ortodoxmezmur | Неотсортированное

Telegram-канал ortodoxmezmur - ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

134932

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . ዝማሬ ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Подписаться на канал

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

😥ምን ያስጨንቀናል?😞

እንኳን ደስ አላችሁ የሥነ ልቡና የምክክር አገልግሎታችንን በአዲሱ ቢሮአችን በአዲስ መልኩ ጀምረናል።

የምንሰጣቸው አገልግሎት፦
👉ድብርት/ድባቴ (Depression)
👉ብቸኝነት(Loneliness)
👉የመኖር ጣዕም እና አላማን ማጣት(Purpose and meaning of life)
👉የተለያዩ የሱስ ፈተናዎች (Drug addictions)
👉የትዳር የምክክር አገልግሎት (Married therapy)
👉እራስን የማጥፋት ሐሳቦች(Suicidal thoughts)
👉ልበ-ሙሉነትን እንዴት ማምጣት እንችላለን (self-confidence)
👉የልጅነት መጥፎ ጠባሳ/ክስተት(Trauma)
👉ጭንቀት(Anxiety)
👉የማንነትን ቀውስ(Identity crisis)
እና ሌሎች የሚያስጨንቁንን ነገሮች ሁሉ በዓለማዊው እና መንፈሳዊ መንገድ የምክክር አገልግሎት የምንሰጥ ሲሆን። ከታች ባለው ስልክ ቁጥር በመደወል ወይም በቴሌግራም አካውንት ቴክስት በመላክ ቀድመው ቀጠሮ ማስያዝ ይችላሉ።

📍ቢሮአችን አዲስ አበባ ፒያሳ Downtown ሕንጻ(ፒያሳ የገበያ ማዕከል) ላይ

☎️ 0912085085 ዲያቆን ዳግማዊ ሰለሞን (Certified psychiatrist from yale,Sydney and Harvard University)

Telegram account- @Orthodoxtewahed0

ይደውሉ ይመዝገቡ የምክክር አገልግሎቱን ያግኙ።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ርግብና ዋኔን

ርግብና ዋኔን
አብረዉ ዘመቱና ዋኔን
ርግብ ደህና ገባች >> /2/
ዋኔን ገደሉና >> /2/

በዘርና ጎሳ ዋኔን
ሠዉ ሁሉ ተከፍሎ >>
ሰይፍንም ጨበጠ >>
ልቦናዉ ቂም አዝሎ>>
ሰላምን የሚያወርድ >>
እንድ የሚያረገንን >>
እባክህን አምላክ >>
ሙሴን አድለን >>
ሠላምህን አብዛ ምድሪቷን አሳርፍ
የቅዱሳን አምላክ በጭንቃችን ድርስ /2/


በወገን ላይ ወገን ዋኔን
ይብቃ መነሳቱ >>
ይስፈን በምድር ላይ >>
የእግዚአብሔር መንግስቱ >>
ጦራችን ይሰቀል >>
እንያዝ በገና >>
ሠላምን እናዚም >>
በፍቅር እንፅና >>
ምድሪቷን አሳርፍ ሰላምህም ይብዛ
በአንድነት አኑረን የአለሙ ቤዛ /2/


የመርገም ጨርቅ ሆነ ዋኔን
ፅድቃችን በሙሉ >>
አንተን ያልበደለ >>
ማነዉ በዘመኑ>>
አማነዉ በማታ >>
ቀን ያከበርነዉን >>
የኛ ስራ ሆኗል >>
መክሰስ የበቃው >>
ፍቅር ባትሆን ኖሮ ባያቅትህ መጥላት
አይታይም ነበር የሰዉ ልጅ በህይወት


ሊቀ ዲያቆናት ነብዩ ሳሙኤል
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ቅዳሴ ክፍል 78 ይህንን ይመስላል ተለማመዱት

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

✞ የአምላክ ዐቃቤ ሕግ ✞

ገባሬ መንክራት በገድሉ ያወቅነው
የእግሮቹ ትቢያ የአራዊት ስንቅ ነው
ገብረ መንፈስ ቅዱስ የአምላክ ዐቃቤ ሕግ
የኢትዮጵያ ዋስ ነው ፈጥኖ የሚታደግ

ፀሐይ(2)የምድራችን ፀሐይ
በገድሉ ያበራል እስከ ጥልቁ ቀላይ
የመላዕክት ወዳጅ(2)ገብረሕይወት ሰማይ
አዝ
መብረቅ(2)ሰረገላው መብረቅ
የቃልኪዳኑ ወንዝ ቢጠጣ የማይደርቅ
የፍጥረቱ ደስታ(2)ገብረሕይወት ፃድቅ
አዝ
ኮከብ(2)ክብረገድላን ኮከብ
ዓለምን የሚያስንቅ መዐዛው የሚስብ
አርከ ሥሉስ ቅዱስ(2)ገብረሕይወት ኪሩብ
አዝ
ስኂን(2)ፄና ልብሱ ስኂን
የነፍስን አዳራሽ በገድል የሚሸፍን
የሚነበብ መፃፍ(2)ገብረሕይወት ድርሳን
አዝ
መቅረዝ(2)የማኅቶት መቅረዝ
ምድረከብድ ዝቋላን ያለመለመ ወንዝ
የዝጊቲው ፈዋሽ(2)ገብረሕይወት ምርኩዝ

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​#ክፍል_2
#ጾም_እና_ሩካቤ|ግብረስጋ ግንኙነት|

ከተጋባን በኋላስ ድንግልና ሳይሆን ወሲብ ቦታውን ይይዛል። በጋብቻ ወስጥ ሩካቤ |ግብረ ስጋ ግኑኝነት| በመጽሐፍ ቅዱስ እንዴት ይገለጻል ??

ዕብ 13፡4 ‹‹ መጋባት በሁሉ ዘንድ ክቡር መኝታውም ንጹሕ ይሁን፤ ሴሰኞችንና አመንዝሮችን ግን እግዚአብሔር ይፈርድባቸዋል››፡፡ ስለሆነም በጋብቻ ውስጥ ያለው መኝታ/ግብረ ስጋ
ግኑኝነት/ ንጹሕ ነው፤ ነውር የለበትም።

ይሄ ማለት ግን ባል እና ሚስት ሌላ ስራ
የለባቸውም፤ ሁሌም ከአልጋ አይውረዱ ማለት አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስ በሁሉ ነገራችን መመሪያ አለው… ‹‹ነገር ግን ሁሉ በአገባብና በሥርዓት ይሁን።›› 1ኛቆሮ 14፡40፡፡

☞ ስለሆነም ሩካቤ ስጋ በቤ/ክ ገደብ ይጣልበታል ሁሌ አይፈጸምም… መቼ እንዴት ብንል?
👉 1ኛ ቆሮ 7፡4 ‹‹ ሚስት በገዛ ሥጋዋ ላይ ሥልጣን የላትም፥ ሥልጣን ለባልዋ ነው እንጂ፤ እንዲሁም ደግሞ ባል በገዛ ሥጋው ላይ ሥልጣን የለውም፥ ሥልጣን ለሚስቱ ነው እንጂ። ለጸሎት ትተጉ ዘንድ ተስማምታችሁ ለጊዜው ካልሆነ በቀር፥ እርስ በርሳችሁ አትከላከሉ ፤ ራሳችሁን ስለ አለመግዛት ሰይጣን እንዳይፈታተናችሁ ደግሞ አብራችሁ ሁኑ።›

