ortodoxmezmur | Неотсортированное

Telegram-канал ortodoxmezmur - ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

134932

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . ዝማሬ ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Подписаться на канал

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ይህን ማድረግ ቀናችሁን ቀና ያደርጋል።


በ2017 ዓ.ም ሕይወታችሁን የሚለውጥ አንድ ልማድ ላጋራችሁ! ሁልግዜ ጠዋት ስራም ሆነ ትምህርት ከመጀመራችሁ በፊት በዕለቱ የሚታሰበውን የአንድ ቅዱስ ታሪክ ከስንክሳር አንብባችሁ ጀምሩ።

እንደው ግዜ አጥሮአችሁ ስንክሳር ማየት ካልቻላችሁ ወይም ስንክሳር ከሌላችሁ ግን ሁልግዜ ጠዋት ጠዋት አንድ ሰዓት ላይ በዝማሬ ዳዊት የቴሌግራም እና የፌስቡክ ገጽ የአንድ ቅዱስ ታሪክ ከስንክሳር በአጭሩ ስለምንለቅ እርሱን ሳያነቡ በፍጹም እንዳይውሉ። እንዲሁም ጠዋት የምንለቃቸውን ዝማሬዎችም በማድመጥ ቀናችሁን በመንፈሳዊነት ጀምሩ።

መልካም አዲስ አመት

የዝማሬ ዳዊት ገጽ አስተዳዳሪዎች
👉 @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

እግዚአብሔር የሚወዳችሁ እናንተም የምትወዱት ልጆቼ!

አዲሱ ዓመት የእውነት አዲስ ዓመት እንዲኾንላችሁ ካሻችሁ ነፍሳችሁን ከኀጢአት ቀንበር አላቋት እንጂ ድጋሜ በኀጢአት ሸክም አትጫኗት፡፡ አሮጌው ዓመት እንዳለቀ ስታዩ እግዚአብሔርን አመስግኑት፡፡

ወደሌላ ዘመን አሸጋግሯቸዋልና እግዚአብሔርን አመስግኑት፡፡ ልቡናችሁንም ውቀሱት፡፡ በዕሜአችሁ ስንት ጊዜ እያለፈ እንደ ኾነ እያሰባችሁም ራሳችሁን እንዲህ ብላችሁ ጠይቁት፡-

ቀናት እየሮጡ ነው፡፡ ዓመታቱም እየነጐዱ ነው፡፡ የዕድሜዬ መንገድም እየተጋመሰ ነው፡፡ ታዲያ ምን በጐ ምግባር ያዝኩ? ከዚህ ምድር የማልፍበት ቀን እየቀረበ ነው፡፡ ታዲያ ምን የጽድቅ ሥራ ሠራሁ? በዚህ ዕድሜዬ መሥራት የነበረብኝ ምግባር ትሩፋት ዕድሜዬ ሲገፋ ማድረግ አልችልም፡፡ ታዲያ ዕድሜዬ ሲገፋ ማድረግ የማልችላቸውም የጽድቅ ሥራዎች (ፆም፣ ጸሎት፣ ስግደት፣ አገልግሎት፣… ዕድሜ ሲገፋ ይከብዳሉና) እንዳቅሜ እያደረግኩ ነውን? በማለት ልቡናችሁን ጠይቁት፡፡


ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🌼አምላክ ሆይ ባርክልን🌼

ውድ የዝማሬ ዳዊት ተከታታዮች እንኳን ከዘመነ ዮሐንስ ወደ ዘመነ ማቴዎስ በሰላም አሸጋገራችሁ።

የዝማሬ ዳዊት ቻናል ለመላው ሕዝበ ክርስቲያን መልካም አዲስ ዓመትን ይመኛል። መልካም በዓል🌼🌼🌼

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

"...ያክለ ክሙ ዘሐለፈ መዋዕል"
"...ያለፈው ዘመን ይበቃችኋል"

፩ኛ ጴጥ ፬ ÷ ፫


ውድ የዝማሬ ዳዊት ቤተሰቦች እንኳን ከዘመነ ዮሐንስ ወደ ዘመነ ማቴዎስ በሰላም አሸጋገራችሁ። የዝማሬ ዳዊት ቻናል ለመላው ሕዝበ ክርስቲያን መልካም አዲስ ዓመትን ይመኛል።

👉 @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🌼ዘመንን ሰጠኝ እንዳመሰግን🌼

ሳይቆጥር ለዚህ ያደረሰኝ
    ማነው እንደ እርሱ
ሳይተሳሰብ በደሌን ትቶ
     ጸጋ ሞገሱ
     ዘመንን ሰጠኝ
እንዳመሰግን በመቅደሱ

ይደንቀኛል ምህረቱ
ርኅራኄው ውበቱ
ገደብ አልባ ከፍታ
ፍቅር ልቡ የጌታ

          አዲሱን ቀን እንዳየው
         ጨለማዬን ሊያበራው
         ከዘመናት ስፋት ላይ
         አስጌጠልኝ በፀሐይ

አ/ዝ


ሲመግበው አለሙን
ሲያረሰርስ ቃዴስን
በፍቅር ዜማ ማራኪ
ወንዙን ውኃውን ባራኪ

            እስከ ልኩ እየሞላ
           ወይንን ጨምርኩ ዘለላ
           ባወድሰው ቀን በቀን
          አይገልጸውም ምሕረቱን

አ/ዝ


እያጠራው ሰማዩን
እየራሰ ምድርቱን
በከዋክብት አስውቦ
ጸጋ ምሕረት ደርቦ

        ተራራውን  ነቅሶታል
         ልምላሜ ኩሎታል
         ከዘመናት እፍታ
        ባርኮ ሰጠኝ ይቅርታ

አ/ዝ


አየዋለሁ ሲሰራ
ዘወትር ለኔ ሲራራ
ያስነባኛል ዘወትር
አዲሱን ቀን ሲቀምር

        አላፍርበት በስሙ
        ስለ ዳንኩኝ በደሙ
        የመውደዱን ፍለጋ
       ገዝቶ አሳየኝ በዋጋ

አ/ዝ


እያጠራው ሰማዩን
እየራሰ ምድርቱን
በከዋክብት አስውቦ
ጸጋ ምሕረት ደርቦ

         ተራራውን  ነቅሶታል
         ልምላሜ ኩሎታል
         ከዘመናት እፍታ
        ባርኮ ሰጠኝ ይቅርታ

ዘማሪ፦ ዲያቆን አቤል መክብብ

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​​​🌼 ልጄ ሆይ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ

ልጄ ሆይ....... ወጣትነት ፈትኖህ፤ለስጋህ አድልተህ፤ነፍስህን አቀጭጨኻት ከአለም የኖርክበትን ዓመትህን ጥለኸው በንሰሐ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ።

ልጄ ሆይ ..... በአዲስ አመት ለአምላክህ የሚገባህን ግብር ትፈፅም ዘንድ በፍቅሩ አፀድ እንድትገኝ ካለመታዘዘ ተለወጥ።

ልጄ ሆይ ....... በአፈር ከሚሸነፈው ስጋዊ ዘርህ ወጥተህ ሰማያዊነትን ከሚያለብስህ ከማይጠፋው ሰማያዊ ዘር ክብረት ታደርግ ዘንድ ሰውን ካለመውደድ ጥላቻ ተለወጥ።

