ortodoxmezmur | Неотсортированное

Telegram-канал ortodoxmezmur - ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

134932

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . ዝማሬ ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Подписаться на канал

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

"እነሆ የጌታ ባርያ" ሉቃ 1:38

       🤲ክፍል ፬🤲

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

የእመቤታችን የድንግል ማርያም ንጽሕና እና ቅድስና እንዴት ነው?🤔

📣ክፍል ፪📣

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🤲🤲🤲ስለ ነገረ ማርያም🤲🤲🤲


ዛሬ ማታ 2:00 ላይ ትምህርታችንን የምንጀምር ስለሚሆን ሁላችሁም 2:00 ላይ ተሰብስባችሁ እንድትገኙ እናሳስባለን።

መምህር ዲያቆን ዳግማዊ ሰለሞን

ይሄንን ትምህርት ጓደኞቻችሁ እንዲማሩ ይሄንን ማስታወቂያ ላኩላቸው ከታች ያለውን ሊንክ በመግባት ይቀላቀሉን።


🌙 የማታ ሰው ይበለን 🌙

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ድል አለ በስምህ
በስልክ የተቀዳ

ድል አለ በስምህ
ድል አለ በቃልህ /2/
ተራራው ይናዳል አማኑኤል ስልህ
ባህር ይከፈላል መድሀኔዓለም ስልህ

ቃዴስን ታላቁን በርሀ
አለፍነው ሳንጠማ ውሀ
ፈርኦንን ከባህር የጣለው
ጌታዬ የጸና ስምህ ነው
አምላኬ የጸና ስምህ ነው
አዝ
በእልልታ ቢፈርስ እያረኮ
ጠላትም ቢወድቅ ተማርኮ
ቢሰጠን ለእኛ ከተማው
የሆነው ሁሉ ካንተ ነው/2/
አዝ
ከክፋት ሁሉ ብናመልጥ
የማረ ውሀ ቢጣፍጥ
ብንበላ መና ከሰማይ
ስለ ሆንክ ነው አ ዶናይ
ስለ ሆንክ ነው ሁሉን ቻይ
አዝ
የቆምነው ዛሬ በህይወት
ሰምህን አድርገን ነው ጉልበት
ከሜዳ ተጠርተን ብንነግስ
ሆነኸን ነው ክብርና ሞገስ

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

በዝማሬ ዳዊት ቻናል የምትለቋቸው መልዕክቶች እኛ ጋር Not supported ነው የሚለን ብላችሁ መልዕክት ለላካችሁልን ተከታታዮች በሙሉ፤ እባክዎ ከስር ባስቀመጥነው ሊንክ የቴሌግራም መተግበሪያዎን ያዘምኑት /Update/ ያድርጉት።

https://play.google.com/store/apps/details?id=org.telegram.messenger

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ኪዳነ ምህረት ልዩ ነሽ ለኔ

ኪዳነ ምህረት ልዩ ነሽ ለኔ
ሳዝን ስጨነቅ አትራቂኝ ከጎኔ
የችግሬ ደራሽ እመ እግዚአብሔር
ቃል ኪዳንሽ ይርዳኝ ካንቺ ጋር ልኑር(፪)
አዝ
የአዳም ተስፋው ነሽ የሴት ቸርነቱ
ኪዳነምህረት ነሽ የኖህ ምልክቱ
አዳም ደጅ የጠናሽ ሲገባ ንስሀ
ኖህም ድኖብሻል ከጥፋቱ ውሃ
አዝ
የአብርሃም ድንኳን ነሽ የሙሴ ፅላቱ
ማርያም አንቺ ነሽ የፈጣሪ እናቱ
የእስራኤል መሰላል የሴም እጣ ክፍሉ
እመብርሃን ስሚኝ ልመናየን ሁሉ
አዝ
የሰሎሞን አክሊል የዳዊት ዝማሬ
ድንግል መሆንሽን ትመስክር ከንፈሬ
ለተጠማው ውሻ የሚራራው ልብሽ
ለኔም እራርቶልኝ አስታርቂኝ ከልጅሽ
አዝ
የአብርሃም ድንኳን ነሽ የሙሴ ፅላቱ
ማርያም አንች ነሽ የፈጣሪ እናቱ
የእስራኤል መሰላል የሴም እጣ ክፍሉ
እመብርሃን ስሚኝ ልመናዬን ሁሉ

ዘማሪት ሲስተር ፋሲካ መኮንን
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ጳጉሜ 1


በዚች ዕለት ቅዱስ ዮሐንስ ወደ እሥር ቤት ገብቷል

ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-

ንጉሡ ሔሮድስ የወንድሙን የፊልጶስን ሚስት ሔሮድያዳን በማግባቱና በመሰል ክፋቶቹ ቅዱስ ዮሐንስ ይገስጸው ነበር። ፊት አይቶ የማያዳላ ነውና ገሰጸው።

ሔሮድስ ቅዱሱን ይፈራው: ያከብረውም ነበር። በኋላ ግን ፈቃደ ስጋው ስላየለበት: በተለይ ደግሞ ከሰባት ቀናት በኋላ ልደቱን ሲያከብር እንዳይረብሸው በመስጋት በዚህች ቀን በወታደሮቹ አስይዞ እስር ቤት ውስጥ አስገብቶታል።

