ortodoxmezmur | Неотсортированное

Telegram-канал ortodoxmezmur - ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

134932

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . ዝማሬ ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Подписаться на канал

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🌺 ሰላም፡ለኵልክሙ። እነሆ የምስራች ግእዝን በዐቢይ ጾም በሚል ልዩ ዝግጅት የግእዝ ቋንቋን ኮርስ ለመስጠት ምዝገባ ጀመርን።

📜 እርስዎም ግእዝ ቋንቋን ቀለል ባለና ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅታችንን አጠናቀናል ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመመዝገብ ጥንታዊና ውዱ ቋንቋችንን እናጥና ፥ ዕንወቅ።

📖 ትምህርቱን ከ14 ዓመት ዕድሜ በላይ የሆነ ማንኛውም ሰው ፤  ስልክ፣ ላፕቶፕ ወይም ዴስክቶፕ በመጠቀም መማር ይቻላል።

✅ ምዝገባውን ለማካሄድ በዚህ ውስጥ ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር በመላክ የመማማሪያ ቦታዎችን መቀበል ነው ✅
@Geez202
@Geez202
@Geez202 👈
                

⛳️ ለበለጠ መረጃ በምዝገባው ይደርስዎታል። ጥያቄ ሲኖር ከታች በተቀመጠው በስልክ ያግኙን። ሠናይ፡ጊዜ።

🗣 ለሌሎችም ሼር በማድረግ እንድናዳርስ በአክብሮት እንጠይቃለን
🌺 መሠረተ፡ግእዝ 🌺
@MesereteGeez - 0918026533

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

👉 @ortodoxmezmur
የአድዋ ጦርነት አዋጅ ደብዳቤ

የአድዋን በዓል መላው ሕዝብ በሰላም የሚያከብርበት ግዜ እሩቅ አይደለም።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

 
           በአድዋ እንዴት ልናሸንፍ ቻልን?
 
የቤተ ክርስቲያናችን አስተዋጽኦ የሚገለጠው “እንዴት አሸነፍን?” የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ስንመረምር ነው፡፡ ይህ ዓለምን በብርቱ ጠፍንጎ የያዘና አንዱን ባሪያ ሌላውን ጌታ የሚያደርግ፣ ሰውን ያህል ፍጡር እንደ ከብት ነድቶ፣ እንደ ዕቃ ጎልቶ፣ ለገበያ አቅርቦ የሚሸጥ እኩይ አስተሳሰብ ከመሠረቱ የናደ፣ ነጻነት ማለት ምን ማለት እንደ ሆነ ለሌሎች ያሳየ፣ የአስተሳሰቡ ሰለባ የነበሩ ነጮችንም ያስደነገጠ ድል ኢትዮጵያውያን እንዴት ሊቀዳጁ ቻሉ? ዓቅሙና ብርታቱስ ከየት ተገኘ? ምዕራባውያን ያላቸው የሠለጠነ ወታደር፣ የጦር መሣሪያ ልዩነት እና ዓለምን የተቆጣጠረው “የነጮች” የበላይነት አስተሳሰብ እያለ የመግጠምስ ሞራሉና እምነቱ ከወዴት መጣ? ኢትዮጵያውያንን ከዚህ የአስተሳሰብና የሞራል ከፍታ ያደረሳቸው ገፊ ምክንያትስ ምንድን ነው? የሚሉ ጥያቄዎችን ስንጠይቅ መልሱ ቤተ ክርስቲያናችን ዘንድ ያደርሰናል፡፡
 
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀደም ብላ ያስተማረችው ትምህርት፣ በነገሥታቱ እና በሕዝቡ ላይ ያሳደረችው በጎ ተፅዕኖ፣ “የእኔም ጦርነት ነው፤ በህልውናዬ ላይ የመጣ ነው” ብላ በማሰብ ደወል ደውላ፣ ዐዋጅ ነግራ ታቦት ይዛ ቀጥተኛ ተሳታፊ በመሆኗ ለኢትዮጵያውያን የአስተሳሰብ ከፍታ የነበራት አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው፡፡
 
ኢትዮጵያውያን በእግዚአብሔር የሚያምኑ፣ የካህናትን ትእዛዝ የሚቀበሉ፣ እግዚአብሔርን መፍራትንና ንጉሥ ማክበርን የሚያውቁ፣ መመካት ቢገባቸውም ምሕረትን፣ ፍርድንና ጽድቅንም በምድር ላይ በሚያደርገው በእግዚአብሔር እንጂ በጉልበት፣ በሠራዊት ብዛት፣ በመሣሪያ ጥራት እንዳልሆነ ሲሰበኩ የኖሩ፣ ይህን እውነትም በልባቸው የጻፉ ስለ ነበሩ ነው፡፡ (ኤር.፱፥፳፬)
 
የአድዋ አርበኞች “እኛኮ ዘመናዊ ትጥቅ የለንም፤ እኛኮ “ጥቁሮች” ነን፤ “ነጭን” ማሸነፍ አንችልም፤ እኛኮ እንበርበት አውሮፕላን፣ እንሽከረከርበት አውቶሞቢል የለንም፤ እንዴት እናሸንፋለን? እንዴትስ ይቻለናል?” የሚል ጥያቄ በፍጹም አልጠየቁም፡፡ ምክንያቱም ‹‹ኢይድኅን ንጉሥ በብዝኀ ሠራዊቱ ወያርብኅኒ በብዝኀ ኃይሉ….፤ንጉሥ በሠራዊቱ ብዛት አይድንም፤ ኀያልም በኃይሉ ብዛት አያመልጥም›› የሚል ትምህርትን ያስተማረችው፣ የእምነት ስንቅም ያስቋጠረችው ቤተ ክርስቲያን ናትና፡፡ (መዝ.፴፪፥፲፮) ብዙዎች የሚዘነጉት ጉዳይ ጦርነትን የሚያሸንፈው የሠራዊት ብዛት፣ የመሣሪያ ጥራት ብቻ ስለሚመስላቸው ነው፡፡
 
ይህ የአስተሳሰብ ችግር በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ረጅም ዘመናትን የተሻገረ፣ አሁንም ድረስ ያልተቀረፈ አስተሳሰብ ነው፡፡ ብዙ ሰው መግደል ማለት ጦርነትን ማሸነፍ ማለት አይደለም፡፡ ብዙ ሠራዊት ያላቸው፣ ብዙ የጦር መሣሪያ የታጠቁ ሁሉ ብዙ ሰው ይገድሉ ይሆናል እንጂ ጦርነትን ያሸንፋሉ ማለት አይደለም፡፡ ምክንያቱም እውነተኛ አሸናፊነት፣ እውነተኛ ድል የሚገኘው እግዚአብሔርን ከሚያምን ንጉሥ፣ እግዚአብሔርን ከሚያምኑ ሠራዊት ወይም ከእውነተኛ ተዋጊዎች ነውና፡፡ ድል የሚነሡት ‹‹ድል መንሣት ዕውቀትም ካንተ ይገኛል፤ ጌትነትም ያንተ ገንዘብ ነው፤ እኔም ያንተ ባሪያ ነኝ›› የሚሉ ነገሥታትና ሠራዊት ናቸውና፡፡ (ዕዝ.ካልእ ፬፥፶፱)
 
ጣሊያን መካናይዝድ ጦር አሰልፎ፣ የሠለጠነ ሠራዊት አሰማርቶ፣ ዘመኑ ያፈራቸውን ትጥቆች ታጥቆ በባዶ እግራቸው በሚሄዱት፣ ሰይፍና ጎራዴ በታጠቁት ሊሸነፍ የቻለው ኢትዮጵያውያኑ ‹‹ድል መንሣት በእግዚአብሔር ኃይል ነው›› ብለው በመግጠማቸው ነው፡፡(፩ኛ መቃ.፳፩፥፫)  ቁም ነገሩ ስለ ጣሊያን ሽንፈት ሳይሆን ስለ ኢትዮጵያውያኑ አሸናፊነትና የሥነ ልቡና የበላይነት ምክንያቱን ማንሣት ስለሆነ ቤተ ክርስቲያን በእምነት፣ በሥነ ልቡና፣ በአብሮነት፣ የገነባችው ሰብእና አድዋ ላይ አሸናፊ ሆኗል፡፡
 
ባለ ርእይ የነበሩ ሊቃውንቶቿ በጸሎት ተግተው፣ ራእይ አይተው፣ በቅኔያቸውና በስብከታቸው የጦርነቱን አይቀሬነት እየገለጹ፣ ዝግጅት እንዲደረግ እያሳሰቡና የሥነ ልቡና ግንባታ ሲያደርጉ ቆይተዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን አድዋ ላይ ታሪክ መሥራታቸው ቤተ ክርስቲያን በአማኞቿ ላይ በሠራችው ሥራ በገነባቸው የሥነ ልቡና የበላይነትና የአሸናፊነት መንፈስ ነው፡፡
 
የሮም ካቶሊክ መሣሪያ ባርካ ለወረራ ልካለች፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ሠራዊቱን በጸሎት ባርካ ራስን፣ ሀገርን፣ ሃይማኖትን ለመከላከል ልካለች፤ ካቶሊክ በመሣሪያ ተማምናለች፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ በጸሎት ተማምናለች፤ እነርሱ በታንክ ሊያሸንፉ መጡ፤ እኛ በታቦት ልናሸንፍ ታቦት ተሸክመን ወጣን፤ እኛም አሸነፍን፤ እነርሱም ተሸነፉ፡፡ ቤተ ክርስቲያን በእግዚአብሔር መታመንን አስተማረች፤ ካቶሊክ በሠራዊትና በመሣሪያ ታምኖ ለወረራ የሚሄድን ባርካ ሸኘች፡፡ እናም ምዕራባውያኑ እስከ ክፉ መሻታቸው ተሸነፉ፡፡ አሸናፊነት ከእግዚአብሔር ነውና፡፡ መጽሐፍ እንደ ተናገረ ‹‹አንተ ከሠራዊታቸው ጋር በከሃሊነትህ አጠፋሃቸው፤ ቤተ መቅደስህን ያጎሳቁሉ ዘንድ የስምህ ጌትነት ማደሪያ የሆነች ደብተራ ኦሪትንም ያሳድፉ ዘንድ መክረዋልና በብረትም የመሠዊያህን ቀንዶች አፍርሰዋልና›› ይላል፡፡ (ዮዲት ፱፥፰)
 
ሌላኛው የአድዋ ድል ምክንያት ደግሞ ካህናቱ ዘምተዋል፤ ሊቃውንቱ ዘምተዋል፤ ታቦቱ ዘምቷል፤ በየድንኳኑ ሰዓታት እየቆሙ ቅዳሴ እየቀደሱ፣ የሚያቆርቡ ነበሩ፤ የሞቱ እየተፈቱ በጸሎትና በምሕላ፣ በሞራልና በስንቅ ንጉሡንና ሠራዊቱን እየተራዱ ብዙ ሥራ የሠሩ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ናቸው፡፡ የጦርነቱን ፍትሐዊነት፣ ለሃይማኖት፣ ለርስት፣ ለሚስት፣ ለልጅ ተብሎ የሚከፈል መሥዋዕትነት መሆኑን እና አሸነፊነት ደግሞ ከእግዚአብሔር መሆኑን፣ ቤተ ክርስቲያን አስተምራለች፤ አበረታታለች፤ ብዙዎቹም ሊቃውንትና ካህናት ከአርበኞች ጋር በግንባር ተሠውተዋል፤ አጥንታቸውን ከስክሰዋል፤ ደማቸውን አፍስሰዋል፤ ይህም ለተዋጊዎች ኃይልና ብርታት ሰጥቷቸዋል፡፡
 
በመጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ የሚል፤ ታሪክ አለ፡፡ ‹‹ሳሙኤልም የሚቃጠለውን መሥዋዕት ሲያሳርግ ፍልስጥኤማውያን ከእስራኤል ጋር ሊዋጉ ቀረቡ፤ እግዚአብሔርም በዚያች ቀን በፍልስጥኤማውያን ላይ ታላቅ ነጎድጓድ አንጎደጎደ፤ አስደነገጣቸውም፤ በእስራኤል ፊት ድል ተመቱ›› ይላል የሚገርም ነው፡፡ (፩ኛ ሳሙ.፯፥፲) አድዋ ላይ የሆነውም ይህ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትም በጦር ግምባር በድንኳን በቅዱስ ጊዮርጊስ ታቦት ላይ የሚቃጠለውን መሥዋዕት ሲያሳርጉ፣ ንጉሡም ቅዳሴውን ሲያስቀድሱ፣ የልዳው ኮከብ የፋርሱ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ በጣሊያኖቹ ላይ አንጎደጎደባቸው፤ አስደነገጣቸውም፡፡ በእነዚያ ልበ ሙሉዎች ጎራዴ ይዘው በመድፍ ፊት በሚቆሙ ደፋሮች ኢትዮጵያውያን ድል ተመቱ፡፡
 
እነሆ ዛሬ እኛ የድል አድራጊዎች ልጆች ተባልን፤ “ነጭም” “በጥቁር” ተሸነፈ፤ የነጻነትን ጣዕም ጥቁሮች ቀመሱ፤ የነጭ ፍልስፍና ተሻረ፤ ሰውን ያህል ፍጡር ባሪያ የሚያደርገው፣ አንዱን ገዥ ሌላውን ተገዥ የሚያስብለው የቅኝ ገዥዎች አስተሳሰብም ታሪኩ በጥቁር መዝገብ ተጻፈ፤ ይህም ከሆነ እነሆ ፻፳፰ ዓመታት ተቆጠሩ፡፡ አባቶቻችን  ድል አድርገው ታሪክ ሠሩ፤ እኛ ደግሞ ድል ማድረግ፣ ታሪክ መሥራት ቀርቶ ታሪክን መሸከም ከብዶን ለመውደቅ እንፍገመገማለን፡፡

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ሰይጣን ጾመኛ ነው በተፈጥሮው መልአክ ነበርና። ሰይጣን ድንግል ነው እንደ ሰው አይጋቡምም አይወልዱምምና። ትህትና ስለሌለው ግን ወደቀ!

አንተም ጾመኛም ብትሆን ድንግልም ብትሆን ትህትና ከሌለህ ግን ከሰይጣን እኩል ነህ።

እግዚአብሔር ስለ ንጽሕናው /ድንግልናው/ ከሚመካ ጻድቅ ይልቅ ስለ ዝሙቱ የሚያለቅስ ኃጥያተኛን ይወዳል።

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

1. የተከበራችሁ አበው ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ሆይ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ “በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፡፡ እንዳለ በዚህ ታላቅ የፈተና ወቅት የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ለማስጠበቅ፤ ቅዱስ ሲኖዶስ የሰጣችሁን ኃላፊነት ለመወጣት ምእመናንን አቅጣጫ በመስጠት የቀደሙ አባቶቻችሁን ፈለግ በመከተል ዛሬም በጽናት እንድትተጉ፤ ያከበረቻችሁን ቤተ ክርስቲያን በአንድነት ሆናችሁ እንድትጠብቁ በልጅነት መንፈስ በትሕትና እንጠይቃለን፡፡ በተጨማሪም የአባትነት የዋህ ልቦናችሁን በመጠቀም ያዘኑ፣ የጠቀሙ፣የተቆረቆሩ መስለው ቀርበው የግል ፍላጎታቸውን ለመፈጸም የሚጥሩ ስለሚኖሩ ሁሉንም በጥንቃቄ እንድትመረምሩ፤ቀኖች ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን በመዋጀት አንድነታችሁን እንድታጠነክሩና በቤተክርስቲያን ዙሪያ ስለሚፈጠሩ ችግሮች በጥልቀት እንድትወያዩና እንድትመካከሩ እናሳሰስባለን።

2. ከዚህ ውጭ ቤተ ክርስቲያንን በማይጠቅማት ጉዳይ የግል ፍላጎትንና ምድራዊ ዓላማን መሠረት አድርጋችሁ ከቤተ ክርስቲያን ሕግና ቀኖና ውጭ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊን ለመተካት፣ ፓትርያርክ ለመሾምና የመሳሰሉትን ለመፈጸም የምትንቀሳቀሱ አንዳንድ አባቶች ከድርጊታችሁ እንድትታቀቡ ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡ ማኅበራችን ይህንን ጉዳይ እየተከታተለ መረጃውን ለምእመናን የሚያደርስ መሆኑንም በዚሁ አጋጣሚ እንገልጻለን፡፡

3. ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ መምህራነ ወንጌል፣ ካህናት ሆይ በጸሎትና በትምህርት ምእመናንን በማጽናናት፤ ከእውነት ጋር በመቆም እውነታውን በማሳየት ምእመናን ለቤተ ክርስቲያን ዘብ እንዲቆሙ በማድረግ ድርሻችሁን እንድትወጡ እናሳስባለን።

4. ውድ ምእመናንና የማኅበራችን አባላት የታሪክ አጋጣሚ ሆኖ በዚህ ዘመን ቤተ ክርስቲያንን ከአሳዳጆቿ የመጠበቁ ዋነኛ ኃላፊነት በዘመኑ ባለን ብፁዓን አባቶች፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርሰቲያን፣ ካህናትና ምእመናን ሁላችን እጅ ላይ ወድቆአል፡፡ የቤተ ክርስቲያንን ጉዳይ ለአባቶችና ለካህናት ትተን “እኔ አያገባኝም፤ አይመለከተኝም” ልንል አይገባም፡፡ ሁሉም በየድርሻው ቤተክርስቲያኑን ለመጠበቅ መትጋት አለበት፡፡ በቤተ ክርስቲያን ላይ የደረሰውን ጥፋትና ሊመጣ ያለውን ፈተና አስቀድሞ በመረዳት ቅዱስ ሲኖዶስ ቀደም ሲል በወሰነው መሠረት በየአጥቢያችን፤ በተለያየ መልኩ በመደራጀት፤ በቤተክርስቲያን ላይ ጥፋት ለማድረስ የሚመጡትን በመከላከል የቤተ ክርስቲያንን ስደት ለማስቆም መንፈሳዊ ግዴታችንን እንድንወጣ እንጠይቃለን፡፡

5. በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በልዩ ልዩ አገልግሎት እየተሳተፋችሁ ያላችሁ ሰንበት ትምህርት ቤቶች፣ ማኅበራትና ሌሎችም ሁላችንም አንድነታችንን በመጠበቅ በጋራ አገልግሎቶችን በመፈጸም ድርሻችንን እንድንወጣ ለተግባራዊነቱ ጥሪ እናቀርባላን፡፡

6. ገዳም ድረስ ገብቶ መሣሪያ ያልያዙና: ራሳቸውን እንደሞቱ ቆጥረው እየኖሩ ያሉ መነኮሳት ላይ ግድያ የፈጸመ ማንኛውም የታጠቀ ኃይል (መደበኛም ይሁን ኢመደበኛ: በግልም ይሁን በቡድን: አማኝም ይሁን ኢአማኝ) ድርጊቱ ከሰውነት ተፈጥሮ የወጣ ነው፡፡ ምናኔንና የክህነት ክብርን በተቃረነ መልኩ ሰብእና የጎደለው ጥቃት ማድረስ ኢትዮጵያዊ ባህልም አይደለም፡፡ ጥቅም የሌለው ከንቱ ተግባር ነው፡፡ በዚህ የሚገኝ የፖለቲካ ትርፍ ይኖራል ብለን አናምንም፡፡ ጤነኛ በሆነ አእምሮ ታስቦ የተፈጸመ ነው ማለትም አይቻልም፡፡ ማስተዋል ተወስዶባቸው እውቀት ተሰውሮባቸው እንጂ ይህንን ማድረግ ቀርቶ ማሰቡም የሙት ሐሳብ ነው፡፡ ቀድሞ የሞተው ሟቹ ሳይሆን ገዳዩ ነው፡፡ በዚህ መንገድ የቤተ ክርስቲያን አማኞች ሲበዙ እንጂ ሲያንሱ በታሪክ አልታየም:: ይህ ድርጊት ክርስቲያኖችን ሲያጠነክር እንጂ ሲያዳክም ታይቶ አይታወቅም፡፡ መጽሐፍ “ጎርፍም መጣ ነፋስም ነፈሰ ያንን ቤት ገፋው በዓለት ላይ ስለተመሠረተ አልወደቀም ” ባለው መሠረት ቤተክርስቲያን በጽኑ ዐለት ላይ የተመሠረተች ስለሆነ አታሽነፏትም። ዲዮቅልጥያኖስም አላጠፋትም:: ዲያብሎስም ዝናሩን እንዲሁ ጨረሰ:: ስለዚህ አትድከሙ: አትሳቱም እናንተ ሳትወለዱ የነበረች ቤተ ክርስቲያን እናንተ አልፋችሁም እንደ እናንተ ላሉት በስሑት መንገድ ለሚጓዙት ሁሉ እየጸለች ትቀጥላለች:: ሐሳቧም፣ ሥራዋም፣ ዓላማዋም፣ ግቧም ሰማያዊ ነውና።

በመጨረሻም ማኅበረ ቅዱሳን ከቤተ ክርስቲያን ህልውና በላይ የሚያስቀድመው አንዳች ነገር የሌለ በመሆኑ ቤተ ክርስቲያናችን የገጠማትን ፈተና ለማለፍ ከሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን አካላት ጋር በመናበብ የሚጠበቅበትን መንፈሳዊ ግዴታ ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን በዚሁ አጋጣማ እያሳወቅን፥ የሁላችንም የመሰባሰብና የአገልግሎት ማእከል ቤተ ክርስቲያን በመሆኗ ከሁሉም ነገር በፊት ቅድሚያ ሰጥተን ሊመጣ ካለው አደጋ ቤተ ክርስቲያናችንን የመጠበቅ ኀላፊነት በትጋት እንወጣ ሲል ማኅበረ ቅዱሳን በመግለጫው ጥሪ አቅርቧል፡፡

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ቅዳሴ ክፍል 78 ተለማመዱት።

ለምትወዷቸው እህት ወንድሞቻችሁ አጋሯቸው። ቅዳሴ በአጭር ጊዜ እንዲለማመዱ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ቅዳሴ ክፍል 77 ተለማመዱት።