ይሄ የቅዱስ ጳውሎስ መልዕክት ስለ ግብረስጋ ግኑኝነት ግልጽ መመሪያ ነው። ሚስትም ባልም በገዛ ስጋቸው ስልጣን የላቸውም ስልጣኑ የትዳር አጋራቸው ነው ማለት። ባል ወይም ሚስት ከሁለት አንዳቸው ግብረ ስጋ ግኑኝነት ቢፈልጉ ሌላውን ወገን "አካሉ የኔ ነው" ብሎ መከልከል የለበትም ፤ ስልጣኑ የሱ አይደልም… ይልቁን ለትዳር አጋራችሁ
ፍላጎት የነቃችሁ ሁኑ ማለት ነው… ነገር ግን ሁሌ መፈጸም አትችሉም አለ እና የማይፈጸምበት ጊዜን ሲገልጽ ‹‹ ለጸሎት ትተጉ ዘንድ ተስማምታችሁ ለጊዜው ካልሆነ በቀር፥ እርስ በርሳችሁ አትከላከሉ ፤›› 1ኛ ቆሮ 7፡5፡፡

#ይቀጥላል
በቀጣይ ክፍል 👉 መቼ ነው ለጸሎት የምንተጋው?

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ቅዱስ

ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ኢየሱስ ክርስቶስ
ኃያል ኃያል ኃያል አማኑኤል

አስቀድሞ የነበረ አሳልፎ የሚኖር
በሥልጣኑ ያጠፋልን ሙስና መቃብር
ከአባቱ ጋር ትክክል ነው በኃይል በጌትነት
በዓለም ሊፈርድ የሚመጣው በክብር በትስብእት

ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር
ኃያል ኃያል ኃያል አማኑኤል

የሰው ፍቅር አገብሮት ወደ ምድር የመጣ
ከሰማያት የወረደው ወደ ሰማይ የወጣ
ከምስጉኖች ይልቅ ምስጉን ከግሩማን ግሩም
የጠቢባን ጠቢብ ጌታ የሚመስልህ የለም

ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ አማኑኤል

ብንዳስሰው ብንበላው ደግሞም ብንጠጣው
ረቂቁ የገዘፈው ሥጋን ተዋሕዶ ነው
በደመናት መጋረጃ የተሰወረ እሳት
በግርግም ውስጥ አገኘነው በግዕዘ ሕፃናት

ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ኢየሱስ ክርስቶስ
ኃያል ኃያል ኃያል አማኑኤል

ሰማያትን የዘረጋ ውኆችን የፈጠረ
የማይታይ የሚታየው በእርሱ ተፈጠረ
ሁሉን በእጁ የጨበጠ አሸናፊው ልዑል
በቤተልሔም ተወለደ ከማርያም ድንግል

ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር
ኃያል ኃያል ኃያል አማኑኤል

ዘማሪ መምህር አቤል ተስፋዬ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​​«በዐቢይ ጾም የተከለከሉ»
ክፍል 2

(ለሚጠጡ፣ ለሴቶች፣ ላገቡ፣ ለወለዱ፣ ለካህናት)

የአጽዋማትን ሱታፌ አስመልክቶ የተከለከሉ ነገሮች አሉ። የሚከተሉትን እንመልከት።

👉 “በዐቢይ ጾም ሰርግ ማድረግም አይገባም፣
👉 ሰውን ወደ መጠጥ ቤት መጥራትም አይገባም፣
👉 ሰው ሁሉ ከሚስቱ ጋር አይተኛ” በማለትም መጠጥ እና የባልና ሚስት ሩካቤም ተከልክሏል። (ፍት.ነገ አን 15፥592 – 593)

በተጨማሪም “በዓቢይ ጾም አያጊጡ፣ ሴቶች ጌጣቸውን ይተው፣ ሁሉም ለእያንዳንዱ በጾመ ዐርብዓ እና በሰሙነ ሕማማት መጠበቅ ይቀባዋል፣ በምንጣፍ የሚገናኙ ሰዎች ከጋብቻ ህግ የወጣ ነው፣ ክብርት በምትሆን በሰሙነ ሕማማት ይህቺን ኃጢአት የሚሠራት ወዮለት!” ብሎ ጌጥን ከልክሎ ሩካቤን በሰሙነ ሕማማት ይበልጥ መከልከሉት «ወዮለት» በሚል ቃል ጠበቅ ያደርገዋል። (ፍት.ነገ አን 15፥597)

እንደገናም “በሰሙነ ሕማማት ክርስትና ማንሳት፣ ክህነት መስጠት፣ ለሞቱ ሰዎች መጸለይ አይገባም፣ በእነዚህ ቀናት ለሚሞቱ ሰዎች ግንዘትና ፍታት በሆሣዕና በዓል ቀን ይነበብ እንጂ” (ፍት.ነገ አን 15፥600) ካለ በኋላ ቁጥር 601 ላይ “በዓርባው ቀናትም ደስታ ማድረግ መጋባት ክህነት መሾም ክርስትና ማንሳት አይገባም፤ ይሞታል ተብሎ ለሚያስፈራው ግን ጥምቀተ ክርስትና ይደረግለታል” በማለት ልዩ ምክንያትን (Exception) ብቻ ክርስትና ለማንሳት በመፍቀድ አዝዘዋል።

“በዐቢይ ጾም የሰማእታት በዓል ልናከብር አይገባም፣ የሰማእታት መታሰቢያ በእሑድ በቅዳሜ ይሁን እንጂ” (ፍት.ነገ አን 15፥591) በማለት የንግሥ ክብረ በዓላት በተለይ ከሰንበት ውጪ ባሉት ዕለታት ተከልክለዋል።

ጾም ላይ ብቻ ሳይሆን ትንሳኤንም ጨምሮ “በዕለተ እሑድ የትንሳኤ ዕለት ግንዘት ማድረግ በፋሲካ ቀንም ማልቀስ አይገባም” (ፍት.ነገ አን 15፥601) በማለት ይከለክላል።

👉 “ዓቢይ ጾምንና እሮብንና አርብን የማይጾም ሰው ካህን ከሆነ ይሻር ምእመን /ሕዝብ/ ቢሆን ይለይ” የሚልም ለውግዘት የሚያበቃም ህግ አለ። (ፍት.ነገ.አን 15፥589)

በተቃራኒው ከካህናት ወገን የማይገባ ጾም የጾመም የተከለከለ መሆኑን “ከስዑር ቅዳሜ ዉጪ ሰንበታን የጾመና በሰሙነ ሕማማት ቀንና ሌሊቱን ሳያስተካክል የቀኑን ሥርዓት አስቀድሞ ቢያውል ከክህነቱ ይሻር” ተብሏል። (ፍት.ነገ.አን 15፥590) ለምመን ደግሞ ቀኖና የሚያስፈልገው መሆኑ ነው።

