኛን በማገናኘት የማሠራት ችግር መሆኑን ጉባኤው ተረድቷል በመሆኑም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ግንቦት 18 ቀን 2014 ዓ.ም ቋሚ ሲኖዶስ ጥር 27 ቀን 2014 ዓ.ም. ፣ መስከረም 27 ቀን 2015 ዓ.ም እና ጥቅምት 30 ቀን 2016 ዓ.ም. በወሰነው መሠረት ለሥራው ሲባል መተዳደሪያ ደንቡ ተጠብቆ ከሚደረግ የውስጥ ዝውውርና ሽግሽግ በስተቀር ይህ ውሳኔ ከተወሰነበት ቀን ጀምሮ ምንም ዓይነት ቅጥር እንዳይፈጸም፤

3.ሽልማትና ልዩ ልዩ ስጦታዎችን በተመለከተ አንድ ሰው ሊሸለም የሚችለው ዕለት ተዕለት እንዲያከናውን ከተሰጠው የሥራ ተልዕኮ በላይ ለተቋሙ እድገትና ለተሻለ አሠራር በእራሱ ተነሳሽነት ላከናወናቸው ተጨማሪ የሥራ አፈጻጸም የተለየ ብልጫ እንዳስመዘገበ ሲታመን ለበለጠ ሥራ ለማነሳሳትና ለሌሎቹ ምሳሌ መሆኑ የታመነ ነው፤ ነገር ግን እውነታው ይህ ሆኖ እያለ ከሀ/ስብከት እስከ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያን ድረስ እየተፈጸመ ያለው ሽልማት ግን ለብዙ ትችትና የሐብት ብክነት የተጋለጠ በመሆኑ ሽልማት መስጠት አስፈላጊነቱ ሲታመንበት የሥራ አፈጻጸምንና የአገልግሎት ትጋትን መሠረት አድርጎ እንዲከናወን እንዲደረግና ከነዚህ መመዘኛ መሥፈርት ውጪ ያሉ ሽልማቶች እንዲቆም፤

4. የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እስከአሁን ሲያደርገው እንደቆየው ሁሉ ሒሳቡን በውጭ ኦዲተር ለማስመርመር በያዘው እቅድ መሠረት ኦዲተሮችን አወዳድሮ ሥራውን ለማስጀመር ዝግጅቱን ያጠቃለለ ሲሆን ሀ/ስብከቱም በአስቸኳይ እስከ ክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ድረስ የሚገኙትን ሒሳቦች በገለልተኛ የውጭ ኦዲተር አስመርምሮ ለጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ሪፖርት እንዲያቀርብ፤

5. በክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ደረጃ ለፐርሰንት መሰብሰቢያ በሚል የተከፈቱ የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች እስከ አሁን ድረስ በሀ/ስብከቱና በክፍለ ከተማው ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ ጣምራ ፊርማ ሲንቀሳቀስ የቆየ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ከሁለቱ ፈራሚዎች በተጨማሪ የሀ/ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ተጨምረው በሦስት ጣምራ ፊርማ ብቻ እንዲንቀሳቀስና ከፐርሰንቱ የሚገኘው የባንክ ወለድም ተጠቃሎ ወደ ሀ/ስብከቱ የባንክ ሒሳብ ፈሰስ እንዲደረግ፤

6. ከአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ጀምሮ እስከ ሀ/ስብከቱ ጽ/ቤት ድረስ መስተንግዶ በሚል ሽፋን ከፍተኛ የሆነ የገንዘብ ብክነት እየደረሰ እንደሚገኝ ጉባኤው በጋራ ውይይቱ ከተነሱ ሐሳቦች ተገንዝቧል፤ ስለሆነም አስቀድሞ በእቅድ ላይ ተመሥርቶ ከጸደቀ የእህል ውሃ መስተንግዶ በጀት ውጭ ምንም ዓይነት የመስተንግዶ ወጪ እንዳይደረግ፤

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

✞✞✞ እንኳን ለታላቁ ሰማዕት "ቅዱስ መርቆሬዎስ (ፒሉፓዴር)" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞

#ቅዱስ_መርቆሬዎስ_ኃያል

ለክርስትና ሃይማኖት የሚከፈል ትልቁ ዋጋ ሰማዕትነት ነውና ቤተ ክርስቲያን ለምስክሮቿ ሰማዕታት ልዩ ክብር አላት:: ከኮከብ ኮከብ እንዲበልጥ ሁሉ ከሰማዕታትም ቅዱስ ጊዮርጊስን እና ቅዱስ መርቆሬዎስን የመሰሉት ደግሞ ክብራቸው በእጅጉ የላቀ ነው::