ጌታችን ኢየሱስ ለሕዝብ ስለ ዮሐንስ ሊናገር ጀመረ ምን ልታዮ ወጣችሁ? ነቢይን? አዎን እላችኋለሁ ከነቢይም የሚበልጠውን...እውነት እላችኋለሁ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሳም...ነቢያት ሁሉና ሕጉ እስከ ዮሐንስ ድረስ ተናገሩ። ልትቀበሉትስ ብትወዱ ይመጣ ዘንድ ያለው ኤልያስ ይሕ ነው። (ማቴ 11÷7-15)


ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ

የቅዱሳኑ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ልጅ: በማኅጸን ሳለ መንፈስቅዱስ የሞላበት: በበረኀ ያደገና በገዳማዊ ቅድስና ያጌጠ:እሥራኤልን ለንሰሐ ያጠመቀ:ጌታውን ያጠመቀ:የጌታችንን መንገድ የጠረገና ስለ እውነት አንገቱን የተቆረጠ ቅዱስ ሰው ነው።

በረከቱ ይደርብን! አሜን
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ሰላም ውድ የዝማሬ ዳዊት ተከታታዮች በዝማሬ ዳዊት ገጽ የሚለቀቁትን ለወዳጅዎ ለማጋራት ካሰቡ ከታች ያስቀመጥነውን ቅደም ተከተል ተከተሉ።

1. ማጋራት የፈለጉትን መልዕክት ሲነኩ ከሚዘረዝርልዎ አማራጭ መካከል Copy link የሚለውን ይንኩት።

2. ለሚፈልጉት ሰው ወይም ማጋራት ወደሚፈለጉበት ቻናል ወይም ግሩፕ ላይ Copy ያደረጉትን ወስደው Past ማድረግ።

3. የዝማሬ ዳዊት ገጽን ከፍተው ሲገቡ ከስር UNMUTE የሚል ከሆነ የሚታይዎት ወደ MUTE መቀየርዎን አይዘንጉ።

ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን! አሜን።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ዮሐንስ መጥምቅ

መብልዕ ዜና ፍቅርከ ወነገረ ጽድቅከ ስቴ(፪)
ያስተፌስህ መላዕክተ ወሰብአ መዋቴ(፪)

ዘካርያስ አየ የገብርኤልን እውነት
በእርጅና ዘመንዋ ስትወልድ ኤልሳቤጥ
የልቦና መንገድ ከጥርጥር ጸድቶ
ዓለም ተደሰተ ልደትህን ሰምቶ

ዮሐንስ መልአክ ለእግዚአብሔር ቅሩቡ
ወርቀ ኪዳንከ ለነዳይ መዝገቡ

አዝ
እንደምን ሰገደ በረታ ጉልበትህ
መለኮትን ጸንሳ ድንግል ስትጎበኝህ
ነፍሴ ታመስግንህ ትዘምር ልሳኔ
ውዳሴህን ላንሳ ላቅርብልህ እኔ
ዮሐንስ ዘኮንከ ደመና ሰማይ ኮናኔ
አዝንም መና አእምሮ ወህብስተ ወጥበበ መድኃኒት

አዝ
የራጉኤል ትጋት የኢዮብ መታመን
መች ቻለ ሊዳስስ ነደ ነበልባሉን
በዮርዳኖስ ባሕር አሳየህ መስዋዕቱን
የዓለምን ኃጢአት  የሚያስወግደውን
ዮሐንስ ጠቢብ ሐመረ ክርሰቲያን አዳፊ
ኢይትዔየረከ በዕበይ በሰማይ ሱራፊ

አዝ
ከሴቶች ልጆች መሃል ዮሐንስ በለጠ
ናቡቴን መሠለው ለእውነት የተሰጠ
በመንፈስህ ትጉህ በኤልያስ ኃይል
ሳትፈራ መሰከርክ የእውነትን ቃል
ዮሐንስ አንተ ጽልመተ አበሳ ሰዳዴ
በአየረ ሰማይ ይጸርሕ ቃልከ ዓዋዲ

አዝ
መስክሪ ሄሮድያዳ የዮሐንስ ነገሩን
ታምኖ ቢሞት እንኳን በክንፍ መብረሩን
ምንኛ ታላቅ ነው ዮሐንስ ተጋድሎህ
ፈጥነህ ትደርሳለህ ዛሬም ለሚጠሩህ
ዮሐንስ ልብ መዝገበ ጥበብ ወአእምሮ
ፍጹመ መነንከ አብያተ ዘውቅሮ

      
ነብየ ልዑል ሰማዕት ወጽድቅ ካህን ሐዋርያ
መምህር ወመገስጽ  ባሕታዊ ድንግል መጥምቀ መለኮት
ርዕሰ ዓውደ ዓመት ጸያሔ ፍኖት
አርኩ ለመርአዊ ዮሐንስ መጥምቅ (፫)

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ነሐሴ 30


በዚህች ዕለት ከዐሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ የሆነው ታላቁ ነቢይ ሚልክያስ አረፈ።

እግዚአብሔር አምላክ በነቢዩ አንደበት አድሮ እንዲህ ይለናል።
ሰው እግዚአብሔርን ይሰርቃልን? እናንተ ግን እኔን ሰርቃችኋል። እናንተም። የሰረቅንህ በምንድር ነው? ብላችኋል። በአሥራትና በበኵራት ነው። ትንቢተ ሚልክያስ 3:8


እንዴት አድርጌ ነው ከ5ሺህ ብር ደሞዝ በዛ ላይ የኑሮ ውድነቱ ተጨምሮበት አስራት የማወጣው? ብላችሁ ብትጠይቁም እግዚአብሔር በነቢዩ አድሮ እንዲህ ይለናል።
በቤቴ ውስጥ መብል እንዲሆን አሥራቱን ሁሉ ወደ ጎተራ አግቡ፤ የሰማይንም መስኮት ባልከፍትላችሁ፥ በረከትንም አትረፍርፌ ባላፈስስላችሁ በዚህ ፈትኑኝ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። ትንቢተ ሚልክያስ 3:10