ሙሉ የቅዳሴ ትምህርትን ለምዕመናን።

በዝማሬ ዳዊት ቻናላችን ላይ ያገኙታል

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🌺 ሰላም፡ለኵልክሙ። እነሆ የምስራች ግእዝን በዐቢይ ጾም በሚል ልዩ ዝግጅት የግእዝ ቋንቋን ኮርስ ለመስጠት ምዝገባ ጀመርን።

📜 እርስዎም ግእዝ ቋንቋን ቀለል ባለና ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅታችንን አጠናቀናል ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመመዝገብ ጥንታዊና ውዱ ቋንቋችንን እናጥና ፥ ዕንወቅ።

📖 ትምህርቱን ከ14 ዓመት ዕድሜ በላይ የሆነ ማንኛውም ሰው ፤  ስልክ፣ ላፕቶፕ ወይም ዴስክቶፕ በመጠቀም መማር ይቻላል።

✅ ምዝገባውን ለማካሄድ በዚህ ውስጥ ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር በመላክ የመማማሪያ ቦታዎችን መቀበል ነው ✅
@Geez202
@Geez202
@Geez202 👈
                

⛳️ ለበለጠ መረጃ በምዝገባው ይደርስዎታል። ጥያቄ ሲኖር ከታች በተቀመጠው በስልክ ያግኙን። ሠናይ፡ጊዜ።

🗣 ለሌሎችም ሼር በማድረግ እንድናዳርስ በአክብሮት እንጠይቃለን
🌺 መሠረተ፡ግእዝ 🌺
@MesereteGeez - 0918026533

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

In apostasy age, Our Lord thought the Holy Gospel for three years and suffered at the Calvary for three hours. After His death upon the cross, He rose up on the third day. This is not the only work of God He willed on the number three, but has done many miraculous in the Angelology and stories of holies as written in their hagiographies.

For instance, our Righteous Father Abune Tekle Haymanot praised Holy Trinity saying, “One is the Holy Father. One is the Holy Son. One is the Holy Spirit” after three days after his birth, coming down from his mother’s embrace. Apostle Saint Paul went to the third heavens and saw a mystery he could not speak of through his voice. We can mention many stories but are limited with in time. (Hagiography of Abune Tekle Haymanot, 2 Corinthians 12:2)

For this topic, we have focused on the three days fast God ordered. In atoning any of our sin, prayer, fasting and prostration is of the essence and thus our Lord has made the liturgy for us. As we find it in scripted in the Holy Bible, due to their heinousness, onwards God’s warning to the Nineveh people from being entirely destroyed within three days, they fasted the Fast of Nineveh, the three days fast.

When our Lord, God ordered Prophet Jonah, instead of obeying, he chose to flee to Tarshish not because he thought he could escape from Him, but knowing His mercy to save the Nineveh people after his prophecy that the city of Nineveh will be entirely destroyed and frightened to be called a False Prophet.

“The word of the Lord came to Jonah the son of Amittai, saying, “Arise, go to Nineveh, that great city, and cry out against it; for their wickedness has come up before Me.” But Jonah arose to flee to Tarshish from the presence of the Lord. He went down to Joppa, and found a ship going to Tarshish; so he paid the fare, and went down into it, to go with them to Tarshish from the presence of the Lord.” (Jonah 1:1-3)

God knew the dovelike Jonah and so He changed the direction of his journey to Nineveh. He first sent a great storm on the ship; then the ship was nearly broken frightening all the passengers. Unaware of the cause of the storm, they had to ask the fast asleep Jonah. They then had to cast lots and surprisingly, it fell onto Jonah. After acknowledging the truth from him, they threw him out of the ship, in to the sea. Then God prepared a great fish to swallow him in which he stayed for three days and nights. This has become the example for the burial of Lord and Savior Jesus Christ in the grave for three days. (Jonah 1:4-17, Matthew 12:40-41)

Later on, God made the great fish to vomit out Jonah onto dry land. Jonah had to make a three days walk to the city of Nineveh but walked a day long street and started to shout. “Yet three days, and Nineveh shall be overthrown!” Therefore, the people of Nineveh believed the word of God and accepted His words. Wore sackcloth, abstained from consuming any kind of nourishment and fasted for three days. Even the King Shalmaneser over three his throne and wore sackcloth and fasted ordering all saying “Let neither man nor beast, herd nor flock, taste anything; do not let them eat, or drink water. But let man and beast be covered with sackcloth, and cry mightily to God; yes, let everyone turn from his evil way and from the violence that is in his hands. Who can tell if God will turn and relent, and turn away from His fierce anger, so that we may not perish? (Jonah 3:8-9) Children were prohibited from breast milk and all animals banned from the consuming anything.

Certainly, we can comprehend from the Book of Jonah that our Lord, God had mercy on the people and save the ninevites after their fast. But we can also see from the consequent story about Prophet Jonah’s resentment. “But it displeased Jonah exceedingly, and he became angry.

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🌺 ሰላም፡ለኵልክሙ። እነሆ የምስራች ግእዝን በዐቢይ ጾም በሚል ልዩ ዝግጅት የግእዝ ቋንቋን ኮርስ ለመስጠት ምዝገባ ጀመርን።

📜 እርስዎም ግእዝ ቋንቋን ቀለል ባለና ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅታችንን አጠናቀናል ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመመዝገብ ጥንታዊና ውዱ ቋንቋችንን እናጥና ፥ ዕንወቅ።

📖 ትምህርቱን ከ14 ዓመት ዕድሜ በላይ የሆነ ማንኛውም ሰው ፤  ስልክ፣ ላፕቶፕ ወይም ዴስክቶፕ በመጠቀም መማር ይቻላል።

✅ ምዝገባውን ለማካሄድ በዚህ ውስጥ ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር በመላክ የመማማሪያ ቦታዎችን መቀበል ነው ✅
@Geez202
@Geez202
@Geez202 👈
                

⛳️ ለበለጠ መረጃ በምዝገባው ይደርስዎታል። ጥያቄ ሲኖር ከታች በተቀመጠው በስልክ ያግኙን። ሠናይ፡ጊዜ።

🗣 ለሌሎችም ሼር በማድረግ እንድናዳርስ በአክብሮት እንጠይቃለን
🌺 መሠረተ፡ግእዝ 🌺
@MesereteGeez - 0918026533

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​ጾመ ሰብአ ነነዌ
በርእሰ ደብር ብርሃኑ አካል


ጾመ ነነዌ ከሰባቱ የአዋጅ አጽዋማት አንዷ ስትኾን የምትጾመውም ለሦስት ቀናት ነው፡፡ ይህቺ ጾም የምትጀመርበት ዕለትም ልክ እንደ ዐቢይ ጾም ሰኞን አይለቅም፡፡ ጾሟ የምትጀመርበት ቀን ሲወርድ ወይም ወደ ኋላ ሲመጣ እስከ ጥር ፲፯ ቀን ድረስ ነው፡፡

ቀኑ ሲወጣ ወይም ወደ ፊት ሲገፋ ደግሞ እስከ የካቲት ፳፩ ቀን ይረዝማል፡፡ ጾመ ነነዌ በእነዚህ ፴፭ ቀናት ውስጥ ስትመላለስ (ከፍ እና ዝቅ ስትል) ትኖራለች፤ ከተጠቀሱት ዕለታት አትወርድም፤ አትወጣም፡፡ በዚህ ዓመትም የካቲት 7 ቀን ትጀመራለች፡፡

‹‹ጾመ ሰብአ ነነዌ፤ የነነዌ ሰዎች ጾም›› የሚለው የጽሑፋችን ርእስ እንደሚያስረዳው ይህቺን የሦስት ቀን ጾም የጾሟት በነነዌ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ከተማዋም (ነነዌ) በጤግሮስ ወንዝ ዳርቻ የምትገኝ ስትኾን መሥራቿም ናምሩድ ነው ዘፍ.፲፥፲፩-፲፪/ ፡፡ ጥንታዊቷ የነነዌ ከተማ ለአሦር መነሻ የኾነች፤ እጅግ ሰፊና ያማረች፤ የቅጥሯ ርዝመትም ፲፪ ኪሎ ሜትር የሚሸፈን ነበር፡፡ በከተማዋ ንጉሡ ሰናክሬም ብዙ ሕንጻዎችን ገንብቶባት ነበር /ዮናስ ፬፥፲፩/፡፡

በዚያ ዘመን የነበሩ የነነዌ ሰዎች ኀጢአታቸው በዝቶ እግዚአብሔር ሊያጠፋቸው ሲል ቸርነትና ምሕረቱ የማያልቅበት እግዚአብሔር መክሮ፣ ዘክሮ እንዲመልሳቸውና ንስሐ እንዲገቡ ነቢዩ ዮናስን ወደ ነነዌ ሕዝብ ላከው /ሉቃ.፲፩፥፴/፡፡

ዮናስ የስሙ ትርጕም ‹ርግብ› ማለት ነው፡፡ በዳግማዊ ኢዮርብዓም ዘመነ መንግሥት የነበረ ነቢይ ነው፡፡ ይህ ነቢይ መኖሪያው በገሊላ በጋትሔፌር ድንበር ከተማ ነበረ፡፡ አባቱም አማቴ ይባላል፡፡ ኢዮርብዓም ሶርያውያንን አባሮ የእስራኤልን ድንበር እንዲመልስ ነቢዩ ዮናስ ትንቢትን ተናግሯል /፪ኛነገ.፲፬፥፳፭፤ ዮናስ ፩፥፩/፡፡

ነቢዩ ኤልያስ ያስነሣው የሰራጵታዋ መበለት ሕፃን ነቢዩ ዮናስ እንደ ኾነ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ያስረዳል /፩ኛ ነገ.፲፯፥፲፱/፡፡ መድኀኒታችን ክርስቶስም የዮናስን ከዓሣ ኾድ መውጣት የራሱ ትንሣኤ ምሳሌ አድርጎ ነግሮናል /ማቴ.፲፪፥፲፱-፵፪፤ ሉቃ.፲፩፥፴-፴፪/፡፡

እግዚአብሔር ‹‹ሔደህ በነነዌ ላይ ስበክ›› ባለው ጊዜ ነቢዩ ዮናስ ‹‹አንተ  መሐሪ ነህ፤ ልትጠፉ ነው ብዬ ተናግሬ ብትምራቸው ሐሰተኛ ነቢይ እባላለሁ››  ብሎ ላለመታዘዝ እስራኤልን ለቆ በመርከብ ወደ ተርሴስ ሸሸ፡፡

እግዚአብሔርም ታላቅ ነፋስን አስነሥቶ መርከቧ በማዕበል እንድትመታ አደረገ፡፡ ከዮናስ ጋር በመርከቧ ተሳፍረው የነበሩ ነጋድያንም ያላቸውን ሀብት ወደ ባሕሩ መጣል ሲጀምሩ ነቢዩ ዮናስ ጥፋቱን ተገንዝቦ ‹‹ማዕበሉ በእኔ ምክንያት የመጣ ስለ ኾነ  ንብረታችሁን  ሳይኾን እኔን  ወደ ባሕር ጣሉኝ›› ብሎ ተማጸናቸው፡፡