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

✥ የዐቢይ ፆም የመጀመሪያ ሳምንት ✥

• በመምህር ዶ/ር ዘነበ ለማ •
═════●◉❖◉●══════
✥ ዘወረደ ✥
═════●◉❖◉●══════
✢ Share ✢
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​ዘወረደ

የመጀመሪያ የአቢይ ጾም መግቢያ እሁድ ዘወረደ ይባላል ደግሞም ጾመ ሕርቃል ይባላል፡፡ «ዘወረደ» ማለት «የወረደ» ማለት ነው፡፡ አምላክ ሰው ሆነ፤ ሰው አምላክ ሆነ ማለት ነው። ይህም ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳንና ፍቅሩን ሊገልጽልን ከሰማያት መውረዱን ከድንግል ማርያም የእኛን ሥጋ መዋሐዱን የሚያዘክር፤ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመላክት፣ የሚታወስበት፣ የሚነገርበት የዐቢይ ጾም አንደኛው ሳምንት ነው፡፡ዮሐ.3-13፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ለአዳም በገባዉ ቃልኪዳን መሰረት “ የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ልጁን ላከ”ገላ 4፥4 እንዳለ ሐዋርያዉ ቅዱስ ጳዉሎስ የጠፋዉን አዳም ፍለጋ ከአባቱ እሪና ሳይጎድል ሳይለይ ከሰማይ መዉረዱን የምናዘክርበት በዓል ነዉ።

ይህ ጾም የጾም መግቢያ የመጀመሪያ ሳምንት የምንጾመው ጾም ሲሆን ሕርቃል የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ለአዳም “ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ በመልዕልተ መስቀል ተሰቅየ አድንኃለሁ” ብሎ ለአዳም ቃል ገባለት ፡፡ ዘፍ. ፫ ፥ ፲፭ ይህ ኪዳነ አዳም ይባላል ፡፡ የቃል ኪዳን ሁሉ መሠረት ነው፡፡

ሁለቱን ኪዳናት (ብሉይ ወሐዲስ) በፅኑዕ ተስፋ ያስተሳሰረ የረጅም ዘመናት የድኅነት ሰንሰለት ነው ፡፡ ዘወረደ እርቀ አዳም ፤ ተስፋ አበው ፤ ትንቢተ ነቢያት ፤ ሱባኤ ካህናት መፈፀሙ ፤ ኪዳነ አዳም መሲህ መወለዱ የሚነገርበት የፍቅር አዋጅ ነው። እኛም በዚህ በአብይ ፆም የለመነውና የጠየቅነው ነገር ሁሉ ከኃጢአት በስተቀር እንዲከናወንልን ፆምን ገንዘባችን እናድርግ።

በተለይ አሁን በቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሰ በሚታየው አስቸጋሪ ፈተና እያንዳንዳችን ልባዊ ፆም በመፆም ልዑል እግዚአብሔር የፀሎታችንን ምላሽ እንዲሰጠን እንማፀን።

ጾም ጸሎታችን የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ይቀበልልን አሜን፡፡

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ሥርዓት ቅዳሴ
ከሠራኢ ካህን፣
ቅዳሴ፡
ዘእግዚእነ
“ዘበእንቲኣነ ለሰብእ ወበእንተ መድኃኒትነ፡ ወረደ እምሰማያት። ተሰብአ፡ ወተሠገወ እመንፈስ ቅዱስ ወእማርያም እምቅድስት ድንግል፤ ስለ እኛ ስለ ሰዎች እኛን ለማዳን ከሰማይ ወረደ፤ በመንፈስ ቅዱስ ግብር  ከቅድስት ድንግል ማርያም ፍጹም ሰው ሆነ፡፡”

ወንጌል፡ ዮሐ.፫፥፲-፳፬
የዕለቱ ምንባባት:-
•  በሠራኢ ዲያቆን (ዕብ.፲፫፥፯-፲፯)
•  በንፍቅ ዲያቆን (ያዕ.፬፥፮-ፍጻሜ)
•  በንፍቅ ካህን (የሐዋ. ፳፭፥፲፫-ፍጻሜ)

ምስባክ፡ “ተቀነዩ ለእግዚአብሔር በፍርሃት ወተሐሠዩ ሎቱ በረዓድ አጽንዕዋ ለጥበብ ከመ ኢይትመዐዕ እግዚአብሔር” (መዝ.፪፥፲፩)

ወንጌል፡ ዮሐ.፫፥፲-፳፬
ስብሐት ለእግዚአብሔር ኪያነ ዘፈጠረ ከመ ናምልኮ፤ እንድናመልከው እኛን ለፈጠረ ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን!

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

እንኳን ለዐቢይ ጾም በሰላም
      አደረሳቹ አደረሰን!

"ጾምንም ቀድሱ፥ ጉባኤውንም አውጁ፥"
👉 ትንቢተ ኢዮኤል 2:15

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በቅዱስ መጽሐፏ እንደምታስተምረን፣ ኃጢአትና ዲያብሎስ የአንድ ሳንቲም _ ሁለት ገጽታዎች ናቸው፤ ይህም ማለት ዲያብሎስ ባለበት ኃጢአት አለ ፤ ኃጢአት ባለበትም ዲያብሎስ አለ ማለት ነው፤ እነዚህ ሁለቱ የሚለያዩ አይደሉም፤ የመጨረሻ ግባቸው ደግሞ ሰውን መጣል ነው፡፡ዲያብሎስ የሰውን ደካማ ዝንባሌ ወይም በሆነ ነገር መጐምጀትን በሰው ሲመለከት ያንኑ የጐመጀበትን ክፉ ምኞት እንዲፈጽም፣ በረቂቅ የሰው ኅሊና ውስጥ ገብቶ በከፍተኛ ደረጃ ይገፋፋል፤ ሰውም በራሱ የመጐምጀት ዝንባሌና በዲያብሎስ ግፊት ለመንፈሳዊ ሕይወቱ ጐጂ የሆነውን ድርጊት ይፈጽማል ፤ ቀጥሎም ድርጊቱ በእግዚአብሔር ፊት በደል ይሆንና ከእግዚአብሔር ይለየዋል፡፡ ሰው ከእግዚአብሔር ከተለየ ደግሞ ዘለዓለማዊ ሕይወትንና ክብርን ጨምሮ ብዙ መልካም ነገርን ያጣል፤ ኃጢአት የሚባለውም ይህ ነው፤ በቀደሙት አባትና እናት ማለትም በአዳምና ሔዋን የተከሠተው ነገርም ይኸው ነው፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት

ኃጢአትን በጽድቅ፣ ዲያብሎስን በጾም በማሸነፍ የአሸናፊነትን መንገድ ሊያሳየን የመጣው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአዳምና በሔዋን የተፈጸመው ውድቀት እንዴት እንደሚቀለበስ በዚህ ጾም አስተምሮናል፡፡ ጌታችን ዐርባ ቀንና ዐርባ ሌሊት ከጾመ በኋላ ተራበ፤ ዲያብሎስም መራቡን አይቶ ይጐመጅልኛል ብሎ በምግብ ፈተነው፡፡ የጌታችን መልስ ግን ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርም ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ የሚል ነበረ፣ በተመሳሳይም በፍቅረ ንዋይና በአምልኮ ባዕድ ፈተነው የጌታ መልስ ግን በተቃራኒው ነበረ፡፡