ቅዱስ ሚልክያስም በበጎ ተጋድሎው እግዚአብሔርን ከአገለገለ በኋላ በዛሬዋ ዕለት ከዚህ ዓለም በመፍለስ በሰላም አረፈ። ሚልክያስ ማለት መልዐክ አንድም የተላከ ማለት ነው።

በረከቱ ይደርብን! አሜን
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ዘማሪ ዲ/ን ሱራፌል ስዩም አባክህን ይህን እየተመከትክ ከሆነ ወይም የምታውቁት ካላችሁ ከታሽ ባስቀመጥነው አድራሻ መልዕክት ይላክልን። አድራሻህ ከስልካችን ስለጠፋብን ነው።

📩 @Zimaredawitmessanger

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ነሐሴ 29

በትሕትናው፣ በትዕግስቱ ይበልጡንም ደግሞ በመታዘዙ የሚታወቀው አባት ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር የፍልሰቱ ዕለት ናት። በአንድ ወቅት አባ ባይሞይ ቅዱስ ዮሐንስን ጠራውና ተፈልጦ የወደቀ ደረቅ እንጨት ሠጠው ከዚያም
ትከለውና እንዲያፈራ አድርገው። ከዚያ አምጥተህ አብላኝ

አለው። ይህ ነገር ከተፈጥሮ ሥርዓት ውጪ መሆኑን እያወቀ ቅዱስ ዮሐንስ እሺ ብሎ ወስዶ ተከለው።  ከ10ኪ.ሜ በላይ እየተጓዘ ወሃ እየቀዳ ለ2 ዓመታት ሳይታክት አጠጣው። በሦስተኛው ዓመት ግን ለመለመ ወስዶም ለመምህሩ
አባቴ እንካ ብላ ብሎ ሰጠው። መምህሩም ወዲያው ያን ፍሬ ታቅፎ ወስዶ ለገዳሙ መነኮሳት
ንሱ ብሉ: በረከትንም አግኙ:: ይህ የዛፍ ሳይሆን የመታዘዝ ፍሬ ነው አላቸው።


ቁመቱ እጅግ ያጠረ: ጽድቁ ግን ከሰማይ የደረሰ ቅዱስ ዮሐንስን ሰላም ሰላም እንለዋለን


በረከቱ ይደርብን! አሜን
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

አብርሃም አብርሃም

አብርሃም አብርሃም ደጉ ምዕመን
ተብለህ ተጠራህ አበ ብዙኃን

የልዑል ምሳሌ ለሆነው ካህን
አክብረህ ሰጠኸው ከአስር አንዱን

አዝ

ትዕዛዙን ጠብቀህ ብትሰጠው አስራት
ዘር አብዝቶልሀል እንደ ከዋክብት
ስንከተል እንጂ የሰራውን ሁሉ
አይጠቅመንም ለእኛ መጠራት በስሙ
አዝ

አስራቱን ካወጣን የታዘዘውን
ትመግበናለች ምድር ፍሬዋን
አዝ

በቸልተኝነት ካስቀረን አስራት
ዳግም አናገኝም የምድር በረከት
አዝ

ልጆቹ እንድንባል ሁላችን በአንድ ቃል
በግብር እንምሰለው ያለፈው ይበቃል
አዝ

አብርሃም አብርሃም ደጉ ምዕመን
ተብለህ ተጠራህ አበ ብዙኃን

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ነሐሴ 28

በዚህች ዕለት የሃይማኖት፣ የደግነት፣ የምጽዋትና የፍቅር አባት፣ የመንግሥተ ሰማያት አበጋዝ፣ የእግዚአብሔር ወዳጅ የሕዝብና የአሕዛብ አባት፣ የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የነገሥታት፣ የካህናት አባት ሥርወ ሃይማኖት (የሃይማኖት ሥር) የሆነው አባታችን አብርሃም ፤ይስሃቅና ያዕቆብ የሶስቱም አባቶች የእረፍታቸው መታሰቢያ ነው።

ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
በረከታቸው ይደርብን

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ኢትዮጵያዊው ጻድቅ

ኢትዮጵያዊው ጻድቅ ማነው ብዬ ጠየቅሁ
በረከት ፈልጌ ልሳለመው ናፈቅሁ
ክብሩን ልመሰክር ተፈታ ምላሴ
በደጁ ደርሼ ፍቅሩን በመቅመሴ/፪/

አዝ
በኢቲሳ ምድር ዘር ሆነህ በቅለህ
ተለየህ ለአምላክ ዓለምን ጥለህ
ደብረ ሊባኖስ ህያው ምስክር
ስለ አንተ ዝና ስለ አንተ ክብር

ተክለሃይማኖት ወዳጄ
ተባርኳል በአንተ ጓዳ ደጄ
አዝ
አክባሪው አምላክ ስላከበረህ
ዛሬም ከኛ ጋር በመንፈስ አለህ
ደጅ እንጠናለን በትህትና
የጻድቅ ጸሎት ኃይል አላትና

ተክለሃይማኖት ጸሐይ
ጸጋህ ይውጣልኝ በሠማይ
አዝ
ወደ ለምለም መስክ ሰብከህ መራኸን
የቃሉን ወተት አጠጥተኽን
ያቀጣጠልከው የወንጌል ችቦ
የአምላክ አድርጓል ትውልዱን ስቦ