ልጄ ሆይ ...... በምክንያቶች ተደልለህ አፅዋማትን ዘለህ፤ምስጋናን ነፍገህ፥አገልግሎትን ንቀህ ከአለም ጫጫታ ውስጥ የዘፈቀውን ማንነትህ እንዳያጠፋህ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ።

ልጄ ሆይ ...... ዲያቢሎስ በቃል እንዳያስትህ፤በማማለል እንዳይጠልፍህ የመንጋውን ጠባቂ ቃልን ስማ፤ የመታዘዝን በረከት ታገኝ ዘንድ ከትምህክትህ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ።

ልጄ ሆይ .....ቀናት ሳይሆን መንፈስህ ይለወጥ፤ፀሐይ ሳትሆን የህይወት ጀንበርህ ይለወጥ።

ልጄ ሆይ ......ዕለታት አይሰልጥኑብህ፤ ዘመናት እስከ ሞትህ ጥግ ድረስ እስኪገፉህ ሳትጠብቅ አንተም እንደ ዘመንህ ተለወጥ

ልጄ ሆይ .....የእግዚአብሔር ፍቅር ለተከፈተ ልብ ቸር ነው ። ርህራሄው ጥልቅ ነው ። በአምሳሉ ፈጥሮሃል እና እንዳትጠፋ አንድያ ልጁን ለሞት አሳልፎ እስከመስጠት የደረስ ጥልቅ ፍቅር አሳይቷል ። ስለዚህ ከዘመንህ ቀድመህ ተለወጥ።

ልጄ ሆይ ...አዛኝቷን ተለማመን፤መላአኩን ተማለደው ፤ቀደምት ቅዱሳን አባቶችህን ጥራ፤ ፃድቃንን ዘክር እንጅ ላለመለወጥ ተማምለው ቀናት ብቻ ከሚለወጥባቸው ሰልፈኞች ተርታ አትገኝ ።

በንስሐ ወደ በረቱ የምንመለስበት ዘመን ይሁንልን! አሜን

🌻 መልካም አዲስ አመት ይሁንልን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🌼ምስባክ
መስከረም 1/1/2017 ዓ.ም
🌼የዐውደ አመት ምስባክ🌼

ምስባክ ፦ መዝ 64 ÷ 11-13

ወትባርክ አክሊለ ዓመተ ምሕረትከ ።
ወይጸግቡ ጠላተ ገዳም ።
ወይረውዩ አድባረ በድው ።

ትርጉም ፦

በቸርነትኽ አመትን ታቀዳጃለኽ
ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል።
የምድረ በዳ ተራራዎች ይረካሉ
ኮረብታዎችም በደስታ ይታጠቃሉ።

🌼 @ortodoxmezmur 🌼
🌼 @ortodoxmezmur 🌼
🌼 @ortodoxmezmur 🌼

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​​​​​​​​​🌼 ዘመን መለወጫ

አስቀድመን ስለ ቅዱስ ዮሐንስ ማንነትና የዘመን መለወጫ መግቢያው ላይ በስሙ ስለመጠራቱ ተመልክተናል፡፡ ዘመን መለወጫ ደግሞ ለምን እንደተባለና ለምን መስከረም ወር ላይ እንደሆነ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን እንዲህ በማለት ያትታሉ፡፡

ሲያትቱም ብርሃናት/ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብት/ የዓመት ዑደታቸውን በጳጉሜ ወር ጨርሰው በመስከረም ወር ስለሚጀምሩ ነው፡፡ ያን ጊዜ ሌሊቱም ከቀኑ ጋር ይተካከላል፡፡ ዓመቱንም ጠንቀቀው ቢቆጥሩት ፫፻፷፬ ቀናት ይሆናል፡፡ ለዘመን መታወቂያ ይሆን ዘንድ ፀሐይና ጨረቃ ከዋክብትን ፈጠረ ይላልና /መጽሐፈ ሔኖክ ምዕራፍ ፳፩ ቁጥር ፵፱፡፡

በሌላ በኩልም በዘመነ ኖኅ ዓለምን ውኃ አጥለቅልቋት ከቆየ በኋላ ዳግመኛ ከነበረው ውኃ የተገለጠችበት ወር «በመጀመሪያም ወር በምድር ታየች የንፍር ውኃው ከምድር ደረቀ» የሚለውን መሠረት አድረገው የአቡሻኽር ሊቃውንት የዘመን መለወጫን ታሪካዊ አመጣጥ ያስረዳሉ፡፡ /መጽሐፈ ኩፋሌ፡ ምዕ ፯ ቁጥር ፩/

በመሠረቱ ዘመን ተለወጠ ሲባል የሚለወጡት ወራቱ ብቻ አይደሉም፡፡ በወቅቱ የሚከሰቱት/የተከሰቱት/ መልካምም ሆነ ክፉ ነገር /ገጠመኝ ሲሆን ወራቶቹ ግን ያው በየዓመቱ እየተፈራረቁ ይመጣሉ፡፡ ዘመን መለወጫ ላይ የሰው ልጆች ሕይወት ሊለወጥ ይገባል፡፡

ተማሪው ተምሮ ወደቀጣዩ ክፍል /ደረጃ/ የሚለወጥበት፣ ገበሬው የክረምትን ወራት በሚገባ ተጠቅሞ የሚቀጥለውን የበጋወራት የሚቀበልበት፣ ሠራተኛው የክረምቱን ዝናብ ታግሶ የፀሐይን ወራት የሚቀበልበት ሌላውም እንደዚያ ሆነው ወራቶቹ በዚያ ዘመን ያለው የተፈጥሮ ክስተቶች የሚለወጥበት ዘመን ተለወጠ እየተባለ ይነገራል፡፡

👉 በቀጣይ የዕንቁጣጣሽ ስያሜ አመጣጥ?

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ይቺን ዓመት ተወኝ

ከአመት እስከ አመት ፍሬን ሳላፈራ ደረቅ እንደሆንኩኝ
በራድ ወይም ትኩስ ሁለቱንም ሳልሆን እንዲያው ለብ እንዳልኩኝ አለሁኝ በቤትህ ለሙን መሬትህን እንዳጎሳቆልኲኝ