ቅዱስ መርቆሬዎስን ብዙ ጊዜ ሊቃውንት "ካልዕ (ሁለተኛው) ሊቀ ሰማዕታት" ሲሉ ይገልጹታል:: ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-

በ2ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ ከሮም ግዛቶች በአንዱ (አስሌጥ) ከአባቱና ከሚስቱ ጋር የሚኖር "አሮስ" የሚሉት ሰው ይኖር ነበር:: ሚስቱ ደም ግባት የሠመረላት: እርሱም ደግነት ያለው ሰው ቢሆኑም የሚያመልኩት ግን ጣዖትን ነበር::

አንድ ቀን አሮስ ሚስቱን ከቤት ትቶ ለአደን ከአባቱ ጋር ወጣ:: እንደ ልማዳቸው ወጥመዱን አስተካክለው ተደበቁ:: የወጥመዱ ደወል ሲያቃጭል: "እንስሳ ተያዘልን" ብለው ሲሯሯጡ ዐይናቸው ያየው ነገር በድንጋጤ እንዲፈዙ አደረጋቸው:: 2 ገጻተ ከለባት በወጥመዱ ውስጥ ተይዘው ነበር::

እነዚህ ፍጡራን ሰዎች ናቸው:: ግን ባልታወቀ የተፈጥሮ አጋጣሚ እንደዚህ እንደ ሆኑ ይታመናል:: ግን እጅግ ግዙፍ: ከአንገታቸው በላይ እንደ ውሻ: ወገባቸው እንደ ሰው: ጉልበታቸው እንደ አንበሳ ሲሆን ታችኛው እግራቸው የጋለ የናስ ብረት ነው የሚመስል::

እነዚህን ፍጡራን ሰማያዊ ካልሆነ ምድራዊ ፍጡር አይችላቸውም:: አንበሳና ነብርን እንኩዋ እንደ ጨርቅ በጣጥሰው ይጥሏቸው እንደ ነበር ይነገራል:: ዐይናቸው እንደ እሳት ይነድ ስለ ነበር ማንም ትክ ብሎ ሊያያቸው አይችልም:: ምሥጢራቸውን ግን የሚያውቀው የፈጠራቸው አምላክ ነው::

ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና:- አሮስና አባቱ ባዩአቸው ጊዜ ደንግጠው ወደቁ:: ገጻተ ከለባቱ የብረት ወጥመዱን እንደ ክር በጣጥሰው የአሮስን አባት በቅጽበት በሉት:: አሮስን ሊበሉት ሲሉ ግን ድንገት ቅዱስ መልአክ ወርዶ በእሳት ሰይፍ አጠራቸው::

"ከእርሱ የሚወጣ ቅዱስ ፍሬ አለና እንዳትነኩት" አላቸው:: ወዲያውም መልአኩ ያንን ኃይለኝነታቸውን አጠፋው:: በዚህ ጊዜ 2ቱም ወደ አሮስ ሒደው ሰገዱለት:: አሮስም ወደ ቤቱ ወስዶም ደበቃቸውና የሆነውን ሁሉ ለሚስቱ ነገራት::

ጥቂት ቆይታም ጸንሳ ወለደች:: ልጃቸውን ፒሉፓዴር (ፒሉፓተር) ሲሉ ስም አወጡለት:: ትርጉሙም "መፍቀሬ አብ - የአብ ወዳጅ" ማለት ነው:: ከዚያም አሮስ ሚስቱን : ልጁንና 2ቱን ገጻተ ከለባት ይዞ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሒዶ ተጠመቀ::

አበው ካህናት እሱን "ኖኅ" : ሚስቱን "ታቦት" : ልጁን ደግሞ "መርቆሬዎስ" ሲሉ ሰየሟቸው:: መርቆሬዎስ ማለትም "ገብረ ኢየሱስ ክርስቶስ - የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ" እንደ ማለት ነው::

ከዚያም ደስ እያላቸው: ክርስቶስን እያመለኩ: ነዳያንን እያሰቡ: ልጃቸውን መርቆሬዎስን አሳደጉ:: ነገር ግን የገጻተ ከለባት ወሬ በመሰማቱ ንጉሡ "ካላመጣሃቸው" አለው:: ኖኅ ጸልዮ ወደ ኃይለኝነታቸው መልሷቸው ስለነበር ፊታቸው ገና ሲገለጥ ብዙ አሕዛብ በድንጋጤ ሞቱ::

ንጉሡም ስለ ፈራ ኖኅን የጦር መኮንን አደረገው:: በጦርነት ጊዜም ገጻተ ከለባቱ ኃይላቸው ስለሚመለስ ተሸንፎ አያውቅም ነበር:: አንድ ጊዜ ግን 2ቱን ገጻተ ከለባት ንጉሡ አታሎ ወሰዳቸው:: ሃይማኖታቸውን ሊያስክዳቸው ሲል "እንቢ" በማለታቸው አንዱ ሲገደል ሌላኛው አምልጦ ጠፋ::

