ortodoxmezmur | Неотсортированное

Telegram-канал ortodoxmezmur - ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

134932

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . ዝማሬ ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Подписаться на канал

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ቅዳሴ ክፍል 76 ተለማመዱት።


✝እስከ አሁን ግን ስለ ቅዳሴ ትምህርቱ ምንም አይነት ሐሳብ አልሰጣችሁንም። እየተለማመዳችሁት ነው? ✝

ምን ላይ ደረሳችሁ እስኪ አሳውቁን

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ድንግል ማርያም ሆይ ኢትዮጵያሽን አስቢያት😭

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

እግዚአብሔር አምላክ ማስተዋሉን ያድለን።
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​VALENTINE'S DAY
ሼር በማድረግ ትውልዱን ከጥፋት እንታደግ❗

አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኛ ቤዛ ሆኖ በፍቅሩ የገዛን እጃችንን ለጣኦት እንድንሰጥ አይደለም ብዙ ዋጋ የተከፈለብን እስከ ሞት እንከን በሌለው ፍቅሩ የወደደን መንግስቱን እንድንወርስ እንጂ እንድንጠፋ አይደለም።

የቫላንታይ ቀን ድብቅ እውነታ ስንቶቻችን እናውቃለን? ይህን የቫላታይን ቀን (የፍቅረኛሞች ቀን) ብለን ስንቶቻችን ነን የምናከብረው ? ወይስ ሰው ስላከበረውና የስልጣኔ መገለጫ መስሎን ነው የምናከብረው ???

ከክርስቶስ ልደት በፊት በባቢሎን ፤ቤልዘቡል ፤በግሪክ ፓን ፤ ሮማ ሞሎቅ ፤ በላቲን ሳተርን ለሚባሉት ሰይጣኖች ያላገቡ ሴቶች ደም የሚፈስላቸው ቀይ ልብስ የሚለበስላቸው ጣኦቶች ናቸው ይህ ዛሬ ቫለንታይን ተብሎ የመጣው ማለት ነው።

የሚገርመው ደሞ ሴቶቹ በዚህ ቀን ለመደፈር ብለው እራቁታቸውን ጫካ መግባታቸው ነው በዚህ ቀን የተደፈረች እና ደሟን ያፈሰሰች ሴትም ሆነ ወንድ በጣኦቱ የተመረጠ እና የተባረከ ነው መባሉ ነው ይበልጥ ነገሩን ሰይጣናዊ የሚያደርገው።

ግሪክ አርኬዲያ ብለው በሚጠሩት አስቀያሚ ትርጉም ባለው ተራራቸው ላይ በዚህ ቀን ላይ ነው ያላገቡ ወንድ እና ሴቶቻቸውን ጣኦቱ ስር ወሲብ በመፈጸም ገላቸውን አርክሰው ለሰይጣን የሚገብሩት።

ይህ የሰይጣን ቀን ነው ክርስትና ይሄን ትከለክላለች ታወግዛለች። (ሁሉም ቀን የእግዚአብሔር ነው ግብሩ ነው የሰይጣን የሚያደርገው)

ኢየሱስ ክርስቶስ ከመውለዱ ከዘመናት በፊት አረማውያን ሮማውያኖች Feb 14 ማታ እና ለ Feb 15 ንጋት አጥቢያ የተኩላ አዱኚ ለሚሉት ሉፐርካልያ (luperkalya ) ጣኦት የሚዘጋች ክብረ በአል ነው፡፡

ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ክርስትና ተቀብሎ እውነተኛ የጽድቅ ሃይማኖት መሆኑን በማውጁ ማንኛውም የጣኦት አምልኮ እንዲቀር ቢያስጠነቅቅም የተውሰኑ የሮማውያን ሰዎች ግን በአሉን ማክበር አልተውም።

እንዴት ይህ አረማዊ ባህል ቫለንታይን የሚል ሰያሜ ተሰጠው? ቫለንታይን የሚል ስም በሮማውያን ዘንድ የተለመደ ስያሜ ነው፡፡ ቫለንታይን የጥንታዊ ታዋቂው ሉፐርኩስ ጣኦት ነው።

ሉፐርኩስ በግሪካዎያን ፓን (pan) ተብሎ ሚጠራው ከወገቡ በታች በግ አናቱ ላይ ቀንድ ያለው ጣኦት ነው። በጥንታውያን አይሁድ ደግሞ ይህ ፓን ባል (baal) በሚል ስያሜ ይታወቃል።

ጥንታውያን ሮማውያን ከባቢሎናውያን የቀዱት አረማዊ የልብ (heart) ምልክት ይጠቁማሉ፡፡ በባቢሎናውያን ባል (bal) ልብ የሚል ፍች ነው ያለው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ይህ አረማዊ የልብ ምልክት ለቫለንታይን ቀን (የፍቅረኛሞች ቀን) የምንለው መግለጫነት እንጠቀምበታለን። ባል የባቢሎናውያን ጣኦት ነበር።

በዚህ የሃጥያት ቀን በትንቹ ይህ ይሆናል

1. በዚህ ቀን February 14 በብዙ የሚቆጠሩ እህቶቻችንን ክብረ ንጽህናቸውን (ድንግልናቸውን) ያጣሉ❗

2. በርካታ ወጣቶች በስካር ምክንያት በሚያሽከረክሩት መኪና ህይወታቸውን እና አካላቸውን ያጣሉ❗

3. በአለማችን ላይ በከፍተኛ ሁኔታ የአልኮል መጠጥ ሽያጭ የሚከናወንበት ቀን ነው በአጠቃላይ የዝሙት እና ስካር መንፈስ የሚነግስበት በከፍተኛ ሁኔታ ሰይጣን በደም የሚረካበት ቀን ነው።

Valentine day ማለት ሰይጣን በጥልቅ እና ረቂቅ ሃሳብ ብዙዎችን የሚያጠምድበት ቀን ነው አስተውሉ ሰይጣን ከ7ሺህ አመት በላይ የክፋት ልምድ አለው።

እንግዲህ ምርጫው ያንተ/ቺ ነው :- የእግዚአብሔር ወይም የሰይጣን ልጅ መሆን???

" ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ አንተም እውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፤ የአምላክህንም ሕግ ረስተሃልና እኔ ደግሞ ልጆችህን እረሳለሁ። "
(ትንቢተ ሆሴዕ 4 : 6)

እግዚአብሔር አምላክ ማስተዋሉን ያድለን።
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ይህንንም ግብረ ርኩሰት ቅዱሳት መጻሕፍት በተለያየ ሥያሜ ጠርተውታል፤ ከእነዚህም ርኩሰት፣ ጸያፍ፣ ትልቅ ኃጢአት፣ በደልና አመጻ የሚሉት ቃላት ይገኙበታል፡፡ (ዘሌ ፲፰-፳)

የኃጢአተኛውን ሞት የማይሻው እግዚአብሔር ሌሎች ሕዝቦች በሚበድሉበት ጊዜ በዕዶምና በገሞራ የደረሰውን ጥፋት እየጠቀሰ ከጥፋታቸው እንዲመለሱ ማስጠንቀቁን በቅዱሳት መጻሕፍት በሰፊው ተመዝግቦ ይገኛል፡፡ (ኢሳ፫÷፱፣ኤር፶÷፵፣ ሰቆ ኤር ፬÷፮፣ ሕዝ ፲÷፵፱፣ አሞ ፬÷፲፩፣ ማቴ ፲÷፲፭፣ ፪ ጴጥ ፪÷፮) በመሆኑም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ማንኛውም በጾታ ተፈጥሯዊ ስጦታ ላይ የሚሠራ ኃጢአት ሕገ ተፈጥሮን የሚጻረር ጽኑዕ በደል እንደሆነ ታስተምራለች። የያዕቆብ ወንድም ይሁዳም “እንደ እነርሱ ዝሙትን ያደረጉና ሌላን ሥጋ የተከተሉ ሰዶምና ገሞራ በዙሪያቸውም የነበሩ ከተማዎች በዘላለም እሳት እየተቀጡ ምሳሌ ሆነዋል” በማለት ይህ ተግባር የተወገዘና በዘላለም እሳት የሚያስቀጣ መሆኑን አስረግጦ ይናገራል።

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ግብረ ሰዶማዊነትን የምትቃወመው ተፈጥሮዋዊ ስላልሆነ ብቻ ሳይሆን በብሉይ ኪዳንም ሆነ በሐዲስ ኪዳን ትምህርት በእግዚአብሔር ዘንድ የረከሰ፣ ተቀባይነት የሌለው፣ ኃጢአት በመሆኑ ነው፡

ጌታችንም ሲያሰተምር “ፈጣሪ በመጀመሪያ ወንድና ሴት አደረጋቸው" በማለት ጾታ የፈጣሪ ሥጦታ መሆኑን እና ይህንም መጠበቅ ግዴታ እንደሆነ ያስረዳል። (ማቴ፲፱÷፲፭) ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ግብረ ሰዶማዊነት አጸያፊ ድርጊት መሆኑን “እግዚአብሔር ለሚያስነውር ምኞት አሳልፎ ሰጣቸው፤ ሴቶቻቸውም ለባሕርያቸው የሚገባውን ሥራ ለባሕርያቸው በማይገባው ለወጡ እንዲሁም ወንዶች ደግሞ ለባሕርያቸው ሴቶችን መገናኘት ትተው እርስ በርሳቸው በፍትወታቸው ተቃጠሉ፤ ወንዶችም በወንዶች ነውር አድርገው በስሕተታቸው የሚገባውን ብድራት በራሳቸው ተቀበሉ የሚገባውን እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልወደዱት መጠን የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው"በማለት ገልጾታል፡፡

ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ጾታዊ ግንኙነት ወይም የተቀደሰ ጋብቻ በተቃራኒ ጾታዎች ብቻ የሚፈጾም እንዲሆን የምታስተምረው ከዚህ የተነሣ ነው። (፩ ቆሮ ፯፡፪፣ ፩ ጢሞ ፩፡፱)ግብረ ሰዶማዊነት የሰውን ልጅ ተፈጥሯዊ ማንነት የሚንድ፣ መሠረተ እምነትንና ቀኖናን የሚሽር፣ ማኅበራዊ ዕሴት የሚያጠፋ፣ ከሥነ ምግባር መገለጫዎች በአሉታዊ ገጽ የቆመ፣ ሕሊናን የሚያውክ ለትውልድ ጥፋት፣ ለሀገር መውደም ምክንያት የሆነ አጸያፊ ተግባር ነው፡፡

በመሆኑም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይህን ተግባር የሚፈጽሙ ሰዎች ወደ ንሥሓና ድኅነት እንዲመጡ፣ ከሥጋና ከመንፈስ ስብራት እንዲፈወሱ ዘወትር ጥሪ ታደርጋለች እንጅ ማንም ሰው የኃጢአቱ ወይም የርኩሰቱ ተባባሪ እንዲሆን አትፈቅድም።

በ፲፱፻፺፮ በወጣው የሀገራችን የወንጀል ሕግ ክፍል፪ አንቀጽ ፮፻፳፱ ጠቅላላ ድንጋጌ “ግብረ ሰዶምና ለንጽሕና ክብር ተቃራኒ የሆኑ ሌሎች ድርጊቶች፤ በሚለው ንዑስ አንቀጽ ርእስ ሥር ይህ ድርጊት ወንጀል ስለሆነ በትክክል የሚያስቀጣ መሆኑን አስቀምጧል። በተለይ አንቀጽ ፮፻፴፩ ዕድሜያቸው ፲፰ ዓመት ያልሞላቸው ለአካለ መጠን ያልደረሱ ልጆች ላይ ለሚፈጸም ግብረ ሰዶማዊነት ከ፭ እስከ ፳፭ ዓመታት የሚያስቀጣ መሆኑ በግልጽ ተጽፏል።በተሻሻለውም የሀገራችን የቤተሰብ ሕግ በአንቀጽ 13 መሠረት የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ በሕግ የተከለከለ መሆኑ ተደንግጓል፡፡

ይሁን እንጅ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ይህን ተግባር በግልጥ በሕገ መንግሥታቸውና በልዩ ልዩ ማኅበራዊ ድንጋጌዎቻቸው እንደ ጥሩ ነገርእንደ ፍትሐዊነትና አካታችነት በመቁጠር በይፋ የደነገጉ የምዕራቡ ዓለም ሀገራት መኖራቸው ግልጽነው።

እነዚሁ ሀገራት ያላቸውን የፖለቲካና የኢኮኖሚ አቅም መከታ በማድረግ በእምነታቸው፣ በባሕላቸው በማኀበራዊ መገለጫቸው ይህን አጸያፊ ድርጊት ፈጽመው በማይቀበሉ የአፍሪካና የምሥራቁ ዓለም ሀገራት ላይ ቢቻል በማግባባት፣ ካልሆነም የፖለቲካና የኢኮኖሚ ጫና በማሳደር እንዲቀበሉ የጥፋት ልማዳቸውን እንዲጋሩ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉትን ድብቅና ግልጽ እንቅስቃሴዎች ቋሚ ሲኖዶስ በጽኑ ይቃወማል፡፡

ይህ ግብረ ርኩሰት በዘመናችን ተቀባይነት እንዲኖረው፣ የሚደረጉ ሁለገብ ማግባባቶች፣ ተጽዕኖዎችና ተያያዥነት ያላቸው ስምምነቶች በሀገራችን መንግሥት ተቀባይነት አግኝተው እንዳይፈጸሙ ቋሚ ሲኖዶስ በጥብቅ ያሳስባል።

ከመገናኛ ብዙኃንና ከሌሎችም የመረጃ ምንጮች ለማወቅ እንደተቻለው ግብረ ሰዶማዊነትንና ተያያዥነት ያላቸውን ተግባራት የንግድ፣ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የፍትሕና የሰብዓዊነት ግንኙነቶች አካል በማድረግ በቃላትና በዓረፍተ ነገሮች ውስጥ አስርጎ በማስገባት አሣሪ ስምምነቶች እንዲፈጸሙ ለማድረግ ያለው ሃደት በአፋጣኝ እንዲፈተሽ የሀገራችን መንግሥት ብሎም የአፍሪካ መንግሥታት የአህጉራችንን ሃይማኖታዊ ማኅበራዊና ሥነ ልቦናዊ ዕሴቶች አስጠብቀው እንዲቀጥሉ ቋሚ ሲኖዶስ ጥብቅ የሆነ የአደራ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