አውቃለሁ አምላኬ ፍሬን ለመቀበል እንዳመላለስኩሁህ
ዛሬም ሳላፈራ እሾህን አብቅዬ ደርቄ ጠበኩህ
ያልተደረገልኝ ያላፈሰስክብኝ ያልሰጠኸኝ የለም
ነገር ግን ይህ ሁሉ አላርምህ አለኝ አለየኝም ከዓለም
አዝ
የማትሰለቸኝ ሆይ ተነስቼ እስክቆም እባክህ ታገሰኝ
የኔን ክፋት ተወው መላክህን ሰምተህ ይቺን ዓመት ተወኝ
አዝ
አውቃለሁ ታውቃለህ ቀጠሮን ሰጥቼ እንደማላከብር
ብዙ ጊዜ አቅጄ ብዙ ጊዜ ዝቼ በወሬ እንደምቀር
ዘንድሮስ እንዳልኩኝ አምና ይሔን ጊዜ ሰምተኸኝ ነበር
ምንም ሳልለወጥ ዘንድሮዬ አልፎ በአዲስ ተቀየረ
አዝ
ፍሬ የማይወጣኝ እኔን በመኮትኮት እጆችህ ደከሙ
እኔ ግን አለሁኝ ዛሬም አልበቃኝም በኃጢአት መታመሙ
የቃልህን ውሃ በድንጋይ ልጅህ ላይ ሳታክት ስታፈስ ዘመን ተቆጠረ
ወደ ልቤ ሳይሰርግ ሕይወቴን ሳይለውጥ እንዲያው ፈሶ ቀረ
አዝ
ቃልህን ጠግቤ እያገሳሁት ነው ሌሎች እስኪሰሙ
በቃልህ መኖር ግን አልያዝህ አለኝ ከበደኝ ቀለሙ
ብዙ ጥቅስ አገኘው ከቅዱስ መጽሐፍህ ገልጬ አይቼ
ከራሴ ላይ ብቻ አንድ ጥቅስ አጣሁኝ በበደል ተኝቼ
አዝ
ውጤቴ ደካማ ትምህርት የማይሰርፀኝ ተማሪ ብሆንም
ይቺን ዓመት ተወኝ ደግሞ ትንሽ ልማር ታገሰኝ አሁንም
እባክህ አልቆረጥ በቅዱስ መሬትህ ልቆይ ፍቀድልኝ
ያፈሩት ቅዱሳን የፍሬያቸው ሽታ መዓዛ እንዲደርሰኝ
አዝ
የተሸከምከኝ ሆይ ዛሬም ተሽከመኝ አትሰልቸኝ አደራ
ማን ይታገሰኛል ጠላት እየሆንኩት አይሰሩ ስሰራ
አታውጣኝ ከቤትህ ብዙ ቦታ አልይዝም ፍሬ ስለሌለኝ
ስፍራ የማያሻኝ ቤት የማላጣብብ ፍሬ አልባ በለስ ነኝ
አዝ
ቦታስ የሚይዙ ባለምግባሮቹ ቅዱሳንህ ናቸዉ
ልክ እንደ ዘንባባ የተንዥረገገ ተጋድሎ ፅድቃቸው
ከሊባኖስ ዝግባ እጅጉን የበዛ ገድል ትሩፋታቸው
አዝ
እኔ አይደለሁም ቦታስ የሞትይዘው ያንተው እናት ናት
ስሮቿ በምድር ጫፎቿ በሰማይ ሲደርሱ ያየናት
ይቺን ዓመት ተወኝ ከስሯ ሆናለው ባፈራ ምናልባት
አዝ
ይቺን ዓመት ተወኝ እባክህ አምላኬ አንድ ዓመት ምንህ ናት
ሺ ዓመት አንድ ቀን አይደለም ወይ ላንተ ዓመት ኢምንት ናት
ይሔ ዓመት አልፎ ዳግም ዓመት ስጠኝ እስከምልህ ድረስ
እባክህን ጌታ ይቺን ዓመት ተወኝ የወጉን እንዳደርስ

ዘማሪ ዲያቆን ቀዳሚ ጸጋ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ጷጉሜ 5


አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስቅዱስ ስም ጷጉሜ አምስት በዚች ቀን ንፁሕ ድንግል አባት፤ የምስር ሀገር ኤጲስቆጶስ አባ ያዕቆብ አረፈ።

አባታችን ገና በታናሽነቱ የምንኩስናን ልብስ ይለብስ ዘንድ ነፍሱ ወደደች ከሀገሩም ወጥቶ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔደና በአባ ዮሐንስ ሐጺር በዓት ውስጥ በጽኑ ተጋድሎ ኖረ።

የደግነቱ የትሩፋቱና የቅድስናውም ዜና ተሰማ በእግዚአብሔር ፈቃድ በምስር ሀገር ላይ ኤጲስቆጶስነት ሾሙት። በሹመቱ ወንበርም በተቀመጠ ጊዜ ጾምን ጸሎትን ተጋድሎውንም ጨመረ።

ስለ ሹመቱም ተጋድሎውንና አገልግሎቱን አበዛ እንጂ ቸልም አላለም።


ሕዝቡንም ሁልጊዜ ያስተምራቸዋል ኃጢያትን በመስራት የሚኖሩትን ይገስጻቸዋል። በንስሐ እስኪመለሱም ሥጋውና ደሙን ከመቀበል ያግዳቸዋል።

በጎ ተጋድሎንም በፈጸመ ጊዜ ጥቂት ታመመ መንጋዎቹንም ጠርቶ በቀናች ሃይማኖት እንዲጸኑ አዘዛቸው። ካህናቱንም ጠርቶ በጸሎትና
በአገልግሎት ጊዜ ቸል እንዳይሉ አዘዛቸው። በዚህች ዕለትም አረፈ።

በረከቱ ይደርብን! አሜን
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​🌼 አበባ አየሽ ወይ 🌼

እሰይ /ደስ ደስ ይበለን/(2)
አዲሱ አመት መጣልን ደስ ደስ ይበለን

ሆ ብለን መጣን ሆ ብለን(2)
ጌቶች አሉ ብለን
ሆ ብለን መጣን ሆ ብለን(2)
እሜቴ አሉ ብለን
ሆ ብለን መጣን ሆ ብለን(2)
ዘመን መጣ ብለን

አበባ አየሽ ወይ           ለምለም(2)
ባልንጀሮቼ                        "
ግቡ በተራ                       "
በእግዚአብሔር መቅደስ     "  
በዚያች ተራራ                   "   
እንድታደንቁ                      "          
የአምላክን ሥራ                 "    
ህይወት ያገኛል                 "  
እርሱን የጠራ                    "      

አበባ አበባ ፈካ ዘመን ሲተካ(2)

አበባ አየሽ ወይ          ለምለም (2)
ክረምት አለፈ                   "
ጨለማው ጠፋ                "   
የመስቀሉ ቃል                  "
ሆነልን ደስታ                    "   
እናገልግለው                   "  
ቤቱ ገብተን                     "     
ትንሽ ትልቁ                      "  
ተሰልፈን                         "        

አበባ አበባ ፈካ ዘመን ሲተካ(2)

አበባ አየሽ ወይ     ለምለም(2)
ያንን ኩነኔ                    "
ዘመነ ፍዳ                    " 
የሞቱ በራፍ                 "
ያ ምድረበዳ                 "
ልክ አንደ ክረምት         "
ሄደ ተገፎ                    "
ፀሐይ ወጣልን             "
ጨለማው አልፎ           "

አበባ አበባ ፈካ ዘመን ሲተካ (2)

አበባ አየሽ ወይ         ለምለም(2)
ይኸው መስከረም           "
ይኸው ፀሐይ                 "    
ንጉሡ ወርዶ                  "       
ከላይ ሰማይ                  "        
አውደ ዓመት ሆነ            "
ደስታ ሰላም                   "
ፍቅር ሲገለጥ                "   
በአርያም                       "       