በዚያ ወራትም ኖኅ ለጦርነት ወጥቶ ተማረከ:: ንጉሡ ደግሞ ታቦትን "ላግባሽ" ስላላት የ5 ዓመት ልጇን ቅዱስ መርቆሬዎስን ይዛ ተሰደደች:: በስደት ጥቂት እንደ ቆየች ግን ባሏን ኖኅን አየችው::

እርሷ ብታውቀውም እርሱ ዘንግቷት ነበር:: በሁዋላ ግን በሕጻኑ መርቆሬዎስ አማካኝነት ማስታወስ በመቻሉ ደስ አላቸው:: በዚያው በሮም ዙሪያ ሳሉም አንዱ ገጸ ከልብ መጥቶ አገኛቸው:: በዚህም ምክንያት በስደት ሃገርም መኮንን ሆኖ ተሾመ::

በዚያም ቤተ ክርስቲያንን አንጾ: ቤቱን ቤተ ነዳያን አድርጐ ኖኅ ለዓመታት ኖረ:: ቅዱስ መርቆሬዎስ ወጣት ሲሆንም ወላጆቹ ታቦትና ኖኅ ዐረፉ:: እርሱ ከባልንጀራው ገጸ ከልብ ጋር ሆኖ በጾምና ጸሎት ሲኖር ስለ አባቱ ፈንታ የጦር መሪ አደረጉት::

በጦርነትም እጅግ ኃያል: በሰው ዘንድም ፍጹም ተወዳጅ: የጾምና የጸሎት ሰው ሆነ:: ያን ጊዜ ግን ዳክዮስ ንጉሡ ክርስቶስን በመካዱ ምዕመናን ላይ ሞት ታወጀ:: በጊዜው ደግሞ የበርበር ሰዎች በሮም መንግስት ላይ ጦርነትን በማንሳታቸው ዳኬዎስና ቅዱስ መርቆሬዎስ ለጦርነት ወጡ::

ነገር ግን በርበሮች እንደ አሸዋ ፈሰው ብዛታቸውን ሲያይ ንጉሡ ደነገጠ:: ለማግስቱ ቀጠሮ ተይዞ ቅዱስ መርቆሬዎስ ሲጸልይ ቅዱስ ገብርኤል ወርዶ ሰይፍ ሰጠው::

በማግስቱም "ምን ይሻላል?" ሲባል ቅዱስ መርቆሬዎስ "እኔ የክርስቶስ ባሪያ ነኝና ብቻየን እቁዋቁዋማቸዋለሁ" ቢል ሳቁበት::

እርሱ ግን በጥቁር ፈረሱ (አብሮት ያደገ ነው) ተጭኖ በርበሮችን "ጠብ ይቅርባችሁ: በሰላም ሒዱ" ቢላቸው ተሳለቁበት:: ያን ጊዜም ጸሎት አድርሶ የመልአኩን ሰይፍ ሲመዘው ብዙዎቹ ወደቁ:: ከበርበሮችም ለወሬ ነጋሪነት እንኩዋ የተረፈ አልነበረም::

ነገሩ በሮም ሲሰማ ታላቅ ሐሴት ሆነ:: ዳሩ ግን ከሃዲው ዳኬዎስ "ድሉ የጣዖቶቼ የነ አዽሎን ነው" በማለቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ ሲያዝን አደረ::

በ3ኛው ቀንም "ለጣዖት ሠዋ" የሚል ትዕዛዝ ከንጉሡ ዘንድ መጣ:: ቅዱሱ ግን ወደ አደባባይ ሔደ:: የክብር ልብሱንና መታጠቂያውን አውልቆ በንጉሡ ፊት ወረወረው::

"ሃብትከ ወክብርከ ይኩንከ ለኃጉል:: ሊተሰ ክብርየ ክርስቶስ ውዕቱ:: (ለእኔስ ክብሬ ክርስቶስ ነውና ንብረትህ ለጥፋት ይሁንህ)" ሲልም ንጉሡን በአደባባይ ዘለፈው:: ዳኬዎስም በቁጣ እሳት አስነድዶ: የብረት አልጋውንም አግሎ ቅዱስ መርቆሬዎስን በዚያ ላይ አስተኛው::

ያም አልበቃ:: ወታደሮች እየተፈራረቁ ሲደበድቡት ደሙ ፈሶ እሳቱን አጠፋው:: ለዚያ ነው ሊቃውንት:-
"አመ አንደዱ ላእሌከ ውሉደ መርገም::
እምቅሡፍ አባልከ እንተ ውኅዘ ደም::
አርአያ ዝናም ብዙኅ አጥፍኦ ለፍህም::" ያሉት::