እነርሱም ‹‹ስለዚህ ሰው ነፍስ እንዳንጠፋ፣ ንጹሕም ደም በእኛ ላይ እንዳይደረግብን አይኾንም›› አሉ፡፡

ወደ ባሕሩ ለመጣል ዕጣ በተጣጣሉ ጊዜም ዕጣው በዮናስ ላይ ስለ ወጣ ነጋድያኑ ዮናስን ወደ ባሕሩ ጣሉት፡፡ ወዲያውኑ ከእግዚአብሔር ዘንድ የታዘዘ ታላቅ ዓሣ አንበሪ ዮናስን በአፉ ተቀብሎ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት አሳድሮ ወደ ነነዌ አደረሰው፡፡

እግዚአብሔር የቅል ተክልን ምሳሌ በማድረግ ቅጠሉ በመድረቁ ዮናስ ባዘነ ጊዜ ‹‹አንተ ላልደከምክበት እና በአንድ ቀን በቅሎ ላደገ ቅል ስታዝን እነሆ በታላቂቱ ነነዌ ከተማ ያሉ ከአንድ መቶ ሃያ ሺሕ በላይ ሕዝብና እንስሳቱ የእጄ ፍጥረቶች ስለ ኾኑ ያሳዝኑኛል›› በማለት ነቢዩ ዮናስም ውሸታም ላለመባል መኮብለሉ ስሕተት መኾኑን አስረድቶታል፡፡

ዮናስም ነነዌ መሬት ላይ መድረሱን ባወቀ ጊዜ ከእግዚአብሔር መሸሽ አለመቻሉን ተረዳ፤ የነነዌ ሰዎችንም ‹‹ንስሐ ግቡ›› እያለ መስበክ ጀመረ፡፡ የነነዌ ሰዎችም ንስሐ በገቡ ጊዜ እግዚአብሔር ይቅር ብሎ ከጥፋት አድኗቸዋል፡፡ ሐሰት እንዳይባልም እሳቱ እንደ ደመና ኾኖ ከላይ ታይቶአል፡፡

የታላላቁ ዛፍ ቅጠል እስኪጠወልግ ድረስ አድርቆ ለሕዝቡ አሳይቷቸዋል፡፡ ንስሐቸው በከንቱ እንዳልቀረ አስረድቷቸዋል /ትንቢተ ዮናስን በሙሉ ይመልከቱ/፡፡ ታኅሣሥ ፭ ቀን የሚነበበው የመጽሐፈ ስንክሳር ክፍል  ‹‹ወበልዐ አሐደ ኀምለ›› በማለት ንስሐ ያልገቡ አንድ አገር ያህል ሰዎች በእሳቱ እንደ ጠፉ ይነግረናል፡፡

ጾመ ነነዌ የሦስት ቀን ሱባኤ ናት፤ በሦስት ቀናት ጾምና ጸሎት ንስሐ የገቡ የነነዌ ሰዎች ከጥፋት እንደ ዳኑ ዅሉ፣ በብሉይ ኪዳን አስቴር ሦስት ቀን ጾማ፣ ጸልያ በእስራኤል ላይ የመጣውን መቅሠፍት እንዲመለስ አድርጋለች /አስ.፬፥፲፭-፲፮/፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ከበዓል ስትመለስ ሕፃኑ ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ መንገድ ላይ ጠፍቶአት ከሦስት ቀን ፍለጋ በኋላ በቤተ መቅደስ አግኝታዋለች /ሉቃ.፪፥፵፮/፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ለሄሮድስ በሰጠው ምላሽ መልስ ሦስት ቀን የሱባኤ ፍጻሜ መኾኑን ገልጿል /ሉቃ.፲፫፥፴፪/፡፡

ጾመ ነነዌ የእግዚአብሔርን ቸርነትና መሐሪነት የምናስታውስበት ጾም ነው፡፡ ይኸውም እኛ ፍጡራኑ በበደልን ጊዜ ፈጽሞ ከማጥፋት ይልቅ ምክንያት ፈልጎ እንድንድን ያደርገናል፡፡ ዮናስ ለስብከት ፈቃደኛ ባይኾን እንኳን እግዚአብሔር በተለየ ጥበቡ እንዲሔድ አድርጎታል፡፡

በእርግጥ እግዚአብሔር ሌላ የሚልከው ነቢይ አጥቶም አይደለም፤ እርሱንም ጭምር ሊያስተምረው ስለ ፈለገ እንጂ፡፡ የነነዌ ሰዎች የተነሳሕያን ምሳሌ ናቸው፡፡ ይህም ማለት ሰው ጥፋቱን አምኖ ንስሐ ከገባ እግዚአብሔር ይቅር ማለቱን አይተውም፡፡ ለዚህም ነው ዮናስን  ‹‹አንተ  ላልደከምክበት  እና በአንድ  ቀን በቅሎ  ላደገ ቅል  ስታዝን እነሆ  በታላቂቱ  ነነዌ ከተማ  ያሉ ከአንድ  መቶ ሃያ ሺሕ በላይ ሕዝብና እንስሳቱ  የእጄ ፍጥረቶች ስለ ኾኑ  ያሳዝኑኛል›› ያለው፡፡

ቀደምት የቤተ ክርስቲያን አባቶቻችን ይህን እና ሌሎች አጽዋማትን እንድንጾም የወሰኑልን ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ ሕጉ የተዘጋጀልን እንደ ነነዌ ሰዎች እኛም ጾመን፣ ጸልየን ከኀጢአታችን እንነጻ ዘንድ ነው፡፡ ዛሬ ዓለማችን በኀጢአት ማዕበል እየተናወጠች ባለችበት ወቅት እኛም እንደ ነነዌ ሰዎች ከበደላችን ብንመለስ እና ንስሐ ብንገባ ቸሩ ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ይቅርታና ምሕረት የባሕርይ ገንዘቡ ስለ ኾነ ‹‹ወደ እኔ  ተመለሱ፤  እኔም ይቅር  እላችኋለሁ፤›› ይለናል፡፡

ስለኾነም በነቢዩ ዮናስ ላይ የተደረጉ ተአምራትንና ካለመታዘዝ የሚመጣ ቅጣት ቀላል አለመኾኑን በማስተዋል፣ ለነነዌ ሰዎች የወረደውን ምሕረት በመገንዘብ ለእግዚአብሔርም ኾነ ለሃይማኖት አባቶች እና ለወላጆቻችን መታዘዝ ይገባናል፡፡

ስንጾምም እግዚአብሔር አምላካችን መዓቱን በምሕረት፣ ቍጣውን በትዕግሥት መልሶ በኀጢአት ለጠፋው ዓለም ይቅርታውን ይልካል፡፡ በመጾማችን ራሳችን ከመዓትና ከመቅሠፍት ከመዳናችን ባሻገር በእኛ በደል ምክንያት አገራችን፣ ዕፀዋቱና እንስሳቱም ሳይቀር ከድርቅና ከቸነፈር ይተርፋሉና፡፡

✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

በታላቁ ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የተፈፀመውን ጥቃት አስመልክቶ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ በተገኙበት ከመንግሥት አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡
++++++++++++++++++++++++++++++++

በጥንታዊውና ታሪካዊ ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የተፈፀመውን የመነኮሳት ግድያ አስመልክቶ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት በምሥራቅ ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባቡ ዋቆ መሪነት ተካሂዷል።

በውይይቱ የምሥራቅ ሸዋ ዞን የጸጥታ ክፍል ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ም/ሥራ አስኪያጅ በሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮነን የተመራ ልዑክ፣የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም አበምኔትና የገዳሙ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የሀገረ ስብከቱ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

በግፍ የሰማዕትነትን ጽዋ የተቀበሉ አባቶች መርዶ በትናንትናው ዕለት የተሰማ ሲሆን በመላው ዓለም የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን ሀዘናቸውን በመሪር እንባ እየገለጹ ይገኛሉ።

የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከትም ከገዳሙ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በትኩረት ጉዳዩን ሲከታተል የቆየ ሲሆን በዛሬ ዕለትም በቢሾፍቱ ከተማ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ አየር ኃይል ግቢ ዐራት ሰዓታትን የፈጀ ሰፊ ውይይት ሲደረግ ቆይቷል፡፡

በውይይቱ የተቀመጡ የመፍትሔ ሃሳቦች፡-

1ኛ፡- በመንግሥት የፀጥታ አካላት አማካኝነት የሰማዕታቱን አስክሬን ከወደቁበት አንስቶ በክብር ወደ ገዳሙ በማምጣት ሥርዓተ ቀብር እንዲፈፀምላቸው

2ኛ- በቋሚነት በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሀገር መከላከያ ሠራዊትና በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ጸጥታ መዋቅር ገዳሙንና ገዳማውያንን በዘላቂነት መጠበቅ እንዲቻል

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

የካቲት 16
ኪዳነ ምህረት


‹ ኪዳን › የሚለው ቃል ‹‹ ተካየደ – ተዋዋለ ፤ ቃል ኪዳን ተጋባ ፤ ተማማለ ›› ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲኾን ፣ ትርጕሙም ኪዳን፣ ውል ፣ መሐላ ፣ ቃል ኪዳን ፣ የውል ቃል ማለት ነው /ዘዳ.፳፱፥፩፤ ኤር.፴፩፥፴፩-፴፫፤ መዝ.፹ ፰፥፫/፡፡ በሌላ በኩል ኪዳን የጸሎት ስም ሲኾን፣ ጌታችን ሞትን ድል አድርጎ ከተነሣ በኋላ፣ ከማረጉ በፊት ለሐዋርያት ያስተማራቸው ጸሎት ኪዳን ይባላል፡፡

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ ከወዳጇ ከጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የምሕረት ቃል ኪዳን (ውል ፣ ስምምነት) የተቀበለችበት ዕለት (የክብረ በዓል ስም) ደግሞ ኪዳነ ምሕረት ይባላል፡፡

በየዓመቱ የካቲት ፲፮ ቀን የምናከብረው ይህ በዓል እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በጎልጎታ በልጇ በመቃብር ላይ ኾና ‹‹ ኦ ወልድየ ወፍቁርየ እስእለከ በእንተ ዘተሰባእከ እምኔየ ወበማኅፀንየ ዘጾረተከ፤ ልጄ ወዳጃ ሆይ ከሥጋዬ ሥጋ ፣ ከነፍሴ ነፍስ ነሥተህ ሰው ስለመኾንህ ፤ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ስለቻለችህ ማኅፀኔ ፤ ከአንተ ጋር ከአገር ወደ አገር ስለመሰደዴ መጥተህ ልመናዬን ትሰማኝ ዘንድ እለምንሃለሁ ›› እያለች ስትጸልይ ጌታ እልፍ አእላፍ መላእክቱን አስከትሎ ወደእርሷ መጥቶ ‹‹ ሰላም ለኪ ማርያም እምየ ፤ እናቴ ማርያም ሰላም ላንቺ ይኹን! እንዳደርግልሽ የምትለምኚኝ ምንድን ነው? ›› አላት፡፡