በስምምነቱ ሰነድ ጤናማ መስለው የሠረፁ ዐረፍተ ነገሮች ውስጥ እንደታየው በጾታና ሥርዓተ ጾታ መብት፣ የሥርዓተ ጾታ ትምህርት ጋር በማያያዝ ጾታን በቀዶ ጥገና የመቀየር ውርጃ፣ልቅ የሆነ የተመሳሳይና ተቃራኒ ጾታ ግንኙነትን መፍቀድ፣ ግለሰቦችን እና ማኅበረሰብን መረን በማድረግ ውስብስብ ለሆኑ ሃይማኖታዊ፣ ማኅበራዊና ባህላዊ ችግሮች የሚዳርጉ መሆናቸውን ቅዱስ ሲኖዶስያምናል።

በመሆኑም በብዙ መስዋዕትነት ተጠብቆ የቆየው እምነት፣የባህልና የሥነ ምግባር ማኅበራዊ ዕሴት የክብር ስፍራውን ይዞ እንዲቀጥልና በእጅ አዙር ቅኝ ግዛት
ኃጢአትንና ርኩሰትን አባብሎ በማስረጽ፣ለዚህ አጸያፊ ድርጊት ትውልዱ እንዳይጋለጥ የሚመለከተው ሁሉ በልዩ ጥንቃቄ እንዲመለከተው ቋሚ ሲኖዶስ ጥሪውን ያስተላልፋል።

ግብረ ሰዶማዊነት በማንኛውም የቃላት አግባብ ተገልጦ በጾታ መብት መካተት የማይችል የመደበኛ ተፈጥሯዋዊ ክስተት ጋር በጭራሽ አቻ የማይሆን በመሆኑና ተግባሩንም
መቃወም ቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ ተልእኮዋ ስለሆነ ይህን አስመልክተው የሚደረጉ ስምምነቶች የሀገራችንን ሃይማኖታዊ፣ ማኅበራዊና ሥነ ልቦናዊ ዕሴት የሚጥሱ መሆኑ ታውቆ ሁሉም ዜጎች እንዲቃወሙት፣ የፈዴራል መንግሥትም ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እንዲከታተለው ቋሚ ሲኖዶስ በጥብቅ ያሳስባል፡፡

ግብረ ሰዶምን እና ተያያዥ የጾታ ሥርዓትን የሚበርዙ፣ ጾታን መቀየር፣ ሁለት ዓይነት ጾታን መጠቀምና የመሳሰሉት ተግባራት በሙሉ ሀገራችን በሃይማኖት፣ በሕግ፣ በማኅበራዊ ዕሴቶቿ፣ በሥነ ምግባር መመሪያዎቿ የማትቀበላቸው ጉዳዮችና ልምምዶች ስለሆኑ በማናቸውም ይፋዊ ግንኙነቶች እንደማንቀበላቸው በግልጽ እንዲቀመጡ ቋሚ ሲኖዶስ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

ግልጽ የሆኑ ግብረ ሰዶማዊነትን የሚያበረታቱ፣
የሚያዛምቱ፣ ድብቅና እንቅስቃሴዎች የሚያደርጉ አካላት ከድርጊቸው እንዲቆጠቡ፣ በንሥሓ እንዲመለሱ ቅድስት ቤተክርስቲያን በጥብቅ ታሳስባለች።

ለወደፊቱም ማናቸውም የሥርዓተ ትምህርት መማሪያ ሲዘጋጅ፣ ሀገር በቀል ደንቦችና መመሪያዎች ሲወጡ የዓለም አቀፍ ግንኙነት ስምምነቶች ሲፈጸሙ በሀገሪቱ ያሉ የእምነትና የባህል፣ ዕሴቶችን፣ የሕግ ማዕቀፎችንና የሥነ ምግባር መርሆችን ተጠብቀው እንዲፈጸሙ፣ መላው ሕዝባችንም የእምነት መሠረቱን፣የቀኖና ሥርዓቱን፣ ማኅበራዊ ዕሴቱን ጠብቆ እንዲኖር፣ ሀገራችን ሰላም እንድትሆን ሁላችንም ከወትሮው በተለየ ሁኔታ በጸሎት እንድንተጋ ቋሚ ሲኖዶስ መንፈሳዊ ጥሪውን ያስተላልፋል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ከ97,000member በላይ ባለው ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍ ቻናል የኦርቶዶክስ መጽሐፍ በPDF ያንብቡ።

❣📚❣
1, እመጓ
2, ዝጎራ
3, መርበብት
4, ዴርቶጋዳ
5, ዮራቶራድ
6, ዣንቶዣራ
7,መጽሐፈ ሄኖክ
8, ቤተክርስቲያንህን እወቅ እንዳትሆን መናፍቅ
9, ፍኖተ አእምሮ
9, አዳም እና ጥበቡ
10, ዝክረ መስቀል
11, ሰይፈ ሥላሴ
12, ፍትሐ ነገስት
13, መጽሐፈ መነኮሳት
14, ከአክራሪ እስልምና ወደ ክርስትና
16, ህግጋተ ወንጌል
17, ነገረ ማርያም በጥንታዊቷ ቤተከርስቲያን
18, ድርሳነ ሚካኤል ወ ገብርኤል
19, ውዳሴ ማርያም በግእዝ
20, ግድለ ተክለሃይማኖት
21, ገድለ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሰጫ
22, የወጣቶች ህይወት
23, መጽሐፈ ገድለ ሐዋርያት
24, ኦርቶዶክስ መልስ አላት
25, የዋልድባ ገዳም ታሪክ
26, መጽሐፈ አክሲማሮስ
27, 14ቱ ፍሬ ቅዳሴያት ከነ አንድምታው
28, መልክዓ መለኮት
29, መጽሐፈ አሚን ወ ሥርዓት
30, ሰባቱ ምስጢራተ ቤተከርስቲያን
31, ሐይማኖተ አበው
32, ራዕየ ማርያም
34, የመናኝ ጉዞ
35, ሐሽማል
36, ከርታታ ኮከቦች
37, በርዮድስ



📚📚📚የቱን ኦርቶዶክሳዊ መፅሀፍ ማንበብ ይፈልጋሉ የሚፈልጉትን መፅሀፍ በመንካት ያንብቡ መልካም ንባብ📖

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ስለ ቅዳሴ ክፍል 74
ትርጓሜው ይህ ነው በደንብ አዳምጡት
ቤተክርስቲያን እጅግ ልዩ እና ግሩም ናት😍😍😍

እንወዳታለን በጣም ይህቺን ቤተክርስቲያን

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ አገር እንዳይገቡ ተከለከሉ

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአሜሪካ የነበራቸውን ሐዋርያዊ አገልግሎት ጨርሰው ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ እንዳይገቡ መከልከላቸው ተሰምቷል።