ከዚያም ወስደው ወኅኒ ቤት ውስጥ ጣሉት:: ክርስቶስን ያስክደው ዘንድ በረሃብ: በግርፋት: በእሳት: በስለትም አሰቃየው:: በመጨረሻ ግን አሰቃይተው እንዲገድሉት ወደ እስያ ሰደደው:: በስፍራውም ብዙ አሰቃይተው ኅዳር 25 ቀን አንገቱን ሰይፈውታል::

እርሱ ካረፈ በሁዋላም የተባረከ ፈረሱ ለዓመታት ወንጌልን ሰብኩዋል:: አረማውያንንም ከአፉ በወጣ እሳት አጥፍቷል:: ተአምረኛውና ኃያሉ ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ በ200 ዓ/ም እንደ ተወለደ: በ220 ዓ/ም መከራ መቀበል እንደ ጀመረና በ225 ዓ/ም ሰማዕት እንደሆነ ይታመናል::
<<የቅዱሱ ክብር ታላቅ ነው>>

አምላከ ቅዱስ መርቆሬዎስ በከበረ ቃል ኪዳኑ ይጠብቀን:: ከርስቱም አያናውጠን:: ከበረከቱም ይክፈለን::

#ኅዳር_25 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1. ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕት
2. ቅዱሳን ታቦትና ኖኅ (ወላጆቹ)
3. ቅዱስ ሮማኖስ

ዝክረ ቅዱሳን
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​ኅዳር 24

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ኅዳር ሃያ አራት በዚች ቀን የሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ የበዓላቸው መታሰቢያ ነው፣ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር የሥሉስ ቅዱስን መንበር ያጠኑበት ነው፣ የአቡነ ዜና ማርቆስ ልደታቸው ነው።

ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ

ኅዳር ሃያ አራት በዚህች ቀን በእግዚአብሔር ዙፋን ዙሪያ የሚኖሩ የሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ የበዓላቸው መታሰቢያ ነው።

እሊህም ሥጋ የሌላቸው ረቂቃን የእውነት ካህናት የሆኑ ከቅዱሳን ሁሉ በላይ የሆኑና ከሰማይ ሠራዊት ሁሉ ከፍ ከፍ ያሉ ናቸው እነርሱም ለእግዚአብሔር ቀራቢዎች በመሆን ለሰው ወገን የሚማልዱ ከእጃቸው ውስጥ ካለ ማዕጠንት ጋርነ እንደ ዕጣን የቅዱሳንን ጸሎት የሚያቀርቡ ናቸው ያለእነርሱም አቅራቢነት ጽድቅና ምጽዋት ወደ እግዙአብሔር አይቀርብም።

ወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ እንዲህ ብሎ እንደተናገረ። በዙፋኑ ዙሪያ ሃያ አራት መንበሮች አሉ በእነዚያ መንበሮች ላይም ሃያ አራት አለቆች ተቀምጠዋል ነጭ ልብስ ለብሰዋል በራሳቸውም ላይ የወርቅ አክሊል አለ።

ሁለተኛም እንዲህ አለ ሌላም መልአክ መጥቶ በመሠዊያው ፊት ቆሞ የወርቅ ጽንሐሕ ይዟል በመንበሩ ፊት ባለ በወርቁ መሠዊያ ላይም የቅዱሳንን ሁሉ ጸሎት ያሳርግ ዘንድ ብዙ ዕጣንን ሰጡት ። የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳኑ ጸሎት ጋር በዚያ መልአክ እጅ ወደ እግዚአብሔር ፊት ዐረገ።

የነበረ የሚኖር የአማልክት አምላክ እግዚአብሔር ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ነው እያሉ በመዓልትና በሌሊት ዕረፍት የላቸውም ። እሊህም እንስሶቹ ለዘላለሙ ሕያው ለሚሆን በዙፋን ላይ ለተቀመጠ ለሱ እንዲህ እያሉ ክብር ምስጋና አቀረቡ።

እሊህ ሃያ አራቱ አለቆች አክሊላቸውን በዙፋኑ ፊት አውርደው ለዘላለሙ ሕያው ለሚሆኑ በዙፋን ላይ ለተቀመጠ ለእሱ ሰገዱለት ። አክሊላቸውንም ወደ ዙፋኑ ፊት ወስደው አቤቱ ፈጣሪያችን ኃይልና ምስጋና ክብር ላንተ ይገባል ይሉታል አንተ ሁሉን ፈጥረሃል የተፈጠረውም ሁሉ በአንተ ፈቃድ ይኖራልና ።