ተክለሃይማኖት ወዳጄ
ተባርኳል በአንተ ቤቴ ደጄ
አዝ
ሠላሳ ሥድሳ መቶ ያፈራህ
በደብረ አስሶ ቆመህ በአንድ እግርህ
የሞተለሚ መሻት ቀረና
የጌታ መንገድ ጥርጊያውም ቀና

ተክለሃይማኖት ወዳጄ
ተባርኳል በአንተ ጓዳ ደጄ

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🙏አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ🙏
       

      🤲ትርጓሜ ክፍል ፫🤲

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🤲ነገረ ማርያም መግቢያ🤲

📣ክፍል ፩📣

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

👉ስለ ድንግል ማርያም
👉ስለ ፍጹም ድንግልናዋ
👉አምላክን ስለመውለዷ
👉ስለ አማላጅነቷ እና ሌሎችም ጥያቄዎች መልስ ከፈለጋችሁ እነዚህን አዳምጧቸው

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ጳጉሜ 2


ከ72ቱ አርድእት የሆነ የከበረ ቅዱስ ቲቶ በዚች ዕለት አረፈ።

ቅዱሱ ባለፈ ሕይወቱ እግዚአብሔርን ባያመልክም በጠባዩ ግን እጅግ ቅንና ደግ ነበር። እግዚአብሔርም ይህን ቅን ሰው መልካም ስራውን ተመልክቶ በራዕይ ተገለጠለት።
ስለነፍስህ ተጋደል አለው።


ቅዱስ ቲቶም ተነስቶ ወደ ኢየሩሳሌም ሄደ። ጌታችንም በሚያደርጋቸውን አምላከዊ ስራ ተመልክቶ ፍጡር እንዳልሆነ ተረዳ። ሰማያዊና ዘላለማዊ ትምሕርቱን በሰማ ጊዜ  በራዕይ ''ስለ ነፍስህ ተጋደል።'' ያለው ምሥጢር አሁን ተገለፀለት። አምኖም ተከታዩ ሆነ።

ከዚህም በኋላ ከጌታችን እግር ለሦስት ዓመታት ተምሮ በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ በመላው እስያ ለስምንት ዓመታት ወንጌልን ሰብኳል። ዕድሜው በደረሰ ጊዜም በዚህች ዕለት አርፏል።

በረከቱ ይደርብን! አሜን
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​ቅዱሱ ጲላጦስ

ብዙዎቻችን መስፍኑን ጲላጦስ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ጌታችን እንዳይሰቀል ከአይሁድ ጋር ሲከራከር እናውቀዋለን። የጌታችን ሞቱ በፈቃዱ ነበርና አይሁድ እንቢ ሲሉት የክርስቶስን ንጽሕና መስክሮ: እጁንም ታጥቦ ሰጥቷቸዋል። የጲላጦስ ታሪክ ግን እዚህ ላይ አያበቃም።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ ከተነሳ በኋላ ትንሳኤውን በራዕይ ገልጦለት አይሁድን ተከራክሯቸዋል። ውሸታም ወታደሮችንም ቀጥቷል።

ጲላጦስም ከሚስቱ አብሮቅላ ስለ እግዚአብሔር ገናንነት እየተጨዋወቱ ኹለቱም ስለ ትንሣኤው ሲነጋገሩ ከደመና ድምፅ ተሰማ።

ከደመናውም ጲላጦስ ሆይ በዚኽ ደመና ላይ በክብር ተቀምጠው ወደ ገነት የሚወስዷቸውን እነዚህን ነፍሳት ታያለህን፡፡ ይኽም የሄሮድስ ወታደሮች ከመቶ አለቃው ጋራ በመንገድ የገደሏቸው ናቸው፡፡ እንደዚሁም አንተንም በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ምክንያት በሮም አንገትህን በሰይፍ ይቈርጡሃል፡፡

የአንተንና የሚስትህ አብሮቅላን ነፍስ በዚኹ ዐይነት ክብር በደመና ተሸክመው ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም ያሳርጓችኋል፡፡ ጲላጦስ ሆይ ፈጣሪህ ኢየሱስ ክርስቶስ ከዕፀ ሕይወት ሥር ያኖርሃልና አይዞህ ጽና የሚል ድምፅ ተሰማ፡፡

ድምፁም ይኽን ተናግሮ ከእነርሱ ዘንድ ተሠወረ፡፡ ጲላጦስም ስለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ አንገቱን ይቈርጡት ዘንድም እጅግ ተደሰተ፡፡ በመጨረሻም በሮም ቄሳር ተጠርቶ ከእሥራኤል እስከ ሮም ድረስ ሰብኮ በሮም አደባባይ አንገቱ ተሠይፏል።

ቅድስት እናታችን አብሮቅላም የዺላጦስ ሚስት ስትሆን ቁጥሯ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት ነው። ጌታችንን ተከትላ ቤቷን ለሐዋርያት አስረክባ ቤተ ክርስቲያንንም በዘመኗ አገልግላ ዐርፏለች።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ ፦ መጽሐፈ ስንክሳር ሰኔ 25 እና ላሐ ማርያም
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

አልረሳውም ያንን ዕለት

አልረሳውም ያንን ዕለት
አልዘነጋው ያን ደግነት
እናቴ ሆይ ምልሽ ኪዳነ ምሕረት
እምዬ ሆይ ምልሽ ኪዳነ ምሕረት
ስላለኝ ነው ምክንያት/፪/