ብፁዕነታቸው ከሳምንታት በፊት በቋሚ ሲኖዶስ እውቅና ወደ ሀገረ ስብከታቸው በመሄድ የአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ ዓመታዊ በዓል፣ የከተራና የጥምቀት በዓላትን ከመንፈስ ልጆቻቸው ጋር ያከበሩ ሲሆን ለአዳጊ ሕጻናትም ማዕረገ ዲቁና መስጠታቸው ይታወቃል።

ብፁዕነታቸው በአሁኑ ሰዓት ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያው እንደሚገኙ ታውቋል።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

💒ስለ ሀይማኖቴ ማወቅ ግዴታዬ ነው የሚል የማንኛውም ኦርቶዶክስ ሊቀላቀለው የሚገባ ቻናል። በቻናሉ ጥያቄ ይጠየቃል ምዕመኑም ይሳተፋል
ቻናሉን ለመቀላቀል ከስር ክፍት የሚለውን
መጫን በቂ ነው።

               ክፈት        ክፈት               
               ክፈት        ክፈት               
                                                   
ክፈት        ክፈት        ክፈት        ክፈት
ክፈት        ክፈት        ክፈት        ክፈት
                                                    
                                                   
                                                    
                                                    
                                                     
               ክፈት         ክፈት              
               ክፈት         ክፈት              .

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን ክፍል ፪
👉ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን በሐዲስ ኪዳን

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

የቅዳሴ ትምህርት ክፍል 72 እንዲህ ይቀጥላል

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ሀበነ የሚለው ክፍል እነሆ ቅዳሴ ክፍል 71
እየተከፋፈለ የተላከ ነው ተለማመዱት

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

Aster’eyo Mariam
 
Amid the Age of “Aster’eyo / revelation/, not only Lord and Savior Jesus Christ’s as well as the oneness and Threeness of God was revealed, but also the departure of Holy Mother Saint Mary on Tir 21, of which we make a feast known as “Aster’eyo Mariam.”

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​+ አበው ስለ እመቤታችን ዕረፍት እንዲህ አሉ

‹ሌሎች በድንግልና የኖሩ ሴቶች 'ለሞት የሚሆኑ ልጆችን አንሰጥህም" በማለት ሞትን ተቃወሙት፡፡ ድንግል ማርያም ግን አንድ ልጅ በመውለድ በልጅዋ ሞት ራሱ እንዲሞት አደረገችው፡፡ ከዐለት ጋር እንደተጋጨ የተፈረካከሰው በማሕፀንዋ ፍሬ ነውና ሞት ወደ እርስዋ ሲቀርብ ተብረከረከ›› ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ

‹‹ልጃቸው ተሰብስበው ወዳሉበት መጥታለችና አዳምና ሔዋን ዛሬ ደስ አላቸው … በዚህች ቀን ታላቁ ዳዊት በራሱ ላይ የተዋበ አክሊል የደፋችለትን ሴት ልጁን አይቶ ደስ አለው … በዚህች ቀን ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት የተናገረላት ድንግል ወደ ሙታን ሥፍራ ልትጎበኘው መጥታለችና ደስ አለው … በዚህች ቀን ብርሃን ሲበራባቸው አይተዋልና ነቢያት ሁሉ ከመቃብራቸው ራሳቸውን ቀና አደረጉ … አርያም በጣፋጭ የመላእክት ዝማሬ ተሞላ ፣ ምድር ደግሞ ኀዘንን በተሞሉ በሐዋርያት ለቅሶ ተሞላች፡፡ ሙታንም ሕያዋንም ትርጉሙን ሊገልጹት በማይችሉት የተለያየ ዜማ ሰውና መላእክት በዚያች ዕለት አብረው ጮኹ›› ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ (Homily on the Dormition)

‹‹የቃሉ አገልጋዮችና ምስክሮች የነበሩት ሐዋርያት በሥጋ የወለደችውን የእናቱን ዕረፍትና እርስዋን የሚመለከቱ የመጨረሻዎቹን ምሥጢራትም ማየት ነበረባቸው፡፡

ይህም የሆነው የክርስቶስ የዕርገቱ የዓይን ምስክሮች እንደሆኑ ሁሉ የወለደችውም እናቱ ወደዚያኛው ዓለም ለሸጋገርዋ ምስክሮች መሆን ስላለባቸው ነው›› ቅዱስ ዮሐንስ ዘደማስቆ (aka Doctor of Dormition)

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
አስተ ር እዮ ማርያም
ጎተበርግ ስዊድን

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

መልክአ ማርያም
ሰላም ለመቃብርኪ ለኢየሩሳሌም በአድያማ፤ እንተ ይእቲ ጌቴሴማኒ ስማ፤ ማርያም ሰንበት ዕረፍተ ጽዑራን እምፃማ፤ አመ ኀደረ ላዕሌኪ ፀሐየ ቅዱሳን ዘራማ፤ ኃይለ ልዑል ጸለለኪ በመንክር ግርማ።

ዚቅ
ኢይሜንንዋ ኪያሃኒ ወአድያሚሃኒ ነያ ጽዮን ቅድስት ሀገረ እግዚአብሔር።

ማኅሌተ ጽጌ
እግዚአብሔር ጽጌ ትንቢት ለቢሶ ሥጋኪ ሥጋ ዚአነ፤ አመ አስተርአየ በምድር ወተአምረ ለነ፤ ንዌድሰኪ እንዘ ንብል ምክሃ ዘመድነ፤ ዮም በፍሥሃ ለማርያም እምነ፤ አስተርእዮ በሰማይ ኮነ።

ዚቅ
አስተርአየ ዘኢያስተርኢ፤ ኮነ እሙነ አስተርእዮቱ ለመድኃኒነ ክርስቶስ፤ እሙነ ኮነ አስተርእዮቱ፤ እምድንግል ተወልደ፤ እሙነ ኮነ አስተርእዮቱ፤ በሥጋ ረቂቅ፤ እሙነ ኮነ አስተርእዮቱ፤ በ፴ ክረምት በዮርዳኖስ ተጠምቀ፤ በበህቅ ልህቀ።

አንገርጋሪ
ኢኮነ ነግደ ወፈላሴ ሀገሪቶሙ ለቅዱሳን፤ ንሕነ ሰብአ ቤቱ ለእግዚአብሔር ኲልነ፤ አምላክ ኀደረ ውስተ ሥጋ ተአቊረ፤ እንዘ ኢይትጋባዕ በሙላድ፤ ዘድንግል መናሥግተ ኢያርኂዎ፤ ዘኪሩቤል ኢርእዮ።

አመላለስ
ዘድንግል መናሥግተ ኢያርኂሆ/፪/
ኢያርኂሆ ዘኪሩቤል ኢርእዮ ኢያርኂዎ ኢርእዮ ዘኪሩቤል/፪/

ወረብ
'አምላክ ኀደረ'/፪/ ውስተ ሥጋ ተዓቊረ እንዘ ኢይትጋባዕ አምላክ ኀደረ/፪/
ዘድንግል መናሥግተ 'ኢያርኂዎ'/፪/ ኢርእዮ ዘኪሩቤል/፪/