ዲያብሎስ በሦስቱም የማስጐምጃ ፈተናዎች ጌታ ሊሸነፍለት ካለመቻሉም በላይ "አንተ ሰይጣን ከኋላዬ ሂድ" ብሎ ሲገሥጸው ተሸንፎ ትቶት ሂዶአል፡ በአሸናፊነቱ የተደሰቱ መላእክትም ወዲያውኑ መጥተው በክብረ አምልኮ አገለገሉት፤ በዚህ ድርጊት የምንመለከተው እውነታ ቀዳማይ አዳምን ባሸነፈበት ስልት ዳግማይ አዳም ክርስቶስን ለመጣል ዲያብሎስ የሄደበትን ርቀት በአንድ በኩል ስናይ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ዳግማይ አዳም ክርስቶስ የቀዳማይ አዳም ተሸናፊነትና ውድቀት ለመቀልበስ ያሳየውን ጥብዓት እናያለን፡፡

በዚህም የቀደመው ውድቀት በኋለኛው አሸናፊነት ሙሉ በሙሉ ተቀልብሶ፣ ዲያብሎስ ጓዙን ጠቅልሎና ተስፋ ተስፋ ቆርጦ መሄዱን እናስተውላለን።

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!

ጌታችን የአሸናፊነትን መንገድ በቃልና በተግባር አስተምሮናል፤ አሳይቶናልም፤ ይህንም ያደረገው እሱ አሸንፎልናል እያልን ለመኵራራት ሳይሆን፣ በእሱ ኃይል እየታገዝንና እሱ ባሸነፈበት ስልት እየተጠቀምን እንድናሸንፈው ነው፡፡ ሰይጣን የሚሸነፍበት ስልት በሌላ ሳይሆን፤ ሥጋዊ መጐምጀትን ከአእምሮአችን አውጥተን በመወርወር ነው፡፡

ሥጋችን በፍቅረ ንዋይ፣ በሥልጣን፣ በዝሙት እንደዚሁም በተለያዩ ሥጋዊ ምኞቶች ሊጐመጅ ይችላል፤ ያን ጊዜ ሰይጣን እነሱን እንድንፈጽም ሊገፋፋን ከበኋላችን እንደቆመ እናስብና "አንተ ሰይጣን ከኋላዬ ሃድ” እንበለው፡፡ በቃል ብቻ ሳይሆን በተግባር ያስጐመጁን ነገሮችን ከኅሊናችን አውጥተን በመጣል እሱን ማሸነፍ አለብን፤ በዚህ ጊዜ ሰይጣን ይሸሻል፤ መላእክትም ወደኛ መጥተው ይረዱናል፣ ይጠብቁናል፤ ያግዙናል፣ ያድኑናል፡፡ ዲያብሎስ የሰዎችን የመጐምጀት ዝንባሌን ተከትሎ በመገፋፋት ዛሬም ዓለማችንን ለከፋ ውድቀት እየዳረጋት ነው፣ ሀገራችንን ጨምሮ በየአካባቢው የሚቀሰቀሱት አለመግባባቶችና ግጭቶች መንሥኤያቸው ከመጐምጀት ውጭ ሊሆን አይችልም፡፡ ግማሹ በሥልጣን፣ ግማሹ በሀብት፥ ግማሹ በራስ ወዳድነት፣ ግማሹ ደግሞ የበላይ ለመሆን በሚል እሳቤ የሰው ኅሊና በክፉ ምኞት ይጐመጅና በዲያብሎስ ገፋፊነት ወደ ተግባራዊ ጥፋት ይገባል፡ በውጤቱም ሰው ይጎዳል፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት

ጾም ማለት እህልንና የእንስሳት ውጤቶችን ከመመገብ መከልከል ብቻ አይደለም፣ የእንስሳት ውጤት የሆኑትን ላለመመገብ ከምንወስነው በላይ እኩያት ፍትወታትንና ኃጣውእን ላለማስተናገድ በቁርጥ መወሰን ይጠበቅብናል፡፡ ስንጾም መገዳደልን፤ መጣላትን መለያየትን፤ መገፋፋትን በሆነ ነገር መጐምጀትን እርም ብለን በመተው ዲያብሎስን የምናሸንፍበት የአሸናፊነት ኅሊና መላበስ አለብን፣ ከክፉ ኅሊና እና ተግባር የተለየን ያህል በአንጻሩ ደግሞ በጎ ነገርን ለመስራት በእጅጉ መበርታት ይጠበቅብናል፡፡

ዲያብሎስ ተስፋ ቆርጦ የሚሸሸው ይቅር ይቅር ስንባባል፤ ለሰላምና ለአንድነት፣ ለፍቅርና ለስምምነት ስንቆም ነው! ከዚህም ጋር በእግዚአብሔር ፊት እጅግ ጸያፍ የሆነው ግብረ ኃጢአት በዚህች ምድር እንዳይፈጸም ማኅበረ ሰባችን በተጠንቀቅ ሲቆም ነው፤ እንደዚሁም ደም መፋሰስ፣ አለመተማመንና በሴት ልጆቻችን የሚደርስው አካላዊ፣ መንፈሳዊና ሞራላዊ ጥቃት ሲቆም ነው፡፡ ጾማችን በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት የሚኖረው የተፈናቀሉት ወገኖቻችን ወደ ቀያቸው ተመልሰው ሰላማዊ ኑሮ መኖር ሲችሉ፣ የተራቡት ሲደገፉ፣ ፍትሕ ያጡት ፍትሕ ሲያገኙ ነው፡፡

ይህ ዓይነት መልካም ሥነ ምግባር በእያንዳንዱ የማኅበረሰብ አእምሮ ቦታ አግኝቶ ሲተገበር ትክክለኛውን ጾም ጾምን ማለት እንችላለን፣ ዲያብሎስም በእርግጠኝነት በዚህ ይሸነፋል፤ የሰው ጣዕመ ሕይወትም በዚህ ይለመልማል! ምድሪቱም በእግዚአብሔር በረከት ትሞላለች፡፡ ይህን ቅዱስ ተግባር በወርኃ ጾሙ በደንብ እንድንተገብረው ለመላው ኢትዮጵያውያን በተለይም ለኦርቶዶክሳዊው ማኅበረሰብ መንፈሳዊና አባታዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

በመጨረሻም

በሀገራችን ረሃብ የሚያጠቃቸው ወገኖች በበዙበት በአሁኑ ወቅት፤ ሳንመጸውት ጾምን ጾምን ማለት ማጣፈጫ ወጥ የሌለው ምግብ መመገብ ማለት ስለሆነ፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የቁርስ በጀቱን ለተራቡ ወገኖች በመለገስ ወገኖቹን በረሃብ ከመሞት እንዲታደግ ወቅታዊ ጥሪያችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡

መልካም የጾም ወቅት ያድርግልን! እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ !! ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!! አሜን፡፡

አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት መጋቢት ፩ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም. አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​​​ዐቢይ ጾም

ጾም ማለት ሰውን ከምግብ መከልከል ነው፡፡ (ፍትሃ ነገስት አንቀፅ.15) “ጾምሰ ተከልኦተ ብዕሊ ዕምመብልዕ በጊዜ እውቅ” ጾም ማለት በታወቀው ዕለት በታወቀው ሰዓት ሰው ከምግብ የሚከለከለው መከልከል ነው፡፡

መብል መጠጥ የኀጢአት መሠረት ነው በመብል ምክንያት ሞት በሰው ልጆች ላይ መጣ “ይችን ዕፀ በለስ ብትበሉ ሞትን ትሞታላችሁ” ዘፍ.2፥17 ጾም ማለት ሰውነት ከሚፈልጋቸው ነገሮች ሁሉ መከልከል ለሰውነት የሚያምረውን የሚያስጐመዥውን ነገር መተው ማለት ነው። መብል መጠጥ ከልክ ሲያልፍ ከተዘወተረም ከእግዚአብሔር ይለያል፤ “ያዕቆብ በላ ጠገበ ወፈረ ገዘፈ ደነደነ ፈጣሪው እግዚአብሔርን ተወ ሕይወቱ ከእግዚአብሔር ተለየ” ዘዳ.32፥15-17 “የእግዚአብሔር መንግሥት መብልና መጠጥን አትሰብክም” ሮሜ.14፥16፣ 1ቆሮ.8፥8-13 “ዛሬ የሚራቡ የሚጠሙ ብፁአን ናቸው ይጠግባሉና ማቴ.5፥6 ጾም የሥጋ መቅጫ ነው፤ “ነፍሴን /ሰውነቴን/ በጾም ቀጣኋት መዝ.68፥10

ጾም በነቢያት የተመሠረተ በክርስቶስ የጸና በሐዋርያትም የተሰበከና የተረጋገጠ ለክርስቲያኖች ዲያብሎስን ድል የምንነሣበት መንፈሳዊ የጦር ዕቃ ነው፡፡ ስለዚህ ሐዋርያዊትና ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እንደምታስተምረን ይህን ጾም ከምግብ ለመከልከል ጋር ጸሎትን፥ ስግደትን፥ ምጽዋትንና የንስሐ ዕንባን ጨምረን እንጹመው፡፡ ጌታችንና ነቢያት፣ ሐዋርያት የተውልን መንፈሳዊ መሣሪያ ነውና፡፡

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ጾም የጾመው ለአብነት፣ ለማስተማር፣ ለአርዓያ ነው፡፡ በዚህ ታላቅ ጾም ጥንተ ጠላታችን ዲያብሎስ፣ ከሰው የሥጋ ጠባይ የሚመጣ ስስትና ፍቅረ ንዋይ ድል የተነሱበት ነው፡፡ እኛም ይህን እያሰብን በተለያየ መንገድ የሚመጣብንን ፈተና ለማራቅ ከዚህ ታላቅ ጾም በረከት እንድናገኝ እንጾማለን፡፡ ጸልዮ ጸልዩ፣ ጾሞ ጹሙ ብሎናል፡፡ ማቴ.6-16፡፡ ስለዚህም ትእዛዙን ለማክበር እንጾማለን፡፡

የዚህ ታላቅ ጾም ስያሜዎች የሚከተሉት ናቻው ፡-

ዐቢይ ጾም
ባሕርይ አምላክ በሆነዉ በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተመሠረተ በመሆኑ ዐቢይ ወይም ታላቅ ጾም ይባላል፡፡

ጾመ ሁዳዴ
በጥንት ጊዜ ገባሮች ለባለ ርስት የሚያርሱት መሬት ሁዳዴ ተብሎ ይጠራ ነበር፡፡ እኛም ባለቤቱ ኢየሱስ ክርስቶስን እያሰብን የምንጾመው በመሆኑ ጾመ ሁዳዴ ተብሏል፡፡

የካሳ ጾም
አዳምና ሔዋን ከገነት የተባረሩት ለውርደት ሞት ለሲዖል ባርነት የበቁት በመብል ምክንያት ነው፡፡ በመብል ምክንያት የሞተውን የሰው ልጅ ጌታችን በፈቃዱ በፈጸመው ጾም ካሰው፤ መንፈሳዊ ረሃብን በረሃቡ ካሰለት፡፡ ስለዚህም የካሳ ጾም ተባለ፡፡

የድል ጾም
አርዕስተ ኃጣውእ /ማቴ. 4/ ድል የተነሱበት በመሆኑ የድል ጾም ተብሏል፡፡

የመሸጋገሪያ ጾም
ጌታችን ከሕገ ኦሪት ወደ ሕገ ወንጌል ሊያሸጋግረን የጾመው ጾም በመሆኑ የመሸጋገሪያ ጾም ተብሏል፡፡

ጾመ አስተምህሮ
ጌታችን የጾመው ለትምህርት ነው፡፡ እርሱ መጾም ያለበት ሆኖ አይደለም፡፡ ስለዚህም ይህ ጾም ጾመ አስተምህሮ ይባላል፡፡ አርባ መአልትና አርባ ሌሊት ጾመ ማቴ.4፥2

የቀድሶተ ገዳም ጾም
ጌታችን ከከተማ ርቆ ከሰው ተለይቶ /በገዳመ ቆሮንጦስ/ በመጾም ከከተማ ርቆ ከሰው ተለይቶ በብሕትውና መኖርን ቀድሶ የሰጠበት፣ የመጥምቁ ዮሐንስና የነቢዩ ኤልያስን ገዳማዊነት የባረከበት በመሆኑ የቀድሶተ ገዳም ጾም ተብሏል፡፡

የመዘጋጃ ጾም
ሕዝበ እሥራኤል የፋሲካውን በግ ከመመገባቸው በፊት ዝግጅት ያደርጉ ነበር፡፡ እኛም ትንሣኤን ከማክበራችን፣ ሥጋና ደሙን ከመቀበላችን በፊት በጾምና በጸሎት ዝግጅት የምናደርግበት በመሆኑ የመዘጋጃ ጾም ተብሏል፡፡

የሥራ መጀመሪያ ጾም
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ሥጋ ለብሶ በምድር ሳለ ስብከት፣ ተዓምራት ከመጀመሩ በፊት የጾመው ጾም ነውና የሥራ መጀመሪያ ጾም ይባላል።

ሼር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ሰላም ውድ የዝማሬ ዳዊት ቻናል ተከታታዮች በእግዚአብሔር ፍፁም ሰላምታ እንደምን ሰነበታቹ? አሜን! የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን!