አበባ አበባ ፈካ ዘመን ሲተካ(2)

አበባ አየሽ ወይ         ለምለም(2)
ይኸው አበባ                  "
ለምለም ቄጤማ             "
አዲሱ ዘመን                  "
አምጥቷልና                    "    
በሩን ክፈቱ                     "       
መኳንንቶቹ                     "       
የክብር ንጉሥ                 "    
ይግባ ቤታችሁ               " 

አበባ አበባ ፈካ ዘመን ሲተካ(2)

አበባ አየሽ ወይ         ለምለም(2)
ቤታችሁ ይሙላ             "
ሰላም ደስታ                   "
ሰጥቷችሁ እርሱ            "
የሁሉ ጌታ                     "      
ከዘመን ዘመን                "     
ያሸጋግራችሁ                "      
የሽበትን ዘር                  "   
ይሸልማችሁ                 "      

አበባ አበባ ፈካ ዘመን ሲተካ

ይሸታል ዶሮ ዶሮ የእማምዬ ጓሮ
ይሸታል ጠጅ ጠጅ የአባብዬ ደጅ

አብዬ ኧኸ ደግሞም እማምዬ
መጣሁ ለሰላምታ ከቤት አሉ ብዬ
እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሰዎት ብዬ

ከብረው ይቆዩን ከብረው
የክብርን ወንጌል ሰምተው
የበጉን ሥጋ በልተው
የአምላክን ፊቱን አይተው
ከብረው ይቆዩን ከብረው

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ጎሳ ልብየ

ጎሳ ልብየ ቃለ ሰናየ/2/
ወአነ አይድ ቅዳሴሃ ለማርያም/2/

እኔስ የማርያምን ውዳሴዋን እናገራለሁ
እንደ አባቴ ዳዊት በበገና እዘምራለሁ
ቀን ከሌሊት ሳልል ለምስጋና እተጋለሁ
የኃጢአቴ ቁስል እንዲፈወስ እጮሃለሁ
ምርኩዜ ነሽና እመቤቴ በአንቺ እመካለሁ

አዝ

ኦ...እመቤቴ በእውነት እንወድሻለን
የእውነተኛ መብል ክርስቶስን ወለድሽልን
ምክንያተ ድሂን ሆይ ድንግል ማርያም የአምላክ መገኛ
በአማላጅነትሽ በመታመን እንጮሃን እኛ
ምሕረትን አድይን ኪዳነምህረት የዓለም መዳኛ
አዝ

ስለ ቸርነትሽ እመቤቴ ለእኔ እናቴ ነሽ
ስለ ንግሥትነትሽ እመቤቴ ነሽ
ዝናባት ሳያጠጡት አየራት ሳያሳድጉት
ሰማያዊ እንጀራ የሰጠሸን ቤተልሔማዊት
ቅድስተ ቅዱሳን የኖህ መርከብ የአምላክ እናት
አዝ

ቃና ዘገሊላ በሰርጉ ቤት በዚያ ተገኝተሽ ሳለሽ
ውኃውን ወደ ወይን ባንቺ ምልጃ እዳስለወጥሽ
ዛሬም የእኔ ሕይወት ወይኑ አልቆ ባዶ ሆኖአልና
አንቺየአምላክ እናት ንጽሂትቅድስት ርኅሪሂተ ህሊና
ሕይወቴን አድሰሽ ቀድሰሽ ሙይው በምስጋና

ዘማሪ ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ጷጉሜ 4


አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስቅዱስ ስም፤ ጷጉሜ አራት በዚች ቀን ተጋዳይ አባ ባይሞን አረፈ። አባ ባይሞን የተባረኩ ስድስት ታላላቅ መነኮሳት ወንድሞች ያሉት ሲሆን ከኮከብም ኮከብ ይበልጣልና ከስድስቱ ቅዱሳን እርሱ የተለየ ነበር።

መንፈስ ቅዱስ አነሳስቷቸው ሁሉም በአንድ ቀን መነኮሱ። ለእናታቸውም እንዳይቸግራት የሚያስፈልጋትን ሁሉ ካዘጋጁ በኋላ ይህን ዓለም ንቀው ወደ ገዳም ተጉዘው በአንዲት በዓት አረፉ።

አባ ባይሞን በአስቄጥስ ገዳም ፈተና፣ የሃይማኖት ጥርጥርና ደዌ ያገኘውን ሁሉ ይፈውስ፣ያረጋጋም ነበር። ስለ ምንኩስና ሕግ፣ስለ መጋደል እና ስለ አምልኮም ብዙ ድርሳናትን ደረሰ።

ዕድሜውንም በተጋድሎና በትሩፋት ሥራ ከፈጸመ በኋላ ወደ መልካም ዕርግና ደርሶ እግዚአብሔርን አገልግሎ አረፈ።

አባታችን እንዲም ይሉናል
እኛ የወንድማችንን በደል ብንሰውር እግዚአብሔርም በደላችንን ይሠውርልናል።


በረከቱ ይደርብን! አሜን
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

✞ ሩፋኤል ብዬ ✞

ሩፋኤል ብዬ ስጠራው ምስጢሬን ሁሉ ሳወራው
ትላንት የረዳኝ ጸሎትህ ዛሬም ይድረሰኝ ለልጅህ

ሩፋኤል ብዬ  አንደበቴ ለምዶት ስምህን
ሩፋኤል ብዬ  ልጅነቴ  ቀምሶት ፍቅርህን
ሩፋኤል ብዬ የህይወቴ ቅጥር ሲላላ
ነፍሴ ትጮሀለች ሩፋኤል ሩፋኤል ብላ አዝ
ሩፋኤል ብዬ ከአምላኬ ስትላክ ለምህረት
ሩፋኤል ብዬ ስትጠብቀኝ ቀንና ለሊት
ሩፋኤል ብዬ ባስከፋህ በትግስት እለፈኝ
ምልጃህ እረድኤት ያግዘኝ እኔን ይደግፈኝ
አዝ
ሩፋኤል ብዬ ህመሜ እንዳይጸና ክፋቱ
ሩፋኤል ብዬ መድሐኒት እንዲሆን ሀሞቱ
ሩፋኤል ብዬ  ካጠገቤ እንዳትርቅ ከጎኔ
ትዳሬ እንዲጸና ሩፋኤል እንዲበራ አይኔ
አዝ
ሩፋኤል ብዬ ከአምላኬ ስትላክ ለምህረት
ሩፋኤል ብዬ ስትጠብቀኝ ቀንና ለሊት
ሩፋኤል ብዬ ባስከፋህ በትግስት እለፈኝ
ምልጃህ እረድኤት ያግዘኝ እኔን ይደግፈኝ

ዘማሪ ሚኪያስ መንገሻ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​ፈታሔ ማሕፀን

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ " የዘለዓለም ሕይወትን እንዲወርሱ ቅዱሳን መላእክት ምእመናን ለመርዳት ለማገልገል ከእግዚአብሔር የሚላኩ ረቂቃን ፍጥረታት አይደሉምን? ( ዕብ ፩÷፲፬) ብሏል። ቅዱስ ዮሐንስም "የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ"( ራእዩ ለዮሐንስ ፰÷፬) በማለት ተናግሯል።