እስመ ለዓለም
እግዝእትየ እብለኪ ወእሙ ለእግዚእየ እብለኪ፤ ቃል ቅዱስ፤ መንበሩ ዘኪሩቤል ኀደረ ላዕሌኪ፤ ዘመንበሩ ዓቢይ ውእቱ፤ ያቀድም አእምሮ ኅሊና ሰብእ፤ መንበሩ ዘኪሩቤል ኀደረ ላዕሌኪ፤ ግሩም እምግሩማን፤ ዘመጽአ ውስተ ዓለም፤ መንበሩ ዘኪሩቤል ኀደረ ላዕሌኪ፤ ስብሐት ዘኢየኃልቅ፤ ወሰን ዘኢያንጸበርቅ፤ መንበሩ ዘኪሩቤል ኀደረ ላዕሌኪ፤ ዘይሥዕሎሙ ለሕፃናት፤ ወይነግሥ ለመላእክት መንበሩ ዘኪሩቤል ኀደረ ላዕሌኪ፤ እስመ ንጉሥ ውእቱ ሰከበ በጎል፤ ሰገዱ ሎቱ ሰብአ ሰገል፤ መንበሩ ዘኪሩቤል ኀደረ ላዕሌኪ፤ እምግርማሁ ትርዕድ ምድር ዜናዊ ስቡሕ ዘለዓለም፤ ወእስከ ለዓለም ንጉሥ ውእቱ።

ወረብ
ዘመንበሩ ዓቢይ መንበሩ ውእቱ መንበሩ ዘኪሩቤል/፪/
ያቀድም 'አእምሮ'/፪/ ኅሊና ሰብእ/፪/

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

እንኳን ለኢትዮጵያ ጀግኖች ለቤተክርስቲያን የድል ቀን
ለአድዋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን።
ጥራት ያላቸው 100% cotton የሆኑ ቲሸርቶችን ለእናንተ ይዘን ቀርበናል። ከጓደኞቻችሁ፣ከምትወዷቸው ጋር እዘዙን በጥራት እናቀርባለን
ለበለጠ መረጃ 0912085085 ወይም በውስጥ መስመር አነጋግሩን።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

መልክአ ቁርባን


☺️ተለማመዱት☺️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ቅዳሴ ክፍል 75 ተለማመዱት🥰

🙏በገና ክራር እና ከበሮ መማር የምትፈልጉ
አዲስ ዙር ትምህርት ስለጀመርን መመዝገብ
የምትፈልጉ በውስጥ መስመር አሳውቁን
🙏

📒 ለመመዝገብ ከታች ባሉት ስልክ ቁጥሮች ወይም በቴሌግራም አካውንታችን በውስጥ መስመር ልታወሩን ትችላላችሁ።

☎️ 0965083251
     0956861468
     0912085085

ወይም በቴሌግራም
   @Orthodoxtewahed0
ወይም በቲክቶክ
hadafe_nefese

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ
የካቲት ፬ ቀን ፳፻፲ወ፮ ዓ/ም

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻና ግብረ ሰዶማዊነትን አስመልከቶ እየተደረጉ ያሉ ሁለገብ ተጽእኖዎችንና መመሪያ የማስለወጥ ማግባባቶችን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፤

“ወለእመቦ ዘሰከበ ምስለ ተባዕት ከመ አንስት ርኵሰ ገብሩ ክልኤሆሙ … ወጊጉያን እሙንቱ..ማንኛውም ሰው ከሴት ጋር እንደሚተኛ ከወንድ ጋር ቢተኛ ሁለቱ ጸያፍ ነገር አድርገዋል። ደማቸውም በላያቸው ነው" (ዘሌ.፳ ፥፲፫) ግብረ ሰዶማዊነት በሕገ ተፈጥሮም ሆነ በሰው ልጅ ሰብአዊ አኗኗር ፈጽሞ ተቀባይነትየሌለው፣ ዓለምን በልዩ ጥበብ በፈጠረ አምላክ ፈቃድ፣ መለኮታዊ ሥርዓቱ በተገለጠባቸው ቅዱሳት መጻሕፍት ፈጽሞ የተከለከለ፣ በቀኖናተ ቤተክርስቲያን፣ በፍትሕ መንፈሳዊና በፍትሐ ብሔር ድንጋጌዎች፣ በሥነ ልቦና ደንቦች የተወገዘ፣ ሥነ አእምሮዊ ሚዛንን የሚያዛባ፣ግለሰባዊ ማንነትንና ማኅበራዊ ትሥሥርን የሚያናጋ የረከሰ ተግባር ነው፡፡

ግብረ ሰዶማዊነት በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተገለጸው ለአንድ ሀገርና ሕዝብ ከነጎረቤቶቹ መጥፋት ምክንያት የሆነ ተግባር ሲሆን የሰዶምና ገሞራ በመቅሰፍተ እሳት መቃጠል ከእነርሱ መቀጣትም አልፎ ላለውና ለመጪው ትውልድ አስተማሪ የሆነ ምልክት እንዲሆን ነው።

መጽሐፍ ቅዱስም ግብረ ሰዶማውያን የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም በማለት የግብሩን አስከፊነት፣ በማኅበረ ሰብእ ላይም የሚያመጣውን ጥፋት በአጽንዖት ይነግረናል። (ሮሜ ፩፳፮ ፩ቆሮንቶስ ፮፱፣I፣)

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​​​​​ሰንበት
ሰንበተ ክርስቲያን (እሑድ)

እሑድ ማለት ‹‹አሐደ›› ከሚለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጉሙም የመጀመሪያ ማለት ነው፡፡ ይህቺ ዕለት በመጽሐፍ ቅዱስ ‹‹ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን›› በመባል ትታወቃለች፡፡

ዮሐንስም በራዕዩ ‹‹የጌታ ቀን›› ያላት ናት (ራእይ 1፤10)፡፡ ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ ‹‹ዕለተ እግዚአብሔር›› የሚላት ዕለተ እሑድ ናት፡፡

ዕለተ እሑድ እንደ ሰንበት የሚከበርበት ምክንያቶች፡-

👉 እግዚአብሔር ሥራውን የጀመረባት ለሥነፍጥረት መጀመሪያ ዕለተ (ጥንተ ዕለት) ናትና
👉 ዕለተ ሥጋዌ ናት፡፡ ጌታ የተፀነሰባትና እርቅ የተወጠነባት የፍሰሐ ቀን፡፡
👉 ዕለተ ትንሣኤ ናት፡፡ ጌታ ከሙታን ተለይቶ የተነሳባት ዕለት
👉 የቤተ/ክ የልደት ቅን ናት፡፡ መንፈስ ቅዱስ ለሐዋሪያት የወረደባት ኃይልና ፅናትን ያገኙባት ዕለት
👉 ጌታ በክበበ ትስብእት በግርማ መለኮት ዳግም በቅዱሳን መላእክቱ ታጅቦ በጌትነቱ ለፍርድ የሚመጣባት ታላቅ የፍርድ ቀን ናትና የተለያዩ መንፈሳዊ አገልግሎቶች የሚካሄዱባት ዕለት ናት(1ኛ ቆሮ 16፤1)
👉 የሐዋሪያት ዘመንም በጤሮዓዳ ያሉ ክርስቲያኖች እሑድ ቀን ይሰበሰቡ ነበር (የሐዋ. 20፤7 በቤተክርስቲያን ታሪክ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ዕለተ እሑድ የክርስቲያኖች ሰንበት ናት በማለት
ሥራ እንዳይሰራባት አዋጅ አስነግሮ ነበር፡፡