እመቤታችንም በስሟ የሚማጸኑትንና መታሰቢያዋን የሚያደርጉትን፣ ለችግረኛ የሚራሩትን፣ ቤተ ክርስቲያን የሚያንጹትን ፤ ዕጣን ዘይትና መብአ ለቤተ ክርስቲያን የሚሰጡትን ፤ ለእመቤታችንና ለሃይማኖታቸው ካላቸው ፍቅር የተነሣ ልጆቻቸውን በስሟ የሰየሙትን ዅሉ እንዲምርላትና ከሞተ ነፍስ እንዲያድንላት ጠየቀችው፡፡

ጌታችንም ‹‹ ይህን ዅሉ እንዳደርግልሽ መሐልኩ ለኪ በርእስየ ወበአቡየ ወበመንፈስ ቅዱስ ሕያው፤ በራሴ፣ በአባቴ እና በመንፈስ ቅዱስ ማልኩልሽ›› ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶላት ወደ ሰማይ ዐርጓል፡፡ ለዚህም ነው ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ በቅዳሴው ‹‹ … ዳግመኛም በእናትህ በማርያም ተማፅነናል፤ ይህችውም አንተን በመውለድ እመቤታችንና የባሕርያችን መመኪያ ናት፡፡ አንተ ‹ መታሰቢያሽን ያደረገ ፣ ስምሽንም የጠራ ፣ የዘለዓለም ድኅነትን ይድናል› ብለሃታልና …፤›› በማለት የሚማጸነው፡፡

በተአምረ ማርያም መጽሐፍ እንደተመዘገበው በዚህ ዕለት የሚታሰቡ ሁለት ተአምራት አሉ፤ ከእነዚህም አንደኛው የስምዖን ታሪክ ነው፡፡ ስምዖን የሚባል እንግዳ ተቀባይ ደግ ሰው ነበር፡፡ ሰይጣን ለምቀኝነት አያፍርምና ከዕለታት አንድ ቀን በእንግድነት ከቤቱ ገብቶ ‹‹ልጅህን አርደህ ካላበላኸኝ ሌላ ምግብ አልበላም›› አለው፡፡ በዚህ ጊዜ ስምዖን ሲያወጣና ሲያወርድ ቆየና ‹‹አብርሃም ልጁን ሰውቶ ነው የእግዚአብሔር ሰው የተባለው ›› በማለት፣ ‹‹ የእግዚአብሔርን እንግዳ›› ላለማሳዘን ሲል ልጁን አርዶ አቀረበለት፡፡

እንግዳ መሰሉ ሰይጣንም ሥጋውን ቅመስልኝ ብሎ ግድ አለው፡፡ ስምዖንም (በላዔ ሰብእ) አርዶ ያዘጋጀውን የልጁን ሥጋ በቀምሰ ጊዜ ሰይጣን ስላደረበት (ስለተዋሐደው) ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ቤተሰቦቹን፣ ጎረቤቶቹንና መንገደኛውን ዅሉ ይበላ ጀመር፡፡ በአጠቃላይ ፸፰ ሰዎችን ከበላ በኋላ አንድ በቍስል የተመታ ሰው አገኘና ሊበላው ሲል ‹‹ውኃ አጠጣኝ›› ብሎ በሥላሴ፣ በቅዱስ ሚካኤል፣ በቅዱስ ገብርኤል ስም ለመነው፤ እርሱም ዝም አለው፡፡

በመጨረሻም ‹‹ በድንግል ማርያም ስም ›› አለው፡፡ ስምዖን የእመቤታችንን ስም በሰማ ጊዜም ወደ ልቡናው ተመልሶ ‹‹እስኪ ቃሉን ድገመው ›› አለው ፤ በሽተኛውም መልሶ ‹‹ ስለ ድንግል ማርያም ውኃ አጠጣኝ›› ብሎ ለመነው፡፡ ያን ጊዜ ‹‹ይህችስ እንደምታስምር በልጅነቴ ሰምቻለሁ ›› ብሎ ጥቂት ውኃ ሰጠው ፤ ውኃው ጕሮሮውን እንኳን ሳያርስለት ‹‹ ጨረስህብኝ ›› ብሎ ነጥቆት ሔደ፡፡

በሌላ ቦታም አንድ ገበሬ አግኝቶ ሊበላ ሲል ገበሬው ‹‹በላዔ ሰብ የምትባል አንተ ነህ? ›› ባለው ጊዜ ‹‹ ለካስ አመሌን ሰው ዅሉ አውቆብኛል ›› ብሎ ዋሻ ገብቶ በመጸጸት በዚያው ሞተ፡፡ ነፍሱንም መላእክተ ጽልመት መጥተው ሲወስዷት እመቤታችን ‹‹ልጄ በማይታበል ቃልህ ይህችን ነፍስ ማርልኝ? ›› አለችው፡፡

ጌታችንም ‹‹ ሰባ ስምንት ነፍስ ያጠፋ፣ ፈጣሪውን የካደ ሰው ይማራልን? ›› አላት፡፡ እመቤታችንም ‹‹በስሜ የተጠማውን ውኃ አጥጥቶ የለምን?›› ብላ ስምዖንን (በላዔ ሰብእን) አስምራዋለች፡፡ ነፍሱንም መላእክተ ብርሃን መጥተው ወደ ገነት አስገብተዋታል፡፡

ሁለተኛው ተአምር ደግሞ ከብሮ ከኖረ በኋላ ለድህነት በተጋለጠ አንድ ምእመን ላይ የተደረገ ነው ፤ ከክርስቲያን ወገን የኾነ ሀብት አግኝቶ ያጣ አንድ ሰው ነበር፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን ‹‹ ከብሬ በኖርኹበት አገር ተዋርጄ አልኖርም ›› ብሎ ጓዙን ጠቅልሎ ከአገሩ ወጥቶ ሲሔድ ሰይጣን ያዘነ ሰው መስሎ ደንጊያውን በምትሐት ወርቅ አስመስሎ ‹‹ ሥላሴን ፣ ጻድቃንን ፣ ሰማዕታትንን ፣ መላእክትን ካድልኝና ይህን ወርቅ እሰጥሃለሁ ›› አለው፡፡ ዅሉንም ካደለትና ወርቁን ተቀብሎ ዞር ሲል ‹‹ ምእመናን የሚመኩባት ድንግል ማርያም ‹ የአምላክ እናት አይደለችም› ብለህ ካድልኝ ›› አለው፡፡

ሰወየውም ‹‹ እርሷንስ አልክድም ›› ስላው በደንጊያ ቀጥቅጦ ገደለው፡፡ መላእክተ ጽልመት የሟቹን ነፍስ ሊወስዱ ሲሉ መላእክተ ብርሃንም አብረው ቀረቡ፡፡ እመቤታችንም ጌታችንን ‹‹ ልጄ ይህችን ነፍስ ማርልኝ?›› አለችው፡፡ እርሱም ‹‹ከልብኑ ይትመሐር እምየ፤ እናቴ፣ ውሻ ይማራልን?›› አላት፡፡ እመቤታችንም፡- ‹‹‹ ስምሽን የጠራውን፣ መታሰቢያሽን ያደረገውን እምርልሻለሁ › ያልኸው ቃል ይታበላልን? ›› አለችው፡፡ በዚህ ጊዜ ‹‹ምሬልሻለሁ›› አላት፡፡

እግዚአብሔር አምላካችን ‹‹ ከመረጥኳቸው ጋር ቃል ኪዳን አደረግሁ ›› ባለው መሠረት ከቅዱሳን ጋር ያደረጋቸው ቃል ኪዳኖች ብዙዎች ናቸው፡፡ ከእነዚህም መካከል ከላይ በተአምራቱ እንደተመለከትነው አንዱ ለእመቤታችን የሰጠው የአማላጅነት ኪዳን ነው፡፡ ማማለድ ማለት ስለሌላው መጸለይ፣ መለመን ፣ የደረሰውን ችግር እንዲወገድ ማድረግ ፣ ማስማር ( ይቅርታ ማሰጠት ) ማለት ነው፡፡

በዚሁ መሠረት ከእግዚአብሔር በታች ከቅዱሳን ዅሉ በላይ ከፍ ከፍ ያለችና የከበረች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከእግዚአብሔር በተሰጣት የማማለድ ሥልጣን ‹‹ ሰአሊ ለነ ቅድስት ፤ ቅድስት ሆይ ለምኚልን ›› እያሉ ለሚለምኗት ዅሉ ከእግዚአብሔር እያማለደችና እየለመነች ምሕረትን እንደምታሰጥ ቀናውንና የተመሰገነውን ሃይማኖት የምንከተል ምእመናን ዅሉ እናምናለን፡፡ ምክንያቱም ቅድስት ድንግል ማርያም የእግዚአብሔር እናትና አገልጋይ እንደመኾኗ ከዅሉም ቅዱሳን በበለጠ ለእግዚአብሔር ቅርብ ናትና፡፡ በእግዚአብሔር ዘንድም ኾነ በሰው ዘንድ ባለሟልነትን ማግኘት ወይም ቅርብ መኾን ደግሞ አንድን ጉዳይ በቀላሉ ለማስፈጸም ይጠቅማል፡፡ ለምሳሌ፡-

👉 መልአኩ ቅዱስ ገብርአል በእግዚአብሔር ፊት የሚቆም ባለሟል በመኾኑ የድኅነትን ምሥጢር አብሣሪ ኾኗል /ሉቃ. ፩፥፲፱-፳፮/፡፡
👉 አስቴር የንጉሡ አርጤክስስ ሚስት በመኾኗ በወገኖቿ አይሁድ የታወጀውን የሞት አዋጅ አስለውጣለች /መጽሐፈ አስቴር ፫፥፲/፡፡
👉 ነቢዩ ሙሴ በእግዚአብሔር ፊት ባለሟል በመኾኑ ‹‹ይህንን ኀጢአታቸውን ይቅር በላቸው፤ ያለዚያ ግን እኔን ከጻፍከው መጽሐፍህ እባክህ ደምስሰኝ?›› በማለት ለእስራኤላውያን ምሕረትን አሰጥቷል /ዘፀ.፴፪፥፲፬/፡፡

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ሰሞኑን በማኅበራዊ ሚዲያ እየተዘዋወረ ስለሚገኘው "መነኩሴ"ነኝ ባይ ግለስብ በሀገረ ስብከቱ የማይታወቅ መሆኑን ሀገረ ስብከቱ ገለጸ።

የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰሞኑን በማኅበራዊ ድረ ገጾች ራሱን "መነኩሴ"በማስመሰልና በአርሲ ሀገረ ስብከት አገልጋይ እንደሆነ በመግለጽ የሚንቀሳቀሰውን ግለሰብ የማያውቀውና ሐሰተኛ "መነኩሴ" መሆኑን ለጠቅላይ ቤተክህነት በጻፈው ደብዳቤ አስታወቀ።