እነርሱ በእግዚአብሔር ዘንድ በባለሟልነት እጅግ የቀረቡ መሆናቸውንና ስለሁላችን የአዳም ልጆች ስለሚለምኑና ስለሚማልዱ ከብሉይና ከሐዲስ የከበሩ መጻሕፍት ምስክር ሁነዋል ስለዚህም የበዓላቸውን መታሰቢያ እናደርግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አዘዙ።

ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት

አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር የሥሉስ ቅዱስን መንበር እንዳጠኑ፡- አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ መጥተው በሐይቁ ዳር ቆመው ሳለ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦላቸው ነው በእግሩ በውኃው ላይ እየሄደ እያሳያቸው ተከትለውት እንዲሄዱ የነገራቸው። አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖትም መልአኩን ተከትለው ሐይቁን በእግራቸው ተራምደው ተሻግረው አቡነ ኢየሱስ ሞዐን አገኟቸው፡፡ እርሳቸውም አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ እርሳቸው እየመጡ እንደሆነ በመንፈስ ዐውቀው ነበርና ሲያገኟቸው በጣም ተደስተው ከተቀበሏቸው በኋላ አመነኩሰዋቸዋል፡፡

ከዚህም በኋላ አባታችን በዚያው በሐይቅ በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ አክፍሎትንም በየሳምንቱ ያከፍላሉ፣ ከእሁድና ከቅዳሜ በቀር ምንም አይቀምሱም ነበር፡፡ በእነዚህም ዕለት የአጃ ቂጣ ወይም የዱር ቅጠል ይመጉ ነበር፡፡ ወዛቸው እንደ ውኃ ፈስሶ ምድሪቷን እስኪያርሳት ድረስ እስከ 70 ሺህ ስግደትንም በመስገድ ራሳቸውን እጅግ አደከሙ፡፡ በእነደዚህ ዓይነቱ ተጋድሎ ላይ ሳሉ ነው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ድንገት ነጥቆ ወስዶ ከሥሉስ ቅዱስ ዙፋን ፊት ያቆማቸው፡፡

ከዚህ በኋላ ስለሆነው ነገር ራሳቸው አባታችን ተክለ ሃይማኖት ሲናገሩ ‹‹…ከዚህ በኋላ መልአኩ ወደ ሰማይ አውጥቶ ከመጋረጃው ውስጥ አስገብቶ ከሥላሴ ዙፋን ፊት አቆመኝና ሰገድኩለት፡፡ ከዚያ አስቀድሞ በማላውቀው በሌላ ምስጋና አመሰገንኩት፡፡ ‹ተክለ ሃይማኖት ክፍልህ ከ24ቱ ካህናቶቼ ጋር ይሁን› የሚል ቃል ከዙፋኑ ውስጥ ወጣ፡፡ የወርቅ ጽና አምጥተው ሰጡኝና ከእነርሱ ጋር አንድነት አጠንሁ፡፡ ምስጋናዬ ከምስጋናቸው ጋር ልብሴም እንደልብሳቸው ሆነ፡፡ ፈጣሪዬንም በሦስትነቱ ተገልጦ አየሁት፡፡ በጸሎትህ የሚታመን ሰው ሁሉ ስለአንተ ይድናል አለኝ…..›› (ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገጽ 216-223)

ይህንን ታላቅ በዓል ነው ዛሬ የምናከብረው፡፡ አቡነ ተክለሃይማኖት እንኳን አንደበታቸው የለበሱትም ልብሳቸውም ጭምር እግዚአብሔርን በሰው አንደበት እንደሚያመሰግን በቅዱስ ገድላቸው ላይ ተጽፏል።

ለሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ሼር አድርጉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እነዚህን ውብ ቲሸርቶች ተመልከቱ!

በ2016 ዓ.ም በጥምቀት ቀን መላው ሃገሪቱን ያጥለቀልቁታል ከተባሉት እና በብዙዎች ከተወደዱት ቲሸርቶች መካከል እነዚህ ጥቂቶቹ ናቸው።

ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በእነዚህ ክፍለ ሃገር ላላችሁ
👉 ጅማ 👉 ሊሙ
👉 አዳማ 👉 ዝዋይ (ባቱ)
👉 ቦንጋ 👉 ወሊሶ
👉 አሰላ 👉 ሃዋሳ
👉 ሻሸመኔ 👉 ሆለታ
👉 አንቦ 👉 ሆሳዕና
👉 ወላይታ ሶዶ 👉 ድሬድዋ
👉 ሀረር 👉 ጂግጂጋ
👉 ወልቂጤ 👉 ደብረ ብርሃን
👉 ወሊሶ

ከኛ ተረክባችሁ ማከፋፈልበማህበርም ሆነ በግል ማዘዝ ከፈለጋችሁ ከላይ በተጠቀሱት ቦታዎች በሙሉ ያሉበት ድረስ የምናደርስ ይሆናል።