ምንም እንኳን ይህቺ ዕለት በሐዲስ ኪዳን መከበር የጀመረ ቢሆንም በብሉይ ኪዳን ከፋሲካ በፊት የሰንበት (የቀዳሚት) ማግስት በመባል በኩራት እና ቀዳሚያት የሚያቀርቡበት ቀን ነበር። (ራዕ 1፡10)

በቀዳሚት ሰንበት ቅዱስ እግዚአብሔር ከሥራው ሁሉ አርፎ ሥጋዊ እረፍትን ለሰው እንዳስተማረ በእሑድ ቀን (በሰንበተ ክርስቲያን) በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት የተገኘውን የዘላለማዊ የነፍስ ዕረፍት የምናስብበት ነው፡፡ (ዕብ 4፡1-10)

ከሰንበት ረድኤት በረከት ይካፍለን!
ሌሎች እህት ወንድሞች ይማሩበት ዘንድ አጋሩ

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​​​​​ሰንበት

‹‹ስድስት ቀን ስራ፣ተግባርህም ሁሉ አድርግ በሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር ለአምላክህ ሰንበት ነው፡፡ እግዚአብሔርም በሰባተኛው ቀን አርፏልና ስለዚህ እግዚአብሔር የሰንበትን ቀን ባርኮታል ቀድሶታል፡፡ ›› (ዘጸ 20፡10-11)

ሰንበት ማለት ምን ማለት ነው ?

ሰንበት ማለት አቆመ፣ አረፈ ማለት ነው፡፡ይህ ቀን የጌታ ዕረፍት የተባረከም ቀን ነው፡፡ ከማንኛውም ሥጋዊ ሥራ ተቆጥበን የእግዚአብሔርን ውለታ የምናስብበት ቀን ነው፡፡ ሰው እረፍት ያስፈልገዋል፡፡ የሰንበት ቀንም የተፈጠረው ለዚህ ነው፡፡ (ዘዳ 5፡14)፣(ማር 2፡38)

ከሳምንቱ ሰባት ቀናት መካከል ለእረፍት የተቀደሰው የተባረከው ዕለት ሰንበት ብቻ ነው፡፡ ስለሌሎች ቀናት የተነገረው ‹‹ ያ መልካም እንደሆነ አየ›› የተባለው ብቻ ነው፡፡ ሰንበትን ግን ባርኮታል ቀድሶታል፡፡ (ዘፍ 1፡12፣ 18፡20፣ 25፡31)

በሐዲስ ኪዳን ለክርስቲያን ሁለት ሰንበት አለ ቀዳሚት ሰንበት(ቅዳሜ) እና ሰንበተ ክርስቲያን (እሑድ)

1. ቀዳሚት ሰንበት (ቅዳሜ)

ጌታ ያረፈባት ለእስራኤል ዘሥጋ የታዘዘው ሰንበት ነው፡፡ ይህ ቀን እስራኤላውያንን እግዚአብሔር አምላክ ከግብፅ ባርነት ወደ እረፍት እንዳወጣቸው ያመለክታል፡፡ ዘዳ5-2-16

በእግዚአብሔር እና በህዝቡ መካከል ምልክት ነበረ ሰንበትን አለማክበር ግን ከባድ ቅጣት ያስከትል ነበር፡፡ (ዘጸ 3፡17) ፣ (ሕዝ 20፡12) ፣ (ዘኁ 15፡32-36) ፈሪሳውያን በነበራቸው የተሳሳተ አመለካከት በሰንበት ቀን እንኳን መልካም ሥራን አይሰሩም ነበር፡፡

ስለዚህም በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ተወቅሰዋል፡፡ (ማቴ 12፡14) ፣ (ሉቃ 4፡16) በዘመነ ሐዲስ የክርስቲያኖች የቀዳሚት ሰንበት አከባበር እንደ አይሁድ ለሰው የሚከብድ እንዳይሆን በፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 19 ላይ ተገልጿል፡፡

2. ሰንበተ ክርስቲያን (እሁድ)
ይቀጥላል
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🎁ይህን አንብቡና የሳምንቱ መጀመሪያ ቀናችሁን ብሩህ አድርጉ🤗


🥹እግዚአብሔር ሆይ! ስለምን ተውኸኝ? እኔን ከማናገር ዝምታን፣ እኔን ከመዳሰስ ርቀትን ለምን መረጥህ? አምላክ እንደሌለው ስረገም፣ ወዳጅ እንደሌለው ስከሰስ፣ ዳኛ እንደሌለው ስኰነን ለምን ዝም ትላለህ?

የእኔና የአንተ የጥንቱ ፍቅራችን የት ደረሰ? በእኔስ አንጀትህ እንዴት ጠና?

በስንት ተራራ አብረኸኝ ስለነበርህ ከባዱ ቀለለኝ፣ ዛሬ ግን ቀላሉ ከበደኝ፡፡ ያላንተ መስኩ ተራራ፣ ሜዳው ሸለቆ ነው፡፡

አንተ የሌለህበት፣ የራስን ድምፅ በልዑል ድምፅ የሚሰሙበት ባዶ አዳራሽ ነው፡፡ ያሳለፍኩትን የልቅሶ ዓመታት ሳስብ ከዚህ በኋላ ሌላ ልቅሶ ይኖራል ብዬ አስቤም አላውቅ ነበር፡፡

ልቅሶ ግን ርእሱ ይቀየራል እንጂ እንደማይቀር አውቅሁ፡፡ ዛሬ ለእኔ ጥቁር ቀን ነው፡፡ ያንን የቤትህን ክብር፣ የካህናትህን ሞገስ የት ወሰድከው?

የእግዚአብሔር መልስ፡– ልጄ  ሆይ!...ሙሉውን ጽሑፍ ለማንበብ


         ሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን
            BINI GIRMACHEW

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን ክፍል ፫
👉ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን በብሉይ ኪዳን

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

💍💍 የጋብቻ ወቅት እንደመሆኑ የሠርግ መዝሙራትን ከግጥምና ከ ዜማቸው ጋር ማግኘት ከፈለጉ ይቀላቀሉን

/channel/+0nmdk7ixreBhZDc0

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​እንኳን ለቅዱስ ዑራኤል አመታዊ የመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳቹ አደረሰን!