ከየካቲት 12/20916 ዓ.ም ጀምሮ በማኀበራዊ ሚዲያ እየተዘዋወረ የሚገኘው ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ተችቶ የማስተቸት ድራማዊ ትዕይንት ላይ የቀረበው አስመሳይ "መነኩሴ"ግለሰብ በሀገረ ስብከታችን በተለይ በአሰላ ከተማ በቅዳሴ መምህርነት በስብከተ ወንጌል እንዳገለ በማስመሰል በሰጠው የሀሰት ምስክርነትን በተመለከተ እውነተኛ ምላሽ መስጠት ማስፈለጉን የጠቀሰው ሀገረ ስብከቱ"መንኩሴ "መሳዩ ግለሱብ በሀገረ ስብከቱ በየተኛውም የከተማና የገጠር ገዳማትና አድባራት የማይታወቅና ምንም ዓይነት አገልግሎት ሲሰጥ ያልነበረ መሆኑን ገልጿል።

በተጨማሪ በሀገረ ስብከቱ የሚገኙት ሁሉንም አገልጋዮች የሚታወቁና የተመዘገቡ መሆኑን የጠቀሰው ሀገረ ስብከቱ ግለሰቡ በሀገረ ስብከቱ ካሉት አገልጋች መካከል የማይታወቅና ያልተመዘገበ ከመሆኑም በላይ ሀገረ ስብከቱ በፍጹም የማያውቀው ቀሳጢ ነው በማለት ሐሰተኛ ማንነትን በመላበስ የቤተክርስቲያንን ስም ለማጠልሸተ የተሰማራ መሆኑን ገልጿል።

ስለሆነም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ግለሰቡ የቤተ ክርስቲያናችንን ዓርማ ወይም አልባሳት በመልበስና የሀገረ ስብከታችንን መልካም ገጽታ በማጉደፉ ግለሰቡንና እዩ ጩፋ የተባለውን አጽራረ ቤተ ክርስቲያን በህግ እንዲጠይቅን ስንል በታላቅ አክብሮት እናሳስባለን፤በማለት ለጠቅላይ ጽሕፈት ቤቱ በጻፈው ደብዳቤ ጨምሮ ገልጿል።

ምንጭ: የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​"4 ተገድለው 1 ጠፍተዋል፤ ገዳሙን እና እኛን ለማዳን እነሱ ተሰው፤ የእኛንም በደል እነሱ ከፈሉ"
የደብረ ከዋክብት ዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም አባቶች
++++++++++++++++++++++++++++++

የገዳሙን መጋቤ እና ዋና ጸሐፊ ጨምሮ የደብረ ከዋክብት ዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም 4 መነኮሳት በታጣቂ ኃይሎች መገደላቸውን ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን የደረሰው መረጃ ያመላክታል።

ከገዳሙ በስልክ ያገኘነው መረጃ እንደሚያሳየው የካቲት 12/2016 ዓ.ም የታጠቁ ሰዎች ወደ ገዳሙ በመግባት ሁለት መነኮሳት መውሰዳቸውን እነሱ ይመለሳሉ ብለው ሲጠብቁ በማግስቱ የካቲት 13/2016 ዓ.ም ታጣቂዎቹ ድጋሚ መጥተው ለውይይት እንፈልጋችኋለን በማለት 3 መነኮሳትን ወደ "ጂዳ ተክለ ሃይማኖት" ወስደዋል ብለዋል።

መነኮሳቱ "ለውይይት" ሲባሉም "ችግር የለውም እናንተ አባቶች እዚህ ቆዩ እኛ አነጋግረናቸው እንመጣለን፤ ተረጋጉ" ብለው ታጣቂዎቹን ተከትለው ከገዳሙ ሂደዋል።

ቀኑን ሙሉ ስልካቸው ክፍት እንደነበረ አመሻሽ ማግኘት ባለመቻላቸው ተጨንቀው የአካባቢውን ምእመናን ሲያጠያይቁ 4ቱ መገደላቸውን እንደነገሯቸው አንደኛው አባት ግን ተለቀዋል ቢባልም እስካሁን ያሉበት እንዳልታወቀ አባቶቹ ለጣቢያችን በእንባ ተናግረዋል።

በታጣቂዎቹ የተገደሉት አባቶች

፩ አባ ተክለ ማርያም አሥራት (የገዳሙ መጋቤ)

፪ አባ ኪዳነ ማርያም ጥላሁን (የገዳሙ ዋና ጸሐፊ)

፫ አባ ገብረ ማርያም አበበ (ቀዳሽ ካህን፣የመጽሐፍ መምህርና የገዳሙ አስተዳደር አባል)

፬ ባህታዊ ኃ/ማርያም ስሜ (የገዳሙ የአስተዳደር አባል)
ሲሆኑ
እስካሁን ያሉበት ያልታወቀው ደግሞ አባ ኪዳነ ማርያም ገ/ሰንበት ናቸው።

ገዳሙ በተደጋጋሚ በታጠቁ ሰዎች ዐይነተ ብዙ ጥቃት እንደሚደርስበት ነገር ግን መፍትሔ እንዳላገኙ በመግለጽ የአሁኑ ጥቃት ግን በቃላት የማይገለጽ ነው ብለዋል።

"ገዳሙን እና እኛን ለማዳን እነሱ ተሰው፤ የእኛንም በደል እነሱ ከፈሉ፤ ጻድቁን አገልግዬ እዚሁ አርፋለሁ ሲሉ ደመ ከልብ ሆነው ዐፈራቸውንም ሳይቀምሱ ቀርተዋል" ሲሉም መረጃ የሰጡን አባቶች በከፍተኛ ሐዘን ገልጸዋል።

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

😥ምን ያስጨንቀናል?😞

እንኳን ደስ አላችሁ የሥነ ልቡና የምክክር አገልግሎታችንን በአዲሱ ቢሮአችን በአዲስ መልኩ ጀምረናል።

የምንሰጣቸው አገልግሎት፦
👉ድብርት/ድባቴ (Depression)
👉ብቸኝነት(Loneliness)
👉የመኖር ጣዕም እና አላማን ማጣት(Purpose and meaning of life)
👉የተለያዩ የሱስ ፈተናዎች (Drug addictions)
👉የትዳር የምክክር አገልግሎት (Married therapy)
👉እራስን የማጥፋት ሐሳቦች(Suicidal thoughts)
👉ልበ-ሙሉነትን እንዴት ማምጣት እንችላለን (self-confidence)
👉የልጅነት መጥፎ ጠባሳ/ክስተት(Trauma)
👉ጭንቀት(Anxiety)
👉የማንነትን ቀውስ(Identity crisis)
እና ሌሎች የሚያስጨንቁንን ነገሮች ሁሉ በዓለማዊው እና መንፈሳዊ መንገድ የምክክር አገልግሎት የምንሰጥ ሲሆን። ከታች ባለው ስልክ ቁጥር በመደወል ወይም በቴሌግራም አካውንት ቴክስት በመላክ ቀድመው ቀጠሮ ማስያዝ ይችላሉ።

📍ቢሮአችን አዲስ አበባ ፒያሳ Downtown ሕንጻ(ፒያሳ የገበያ ማዕከል) ላይ

☎️ 0912085085 ዲያቆን ዳግማዊ ሰለሞን (Certified psychiatrist from yale,Sydney and Harvard University)

Telegram account- @Orthodoxtewahed0

ይደውሉ ይመዝገቡ የምክክር አገልግሎቱን ያግኙ።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

 
አድዋን ያለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መዘከር የሚፈልግ ትውልድ መጣ፡፡ አድዋ ነጻነት ነው፤ አድዋ የሰው ልጆች የከፍታ፣ የእኩልነት ምልክት ነው፤ አድዋ የአሸናፊዎች ዓርማ ነው፡፡ አድዋ አንድነት የታየበት፣ የመለያየት ግንብ የፈረሰበት፣ ንጉሥ ከሠራዊቱ፣ ካህናት ከታቦቱ፣ ሳይለዩ በጋራ ለነጻነት የተሰለፉበት፣ የብርቱዎች ሰልፍ ነው፡፡ ነገር ግን አሁን የአድዋ ባለቤቶች ተገፍተዋል፤ ለፍላጎታቸው ባሪያ የሆኑ በተሸናፊው ጣሊያን ሐሳብ የተማረኩ፣ ኢትዮጵያዊ ሳሉ በግብራቸው ጣሊያናዊ የሆኑ አሸናፊዎቹን ሲሳደቡ የማይደነግጡ አንደበታቸው ያልተገራ፣ ውኃ የሌለባቸው ጉድጎዶች፣ ዝናብ አልባ ደመናዎች ዛሬ አገሩን ሞልተውታል፡፡
 
ታሪክ መሥራት አቀበት የሆነባቸው ታሪክንና ባለ ታሪኮችን የሚያዋርዱ፣ የድሉ  መሐንዲስ፣ የጦሩ ፊታውራሪዎችን የሚያናንቁ፣ ድንቁርናቸው በሱፍና በከራባት የተሸፈነ ብዙዎች ዛሬ የአድዋ ባለውለታዎችን ያራክሳሉ፤ ቤተ ክርስቲያንንም ከአድዋ ነጥለውና ውለታዋን አቃለው ይናገራሉ፡፡ አይችሉም እንጂ ክብሯን ለመዳፈር፤ ልዕልናዋን ለዋረድ ይመረምራሉ፤ ‹‹ወርቅ ላበደረ ጠጠር እህል ላበደረ አፈር›› የሚሉት ብሂል ዛሬ በቤተ ክርስቲያን ላይ ተፈጽሟል፡፡ ቤተ ክርስቲያንን ከአድዋ ለመነጠል ጥረት ተደርጓል፡፡
 
በጥቅሉ አድዋን ያለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ማክበር ማለት ይህ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን አርበኞቿን አስተባብራ ባዕዳንን አሸንፋ ጠማማ ልጆቿን ማሸንፍ ተስኗታል፡፡ የሀገር አንድነትን የጠበቀች በአንድነት መቆም ርቋታል፡፡ ቁሳዊ ፍላጎቱን ያሸነፈ፣ ለእግሩ ጫማ ለሰውነቱ ሸማ የማይጨነቅ፣ ለሀገርና ለሃይማኖት ቅድሚያ የሚሰጥ ማኅበረሰብ የፈጠረች ቤተ ክርስቲያን ዛሬ የቁስ ፍላጎታቸው ጦር ሆኖ የሚወጋቸው አገልጋዮች ሞልተዋታል፡፡ ይህም ለታሪካዊ ጠላቶቿ በቀል በር የከፈተባት ትልቁ ክፈተት ነው፡፡
 
አድዋ አንድነት ነው፤ አድዋ እኩልነት ነው፤ አድዋ ነጻነት ነው፡፡ አድዋ የድሉ ባለቤቶችን መዘከር ነው፡፡ እነዚህን ዘንግቶ፣ የድሉ ፊታውራራዎችን በማንኳሰስ፣ የቤተ ክርስቲያንንም ሚና በመዘንጋት የሚከበር የአድዋ በዓል ትርጉም አልባና ታሪክን የማጥፋት ሴራ ነው፡፡   

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

አድዋን ያለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ማሰብ ትርጉም አልባ ነው!
 