እንደሚታወቀው ፊታችን ታላቁ የዐቢይ የጾም ወቅት ነው በመሆኑም
👉 ስለ ዐቢይ ጾም ምንነት
👉 እያንዳንዱን ሳምንታት ስም፣ ምንነት እና ትርጉም
👉 እንዲሁም የጾም፣ የበገና መዝሙራትን ወደናንተ ለማድረስ ዝግጅቱን ጨርሷል

ይህን መልዕክት ለሁሉም ሰው #ሼር በማድረግ እንዲዳረስ የማድረግ ሃላፊነት የናንተ ነው።

👉 @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​#ትንሽ_ይበቃኛል
አስተማሪ ታሪክ

በአንድ የገጠር መንደር በቤተሰቦቻቸው የእርሻ ማሳ በጋራ እያመረቱ የሚተዳደሩ ሁለት ወንድማማቾች ነበሩ፡፡ #አንደኛው ትዳር መስርቶ ብዙ ቤተሰብ የሚያስተዳደር ሲሆን አንደኛው ግን ገና አላገባም፡፡ ብቻውን ነው የሚኖር፡፡ በምርት መሰብሰቢያ ወቅት ያገኙትን ምርት እኩል ይካፈሉም ነበር፡፡

ታዲያ አንድ ቀን ትዳር ያልመሰረተው ለእራሱ እንዲህ አለ፡፡ “ያገኘነውን ምርት እኩል መካፈል ፍተሃዊ አይደለም፡፡ እኔ ብቻየን ስለሆንኩ ትንሽ ነገር ነው ሊበቃኝ የሚችለው፡፡” እንዲህ ብሎ መሸት ሲልለት ጨለማውን ተግን አድርጎ ከጎተራው ኬሻ ሙሉ ጥራጥሬ እያነሳ በቤታቸው መካከል ባለው መስክ አቋርጦ ከወንድሙ ጎተራ ይሞላለት ነበር፡፡ በተመሳመሳይ ሁኔታ ትዳር የመሰረተው ወንድሙም ለእራሱ እንዲህ ይላል “ምርታችንን እኩል መካፈላችን ትክክል አይደለም፡፡ ሁኖ ሁኖ እኔ ባለ ትዳር ነኝ በመጭዎቹ ዓመታት አንዳች ነገር ቢፈጠር እንኳን ልጆቼና ሚስቴ ይንከባከቡኛል፡፡ ይሄ ወንድሜ ግን ብቻውን ነው፡፡ ማንም የሚንከባከበው የለውም ስለሆነም” አለና መሸት ሲልለት ጨለማውን ተግን አድርጎ ኬሻ ሙሉ ጥራ ጥሬ እየወሰደ ከላጤ ወንድሙ ጎተራ ይጨምራል፡፡

እንዲህ እንዲህ እያሉ ዓመቱ ተጋመሰ፤ የእህል ጎተራቸው ያልቀነሰበት ምክንያት ግን እንቆቅልሽ ሆኖባቸዋል፡፡ ከዛም አንድ ቀን ምሽት ሁለቱም እንደልማዳቸው አንደኛው ላንደኛው ኬሻ ሙሉ ጥራጥሬውን ይዘው ሲተላለፉ ሁኔታዎች ተገጣጠሙና መንገድ ላይ ይጋጫሉ፡ ቀስ አድርገው ሸክማቻን አውርደው ሲተያዩ ወደንድማማቾቹ ነበሩ፡፡ በልባዊ ፍቅር ተቃቀፉ፡፡

#ጭብጥ - ፊት ለፊት ተነጋግረው የበለጠውን አንደኛው መውሰድ እንዲችል ማድረግ ጠፍቷቸው አይደለም ግን አንተ ትብስ አንተ ትብስ እየተባባሉ ውሳኔ ላይ መድረስ እንደማይችሉ ስላወቁ የፈጠሩት መላ ይመስላል፡፡

እንኳንስ ስጡ ሳይባሉ ለመስጠት መፍቀድ ቀርቶ ቢጠየቁ እንኳ እኩል ድርሻየ ነው ማለት በሚቻልበት ሁኔታ የበለጠውን ለመስጠት መሻት ከልባዊ ፍቀር ውጭ ሊመጣ አይችልም፡፡ ለሰጨውም ሆነ ለተቀባዩ ሳይቀንስ የሚሰጥ ስጦታ ቢኖር ልባዊ ፍቅር ብቻ ነው፡፡ እንዲህ አይነት ፍቀር ይስጠን፡፡

ለእህት ወንድሞች ይማሩበት ዘንድ አጋሩ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

የምንጠብቀው መልስ ከላይ እንደሆነ ተነጋግረን ከጨረስን በኋላ ወደ ታች ድጋሚ መጠየቁ ስለምን ይሆን??? ምንስ አገኘን???

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ዐብይ ጾም ለምን የንሰሐ መዝሙር ብቻ ሆነ?

🎙 ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ድምፀ
👉🏾በዐብይ ጾም ለምን ከበሮ አይመታም❓
👉🏾በዐብይ ጾም ለምን ፅናፅል አንጠቀመም❓
👉🏾በዐብይ ፆም መብላት የሌለብን ምግቦች በየአመቱ ጥያቄ እሚያስነሳው 👉🏾🐠🐟 ዓሳን አለመብላት

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

እንኳን ለአባታችን ለአቡነ ገብረ መንፈስቅዱስ አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ

#ለሀገር_ኢትነ

ለሀገር ኢትነ ሰላማ ኪያከ ተአቅብ
አባ ኦ አባ(2) ገብረ መንፈስ ቅዱስ

በዘማሪት #ገነት

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​​​✝ እንኳን ለአባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ በዓለ እረፍታቸው በሰላም አደረሰን!

🕕 ቀኑ መጋቢት 5 ዕለቱ ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ ሰዓቱ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ሆኗል፤ አሁንም ህማሙን እየታገለ እያላበው በድካም ለፍጥረቱ ሁሉ ይለምናል፤

“አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህን ኢትዮጰያንም ባርክ” ይላል።

ህመም የጀመረው መጋቢት 3 ዓርብ ቀን ነው፤ መታመሙን የሰሙ እንደርሱ ቅዱሳን የሆኑት ዘርአቡሩክ፤ ፍሬ ቅዱስ፤ ያዕቆብ፤ ብንያምና ዮሴፍ እንዲሁም በወቅቱ የኢትዮጰያ ንጉስ የነበረው እንድርያስ ሊጠይቁት ተሰብስበዋል ወደ አጠገቡ መድረስ ግን አልተቻላቸውም አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ የሚጋርደው እንጨት ዛፍ በሌለበት በርሃ እንደ አንበሳ ተኝቶ አዩት በላዩ ያረፈው የእግዚአብሔር ጸጋ ከፊቱ የሚወጣው ብርሃን ቀይ መልኩ ረዥም የራስ ጠጉሩ እንደ ነጭ ሐር የሚሆን ጽሕሙ አስደነቃቸው።

ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ሲሆን ከሰማይ ታላቅ ነጎድጓድ ድምጽ ተሰማ ጌታችን መላአክትን አስከትሎ ወደ አባታችን ወረደ፤ ከሰማይ ወደ ምድር ህብሩ አምሳያው ልዩ ልዩ የሆነ እንደ ጸሐይና እንደ ጨረቃ የሚያበራ እንደ ወንጪፍ ድንጋይ ይወረወር ነበር ከዚያ የነበሩ ሁሉ ፈሩ ወደ ኋላም ሸሹ ምድር ራደች ተራሮች ኮረብቶች ተናወጡ ብርቱ ጩኸት ንውጽውጽታ ሆነ።