ለሠው ተናግሬ ያልተረዳኝ ሰው
ዕንባዬ በምሬት ከዓይኔ የሚፈሰው
የቤቴን ገመና ሁሉን ስነግርሽ
አዛኝት ነሽና እራራልኝ ልብሽ
አረሳው መቼም የአንቺን ደግነት/፪/
ውለታ አለብኝ ኪዳነ ምሕረት
አዝ
ልቤ በሐዘን ጠቁሮ ውስጤ እየደማ
መቅረዜ ሲጨልም ስዋጥ በጨለማ
በራፌን ዘግቼ ዝም ብዬ አለቅሳለሁ
ግን እኔ አቀርቅሬ እናቴ እልሻለሁ
ዘንበል አልሽልኝ ሠምተሽ ፆሎቴን/፪/
አልተጸየፍሽም ብቸኝነቴን
አዝ
እናት የለኝ ብዬ ከቶም አልከፋ
እኔስ አይቻለሁ ስትሞይኝ በተስፋ
ምድራዊዋ እናቴ ለጊዜው ነው ፍቅሯ
ያንቺስ ግን ልዩ ነው ኧረ ስንቱን ላውራ
ማርያም ማርያም ብል አልሠለችሽ/፪/
በልቤ ጽላት ስለ ታተምሽ
አዝ
ሲረበኝ መጥተሻል ሲጠማኝ ደርሰሻል
ለጎደለው ቤቴ በረከት ሆነሻል
ጭንቄም ቀለለልኝ ሐዘኔም ራቀ
ያስጨነቀኝ ጠላት ራሱ ተጨነቀ
መዳኒት ወልደሽ ዳንኩኝ ከህመሜ/፪/
ይኸው ዘመርኩኝ በምልጃሽ ቆሜ

ዘማሪ ዲ/ን ሙሉቀን ከበደ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

👉 ጳጉሜ ለምን እንጠመቃለን?
🎤 ቀሲስ ሄኖክ ወልደ ማርያም

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​​​በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

ጾመ ዮዲት

በናቡከደነጾር ዘመነ መንግሥት ንጉሡ ሥልጣኑን መከታ በማድረግ የእግዚአብሔርን ሕዝብ በግድ እያስገደደ እጅ መንሻ ይቀበል ነበር፡፡ የመንግሥቱን ትእዛዝ ያልተቀበለውንም እየገደለ፣ ጭፍሮቹ ኃያልነቱንና ገናናነቱን በዓዋጅ በጦር አዛዦች ጭምር እያሳወጀ፣ በርካታ የጦር ሠራዊቶችን አሰልፎ ከአይሁድ ከተማ ገባ፡፡

በዚያም ነዋሪዎችን በማስፈራራት የመንግሥቱን ትእዛዝ ያልተቀበሉትን ሁሉ እያሳደደ ስላስጨነቃቸው ማቅ ለብሰው፣ አመድ ነስንሰውና ድንጋይ ተንተርሰው ወደ ፈጣሪያቸው በመጮህ መለመን ጀመሩ። በጭካኔ የተሞላው የጦር አበጋዙ ሆሎፎርኒስም ይበልጥ እጅግ እንዲሰቃዩ ውኃ የሚቀዱበትን ስፍራ ተቆጣጠረው፤ በግዴታ ማርኮም እጅ እንዲሰጡ እንዳደረጋቸው በመጽሐፈ ዮዲት ፪፥፪ ላይ ተጽፏል፡፡

በአካባቢው ይኖር የነበረ ዖዝያን የተባለ አንድ ሰው የአባቶቻቸው አምላክ ጸሎታቸውን እንዲሰማቸው ለአምስት ቀናት በትዕግሥት ይጾሙና ይጸልዩ ዘንድ ሕዝቡን መከራቸው፤ እነርሱም በትዕግሥት ሊጠብቁ ተስማሙ፡፡

የእስራኤል ልጆች የናቡከደነጾርን ጦር ብንችል ተዋግተን እንረታለን፤ ካልሆነም እጅ እንሰጣለን በማለት ይመካከሩ ጀመር።
በዚያን ጊዜ ባሏ የሞተባትና በንጽሕና ተጠብቃ፣ በጸሎትና በሕገ እግዚአብሔር የምትኖር ዮዲት የተባለች ሴት ነበረች። (ዮዲት ፯፥፲)

እግዚአብሔርን የምትፈራ ብቸኛዋ ሴት እርሷ ነበረችና ምክክራቸውን ስትሰማ

ለምን እግዚአብሔር ያድነናል አትሉም ብላ ገሠጸቻቸው፡፡


ማቅ በመልበስ፣ አመድ በመነስነስና ድንጋይ በመንተራስም ሱባኤ ገባች። በሦስተኛው ቀንም እግዚአብሔር አምላክ ሕዝቧን የምታድንበትን ጥበብ ገለጸላት፤ ዮዲትም እግዚአብሔር የሰጣትን ውበት ተጠቅማ ሕዝቧን ከጥፋት የምትታደግበትን ጥበብ ተረዳች።

የክት ልብሷን ለብሳ፣ ሽቱ ተቀብታና ተውባ የጠላት ሠራዊት ወዳሉበት የጦር ሰፈር በድፍረት አመራች፡፡ ሠራዊቱም ውበቷን አይተው እጅግ በመደነቅ
«ይህችስ ለአለቃችን ትገባለች» ተባብለው ከጦር መሪያቸው ዘንድ ወሰዷት።