ሌሎቹንም በኦርቶዶክሳዊ ዲዛይነሮች ተውበው የተሰሩ የጥምቀት ቲሸርቶችን ለማየት እና ለማዘዝ የስር ያለውን የቴሌግራም ሊንክ ይጠቀሙ።
👉 /channel/KABAPrint
👉 /channel/KABAPrint

ማሳሰቢያ - በምታዙበት ወቅት ለምትከፍሉት የቀብድ ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ሀላፊነቱን እኛ እንወስዳለን። አንዳንድ ጥያቄዎች እየደረሱን ስለሆነ ነው።

   ለበለጠ መረጃ
👉 0965875219
👉 0922501999
👉 0913655116

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🎁ሕይወት ቀያሪ የሆኑ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ መጽሐፍትን በትረካ ማዳመጥ ለምትፈልጉ ከታች በPLAYLIST አስቀምጠናል linkun በመንካት ያዳምጡ

የብፁዕነታቸው በረከታቸው ይደርብን

በYoutube ሙሉ PLAYLIST
https://youtube.com/playlist?list=PLzzbdWKORZlUDVInB0WofbPoIteHCUKC5&amp;si=8Xr0ON_93mgDwzz6

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

✝ መስቀሉን ስትነኩት የሚወስዳችሁ ቻናሎች ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶችን የሚያስተምር ጠቃሚ ቻናሎች ስለሆኑ መስቀሉን  ይጫኑ Join ይበሏቸው
/Start


                 🔳🔳
                 🔳🔳
        🔳🔳🔳🔳🔳🔳
        🔳🔳🔳🔳🔳🔳
                 🔳🔳
                 🔳🔳
                 🔳🔳
                 🔳🔳


         ✝መስቀሉ አርማችን ነው።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

እንደምታውቁት መንፈሳዊ ቻሌንጅ ከጀመርን ዛሬ አምስተኛ ቀናችን ነው። ከቻሌንጃችን መካከል 3ኛው ቻሌንጅ ምን ነበር? እስቲ ሁላችሁም መልሱ! ቻሌንጁን ለራሳችሁ ቃል በገባችሁት መሰረት ተግባራዊስ እያደረጋችሁ ነው?

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ሕዳር 21/03/2016 ዓ.ም
የሕዳር ጽዮን ማርያም

✝ በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ።

ዲያቆን፦ 2ቆሮ 7÷12-ፍ.ም
ንፍቅ ዲያቆን፦ 1ጴጥ 2÷5-11
ንፍቅ ካህን፦ ግብረ ሐዋርያት፦ 7÷44-59

ምስባክ ፦ መዝ 131÷13-15
እስመ ሐረያ እግዚአብሔር ለጽዮን
ወአብደራ ከመትኩኖ ማህደሮ
ዛቲ ይእቲ ምዕራፍየ ለዓለም

ትርጉም
እግዚአብሔር ጽዮንን መርጧታልና
ማደርያውም ትሆነው ዘንድ
ወዷታልና እንዲህም ብሎ
ይህች የዘለዓለም ማረፊያዬ ናት

ወንጌል ፦ ማቴ 21÷42-ፍ.ም
ቅዳሴ ፦ ዘእግዝእትነ

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​ኅዳር 20
ቅዱስ አባት አንያኖስ

በዚህች ቀን ቅዱስ አባት አንያኖስ አረፈ። እርሱም ለወንጌላዊ ማርቆስ ሁለተኛ የሆነ የእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት ነው።

የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ አረማውያን ናቸው እርሱም ጫማ ሰፊ ነበር ቅዱስ ወንጌላዊ ማርቆስም ወደ እስክንድርያ አገር መጀመሪያ በገባ ጊዜ እግሩን ተደናቅፎ ጫማው ተቆረጠ እንዲሰፋለትም ወደ ጫማ ሰፊ አንያኖስ ዘንድ ሔደና ጫማውን ሰጠው መስፋትም በጀመረ ጊዜ መስፊያው ጣቱን ወጋው በዮናኒም ቋንቋ አታኦስ አለ ትርጓሜውም አንድ እግዚአብሔር ማለት ነው። ቅዱስ ማርቆስም የእግዚአብሔርን ስም ሲጠራ በሰማ ጊዜ ደስ ብሎት የክብር ባለቤት ክርስቶስን አመሰገነው።

ከዚህም በኋላ አፈር አንሥቶ በምራቁ ጭቃ አድርጎ በአንያኖስ ጣት ላይ አደረገውና በዚያን ጊዜ አዳነው አንያኖስም ከዚህ ድንቅ ምልክት የተነሣ አደነቀ ቅዱስ ማርቆስንም ወደ ቤቱ ወሰደው ስለ ሥራው ስለ አምልኮቱም የመጣውም ከወዴት ቦታ እንደሆነ ጠየቀው።