ቅዱሳን መላእክት ያለማያቋረጥ ለፈጣሪያቸው ምስጋና የሚያቀርቡ ረቂቃን ፍጥረታት ናቸው። በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ለተልእኮ ይፋጠናሉ። የሰውን ጸሎትና ልመና ወደ እግዚአብሔር ያደርሳሉ፤ የእግዚአብሔርን ቸርነትና ምሕረት ወደ ሰው አድርሰው በእምነት ያጸናሉ። "በእግዚአብሔርም ፊት የሚቆሙትን ሰባቱን መላእክት አየሁ፥ ሰባትም መለከት ተሰጣቸው" (ራእ. ፰÷፪) የሚለው የሚያስረዳን ለተልእኮ መፋጠናቸውን ነው። ሄኖክም “በሰው ሰውነት ላይ የተሾሙ ከከበሩ ፯ቱ ሊቃነ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል አንዱ ነው” (ሄኖ.፮÷፩-፵፪) ብሏል።

የሰዎችን ልመና ወደ እግዚአብሔር፣ የእግዚአብሔርን ምሕረት እና በረከት ወደ ሰው የሚወርድባት ዕለት"ርኅወተ ሰማይ” ትባላለች። ይህች ዕለት የሰዎች ሁሉ ጸሎት የሚያርግባት፣ አራተኛው መጋቢ ኮከብ የሚያልፍባት፣ ለሰው ልጆች ከፈጣሪያቸው ጸጋ በረከት የሚሰጥባት ስለሆነች "ርኅወተ ሰማይ-ሰማይ የሚከፈትባት ቀን" ትባላለች። እንዲህ የሚባለው በሰማይ መዘጋት መከፈት ኑሮበት አይደለም። የሰው ልጆችን ልመና ቅዱሳን መላእክት የሚያሳርጉበት፣ አንድም ቅዱስ ሩፋኤል የዓመቱን የጸሎት መዝገብ የሚከፍትበት ቀን ስለሆነ እንጂ።

ቅዱስ ሩፋኤል ልቡናን ደስ የሚያሰኝ፣ ባለ መድኃኒት፣ የጸሎት መዝገብ መክፈቻ ቍልፍ የተሰጠው፣ የሴቶችን ማሕጸን የሚፈታና ሳይጨነቁ እንዲወልዱ ምጥን የሚያቀል መልአክ ነው። "ለሰብእ ወለእንሰ ፈታሔ ማሕጸኖሙ አንተ" እንዲል። የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ወደ ከበረና ወደ ገነነ ወደ እግዚአብሔር ጌትነትም ከሚያገቡ ከከበሩ መላእክት መካከል አንዱ እኔ ሩፋኤል ነኝ "(ጦቢያ ፲፪÷፲፭) የሚለው የሚያስገነዝበው ተራዳኢነታቸውን፣ ባለሟልነታቸውን፣ አማላጅነታቸውን ነው።

ጸሎትህና ምጽዋትህ በእግዚአብሔር ፊት ለመታሰቢያ እንዲሆን ዐረገ"(ሐዋ. ፲÷፬) የሚለው የመላእክትን አገልግሎት የሚገልጥ ነው። መላእክት ሰዎችን ይራዳሉ፣ የሰውን ጸሎት ያሳርጋሉ፣ ያማልዱሉ፣ ሰዎችን ከመከራ ነጥቀው ያወጣሉ። "የእግዚአብሔርም መልአክ መልሶ። አቤቱ፥ የሠራዊት ጌታ ሆይ፥ እነዚህን ሰባ ዓመት የተቈጣሃቸውን ኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ከተሞች የማትምራቸው እስከ መቼ ነው? አለ፣ እግዚአብሔርም መልሶ ከእኔ ጋር ይነጋገር ለነበረው መልአክ በመልካምና በሚያጽናና ቃል ተናገረው። ስለዚህም ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረው መልአክ እንዲህ አለኝ። ስበክ እንዲህም በል። የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል (ዘካ፣ ፩÷፲፪÷፲፬) የሚለው አማላጅነታቸውን የሚገልጥ የማጽናኛ ቃል ነው።

ጦቢያና መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ወደ ራጉኤል ቤት በደረሱ ጊዜ ሣራ ተቀብላ ደስ አሰኘቻቸው። መልአኩም ለጦቢያ አባትህ ከዘመዶችህ ወገን አግባ ያለህን ቃል አስብ አለው። ራጉኤልም ልጁ ሣራን ለጦቢያ አጋባት። ተመግበውም ከጨረሱ በኋላ ጦቢያን ወደ እርሷ አገቡት፤ ወደ እርሷም በገባ ጊዜ የመልአኩ የቅዱስ ሩፋኤልን ነገር አሰበ፤ የዕጣን እራሪ ወሰደ፤ ከዚያም ዓሣ ከልቡና ከጉበቱ ጨምሮ አጤሰው። ሽታውም ያን ጋኔን በሸተተው ጊዜ እስከ ላይኛው ግብፅ አውራጃ ድረስ ሸሸ። መልአኩም ጋኔኑን አሰረው( ጦቢ ፰÷፩) የተባለው የሚያስረዳን የመላእክትን ተራዳኢነት ነው።

ጦቢያ የሰርጉን በዓል በጨረሰ ጊዜ ወደ አባቱ ቤት ከሚስቱ ከሣራና ከመልአኩ ከቅዱስ ሩፋኤል ጋር ተመለሱ። ሩፋኤልም አለው፥ "ያባትህ ዐይኖች እንዲበሩ አውቃለሁ፤ አንተ ግን ያን ሐሞት ያባትህ ዓይን ኳለው፤ በተኳለም ጊዜ ብልዙ ከአይኑ ይወጣል በደህናም ያያል። ጦቢያም የአባቱን አይን ኳለው ዓይኑም በራለት”( ጦቢ ፲፩÷፮) ተብሎ እንደተነገረው እግዚአብሔር ከዚህ ክፉ ወረርሽኝ ጠብቆን በሰላም በጤንነት ለሚመጣው ዓመት ያድርሰን። የጦቢትን ዓይን ያበራውን የቅዱስ ሩፋኤልን ዓመታዊ በዓል አክብረን በረከት ለማግኘት ያብቃን።አሜን!!