እርሷም ቀድማ ማምለጫ መንገድ አዘጋጅታ ነበርና ወደ አዛዡ ከገባች በኋላ
«ክቡር ጌታዬ ሆይ ርስት ተወስዶብኛል፤ እንድትመልስልኝ አስቀድሜ ደጅ ልጠና መጥቻለውና ርዳኝ፤ ትብብርህ አይለየኝ» አለችው፡፡

በስሜት ፈረስ ታውሮ የነበረው የሠራዊቶቹ አዛዥም የጠየቀችውን እንደሚፈጽምላት ቃል ገባላት።

ባማረ ድንካን እንዲያስቀምጧት ሎሌዎቹን አዘዘ። ዮዲትም የተሰጣትን ጥበብ ተጠቅማ፣ መውጣት ስትፈልግ የምትወጣበትን እና የምትገባበትን ዕድል በእግዚአብሔር አጋዥነት ዐወቀች፡፡ ከቀናት በኃላ የጦር አበጋዙ ለሠራዊቱ የምሳ ግብዣ አዘጋጅቶ ዮዲትን ከጎኑ አስቀመጣት፤ ከበሉና ከጠጡ በኋላም ሁሉን ሰው አስወጣ፤ እልፍኙን በመዝጋት ከእርሷ ጋር ብቻውን ሆነ፤ ነገር ግን እንቅልፍ ጣለው፡፡ (ዮዲት ፰፥፪)

እርሷም ወደ አምላኳ ጸለየች፤ ፈጣሪዋ እንዲረዳትም አጥብቃ ለመነች። በኋላም ከራስጌው ሰይፍ አንስታ አንገቱን ቀላችው፤ በድኑንም ከመሬት ጣለችው። የሆሎፎርኒስን ሞት ሠራዊቱ ሲሰሙ አውራ እንደሌለው ንብ ተበተኑ፤ ከፊሎቹ ሞቱ።

እስራኤላውያንም ከሞት ተርፈው በእግዚአብሔር ኃይል ድል አደረጉ፤ በደስታም ፈጣሪያቸውን አመሰገኑ። ይህ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ታሪክ የሚያስረዳን ዮዲት ጠላቶቿን ድል ያደረገችው በጾምና በጸሎት እንደሆነ ነው፡፡

ለእኛም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ምንም እንኳ ወርኃ ጳጉሜን የፈቃድ ጾም ቢሆንም በሀገራችን የተጋረጠውን ችግር እናልፍ ዘንድ በፈቃደኝነት እንጾማለን። እግዚአብሔር አምላካችን ለሁላችንም ጥበብ ሰጥቶናል።

ይህም ችግሮችን ሁሉ የምንፈታበት መንገድ ነው። በዚህም የዓመተ መሸጋገሪያና የክረምቱ ወር ማብቂያ በመሆኑ ዕለተ ምጽአት ስለሚታሰብበት በየዓመቱ በጳጉሜ ወር ከሌሊት ጀምሮ በቤተ ክርስቲያን ተገኝተን ጠበል በመጠመቅ፣ በማስቀደስና በመጸለይ እንዲሁም ሥጋ ወደሙን በመቀበል ልናሳልፍ ይገባል።

ዕለተ ምጽአትም ከዚህ ዓለም ወደ ወዲያኛው ዓለም መሸጋገሪያችን ነውና በቀኙ እንቆም ዘንድ እንጾማለን፡፡

የሚመጣውን አዲስ ዘመንም በንጽሕና ለመቀበል ስላለፈው ዓመት ኃጢአታችን ንስሓ የምንገባበት ጾምም ነው።
ከተጋረጠብን ችግር እግዚአብሔር ያድነናል

በማለት ልክ እንደ ዮዲት ሱባኤ ገብተን፣ ማቅ ለብሰን፣ አመድ ነስንሰንና ድንጋይ ተንተርሰን አብዝተን ልንጾምና ልንጸልይ ይገባል፡፡ ሊለያየን፣ ሊነጣጥለን፣ ሊበታትነን እና ሊገድለን ካሰበው እንዲሁም ፍቅርን፣ መተሳሰብንና አንድነትን ሊነፍገን ከቃጣው ጠላትና ሃይማኖታችንን ሊያስተወን ከሚመጣ ፀረ ሃይማኖት እንድናለን።

ስለዚህ ከፊታችን ያለችውን ስድስቱን የጳጉሜን ቀን በፍቅር፣ በአንድነትና በሃይማኖት ጸንተን፣ ጾመን፣ ጸልየን ለዘመነ ማቴዎስ እንድንደርስ እግዚአብሔር አምላካችን ይርዳን፤ አሜን።

ምንጭ፦ ከማኅበረ ቅዱሳን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ምን አለ ያጎደልክብኝ

ምን አለ ያጎደልክብኝ
ሳትነፍገኝ ሁሉን ሰጠኸኝ
ሁነኸኝ እናት እና አባት
አለፈ ብዙ ዘመናት (2)