ቅዱስ ማርቆስም ከብሉያትና ከሐዲሳት መጻሕፍት የአንድ እግዚአብሔርን ህልውና ስለ ዓለሙ ሁሉ ድኅነት የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን፣ መከራ መስቀልንም ተቀብሎ ስለመሞቱ፣ ስለ ትንሣኤውና፣ ስለዕርገቱ፣ ዳግመኛም ለፍርድ ስለ መምጣቱ ይነግረው ጀመረ።

የአንያኖስም ልቡ ብሩህ ሆኖለት በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ ከቤተሰቡ ሁሉ ጋር ተጠመቀ። የመንፈስ ቅዱስም ጸጋ በላያቸው ወረደ አዘውትሮ በመጠመድ የሐዋርያ ቅዱስ ማርቆስን ትምህርት የሚሰማ ሆነ የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት ሕጓንና ሥርዓቷንም ተማረ።

ቅዱስ ማርቆስም ወደ ሌሎች አገሮች ሒዶ ለማስተማር በፈለገ ጊዜ እጆቹን በአንያኖስ ላይ ጭኖ በግብጽ አገር ለወገኖቹ ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ ሊቀ ጵጵስና ሾመው እርሱም ብዙዎችን አስተምሮ አጠመቃቸው በቀናች ሃይማኖትም አጸናቸው ቤቱንም ቤተ ክርስቲያን አደረጋት እርሷም በስተምዕራብ ከእስክንድርያ ከተማ ውጭ ያለች ዛሬ የሰማዕት ቅዱስ ሰርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሁና የታወቀች ናት።

ይህ የተመሰገነ አባት አንያኖስም በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበር ዐሥራ ሁለት ዓመት ኖረ እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።

ለሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ሼር አድርጉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

አረጋጊው መልዐክ

አረጋጊው መልአክ የመላእክትን ዓለም
ገብርኤል አንተ ነህ አብሳሪ ለማርያም
መተህ አረጋጋን ሰላምን ተናገር
እንጽና በእምነት እንኑር በፍቅር(2)

ባለንበት እንቁም እንፅና በእምነት
እስከምናውቅ ድረስ የፍጥረቱን አባት
ብለህ ስትናገር ገብርኤል በአርያም
በቃልህ ጸንተዋል እስከ ለዘለዓለም
አዝ
የዱራውን ሜዳ ያንን የሞት መንደር
ከሰማያት ወርደህ ሞላኸው በመዝሙር
መጠፋፋት ይብቃ ይብዛ ሰላማችን
ገብርኤል አትለይ ቁም ከመኃላችን
አዝ
በገሊላ መንደር ተልከህ ከእግዚአብሔር
ደስታ ይገባሻል ውዳሴ እና ክብር
ብለህ በትህትና የምስራች አልካት
ለድንግል ማርያም ደስታን አበሰርካት
አዝ
ቂርቆስ ኢየሉጣ ለአምላክ ቢታመኑም
በሚፍለቀለቀው ቢጣሉ ከጋኑም
ገብርኤል ስትደርስ ውኃው ቀዘቀዘ
ሞትን ያሸንፋል ለአምላክ የታዘዘ

   ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

​​ኅዳር 19

ቅዱስ ቴዎፍሎስ ከሚስቱ ጰጥሪቃ ከአምስት ወር ልጁም ከደማሊስ ጋር በሰማዕትነት ያረፈበት

ቅዱስ ቴዎፍሎስና ሚስቱ ጰጥሪቃ ደማሊስ (ልጁ)

በዚችም ዕለት ቅዱስ ቴዎፍሎስ ከሚስቱ ጰጥሪቃ ከአምስት ወር ልጁም ከደማሊስ ጋር በሰማዕትነት አረፈ።

ይህም ቅዱስ እግዚአብሔርን በመፍራትና በአማረ አምልኮ ያደገ ነው ሰዎች ሒደው ቅዱስ ቴዎፍሎስ ክርስቲያን መሆኑን ለመኰንኑ ለአንቲጳጦስ ነገሩት መኰንኑም በዜውስ ጣዖት ቤት ሳለ ወደርሱ ያመጡት ዘንድ አዘዘ።

ቅዱሱንም በአቀረቡት ጊዜ አንተ ከወዴት ነህ ሃይማኖትህስ ምንድን ነው አለው። እርሱም የክብር ባለቤት ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስን የማምን ክርስቲያን ነኝ አለ መኮንኑም በክፉ አሟሟት እንዳትሞት ለአማልክት ሠዋ አለው ቅዱሱም ክብር ይግባውና ከጌታዬ ከኢየሱስ በቀር ለረከሱ አማልክት አልሠዋም አለው።