ዲ/ን ተመስገን ዘገየ
ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🌼 እንደምን በረታች 🌼

እንደምን በረታች ዳነች ሰውነቴ
ብትወደኝ እኮ ነው አቤት መድኃኒቴ
ይቺን ዓመት ደግሞ አንተ ብትተወኝ
ወዳጄ  መውደድህ ፍቅርህ አስለቀሰኝ ×2

የአህዛብን ፈቃድ ያደረኩበት ቀን
እንደምን ይቆጠር ገብቶ በእኔ ዘመን
ካየሁ ጀምሮ ይቆጠር እድሜ
ሳላውቀህ የኖርኩት እኔ አይደል ጌታዬ
×2

አዝ

የትግስት መጠን ስፋቱ ጥልቅ ነው
ሁሌም እያጠፋሁ ቃልህ የፍቅር ነው
ረቡኒ ተናገር ላድመጥ በዝምታ
እስራቴ ይውለቅ ስትናገር ጌታ
×2
አዝ

በእኔ ውስጥ ምሰሶ እያለ ተጋርዶ
አይኔ ያያል የሰው የበደልን ነዶ
አልታዘዝ ብዬ ልቤን ሳትታዘብ
ሰው እየከሰስኩም አደረከኝ ገንዘብ
×2
አዝ

ሰው ፊትን እያየ ሞገስን ሲያበዛ
ሚዛንህ ልብ ነው የዓለሙ ቤዛ
ከአገር የሰፋውን የእኔን እዳ ምህረ
ለትንሽ ስጨክን ይቅር አለኝ ፍቅር
ከአገር የሰፋውን የእኔን እዳ ምህረ
ለትንሽ ስጨክን ይቅር አለኝ ልብህ

ስላልተውከኝ ክበር ስላልተውኝ ንገስ
የልቤ መድኃኒት ተስፋዬ ኢየሱስ
×2


ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🌼 አዲስ ዘመን አየን🌼

ኧኸ በጽድቃችን አይደል
ኧኸ በመልካም ስራችን
ኧኸ በቸርነቱ ነው
ኧኸ ለዚህ የደረስን
መውጣት መግባታችን እርሱ ሲፈቅድ ነው
አዲስ አመት አየን ከሞት የተረፍነው

ሜዳው ምድረ በዳው ደምቆ በአበባ
አዲስ ቀን ተሰጠን ይሄው ዘመን ጠባ
የሰማይ ጠል ወርዶ ምድር ረሰረሰ
ዝማሬን ይሰዋ ለዚህ የደረሰ

አ/ዝ


ዘመን አክሊል ሆነ የክብር ሽልማት
ባርኮ ሲለግሰን የምሕረትን ዓመት
የሚያስፈልገንን ስለሚያውቅ ቀድሞ
ለንስሐ ሰጠን ዛሬን እንደከርሞ

አ/ዝ


መልካሞች ቀኖችን ማየት የሚፈልግ
ከክፋ እርቆ መልካም ነገር ያድርግ
ዘመን የሚከፋው መልካም የሚያደርገው
የሰው ልጅ ሕይወት ነው ሁሉን የሚያበጀው

አ/ዝ


ጆሮ ስንቱን ሰማ ስንቱን አየ አይናችን
ባሳለፍነው አመት ባሳለፍነው ዘመን
ዳግመኛ ከቸርከን ፈቅደህ እንድንኖር
የእርቅ አድርግልን የሰላም የፍቅር

አ/ዝ


ሰዓታትን በቀን ቀንን በሳምንታት
እያፈራረቀ ወራትን በአመታት
በበዛው ምህረቱ ጨመረልን እድሜ
ለመንግስቱ ግዛት የለውም ፍጻሜ

ዘማሪ ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🌼 አምላክ ሆይ ባርክልን በዓሉን 🌼
                                           

አምላክ ሆይ ባርክልን በዓሉን /2/      

ባርክልን ኧኸ በዓሉን
ለዛሬ ዓመት ኧኸ አድርሰን
ሠላም ፍቅር ኧኸ አድለን
በዕምነታችን ኧኸ አበርታን
በአንድነት ኧኸ አቁመን                             
አምላክ ሆይ ባርክልን በዓሉን /2/                 

ጽኑ ሠላም ኧኸ ለሐገሪቱ
እንዲጦሩ ኧኸ አዛውንቱ
ወጣቱ እና ኧኸ ሕጻናቱ
ያለ ጊዜ ኧኸ እንዳይሞቱ
አንድም ሳይጎድል ኧኸ በመሃላችን
ለዓመት ያብቃን ኧኸ አምላካችን                                  
አምላክ ሆይ ባርክልን በዓሉን /2/               

አገልጋዩን ኧኸ ከመቅደሱ
እንዲኖሩ ኧኸ ሲያወድሱ
ታቦቱንም ኧኸ ከመንበሩ
አታናውጠው ኧኸ ከደብሩ
ወታደሩን ኧኸ በድንበሩ
ጠብቅልን ኧኸ በበረከት
ቸሩ ጌታ ኧኸ የፍቅር አባት       
ድንግል ሆይ ባርኪልን በዓሉን /2/                  

ለባርኮ ኧኸ አውደ ዓመት
ንዒ ማርያም ኧኸ በምሕረት
ያዘነው ኧኸ እንዲጽናና
የተከዘው ኧኸ እንዲል ቀና
በሐገር ውስጥ ኧኸ ውጭም ላለው
በበረከት ኧኸ አትለይው                             
ድንግል ሆይ ባርኪልን በዓሉን                   

የናቁሽም ኧኸ ጽዮን ብለው
ይሠግዳሉ ኧኸ ፊትሽ ወድቀው
ካኅናቱ ኧኸ በማሕሌቱ
በቅዳሴው ኧኸ በሠዓታቱ
ከልጅሽ ጋር ኧኸ ከዓለም ጌታ
ዘመሩልሽ ኧኸ በዕልልታ
                           
ድንግል ሆይ ባርኪልን በዓሉን               
ባርኪልን  ኧኸ /4/

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

መስከረም 1 


በዚህች ቀን ከአስራሁለቱ ሐዋርያት አንዱ የሆነው በርተሎሜዎስ ምስክር ሆኖ አረፈ።

ወንጌልን እዲሰብክ የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ተመርጦ ወደ ተለያዩ ሀገሮችና እግዚአብሔርን ወደማያውቁ ሰዎች እየተላከ  ወንጌልን እየሰበከ፣ እያስተማረና፣ ተአምራትን እያደረገ ሕዝቡን ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር እየመለሰ ኖረ።

ሙታንን እያስነሳ፣ የተቆረጡ በሰው እጅ ላይ ያሉ የወይን ቅርንጫፎችን ፍሬ እንዲያፈሩ እያደረገና ብዙ ድንቅ ተአምራትን እየሰራ ሕዝቡን ይመልስ ነበር።

በአንድ ሀገር የነበረ ንጉስ አግሪጳም ስለርሱ በሰማ ጊዜ በከበረ ሐዋርያ በርተሎሜዎስ ላይ እጅግ ተቆጣ በማቅ ከረጢት ውስጥ እንዲያደርጉትና አሸዋ ሞልተው ከባሕር እንዲጥሉት አዘዘ እንዲሁም ይህን አደረጉበት። ምስክርነቱንና ተጋድሎውንም በዚች ዕለት ፈጸመ።

በረከቱ ይደርብን! አሜን
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

"...ያክለ ክሙ ዘሐለፈ መዋዕል"
"...ያለፈው ዘመን ይበቃችኋል"                        

      ፩ኛ ጴጥ ፬ ÷ ፫


👉 @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🌼ምስባክ

መስከረም 1/1/2017 ዓ.ም

🌼በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ
መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ።

ዲያቆን፦ 2 ቆሮ 6÷1-11
ንፍቅ ዲያቆን፦ ያዕ 5÷8-13
ንፍቅ ካህን፦ ግብረ ሐዋርያት፦ 5÷12-17

ምስባክ ፦ መዝ 141÷ 6-8

አድኅነኒ እምእለ ሮዱኒ እስመ ይኄይሉኒ።
ወአውጽኣ እሞቅሕ ለነፍስየ።
ከመ እግነይ ለስምከ እግዚኦ።

ትርጉም ፦

እጅግ ተቸግሬያለኹና ወደ ልመናዬ አድምጥ
በርትተውብኛልና ከሚያሳድዱኝ አድነኝ።
አቤቱ ስምክን አመሰግን ዘንድ።

ወንጌል ፦ ማቴ 11÷1-20
ቅዳሴ ፦ ዘወልደ ነጎድጓድ

🌼 @ortodoxmezmur 🌼
🌼 @ortodoxmezmur 🌼
🌼 @ortodoxmezmur 🌼

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​​​​​🌼 "የዕንቁጣጣሽ" ሥያሜ አመጣጥ?