አዝ

አኖርከኝ ዛሬም በጤና
ወጥቸ ገባሁ በደና
መንገዴን ሰጥቸሀለው
ስትመራኝ እከተላለው
አዝ

ወረት አታውቅም ጌታየ
መች ቀረ ፈሶ እንባየ
ህይወቴ በመድሀፍህ ነው
መፍራቴ ከቶ ለምን ነው
አዝ

አውቀኸኝ ሳሰራኝ ገና
ሞልተኸኝ ቅኔ ምስጋና
ካንተ ነው የተቀበልኩት
በመዝሙር የሰለጠንሁት
አዝ

መዛሌ በውሀ ጥም
በባእድ ሀገር መድከም
በብዙ ስጋት ተጉዤ
ቁሜአለው ስምህን ይዤ
አዝ

በትዳር በልጅ ባርከኸኝ
የልቤን ደስታ ሰጠኸኝ
ስለያዝኩ ጌታ ያንተን እጅ
ተባልኩኝ የንጉሱ ልጅ

ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ኑ በብርሃኑ ተመላለሱ

ኑ በብርሐኑ ተመላለሱ ተመላለሱ
ኑ በብርሐኑ በብርሐኑ ተመላለሱ
የፍቅርን ሕይወት እንድትለብሱ
ኑ በብርሐኑ ተመላለሱ/፪/

አዝ

ሁሉን በሚችል በአምላክ ጥላ
በእረፍት ውሃ ሥር አርፈናልና
ሠላም እና ፍቅር ሕይወት በሚሰጥ
ወደ ጌታችን እንሂድ እንሩጥ
አዝ

ምሕረት እና ፍርድ በእጁ የያዘው
የሠላም አባት መድሐኔዓለም ነው
ሕይወት የሆነን በመስቀል ውሎ
ብርሐን ሠጠን ጨለማን ሽሮ
አዝ

የሚያስደነግጥ የሚያስጨንቀን
ይጠፋልና እርሱን ተማጽነን
በቀን ከሚበር ፍላጻ ሁሉ
ይታደገናል በቅዱሥ ቃሉ
አዝ

እግርህ በድንጋይ እንዳይመታ
በፈተና ውስጥ እንድትበረታ
መቅሰፍት ከቤትኽ እንዲከለከል
ይጠብቅሃል ሌሊት እና ቀን
አዝ

ሥሙን ያወቀ ሕይወት መሆኑን
ይመላለሳል ከሐይል ወደ ሐይል
ረጅም ዕድሜ ይጠግባል እርሱ
ብርሐን ይሆናል የጸጋ ልብሱ
አዝ        

አቤቱ አንተ ተሥፋ ነህና
የምትመግብ የፍቅር መና
ማዳንህ እኛን አስደስቶናል
እንዲህ ያለ ክብር ከየት ይገኛል

ለሁሉም ሼር በማድረግ አዳርሱ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

የማይጠፋው

የማይጠፋው የዘላለም ህይወት
የመይፈርሰው የፀና መሠረት
የእግዚአብሔር ቃልን በወለደችልን /2/
በድንግል ማርያም ተገኘልን /2/

አዝ

የመውለድ ችሎታዋ የማይመረመር
ድንግል እናት መሆኗን የማይችል ሊነገር
ዘሩያልተዘራባት ሆናለችና እርሻ
ደስታን አስገኝታለች የሀዘንን መርሻ
አዝ

ከእርሷ የሆነውን ከማድነቅ በቀር
ለስሟ ከመሰዋት ምስጋናና ክብር
ከህሊና በላይ ነው ግብረ መንፈስ ቅዱስ
አይኖራትም ምሳሌ እስከ አፅናፍ ድረስ
አዝ

የመላክት ደስታቸው ጌታን የወለድሽ
የነበያተሰ ዜናቸው ነፅህት የሆንሽ
ክብርና ገናናነትሽን እንናገራለን
በማይነጥፍም መስጋና እናገንሻለን
አዝ

በድንግልና ፀንሶ መዉለድ በድግል
ከቶ ለማን ተሰጠ ከሴቶች መሀል
አለማትም ተፈጥረው ዘመን ቢቆጠር
ለማንም አልተቻለም ከማርያም በቀር

ዘማሪ ዲ/ን ሱራፌል ስዩም
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​ቅዱስ አፈር

ቅዱስ አፈር ከሕመት (እምነት) ጋር ተመሳሳይ ሲሆን በቤተክርስቲያን ፣ በጠበል ቦታና በገዳማት ለቅዱሳን በተሰጣቸው ቃል ኪዳን መሰረት ምዕመናን የምንድንበት በረከት የምናገኝበት መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ቅዱስ አፈር ነው። 

ይህንንም የሚያደርጉት የቦታውን ቅድስና በመረዳት ነው። በዚህም የተቀደሰ አፈር ብዙ ድንቅ ተአምራት በአምላካችን በአግዚአብሔርና በባለሟሎቹ በቅዱሳን ተደርጓል። ይደረጋልም። አንዳንድ ጊዜ የዚህ ምሥጢር ያልገባቸው ሰዎች ይህን ሲመከቱ እንደ ሞኝነት ሊያዩት ይችሉ ይሆናል። ዳሩ ግን ምሥጢሩ ረቂቅ ነው። ከእምነትም የሚመነጭ ነው። መሠረቱም ታላቁ መጽሐፍ ቅዱስ ነው።

ከለምጽ ንዳድ በዮርዳኖስ ጠበል የተፈወሰው የሶሪያው የጦር ጀግና ንዕማን ከዳነ በኋላ ከእግዚብሔር ውጪ ሌላ አምላክ፣ አዳኝ እንደሌለ ተረድቷል፡ አምኗልም። እንዲህም ብሎ መስክሯል

እነሆ ከእስራኤል ዘንድ በምድር ሁሉ አምላክ እንደ ሌለ አወቅሁ።

ይህ ንዕማን ቀድሞ በእግዚአብሔር የማያምን አሕዛብ ነበር። የሚያመልከውም በወርቅና በብር የተሠራ ጣዖትን ነበር። የሚጸልየውና መሥዋዕት የሚያቀርበው “ሬሞን” ለተባለ ከንቱ ጣዖት ነበር።