የየካቲት ወር በኢትዮጵያውያን ዘንድ በብዙ መልኩ የሚታሰብ ወር ነው፡፡ ከአድዋ ድልና “ከሰማዕታት” መታሰቢያ በዓላት ጋር ተያይዞ አዎንታዊም አሉታዊም ስሜቶች እየተፈራረቁባቸው  የሚያሳልፉ ብዙዎች ናቸው፡፡ አድዋ የካቲት ፳፫ ቀን ፲፰፻፹፰ ዓ.ም  በአድዋ ተራራ ላይ ጥቁር ሕዝቦች ለመጀመሪያ ጊዜ የማይቻል የሚመስለውን የቻሉበት፣ አይሆንም የተባለው የሆነበት፣ “ነጮች” “በጥቁሮች” የተሸነፉበት፣ ታላቅ ሁነት የተፈጸመበት፣ የድል በዓል መታሰቢያ ሲሆን  የካቲት ፲፪ ቀን ፲፻፳፱ ደግሞ በኢትዮጵያውያን ዘንድ የማይረሳ ሌላኛው ዕለት ነው፡፡ እርሱም ጣሊያን ከ፴ ሺህ የሚበልጡ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን በግፍ የጨፈጨፈበት መታሰቢያ በመሆኑ ነው፡፡
 
በዚህ ጽሑፍ ልናየው የወደድነው ግን የአድዋን የድል ታሪክና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ምን ያገናኛቸዋል? የሚለውን ነው፡፡ የአድዋን ድል ልዩ ያደረገው አንድ ሕዝብ በጦር ሜዳ ተዋግቶ ያሸነፈበት ታሪክ ስለ ሆነ ብቻ ሳይሆን በዘመኑ ዓለምን የተቆጣጠረውን “ጥቁር ሕዝብ ተፈጥሮውም፣ ኑሮውም ነጭን ለማሸነፍ አያስችለውም” የሚልና እንኳን ገዥዎችን ተገዥዎችንም ጭምር አሳምኖ የነበረ አስተሳሰብን የሻረ በመሆኑ ነው፡፡ ሁለት ለንጽጽር የማይገቡና ያልተመጣጠነ አሰላለፍ የነበራቸው ሕዝቦችና መንግሥታት ተዋግተው እንደ ጎልያድ በሰይፍ የመጣው ሳይሆን እንደ ዳዊት በእምነት ጠጠር የወነጨፈው ያሸነፈበት የማይታመን እውነታ በመሆኑም ነው፡፡

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🌺 ሰላም፡ለኵልክሙ። እነሆ የምስራች ግእዝን በዐቢይ ጾም በሚል ልዩ ዝግጅት የግእዝ ቋንቋን ኮርስ ለመስጠት ምዝገባ ጀመርን።

📜 እርስዎም ግእዝ ቋንቋን ቀለል ባለና ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅታችንን አጠናቀናል ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመመዝገብ ጥንታዊና ውዱ ቋንቋችንን እናጥና ፥ ዕንወቅ።

📖 ትምህርቱን ከ14 ዓመት ዕድሜ በላይ የሆነ ማንኛውም ሰው ፤  ስልክ፣ ላፕቶፕ ወይም ዴስክቶፕ በመጠቀም መማር ይቻላል።

✅ ምዝገባውን ለማካሄድ በዚህ ውስጥ ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር በመላክ የመማማሪያ ቦታዎችን መቀበል ነው ✅
@Geez202
@Geez202
@Geez202 👈
                

⛳️ ለበለጠ መረጃ በምዝገባው ይደርስዎታል። ጥያቄ ሲኖር ከታች በተቀመጠው በስልክ ያግኙን። ሠናይ፡ጊዜ።

🗣 ለሌሎችም ሼር በማድረግ እንድናዳርስ በአክብሮት እንጠይቃለን
🌺 መሠረተ፡ግእዝ 🌺
@MesereteGeez - 0918026533

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ማኅበረ ቅዱሳን ከቤተ ክርስቲያን ህልውና በላይ የሚያስቀድመው አንዳች ነገር የሌለ በመሆኑ ቤተ ክርስቲያናችን የገጠማትን ፈተና ለማለፍ የሚጠበቅበትን መንፈሳዊ ግዴታ ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ዛሬ የካቲት 19/2016 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።

ማኅበሩ በመግለጫው የብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትን መንፈሳዊ አንድነት የጠየቀ ሲሆን "ቤተ ክርስቲያንን በማይጠቅማት ጉዳይ የግል ፍላጎትንና ምድራዊ ዓላማን መሠረት አድርገው ከቤተ ክርስቲያን ሕግና ቀኖና ውጭ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊን ለመተካት፣ ፓትርያርክ ለመሾምና የመሳሰሉትን ለመፈጸም" የሚንቀሳቀሱ ያላቸውን "አንዳንድ አባቶች" ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ በማሳሰብ ጉዳዩንም በመከታተል መረጃውን ለምእመናን አደርሳለሁ ብሏል።፡፡

ይመለከታቸዋል ላላቸው ሌሎች የቤተ ክርስቲያን አካለትም ጥሪውን አስተላልፏል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🌺 ሰላም፡ለኵልክሙ። እነሆ የምስራች ግእዝን በዐቢይ ጾም በሚል ልዩ ዝግጅት የግእዝ ቋንቋን ኮርስ ለመስጠት ምዝገባ ጀመርን።

📜 እርስዎም ግእዝ ቋንቋን ቀለል ባለና ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅታችንን አጠናቀናል ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመመዝገብ ጥንታዊና ውዱ ቋንቋችንን እናጥና ፥ ዕንወቅ።

📖 ትምህርቱን ከ14 ዓመት ዕድሜ በላይ የሆነ ማንኛውም ሰው ፤  ስልክ፣ ላፕቶፕ ወይም ዴስክቶፕ በመጠቀም መማር ይቻላል።

✅ ምዝገባውን ለማካሄድ በዚህ ውስጥ ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር በመላክ የመማማሪያ ቦታዎችን መቀበል ነው ✅
@Geez202
@Geez202
@Geez202 👈
                

⛳️ ለበለጠ መረጃ በምዝገባው ይደርስዎታል። ጥያቄ ሲኖር ከታች በተቀመጠው በስልክ ያግኙን። ሠናይ፡ጊዜ።

🗣 ለሌሎችም ሼር በማድረግ እንድናዳርስ በአክብሮት እንጠይቃለን
🌺 መሠረተ፡ግእዝ 🌺
@MesereteGeez - 0918026533

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

#ተው_ዓለም_ተመለስ

ተው ዓለም ተመለስ ተው ዓለም ተገታ
ተው ዓለም ተመለስ ተው ዓለም ተገታ
በቁጣ መዓቱ ይቀጣሃል ጌታ ይቀጣሃል ጌታ

ትውልዱ ተመታ በታላቅ በሽታ /፪/
ኧረ በልክ ይሁን ጭፈራና ደስታ /፪/
በማዕበል በጎርፍ እያየህ ሲቀጣ/፪/
አሁንም ተመለስ የከፋ ሳይመጣ /፪/
#አዝ
ነነዌን ሊያጠፋ የወረደው እሣት /፪/
አንተን እዳይመታህ ተነሳ ለጸሎት/፪/
ዓለም ብትሰጥኽ አንተ እድትተጋ /፪/
ሀልወተ እግዚአብሔር እንደምን ይዘንጋ
#አዝ
ችግር ለበዛበት እጅግ ለታወከው/፪/
አምላክ መሐሪ ነው ለተንበረከከው/፪/
የዓለም መድሐኒት የዓለሙን ቤዛ /፪/
ጠይቀው ምሕረትን ሠው ሆይ ልብ ግዛ
#አዝ
ተው ዓለም ተመለስ ተው ዓለም ተገታ
ተው ዓለም ተመለስ ተው ዓለም ተገታ
በቁጣ መዓቱ ይቀጥሃል ጌታ ይቀጣሃል ጌታ።

ሊቀ መዘምራን
ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

So he prayed to the LORD, and said, “Ah, Lord, was not this what I said when I was still in my country? Therefore, I fled previously to Tarshish; for I know that You are a gracious and merciful God, slow to anger and abundant in lovingkindness, one who relents from doing harm. Therefore, now, O Lord, please take my life from me, for it is better for me to die than to live!” Then the Lord said, “Is it right for you to be angry?”

So Jonah went out of the city and sat on the east side of the city. There he made himself a shelter and sat under it in the shade, till he might see what would become of the city. And the Lord God prepared a plant and made it come up over Jonah, that it might be shade for his head to deliver him from his misery. So Jonah was very grateful for the plant. But as morning dawned the next day God prepared a worm, and it so damaged the plant that it withered. And it happened, when the sun arose, that God prepared a vehement east wind; and the sun beat on Jonah’s head, so that he grew faint. Then he wished death for himself, and said, it is better for me to die than to live.” Then God said to Jonah, “Is it right for you to be angry about the plant?” And he said, “It is right for me to be angry, even to death!” But the Lord said, “You have had pity on the plant for which you have not labored, nor made it grow, which came up in a night and perished in a night. And should I not pity Nineveh, that great city, in which are more than one hundred and twenty thousand persons who cannot discern between their right hand and their left and much livestock? (Jonah 4:1-11)

This section of the Book of Jonah illustrates about God’s mercy for all who are created in Holy Trinity’s image and likeness. The Lord of mercy God forgave the people of Nineveh who sinned drastically only by the three days fast. Thus, we shall be reminded and commemorate throughout this fast, the truth about the Holy Son coming down from the heavens, who lowered His character, wear the flesh of man, ambulated like humans, endure suffering and pain, crucified and rose up on the third day, for we could be given life and inherit the kingdom of heaven.

May God hear our prayer, receive our pleading and fasting for He have mercy on us, Amen!

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

The Three Days Fast

The number three in the Doctrine of Holy Church has many interpretations as scriptures states. The foremost to be mentioned is the Threeness of Holy Trinity. “The Holy Father, The Holy Son, The Holy Spirit are three in name, in deed and in person.” Holy Spirit’s ascension time upon the Saint Apostles on Sunday is three as well. Our Lord and Savior Jesus Christ was conceived at three o’clock for His coming down from the heavens to redeem the world. In relation to this, Holy Mother Saint Mary was told the good news by Archangel Saint Gabriel at the same hour.

When our Lord was born, the three wise men who came to present gift to the Born King, gold, frankincense and myrrh are three in numbers. (Matthew 2:12) The Book of Miraculous of Mary tells us about the Lord’s disappearance in His 12 age, and his mother Saint Mary and Joseph searching in for Him for three days.