መልዐኩ ቅዱስ ዑራኤልና አገልግሎቱ በጥቂቱ

✍ ዑራኤል የሚለው ስም "ዑር"እና ኤል ከሚለው ሁለት ቃላት የተመሰረተ ነው ። ትርጉሙም ብርሃነ ጌታ አምላክ ብርሃን ነው። ማለት ነው።

✍ ቅዱስ ዑራኤል ከ7ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሲሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ መብረቅና ነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልአክ ነው።በመሆኑም መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበቁ ነጓድጓድ ለሰላም እንዲሆን ያሰማራል። (መጽሐፈ ሄኖክ ፮፥፪)

✍ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ ከወዳጇ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከእየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ግብጽ ስትሰደድ መንገድ እየመራ፤ ከእስራኤል ወደ ግብጽ ከዚያም ከእመቤታችን ጋር በሀገራችን ኢትዮጵያ እየመራ ያመጣት መልአክ ነው።

✍ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ ሆኖ በተሰቀለበት ጊዜ፥ክቡር ደሙ በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ በብርሃን ነሳንስ የረጨው እሱ ነው።

✍ ለነብዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋ ልቦና ያጠጣው፥ጥበብን ማስተዋልን የሰጠው የጠፉ መጽሓፍት በቃሉ አስታውሶ እንደገና ያጻፈው የረዳው መልአክ ነው።(ዕዝ፲፫፥፴፱)

✍ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና ትዕዛዝ ብዙ ድርሰት የደረሱት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ጽዋ ህይወት ስላጠጣቸው ነው።

✍ በዓላቱም በዓመት 3ናቸው።
፩...ጥር። 22 በዓለ ሲመቱ፤
፪....መጋቢት 27 የጌታችንን ደም በዓለም የረጨበት፤
፫...ሐምሌ 21 እና 22 ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት ።

✍ በጸሎቱ የተማጸነ ከእግዚአብሔር አምላክ በረከትን ፣ምህረትን የሚያሰጥ አዛኝ ጠባቂ ና የዋህ መልአክ ነው።በተለይም ህጻናትን የሚጠብቅ የሚለምኑትን ሁሉ የሚሰማ ፥ኃጢአተኞች ካሉበት ቦታ እኔን ላከኝ እያለ አምላኩን የሚማጸን አዛኝ የዋህ መልአክ ነው።

✍ ይህ አለም በአማላጅነቱ አምኖ በእምነት ጸበሉን ቢጠጣ ፥ዝክሩንም ቢዘክር ከክፉ በሽታው እንደሚድን፤ እንደሚፈውሰው ቃል ኪዳን ተሰጥቶታል ።

✍ ቅዱሳን መላዕክት እግዚአብሔርን በሚፈሩ ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራሉ ከመከራም ያድኑዋቸዋል።(መዝ ፴፫÷፯) የአባታችን የጠባቂያችን የአማላጃችን የመልአኩ የቅዱስ ዑራኤል ቃል ኪዳን አይለየን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

 
The Mother of God, Holy Mother Saint Mary lived in this world for 64 years and rested honorably after Holy Spirit informed her. Though our mother died onward all the misery and suffering she bared for the salvation of humans, she has ascended just as her Son, Lord Jesus Christ. This was on a blessed day Nehasse 16.

Saint Mary lived for three years in her parents’ house, 12 years in the temple, 33 years alongside her Son, and for 15 years with the apostle Saint John after our Lord’s ascension, a total of 64 years on earth and died honorably on Tir 21, at 49 E.C.

All Christians shall celebrate this feasts and so Holy Church has made a liturgy for us.  “Aster’eyo Mariam” is a feast to be celebrated amongst the Christian community and thus the entire Orthodox Tewahedo society including our country, make a great feast. We celebrate this feast not just to commemorate the departure of our Holy Mother Saint Mary, but craving and hoping for her intercession and mediation.  

Therefore, we shall celebrate her departure day so that our Mother Saint Mary could plead peace, love and unity for us, as well as salvation for our soul. 

May God’s mercy, the intercession and mediation of our Holy Mother Saint Mary be with us, Amen!!!
 
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

#ሞትማ_ለመዋቲ_ይገባል ✞

ሞትማ ለመዋቲ ይገባል ይገባል(፪)
የድንግል አሟሟት እጅጉን ይደንቃል(፪)

ለልጇ ስትነግር ሞት እንደምትፈራ(፪)
ወሰዷት በሐሴት መላእክተ ሐራ(፪)
ጭንቀቱ ሳይገጥማት ሳታስብ ድንገት(፪)
እንደ እንቅልፍ ወሰዳት ያመልአከ ሞት፪)
#አዝ
ይገርማል ይደንቃል የድንግል ፍልሰታ(፪)
በምስጋና አረገች ከልጇ ተጠርታ
በይባቤ አረገች ከልጇ ተጠርታ
እያሸበሸቡ መላእክተ ሰማይ(፪)
ወስደው አቀረቧት ከልጇ መንበር ላይ(፪)
#አዝ
ሱባኤ እንደገቡ እንደ ሐዋርያት(፪)
እኔም ከቤት ወጣሁ አንቺኑ በመሻት(፪)
ትንሳኤሽን በክብር እንዳሳየሻቸው(፪)
እኔንም ለዚህ አብቂኝ ብርሃንሽን እንዳየው(፪)

ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ ወልደቂርቆስ

"አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና
የመቅደስህ ታቦት።"
መዝ ፻፴፩፥፰

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

❖ የድንግል ማርያም ወዳጆች ✞ እንኳን አደረሳችሁ

☞ አስተርዮ _ ቃሉ የግእዝ ቃል ሲሆን
ትርጉሙም ፦ መታየት ወይም መገለጥ ማለት ነው፡፡

👉 ጥር 21 ቀን ነፍሷ ከሥጋዋ ተለይቶ በደመና ተነጥቃ ወደ ገነት በመግባት በሰማይና በምድር የተሰጣትን ፀጋና ክብር የገለፀችበት እለት ስለሆነ በዓሉም አስተርዮ ማሪያም ይባላል።

❖ የድንግል ማሪያም ጥበቃ ምልጃዋ አይለያቹ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ጥር 21 የአስተርእዮ ማርያም ክብረ በዓል ሥርዓተ ማኅሌቱ ከሊቃውንቱ ጋር ለማመስገን እንዲረዳን እንደሚከተለው ተዘጋጅቷል #በፍጥነት_ሼር_Share_ያድርጉ

የማንኛውም ወርኃ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ "ሥርዓተ ነግሥ"
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፤ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኀቤየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፤ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፣ በአሐቲ ቃል።

መልክአ ሥላሴ
ሰላም ለኲልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወጸ በሣህል፤ እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፣ ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል።

ዚቅ
ሃሌ ሉያ ለአብ፤ ሃሌ ሉያ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሥላሴ ዋህድ፤ ዕፎኑመ እመ አምላክ በከየት ደንጊፃ፤ ከመ ኲሉ ሰብእ ሞት ሶበ ሐወጻ፤ ዮሐንስ በልብሱ ከደነ ገፃ።

ወረብ
እፎኑመ እመ አምላክ በከየት ደንጊፃ በከየት እመ አምላክ/፪/
ከመ ኲሉ ሰብእ ሞት ሶበ ሐወጻ በከየት/፪/

ነግሥ
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤ መሠረተ ሕይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤ እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ።