በእግዚአብሔር ሰው በነቢዩ ኤልሳዕ አማካኝነት ከተፈወሰ በኋላ እግዚአብሔርን አመለከ ኤልሳዕም ቅዱስ መሆኑን ተረዳ።
ስለዚህም ኤልሳዕ የረገጠውን አፈር ለምኖ በበቅሎ ጭኖ ወደ ሀገሩ ተመለሰ፡፡ ፪ነገ ፭፥፲፭-፲፱ (5፥15-19)


ዛሬም እግዚአብሔር አምላክን ያመኑ በቅዱሳን ተራዳኢነትና አማላጅነት የሚታመኑ ምእመናንና ምእመናት ከእምነታቸው ጽናት የተነሣ በእምነት በተቀደሰው አፈር ፍጹም ፈውስን ያገኛሉ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ ፦ መጽሐፈ አሚን ወስርዓት

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ያዕቆብ ከቤርሳቤህ

ያዕቆብ ከቤርሳቤህ ወደካራን ሲሄድ
የለውም ነበረ አማካሪ ዘመድ
ፀሀይ ጠልቃ ነበር ከዛ እንደደረሰ
ከእራሱ በታች ድንጋይ ተንተራሰ

አዝ

ህልምንም አለመ ታላቁን እራእይ
መሠላል ተተክሎ ከምድር እስከ ሠማይ
ሲወጡ ሲወርዱ መላእክት በሷላይ
እግዚአብሔርም ቆሞ ከላይ ከጫፋላይ
አዝ

ያባቶችህ አምላክ እኔ እግዚአብሔር ነኝ
ይህን ምድር ለእርስትህ እሰጥሀለውኝ
ዘርህ እንደ አሸዋ በምድር ይዘራል
በአራቱ ማእዘን ህዝብህም ይሆናል
አዝ

አበው በምሳሌ እንደ ተናገሩት
ከምድር እስከ ሰማይ አምላክ የዘረጋ
በላይ ተቀምጦ በግልፅ የታየባት
የያእቆብ መሰላል እመቤታትን ናት
አዝ

ሰማይና ምድር የሚታረቁባት
ወልድ እጓለመሕያው የተወለደበት
መላእክት ከሰማይ ባንድ የዘመሩላት
ታላቆ መሰላል እመቤታትን ናት

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🎬  🛑 ጻድቃን ላይ ለሚዘባበቱ መናፍቃን እግዚአብሔር አምላክ ልቦና ይስጥልን! የጻድቁ ተክለሃይማኖት አጭር ታሪክ
👤 ዝማሬ ዳዊት ቲዩብ

⚠️ ትምህርቱን ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!
https://youtu.be/6geWAZ_doak
https://youtu.be/6geWAZ_doak

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​እንኳን ለታላቁ ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ

ልደት

መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ ጸጋ ዘአብ ካህኑና እግዚእ ኃረያ ናቸው። እርሱ በክህነቱ እርሷ በደግነቷ በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል።

በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው ቅዱስ ሚካኤል ጸጋ ዘአብን ከሞት እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል። በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል።

ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24 ቀን በ1206 ዓ/ም ሲሆን የተወለዱት ደግሞ ታሕሳስ 24 ቀን በ1207 ዓ/ም ነው። በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል። ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል።

ዕድገት

የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው "ፍሥሃ ጽዮን" ይሰኛል። ይሕንን ስም ይዘው አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል። በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል። በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል። ዲቁናም ከወቅቱ ዻዻስ አባ ጌርሎስ ተቀብለዋል።

መጠራት

አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮስ ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ።

የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ። "ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን። ከዚህ በሁዋላ አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ። ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ። ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ ሰዓትን አላጠፉም። ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ።

አገልግሎት

ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ። በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ። ያን ጊዜ ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት።

1ኛ. ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል።

2ኛው. ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር።

ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ። ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን (ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል::

ገዳማዊ ሕይወት

ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል። እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል።

እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት: በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26 ዓመታት አገልግለዋል።

በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ (ዞረሬ) ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል። በተሰበረ እግራቸውም 6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል።

ስድስት ክንፍ

ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል። ጻድቁ ምድረ እሥራኤል የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር::

የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሚካኤል ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል። ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በሁዋላ ነው ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር።

ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም። በገሃድ:-
-በቤተ መቅደስ ብስራቱን
-በቤተ ልሔም ልደቱን
-በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን
-በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን
-በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር።

የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደ ሆነው ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ። በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን ወደ ሰማይ አሳረገቻቸው።

በዚያም :-
-የብርሃን ዐይን ተቀብለው
-6 ክንፍ አብቅለው
-የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
-ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው
-ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው
-ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
-"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል።

ተአምራት

የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው።
ሙት አንስተዋል
ድውያንን ፈውሰዋል
አጋንንትን አሳደዋል
እሳትን ጨብጠዋል
በክንፍ በረዋል
ደመናን ዙፋን አድርገዋል።

ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል። በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት አብረው ኑረዋል። በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና::

ዕረፍት

ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: እልፍ አእላፍ ፍሬን አፍርተው: በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24 ቀን በ1306 ዓ/ም ዐርፈዋል።

ጌታ: ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል። 10 ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል።

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…
Подписаться на канал