“ወዳጄ ገብረመንፈስ ቅዱስ ሰላም ላንተ ይሁን” እነሆ የማይታበል ቃል ኪዳን እገባልሃለው ስምህን የጠራ መታሰቢያህን ያደረገውን እጣን ቋጥሮ ግብር ሰፍሮ መባ ይዞ ቤትህ የመጣውን እምርልሃለው አንተ ከገባህበት ገነት መንግስተ ሰማያት አገባዋለሁ አለው፤

አባታችንም “አቤቱ ጌታ ሆይ የኢትዮጰያን ህዝብ ማርልኝ” አለው፤ እነሆ ምሬልሃለው አስራት በኩራት አድርጌም ሰጥቼሃለው፤ ከመጋቢት አምስት ቀን ጀምሮ ዝክርህን ያድርጉ በአማላጅነትህም ይማጸኑ አለው።

ከዚህ በኃላ ሰባቱ ሊቃነ መላክት የአባታችንን ነፍስ ሊቀበሉ ወረዱ በታላቅ ምስጋናም ወደ ሰማይ አሳረጉት ስጋውንም ይዘውት ሄዱ የት እንደተቀበረ ግን እስካሁን አይታወቅም አንዳንዱ በእየሩሳሌም ነው ይላሉ፤ ሌላው በምድረ ከብድ ነው ይላል ግን እስካሁን ልክ እንደ ሊቀ ነብያት ሙሴ ስጋ የት እንደ ተቀበረ አይታወቅም።

ገድሉ ትሩፋቱ ከሰማይ ከዋክብት ከምድር አሸዋ ይበዛል ኢትዮጰያን አብዝቶ ይወዳታል፤ ምድራዊ ምግብ አልተመገበም የእናቱን ጡት እንኳን አልጠባም፤ ልብስ፤ መጠለል አልፈለገም፤ የክረምት ቁር የበጋ ሐሩር እየተፈራረቀበት በተጋድሎ 562 ዓመት ኖረ፤ በዛሬዋ ቀን #መጋቢት_5 ሩጫውን ጨረሰ።

ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን እኛንም ከአባታችን በረከት ያሳትፈን፤ ከመጣብን ክፉ መቅሰፍት ይሰውረን! አሜን።

👉 መጽሐፈ ስንክሳር ዘመጋቢት

#ሼር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​ባለ ትዳሮችን ብቻ ሳይሆን የዝሙት ሱሰኞችንም ይጨምራል ሁላችሁም ሼርርርርርር : አድርጉ !!!

ዝሙት የሚሰራውን ብቻ ሳይሆን በዝሙት ሀሳብና ፍትዎት የታመምነውንም ይጨምራል ይህ ትምህርት ለእገሌ ነበር ሳይሆን ለኔ ነው ብለን ልናነበው ይገባል ለሁላችንም ይሆን ዘንድ ከኔ የበረታችሁ አስቡኝ በጸሎታችሁ

👉 ከ10 አንዱ ሊማርበት ስለሚችል ሸር አድርጉት

በጾም ወራት ባለትዳሮች ከግብረ-ስጋ ግንኙነት እንዲታቀቡ ቤተክርስትያን የምትመክረው

#መጽሐፍ_ቅዱሳዊ_ነውን?

፠ ከባለትዳር ወዳጄ ለተጠየኩት ፠
በቤተክርስትያችን ትምህርት ሰው ለአቅመ አዳም እና ለአቅመ ሔዋን ከደረሰ በኋላ ሕይወቱን የሚመራበት ሁለት አይነት ምርጫ አለው፤ ጋብቻ ወይም ምንኩስና።

❖ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለምንኩስና እንዲህ ብሎ ነበር።
#መነኩሴ ፡- ማለት መናኝ ፣ ብቻውን የሚኖር ፣ሴት የማያውቅ ድንግል፣ የገዳም ሰው፣ ባተሌ፣ ከዓለም ከሕዝብ ከገንዘብ የተለየ ማለት ነው /አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት እና
ምንኩስና በኢትዮጵያ ላይ እንደተገለጠው/፡፡

#ምንኩስና- ለሴትም ለወንድም ይሰራል፤ ዓላማው በትዳር አሳብ ሳይጠላለፉ በሙሉ ጊዜ ፈጣሪን የማገልገያ መንገድ ነው፡፡
በአንድ ወቅት ጌታ ስለ ጋብቻ ሕግ ባስተማረ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ‹‹የባልና የሚስት ሥርዓት እንዲህ ከሆነ መጋባት አይጠቅምም ›› ሲሉት እንዲህ ብሎ ዘርዝሮ ነገራቸው።

ከሴት ርቆ ከወንድ ርቆ ንጽህናን ጠብቆ መኖር ስጦታ ነው እንጂ ሁሉ የሚችለው
አይደለም ሲል ‹‹ይህ ነገር ለተሰጣቸው ነው እንጂ ለሁሉ አይደለም›› አለ። ማቴ 19፡11፡፡
ቀጠለና ቁጥር 12 ላይ ‹‹በእናት ማኅፀን ጃንደረቦች ሆነው የተወለዱ አሉ፥ ሰውም
የሰለባቸው ጃንደረቦች አሉ፥ ስለ መንግሥተ ሰማያትም ራሳቸውን የሰለቡ ጃንደረቦች አሉ። ሊቀበለው የሚችል ይቀበለው አላቸው።›› አለ፡፡

ይሄ የጌታ ንግግር የሚያረጋግጠው .. ሶስት ነገሮችን ነው። ደግሞም ብልቶቻቸውን ለግብረስጋ ግኑኝነት የማይጠቀሙበት ሰዎች አሉ ማለት ነው። በነገራችን ላይ ጃንደረባ ማለት ብልቱ የተቆረጠ ማለት ነውና፡፡

1. የመጀመሪያዎቹ በጌታ አገላለጽ በእናት ማኅፀን ጃንደረቦች ሆነው የሚወለዱ ያላቸው ፦
አካል ሳይኖራቸው የሚወለዱ ወይም አካሉ ቢኖርም ተፈጥሮአዊ ሙቀት ሳይኖራቸው የሚወለዱት ናቸው።

2. ሁለተኛዎቹ ደግሞ ሰው የሰለባቸው ጃንደረቦች ናቸው / ይሄ በአንዳንድ የአገራችን ክፍሎች በጎሳዎች መካከል ሲጣሉ እና ለጋብቻ ማጫ እንደሚሰልቡ የሚታወቁ ቦታዎች አሉ… የሚገርመው ነገር እነሱ በጉዳዩ ሊጠቀሙ የሌላውን መጠቀሚያ አካል ቆርጦ ማጫ
ማቅረብ… ምን ያህል… ኢ ፍታዊነት እንደሆነ መረዳት ይቻላል፡፡