ዚቅ
ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ መጽአ ውስተ ዓለም፤ ወዓለሙኒ ኢክህለ ፀዊሮቶ፤ ፆረቶ ወአግመረቶ ማርያም።

ነግሥ
ለምንት ይዜኃር ኃያል በኃይሉ፤ ወባዕል በብዝኃ ብዕሉ፤ ኢያድለወ ሞተ ክርስቶስ ለሥጋ አባሉ፤ ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ፤ ሞታ ለማርያም የአፅብ ለኲሉ።

ዚቅ
እንበይነዝ አእምሩ በውስተ ፍትሕ ከመ ኢያደሉ፤ ትጥዓም ሞተ እሙ ወእመ ኲሉ፤ አዘዘ ወልድ በርቱዕ ቃሉ።

መልክአ ማርያም
ሰላም ሰላም ለዝክረ ስምኪ ሐዋዝ፤ እምነ ከልበኔ ወቊስጥ ወእምነ ሰንበልት ምዑዝ፤ ማርያም ድንግል ለባሲተ ዓቢይ ትእዛዝ፤ ይስቅየኒ ለለጽባሑ ወይነ ፍቅርኪ አዚዝ፤ ከመ ይሰቅዮ ውኂዝ ለሠናይ አርዝ።

ዚቅ
ለዛቲ ድንግል ሠረቀ ላዕሌሃ ብዕለ ጸጋሁ ለአብ፤ ወአግአዛ እምእኩይ ውስተ ሠናይ፤ እሞት ውስተ ሕይወት፤ ወረሰየ ይዝክሩ ስማ ውስተ ኲሉ ዓለም።

ወረብ
ለዛቲ ድንግል ሠረቀ ላዕሌሃ ብዕለ ጸጋሁ ለአብ/፪/
ወአግአዛ እምእኩይ ውስት ሠናይ እሞት ውስተ ሕይወት/፪/

መልክአ ማርያም
ሰላም ለእስትንፋስኪ ዘመዓዛሁ ሕይወት፤ ከመ መዓዛ ዕፅ ኅሩይ ዘውስተ ገነት፤ ማርያም ድንግል ቤተ ቅድሳት፤ ጽንሕኒ ውስተ ሠናይ ወሰውርኒ እሞት፤ በአክናፍኪ ርግብየ ኅሪት።

ዚቅ
አንጺሆ ሥጋሃ ቀዲሶ ኪያሃ፤ ኃደረ ቃል ላዕሌሃ፤ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ ወይቤላ ለድንግል፤ ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ ሰሎሞን ይቤላ እኅትየ መርዓት ርግብየ ሠናይት፤ ፍናወ ዚአኪ ገነት፤ እስመ ኪያኪ ኀረየ ለታዕካሁ፤ ከመ ትኩኒዮ ማኅደረ ለልዑል።

ወረብ
'አንጺሆ ሥጋሃ'/፪/ ላዕሌሃ ኃደረ/፪/
ቀዲሶ ኪያሃ 'ሃሌ ሉያ'/፪/ ይቤላ ለድንግል/፪/

መልክአ ማርያም
ሰላም ለገቦኪ ዘሐመልማለ ወርቅ ክዳኑ፤ በከመ ዳዊት ይዜኑ፤ ማርያም ድንግል ለያዕቆብ ሞገሰ ስኑ፤ በልኒ እግዝእትየ አፈቅረከ አኮኑ፤ እንዘ ረዳኢትከ አነ ዘይክለከ መኑ።

ዚቅ
እምሰማያት ወረደ ወገብረ መድኃኒተ በማዕከለ ምድር፤ ኖላዊ ኄር ኖላዊሆሙ ለ፳ኤል፤ ወረደ ስኖ ለያዕቆብ ዘአፍቀረ፤ ወስኑሰ ለያዕቆብ ዘይቤ ይእቲ ሥጋ እንተ ነሥአ፤ መድኅን እማርያም።

ወረብ
ወስኑሰ ለያዕቆብ 'ዘይቤ'/፪/ ያዕቆብ/፪/
'ይእቲ ሥጋ'/፪/ እማርያም እንተ ነሥአ መድኅን/፪/

መልክአ ማርያም
ሰላም ለፀአተ ነፍስኪ እንበለ
ፃዕር ወፃማ፤ ለነቢር ዘልፈ በየማነ ወልድኪ ፌማ፤ ማርያም ድንግል ለባሲተ ሞገስ ወግርማ፤ አጽንዒ በረድኤትኪ ለሕይወትየ ድካማ፤ እምሕይወተ ኄራን አበው ኢታሕጽጺ ዐቅማ።

ዚቅ
ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና ወረደ ወልድ እምዲበ ልዕልና፤ ጠሊላነ ንግሥ ሶቤሃ ከደና።

ወረብ
ጊዜ ዕረፍታ ለማርያም 'ጊዜ'/፫/ ዕረፍታ ለማርያም/፪/
ወረደ ወልድ ዲበ እምዲበ ልዕልና ወረደ/፪/

መልክአ ማርያም
ሰላም እብል በድነ ሥጋኪ ጽሩየ፤ ዘተመሰለ ባሕርየ፤ ማርያም ድንግል ዐጸደ ወይንየ፤ ንስቲተ ለዕበየኪ እንተ አቅረብኩ ግናየ፤ ኢይትኃደግ ዲበ ምድር ምሥጢ ሰማየ።

ዚቅ
ኦ ትቤ ማርያም እወጽእ እምዝንቱ ሥጋየ፤ ወአሐውር ውስተ ሕይወት ዘለዓለም፤ ኦ ተዘከርኬ ዮሐንስ ዘይቤለከ ሊቅ አመ ትረፍቅ ዲበ ዕንግድዓሁ።

መልክአ ማርያም
ሰላም ለግንዘተ ሥጋኪ በእደ ሐዋርያት አርጋብ፤ በአፈወ ዕፍረት ቅድው ዘሐሳበ ሤጡ ዕፁብ፤ ማርያም ድንግል ወለተ ኅሩያን ሕዝብ፤ ረሰይኩኪ እግዝእትየ ህየንተ እም ወአብ፤ ይሕፅነኒ ከመ ጥብ ፍቅርኪ ሐሊብ።

ዚቅ
ተጋብኡ በቅጽበት ለግንዘተ እሙ ቅድስት፤ ብፁዓን ሐዋርያት ቦኡ ኀቤሃ፤ በሰላም አምኁ ኪያሃ፤ በስብሐት ገነዙ ሥጋሃ።

መልክአ ማርያም
ሰላም ለመቃብርኪ ለጌቴሴማኒ በመርኅባ፤ እንተ ይእቲ ለኢየሩሳሌም ቅሩባ፤ ማርያም ድንግል ለሀገረ መንግሥት ርግባ፤ ትትሜጦ ወረቀ እምአፌር ወጸበለ አፈው እምሳባ፤ ጌቴሴማኒ ለሥጋኪ ምስካባ።

ዚቅ
ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ ዓውዳኒ ዘጽድቅ ወመርኅባኒ ዘዕንቊ፤ አንቀጸ አድኅኖ ሐዳስ ንጽቅ።

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…
Подписаться на канал