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ነነዌን ሊያቃጥል

ነነዌን ሊያቃጥል የወረደው እሳት (፪)
ተመልሶ ዐረገ(፪) በሀዘን በጸሎት (፪)
ስለሆነ ከልብ የሀዘናቸው ምንጩ (፪)
ነበር እንደ ራሔል (፪)እንባን እየረጩ (፪)
ለነነዌ ሰዎች ደስታን ያበሰረ (፪)
ጋሻ እና ጦራቸው(፪)ጾም ጸሎት ነበረ (፪)
እንኳን የሰው ልጆች እንስሳት ሳይቀሩ(፪)
በዮናስ ስብከት (፪)ፆም ጸሎት ተማሩ(፪)

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

3ኛ፡- በመንግሥትና በሀገረ ስብከቱ እንዲሁም በቤተክርስቲያን አባቶች ልባቸው የተሠበረና የተጎዱ የገዳሙ አባቶችና እናቶችን በጋራ ማጽናናት እንዲችል፡፡

የውይይቱ የውሳኔ ሃሳቦች ሲሆኑ ይኼው ግብረ ኃይል ከሀዘኑ በኋላ ዳግም ተገናኝቶ በተሠሩ ሥራዎችና ወደ ፊት አስተማማኝ ሰላም በሚሠፍንበት ጉዳይ ላይ ለመመካከር ቀጠሮ ተይዞ በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዕለቱ ውይይት በጸሎት ተዘግቷል፡፡

ዘገባው የሀገረ ስብከቱ ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ ነው

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​ስለዚህ የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትም እንደ ፀሐይ የበራ ሐቅ ነው፡፡ ይህንን እውነት ቅዱስ ያሬድ ሲመሰክር፡- ‹‹ ወታስተሠርዪ ኀጢአተ ሕዝብኪ ተበውሀ ለኪ እምአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ወከመ ትኩኒ ተንከተመ ለውሉደ ሰብእ ለሕይወት ዘለዓለም ፤ ለሕዝብሽ ፣ ለወገኖችሽ የኃጢአት ይቅርታን ታሰጪ ዘንድ ፤ ዘለዓለማዊ ሕይወትንም ለሚወርሱ ዅሉ መሸጋገሪያ ድልድይ ትኾኚ ዘንድ ከአብ ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ሥልጣን አግኝተሻል ›› በማለት አመስግኗታል /አንቀጸ ብርሃን/፡፡

አባ ጽጌ ድንግልም በማኅሌተ ጽጌ ድርሰታቸው፡- ‹‹ ሶበሰ ኪዳንኪ ምክንያተ ድኂን ኢሀሎ ፈለገ እሳት ወደይን እም አሰጠመ ኩሎ ፤ የድኅነት ምክንያት ቃል ኪዳንሽ ባይኖር ኖሮ የጥፋት እሳት፣ መርገም ( ኀጢአት ) ባጠፋን ነበር ›› ብለዋል፡፡ አባ ሕርያቆስም በቅዳሴው፡– ‹‹ ጥፋትን ያይደለ ይቅርታን አሳስቢ፡፡ መዓትን ያይደለ ምሕረትን አሳስቢ፡፡ ለጻድቃን ያይደለ ለኀጥአን አሳስቢ፡፡ ለንጹሐን ያይደለ ለተዳደፉት አሶስቢ፤ ›› ሲሉ ይማጸኗታል /ቅዳሴ ማርያም ቍ.፻፷፭-፻፸፩/፡፡

ስለዚህም ዘወትር በሥርዓተ ቅደሴአችን፡- ‹‹ ድኅነትን የምንለምንሽ ክብርን የተመላሽ ቅድስት ሆይ ደስ ይበልሽ፡፡ ዅል ጊዜ ድንግል የምትኾኚ አምላክን የወለድነሽ የክርስቶስ እናት ሆይ ኀጢአታችንን ያስተሠርይልን ዘንድ ወደ ልጅሽ ወደ ወዳጅሽ ወደ ላይ ጸሎታችንን አሰርጊልን፡፡

በእውነት የጽድቅ ብርሃን የሚሆን አምላካችንን ክርስቶስን የወለድሽልን ንጽሕት ሆይ ደስ ይበልሽ፡፡ ንጽሕት ድንግል ሆይ ለነፍሳችን ይቅርታን ያደርግ ዘንድ ፤ ኀጢአታችንንም ያስተሠርይልን ዘንድ ወደ ጌታችን ለምኚልን፡፡ በእውነት ለሰው ወገን አማላጅ የምትሆኝ አምላክን የወለድሽ ንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ፡፡

የኀጢአታችንን ሥርየት ይሰጠን ዘንድ በልጅሽ በክርስቶስ ፊት ለምኝልን፡፡ በእውነት ንግሥት የምትኾኚ ንጽሕት ድንግል ሆይ ደስ ይበልሽ፡፡ የባሕርያችን መመኪያ ሆይ ደስ ይበልሽ፡፡ አምላካችን አማኑኤልን የወለድሽልን ሆይ ደስ ይበልሽ፡፡ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፊት እውነተኛ አስታራቂ ሆነሽ ታስቢን ዘንድ እንለምንሻለን፡፡

ለነፍሳችን ይቅርታን ያደርግልን ዘንድ ኀጢአታችንንም ያስተሰርይልን ዘንድ፤ ›› በማለት እመቤታችንን እንማጸናታለን፡፡

በአጠቃላይ ‹‹ ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ፤ ከመረጥኋቸው ጋር ቃል ኪዳን አደረግሁ፤ ›› በማለት በነቢዩ ቅዱስ ዳዊት አድሮ ራሱ እግዚአብሔር ከመረጣቸው አበው ነቢያት፣ ጻድቃን ፣ ቅዱሳንና ሰማዕታት ጋር ቃል ኪዳን እንደ ገባ ፣ እንደሚገባ ተናግሯል /መዝ.፹፰፥፫/፡፡

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ‹‹ እንግዲህ እርሱ ራሱ ካጸደቀ እግዚአብሔር የመረጣቸውን ሰዎች የሚቃወማቸው ማን ነው? ›› በማለት እግዚአብሔር ሰዎችን እንደሚጠራ ፣ እንደሚያከብር ፣ እንደሚቀድስና ቃል ኪዳን እንደሚሰጥ ነግሮናል /ሮሜ.፰፥፴፫/፡፡ ቅዱስ ዳዊት ‹‹ ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ሀገረ እግዚአብሔር ፤ የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ ስለ አንቺ የተነገረው ነገር ድንቅ ነው፤ ›› /መዝ.፹፮፥፫/ በማለት እንደተናገረው እግዚአብሔር አምላካችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የገባው ቃል ኪዳን ከቅዱሳን ቃል ኪዳን ዅሉ ልዩ ነው፡፡ ይህም እንደምን ነው ቢሉ፡-

👉 ለአምላክ እናትነት የተመረጠች ልዩ እናት በመኾኗ፤
👉 አምላክ ከሥጋዋ ሥጋ፣ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ከእርሷ በመወለዱ፤
👉 ከመለለዷ በፊት፣ በወለደች ጊዜ፣ ከወለደች በኋላ ምን ጊዜም ድንግል በመኾኗ፤
👉 በሁለቱም ወገን (በአሳብም በገቢርም) ድንግል በመኾኗ፤
👉 አማላጅነቷ የወዳጅነት ሳይኾን የእናትነት በመኾኑ፤
👉 ዓለም ይድን ዘንድ የድኅነት ምክንያት አድርጎ አምላክ ስለመረጣት ነው፡፡

ስለዚህ ብዙ ከንቱ አሳቦችን ትተን፣ እንደበላዔ ሰብእ በቃል ኪዳኗ ተጠቅመን፣ ንስሐ ገብተን፣ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ተቀብለን፣ የስሙ ቀዳሽ፣ የመንግሥቱ ወራሽ ለመኾን ያብቃን፡፡ የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን አማላጅነት፣ የቅዱሳን ተራዳዒነት አይለየን፡፡

✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞
💚
@ortodoxmezmur 💚
💛
@ortodoxmezmur 💛
❤️
@ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

#ኪዳነ_ምህረት_ልዩ_ነሽ_ለኔ

ኪዳነ ምህረት ልዩ ነሽ ለኔ
ሳዝን ስጨነቅ አትራቂኝ ከጎኔ
የችግሬ ደራሽ እመ እግዚአብሔር
ቃል ኪዳንሽ ይርዳኝ ካንቺ ጋር ልኑር(፪)
#አዝ
የአዳም ተስፋው ነሽ የሴት ቸርነቱ
ኪዳነምህረት ነሽ የኖህ ምልክቱ
አዳም ደጅ የጠናሽ ሲገባ ንስሀ
ኖህም ድኖብሻል ከጥፋቱ ውሃ
#አዝ
የአብርሃም ድንኳን ነሽ የሙሴ ፅላቱ
ማርያም አንቺ ነሽ የፈጣሪ እናቱ
የእስራኤል መሰላል የሴም እጣ ክፍሉ
እመብርሃን ስሚኝ ልመናየን ሁሉ
#አዝ
የሰሎሞን አክሊል የዳዊት ዝማሬ
ድንግል መሆንሽን ትመስክር ከንፈሬ
ለተጠማው ውሻ የሚራራው ልብሽ
ለኔም እራርቶልኝ አስታርቂኝ ከልጅሽ
#አዝ
የአብርሃም ድንኳን ነሽ የሙሴ ፅላቱ
ማርያም አንች ነሽ የፈጣሪ እናቱ
የእስራኤል መሰላል የሴም እጣ ክፍሉ
እመብርሃን ስሚኝ ልመናዬን ሁሉ

ዘማሪት ሲስተር ፋሲካ መኮንን
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
የተላለፈ ወቅታዊ መልዕክት።


ጥንታዊት፣ ታሪካዊት፣ ብሔራዊትና ዓለም አቀፋዊት በሆነችው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥር ከሚገኙት ጥንታዊያን ገዳማት መካከል ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም አንዱና ዋነኛው መሆኑ ይታወቃል።

ይህ ጥንታዊና ታሪካዊ ገዳም በርካታ ቅርሶችና መናንያን የሚገኙበት ገዳም ሲሆን በተለያዩ ጊዜያት በተከሰተበት ዘረፋና ቃጠሎ ከባድ ጉዳቶችን ያስተናገደ መሆኑም ይታወሳል።

በዛሬው ዕለት ከሀገረ ስብከቱ በደረሰን መረጃ መሰረትም፦
1. የገዳሙ መጋቢ አባተክለማርያም ዐሥራት
2. የገዳሙ ጸሐፊ አባ ኪዳነ ማርያም ጥላሁን
3. የገዳሙ የመጽሐፍ መምህርና ቀዳሽ አባ ገ/ማርያም አበበ
4. በአመክሮ የሚኖሩ መናኝ ኃይለማርያም ወልደሰንበት
የካቲት 12 ቀን "ኦነግ ሸኔ" በተባለው ታጣቂ ቡድን ከተወሰዱ በኋላ አራቱም በትላንትናው አለት የተገደሉ ሲሆን አባ ኪዳነማርያም ገ/ሰንበት የተባሉት አባት ቆስለው በገዳሙ እንደሚገኙ ታውቋል።

በአሁኑ ሰዓትም ታጣቂዎቹ ወደ ገዳሙ ለመግባት እንቅስቃሴ የሚያደርጉበት መንገድ እንዳይኖርና መናንያኑና የገዳሙ ቅርስ አደጋ ላይ እንዳይወድቁ የፌዴራልና የክልሉ የጸጥታ አካላት ገዳማዊያኑንና ገዳሙን የመታደግ ሥራ እንዲሠሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከአደራ ጭምር መልዕክቷን ታስተላልፋለች።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት
የካቲት ፲፬ቀኝ ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

የደብረ ከዋክብት ዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም 4 መነኮሳት በታጣቂ ኃይሎች መገደላቸው ተሰምቷል።

ዝርዝሩን እንደደረሰን እናቀርባለን ።

Читать полностью…
Подписаться на канал