መኰንኑም የሆድ ዕቃው እስቲታይ ሰቅለው ይሠነጣጥቁት ዘንድ አዘዘ እርሱ ግን በጌታችን ኃይል ስለተጠበቀ ምንም ምን አልደረሰበትም ሁለተኛም እሳትን አንድደው ከውስጡ እንዲጨምሩት አዘዘ ቅዱሱም በእሳት መካከል በጸለየ ጊዜ እሳቱ ተበተነ ምንም ምን ሳይነካው ከእሳት ውስጥ ወጣ።

መኰንኑም ይህን አይቶ በረኃብ እንዲሞት አሥረው አጽንተው ይጠብቁት ዘንድ አዘዘ ከስምንት ቀንም በኋላ ሚስቱ ጰጥሪቃ ሕፃኗን ተሸክማ መጣች ምስክርም ሁኖ በክርስቶስ ስም ይሞት ዘንድ አጽናናችው።

መኰንኑም ለቅዱስ ቴዎፍሎስ ምግብ የሰጠው እንዳለ ብሎ ሊመረምር ሔደ የእሥር ቤቱንም ደጅ በከፈተ ጊዜ ጣፋጭ የዕጣን መዓዛ ተቀበለው ቅዱስ ቴዎፍሎስንም በተነጠፈ መቀመጫ ላይ ተቀምጦ ሦስት መላእክት ማርና ወተት ሲመግቡት አገኘው በአየውም ጊዜ ደንግጦ ወደኋላው ተመለሰ።

በማግሥቱም ቅዱስ ቴዎፍሎስን ወደ አደባባይ እንዲአመጡት አዘዘ እርሱም ሚስቱ ተከትላው መጣ መኰንኑም ዲዮስ ለሚባል አምላክ ሠዋ አለው። ቅዱሱም እኔ ዓለምን ሁሉ ለያዘ ለእውነተኛው አምላክ ለጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ለሌላ አልሠዋም አለ።

በዚያንም ጊዜ ለአንበሳ እንዲጥሉት መኰንኑ አዘዘ አንበሳውም ሩጦ እግሮቹን ሳመ። ከዚያም በኋላ በእግዚአብሔር ፈቃድ አቆሰለው ተጋድሎውን በዚህ ፈጽሞ ነፍሱን ሰጠ። ቅዱስት ሚስቱ ጰጥሪቃም ሥጋውን አንሥታ ከሣጥን ጨመረች መኰንኑም እርሷንም ወደ አደባባይ አምጥተው ለአንበሳ እንዲሰጧት አዘዘ። ሕፃኑም አንበሳውን በአየው ጊዜ ሣቀ የአምስት ወርም ልጅ ሲሆን አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ አምናለሁ ብሎ ተናገረ ይህንንም ብሎ በአንበሳ አፍ ከእናቱ ጋር ተበላ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ለሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ሼር አድርጉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

🌺 ሰላም፡ለኵልክሙ። እነሆ ግእዝን በአንድ ወር ኮርሳችን በአዲስ መልኩ ለመጀመር በ10ኛው ዙር ትምህርት መርሐ-ግብር ተመልሷል።

📜 በመሆኑም ለጀማሪዎች የግእዝ ቋንቋን ቀለል ባለና ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅታችንን አጠናቀናል ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመመዝገብ ጥንታዊና ውዱ ቋንቋችንን እናጥና ፥ ዕንወቅ።

📖 ትምህርቱን ከ14 ዓመት ዕድሜ በላይ የሆነ ማንኛውም ሰው፤ ስልክ ወይም ላፕቶፕ ወዴስክቶፕ በመጠቀም መማር ይቻላል።

✅ ለመመዝገብ በዚህ ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር በመላክ ግሩፖችን መቀላቀል ነው ✅
@Geez202
@Geez202
@Geez202 👈
                

⛳️ ለበለጠ መረጃ በ @Geez202 ውስጥ ይደርስዎታል ወይም ከታች በተቀመጠው ደውለው ያግኙን። ሠናይ፡ጊዜ።

🗣 ለሌሎችም ሼር በማድረግ እንድናዳርስ በአክብሮት እንጠይቃለን
🌺 መሠረተ፡ግእዝ 🌺
@MesereteGeez - 0977682046

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

በቻሌንጃችን መሰረት ሁላችሁም ጠዋት የለቀቅነውን የቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ታሪክ በጠዋት እናዳነበባችሁ እና ጸሎተ ምህላ እንደተሳተፋችሁ ባለ ሙሉ ተስፋ ነን። ነገም ይቀጥላል!

Читать полностью…
Подписаться на канал