ዓመታት ተፈጽመው አዲስ ዓመት ስንጀምር ቅዱስ ዮሐንስ፣ ዓውደ ዓመት፣ አዲስ ዓመት ፣ ዕንቁጣጣሽ እየተባለ ይጠራል፡፡ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን እንደሚያስረዱት ዕንቁጣጣሽ የሚለው ስያሜው አመጣጥ ወይም ጥንተ ታሪክ በመጀመሪያ ኖኅ ለሦስቱ ልጆቹ አህጉራትን በዕጣ ሲያካፍላቸው አፍሪቃ ለካም ደረሰችው፡፡

በአፍሪቃ ምድርም ሲገባ በመጀመሪያ ያረፈው በኢትዮጵያ ነበር፡፡ ሀገሪቱም በአደይ አበባ አሸብርቃ ነበር፡፡ ወሩ ወርኃ መስከረም በመሆኑ ደስ ብሎት «ዕንቁ ዕጣ ወጣሽልኝ» ይህችን ወቅት እንቁጣጣሽ ብሏታል፡፡

ሁለተኛው ደግሞ የሀገራችን ንግሥት ንግሥተ ሳባ የንጉሥ ሰሎሞንን ዜና ጥበብ እየሰማች ስታደንቅ ትኖር ነበር፡፡ በጆሮዋ የሰማችውን በዓይኗ ዓይታ ለመረዳት ስለፈለገች በግመሎች ላይ ሽቱና እጅግ ብዙ ወርቅ እንዲሁም በኢትዮጵያ የሚገኝ በኢየሩሳሌም የማይገኝ ልዩ ልዩ ገጸ በረከት አስጭና ከብዙ ሠራዊት ጋር ወደ ኢየሩሳሌም ገባች፡፡

ከንጉሡ ሰሎሞንም ጋር ተገናኝታ የያዘችውን ገጸ በረከት ከሰጠችው በኋላ ብዙ ነገሮችን ጠየቀችው፡፡ እርሱም አንድ ነገር ላይ ሰውሮ ሁሉንም ገለጸላት፡፡ ቤተ መንግሥቱንም፣ በቤተ መንግሥቱ የሚገኙ እጅግ በጣም የከበሩ ዕቃዎችን ሁሉ አስጎበኛት፡፡

ሲያበቃ «ዕንቁ ለጣትሽ ጌጥ ይሁንልሽ» ሲል እጅግ በጣም የከበረ ዕንቁ አበረከተላት/ሰጣት/፡፡ ወሩም ወረኃ መስከረም ነበር፡፡ ከዚህ በመነሣት እንቁጣጣሽ የሚለው መጥቷል፡፡ አሁን ከሚፈጸመው ሥነ ሥርዓት ደርሶ በመፈጸም ላይ ይገኛል፡፡ የሚከበረውም መስከረም አንድ ቀን ነው፡፡

አንድም «ዕንቁ ዕፅ አወጣሸ» ብሎ የአበባውን መፈንዳትን ያስረዳናል፡፡

መልካም አዲስ አመት ይሁንልን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ይችን አመት ተወኝ

እንኳን ከዘመነ ዮሐንስ ወደ ዘመነ ማቴዎስ በሰላም አሸጋገራችሁ።

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🌼ዘመን ተሰጠን🌼

ዘመን ተሰጠን ለምስጋና
ዘመን ተሰጠን ለውዳሴ
ተመስገን ሥላሴ

ቸርነትን ሰጠን ዘመን ለፍስሐ
ይቺም እድሜ ለእርቅነች ለንስሀ
ጥበባችን መቼ ሆነ እውቀታችን
ምሕረትህ በዝቶልን ነው መቆማችን

ከሰጠኸን አዲስ ዓመት
ከሰጠኸን አዲስ እለት
እንዘምራለን በደስታ በአኮቴት

አዝ🌼

የለውም ጫፍ የለው ድንበር ያንተ ምህረት
በእድሜያችን ጨመርክልን ይህቺን እለት
ተደነቅን ተገረምን በአንተ ፀጋ
ቀንና ለሊት ሲፈራረቅ ክረምት በጋ

ከሰጠኸን አዲስ ዓመት
ከሰጠኸን አዲስ እለት
እንዘምራለን በደስታ በአኮቴት
አዝ🌼

ምድር ረክታ በዝናቡ በሰማይ ጠል
በአበባ ደምቃ ታየች በሐመልማል
በእድሜያችን ላይ ከጨመርከው ይህን ዓመት
የንስሀ ይሁንልን የመጸጸት

ከሰጠኸን አዲስ ዓመት
ከሰጠኸን አዲስ እለት
እንዘምራለን በደስታ በአኮቴት
አዝ🌼

የእርቅ ይሁን ዘመናችን የይቅርታ
ሰላም ትሁን ሀገራችን ፍቅር ተመልታ
መለያየት መጠላላት የሌለበት
አድርግልን ጌታችን ሆይ ይህን ዓመት

ከሰጠኸን አዲስ ዓመት
ከሰጠኸን አዲስ እለት
እንዘምራለን በደስታ በአኮቴት

ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​🌼 አበባ አየሽ ወይ 🌼

እንኳን ከዘመነ ዮሐንስ ወደ ዘመነ ማቴዎስ በሰላም አሸጋገራችሁ።

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​​​​​🌼 መስከረም 1
ሃይማኖታዊ መሠረት

ቅዱስ ማርቆስ ወንጌሉን ሲጽፍ «የእግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መጀመሪያ እነሆ መንገድህን የሚጠርግ መልእከተኛዬን በፊትህ እልካለሁ የጌታን መንገድ አዘጋጅ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ» ተብሎ በኢሳይያስ እንደ ተነገረ የነቢዩ ዘካርያስ  ልጅ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በዘመነ ብሉይ መጨረሻና በዘመነ ሐዲስ መጀመሪያ ላይ ተነሥቶ «መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ» እያለ ስለ ክርስቶስ አዳኝነት እየመሰከረ በምድረ በዳ የንስሐን ጥምቀት እያጠመቀ ለኃጢአት ሥርየት እየሰበከ መጣ ብሎ በዘመነ ወንጌል የመጀመሪያ ምዕራፍ ገልጾታል።

/የማርቆስ ወንጌል ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፵፤ ትንቢተ ኢሳይያስምዕ ፵ ቁ ፫ - ፬/።

የመጥምቁ ዮሐንስ ተግባር ለዘመነ ወንጌል በር ወይም መነሻ ሆኖ መገኘቱን በመረዳት የቤተክርስቲያን አበው የበዓላቱን ድንጋጌ በወሰኑበት ጊዜ የመጥምቁ ዮሐንስ መታሰቢያ በዓል የኢትዮጵያ ርዕሰ ዓውደ ዓመት በሚሆን መስከረም ፩ ቀን እንዲከበር በየዓመቱ የዘመኑ መጀመሪያ በእርሱ ስም እንዲጠራ አባቶች ደንግገዋል፡፡ / ድርሳነ ዘቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ገጽ 1ጠ 3/

ይህንንም በዓል አባቶቻችን በርእሰ ዓውደ ዓመት ማክበር እንደሚገባ አስበው ያደረጉት ነው፡፡ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በሰማዕትነት ያረፈበት ቀን ሆኖ አይደለም፡፡ ለአዲሱ ዓመት መጀመሪያ ወይም ርእሰ ዓውደ ዓመት «ቅዱስ ዮሐንስ» ይባላል፡፡ 

መጽሐፈ ስንክሳር የዓመቱን መጀመሪያ /መስከረምን/ ሲያትት «ይህ የመስከረም ወር የተባረከ ነው እርሱም የግብጽና የኢትዮጵያ ዓመቶች መጀመሪያ ነው በማለት ያስረዳል፡፡ የዚህ ወር ቀኑና ሌሊቱ እኩል ፲፪ ሰዓት ነው፡፡ ከዚህ በኋላ ከመስከረም አንድ ቀን ጀምሮ ቀኑ እየጎደለ ይሔዳል፡፡

👉 ከዚህ በመቀጠል በዓሉ በተለያየ ስያሜ ስለመጠራቱና ትርጓሜያቸውን እንመለከታለን፡፡

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

የሰማይም የምድርም ጌታ

የሰማይም የምድርም ጌታ
በዝቶልናል እጅግ ስጦታ
በጎነትህ ቸርነትህ
እረድቶናል ክቡር ስምህ። (2)

አዝ

በማይዝሉ ጽኑ ክንዶችህ
ተደገፍን በቸርነትህ
የፍቅር አባት ላመኑህ ጥላ
ክርስቶስ ነህ የእኛ ከለላ።
አዝ

ፍፁም ቆምን በንጹህ ደምህ
ተፈወስን በቅዱስ ቃልህ
መዛል ድካም ከቶ አይነካንም
ኃይላችን ነው ሁሌም የአንተ ስም።
አዝ

ያጣው ሲጮኽ ፊትህ ተደፍቶ
ሲያማክርህ ምስጢሩን ገልጦ
አባት ለልጁ እንደሚራራ
አወጣህን ከሙታን ሥፍራ፡፡
አዝ

ምስክር ነን ለዓለም ሁሉ
ስላዳነን በሕያው ቃሉ
ለውለታው ምላሽ ባይኖርም
ከምስጋና ከቶ አንቦዝንም

ዘማሪ; ቸርነት ሰናይ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

✞ ቅዱስ ሩፋኤል ✞


ምስጢረ መለኮት አድራሽ ነህ ለእስራኤል
መድኃኒት ነው ስምህ ቅዱስ ሩፋኤል (፪)

የሱሳኑ ነቢይ በእጆችህ ተዳስሶ
አይኖቹ በርተዋል ምህረትን ለብሶ
እኔ ራሴን ማየት ተስኖኛልና
ከኔ አልፎ አምላኬን ልየው በጽሞና
አዝ

እረፍትህ ምስጋና ነውና አታርፍም
ችግር የምትጋርድ በያዝከው በእሳት ፍም
በሳት ሰረገላ በሚፋጠን እግርህ
ፈጥነህ ድረስልኝ የልቤን ስነግርህ
አዝ

ከአህዛብ እርሾ ደግሜ እንዳልበላ
እንደ ጦቢት ጋርደኝ በክንፎችህ ጥላ
እግዚአብሔርን ላስብ በፍፁም ልቦና
አንተን እንደሚልክ አምነዋለሁና
አዝ

ሰናክሬም በክፋት ቆሞብኝ ከፊቴ
ናልኝ እልሃለሁ ሩፋኤል አባቴ
የሰራብኝን ግፍ በአንተ ረስቻለሁ
በመድኃኒት እጅህ ደስታን አግኝቻለሁ

ዘማሪት ሲስተር ሕይወት ተፈሪ

ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ። ጦቢት፲፪፥፲፭

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​ሩፋኤል ይቅር በለኝ

አሳድገኝ ብዬህ ሮጬ
ከልጆች ጋር ተሯሩጬ
በጠበልህ እየታጠብኩ
የውኃ ጨው እየቀመስኩ

ሩፋኤል አሳድገኝ
እንደ ታላቆቼ አድርገኝ
ብዬ እየጮህኩኝ ስጣራ
ሰምተኸኛል ከልጅ ተራ

ዘንድሮን ግን ተጠለልኩኝ
ጠበል ሲወርድ  ተሸሸግሁኝ
ከበረከትህ ሸሸሁኝ
ከቡራኬህ አመለጥኩኝ
ሩፋኤል ሆይ ይቅር በለኝ

ስላበቃ ልጅነቴ
በቆሸሸ ሰውነቴ
በረከሰ ማንነቴ
እንዳላረክስ ጠበልህን
ተጠለልኩት ጥምቀትህን

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ጳጉሜ 3


ርኅወተ ሰማይ (ሰመይ የሚከፈትባት)

ይህች ዕለት የሰዎች ሁሉ ጸሎት የሚያርግባት አራተኛው መጋቢ ኮከብ የሚያልፍባት: ለሰው ልጆች ከፈጣሪያቸው ጸጋ በረከት የሚሰጥባት ዕለት ስለሆነች ሰማይ የሚከፈትባት ቀን ትባላለች።

ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት

በመጽሐፈ ጦቢት ላይ ተጽፎ እንደምናገኘው ቅዱስ መልአክ ሰው(አዛርያን) መስሎ ጦብያን ለትዳር አብቅቶ ሣራን አስማንድዮስ ከሚባል ሰይጣን አድኖ የጦቢትን ዓይን አብርቷል።

ዳግመኛም ይህች ቀን ለቅዱስ ሩፋኤል ቅዳሴ ቤቱ ናት።

ቅዱስ ሩፋኤል ልቦናን ደስ የሚያሰኝ: ባለ መድኃኒት ፈዋሽ: የጸሎት መዝገብ መክፈቻ የተሰጠው በዙፋን ለይ በክብር ለሚቀመጡ መላእክት መሪ: የሰውንም ሆነ የእንስሳትን ማኅጸን የሚፈታ: (አዋላጅ: ምጥን የሚያቀል) መላእክ ነው።

በረከቱ ይደርብን! አሜን
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…
Подписаться на канал