3. በጌታ አነጋገር ሶስተኛው አይነት ጃንደረባነት ‹‹ስለ መንግሥተ ሰማያትም
ራሳቸውን የሰለቡ ጃንደረቦች አሉ›› ያላቸው ሲሆኑ... ይሄም ምንኩስና ነው፤ ለመንግስተ ሰማያት ተብሎ ከጾታ ግኑኝነት ራስን ማራቅ ማለት ነው።

❖ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሰለምንኩስና ምን አለ?
1ኛ ቆሮ 7፡17 ቅዱስ ጳውሎስ "እንዳያገቡ አወዳለው" ማለቱ ሲሆን ነገር ግን ‹‹ነገር ግን እያንዳንዱ ከእግዚአብሔር ለራሱ የጸጋ ስጦታ አለው፥ አንዱ እንደዚህ ሁለተኛውም
እንደዚያ።>> በማለት ሁሉ ተመሳሳይ ጸጋ እንደሌለው አረጋግጧል…አንዱ እንደዚህ /አያገባም/ ሁለተኛው እንደዚያ ሲል ደግሞ /ያገባል/ ማለት ነው፡፡

ልክ ጌታ በማቴ 19 ፡12 ‹‹ ሊቀበለው የሚችል ይቀበለው ›› እንዳለ ሊቀበለው የሚችል ሁሉ አይደለም፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ ዘርዘር ሲያደርገው፦
1ኛ ቆሮ 7፡32 ‹‹ነገር ግን ያለ አሳብ ልትኖሩ እወዳለሁ። ያላገባው ጌታን እንዴት ደስ እንዲያሰኘው የጌታን ነገር ያስባል፤ ያገባው ግን ሚስቱን እንዴት ደስ እንዲያሰኛት የዓለምን ነገር ያስባል፥ ልቡም ተከፍሎአል። በአገባብ እንድትኖሩ ሳትባክኑም በጌታ እንድትጸኑ ነው›› ስለሆነም ቅዱስ ጳውሎስ በአጠቃላይ መልዕክቱ ልባቹ እንዳይከፈል ከቻላችሁ አታግቡ ብሎ መክሯል … በመጨረሻው ንግግሩም ‹‹ድንግልን ያገባ መልካም አደረገ ያላገባም የተሻለ አደረገ።›› በማለት ድንግልን ማግባት መልካም ቢሆንም የተሻለው ግን አለማግባት ነው፡፡

ስለዚህ ነገር አንድ የቤ/ክ ሊቅ እንዲህ ብለው ነበር ጳውሎስ ጋብቻን ክቡር ነው ቢልም እርሱ አላገባምና ይ ብልጠቱን ተመልከቱ ብለው ነበር፡፡
እንግዲህ ይሄን የቅዱስ ጳውሎስ ብልጠቱን ማየት /አለማግባት/ ሳይቻለን ቀርቶ ጸጋችን ጋብቻ መሆኑን አውቀን ለማግባት ከመረጥን ደግሞ ቅድመ ጋብቻ ወሲብ እንደማይገባ አውቀን የምንጋባው በድንግልና ነው፡፡ ‹‹ዳሩ ግን ማግባት ወደሚገባው ዕድሜ በደረሰ ጊዜ ስለ ድንግልናው ያፈረ ሰው ቢኖር፥ የወደደውን ያድርግ፤ ኃጢአት የለበትም፤ ይጋቡ።›› 1ኛ ቆሮ7፡36፡፡

ስለድንግልናው ያፈረ ሰው ቢኖር ማለት…. ቆሞ ቀረ ተባልኩ ብሎ ያፈረ ሰው ቢኖር… ያግባ ነው የሚለው… ድንግል ሆኖ በመኖሩ ያፈረ ሰው ድንግልናውን በጋብቻ ብቻ ነው የሚያጣው ማለት ሲሆን ይሄም የቅዱስ ጳውሎስ ቃል ሰው ድንግልናውን ጠብቆ እስከጋብቻ መጽናት እንዳለበት ያረጋግጣል… ‹‹ድንግልን ያገባ መልካም አደረገ ›› 1ኛ ቆሮ7 ፡38፡፡ የሚለው ቃል መጋባት በድንግልና መሆኑን ያረጋግጣል፡፡

አረ ቅዱስ ጳውሎስ እንደዚህም ብሏል ‹‹ከዝሙት እንድትርቁ፥ እግዚአብሔርን እንደማያውቁ አሕዛብ በፍትወት ምኞት አይደለም እንጂ፥ ከእናንተ እያንዳንዱ የራሱን ዕቃ በቅድስናና በክብር ያገኝ ዘንድ እንዲያውቅ፤>> 1ኛተሰ 4፡5፡፡

አንድ መተርጉም ቅዱስ ጳውሎስ "የራስን ዕቃ በክብር ማግኘት" ያለው .. የሚገኝ የራስህ የሆነ የትዳር አጋርህን አካል ነው…. እሱም ያንተ የሆነ ንብረት ነው…. ግን በቅድስና እና በክብር ያገኝ ዘንድ የተባለው ደግሞ በህጋዊ ትዳር በሰርግ ደስታ…. በጋብቻ ስርዓት ተቀበለው ሲል ነው ብሎ ተርጉሞታል… ይሄን የሰማች አንድ እህት በወቅቱ …. እኔማ… ‹‹ብር አምባር ሳላሰኝ›› ሞቼ ነው ብላ ፎክራ ነበር… እኛም ይበል ብለን አልፈነዋል…
እንዲህ አይነቱን አቋም እናበረታታለን…እስካሁን ጉዳዩ ተጠብቆ ካለ… እንዲው አልሆነ ቦታም ከወደቀም… ድጋሚ አይነሳምና ከተክሊል ርቆ በመዓስባን ጋብቻ ለመጋባት የነፍስን ድንግልና በንስሐ መመለስ ነው፡፡

#ይቀጥላል
በቀጣይ ክፍል 👉 በጋብቻ ወስጥ ግብረ ስጋ ግኑኝነት በመጽሐፍ ቅዱስ እንዴት ይገለጻል ??

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

😥ምን ያስጨንቀናል?😞

እንኳን ደስ አላችሁ የሥነ ልቡና የምክክር አገልግሎታችንን በአዲሱ ቢሮአችን በአዲስ መልኩ ጀምረናል።

የምንሰጣቸው አገልግሎት፦
👉ድብርት/ድባቴ (Depression)
👉ብቸኝነት(Loneliness)
👉የመኖር ጣዕም እና አላማን ማጣት(Purpose and meaning of life)
👉የተለያዩ የሱስ ፈተናዎች (Drug addictions)
👉የትዳር የምክክር አገልግሎት (Married therapy)
👉እራስን የማጥፋት ሐሳቦች(Suicidal thoughts)
👉ልበ-ሙሉነትን እንዴት ማምጣት እንችላለን (self-confidence)
👉የልጅነት መጥፎ ጠባሳ/ክስተት(Trauma)
👉ጭንቀት(Anxiety)
👉የማንነትን ቀውስ(Identity crisis)
እና ሌሎች የሚያስጨንቁንን ነገሮች ሁሉ በዓለማዊው እና መንፈሳዊ መንገድ የምክክር አገልግሎት የምንሰጥ ሲሆን። ከታች ባለው ስልክ ቁጥር በመደወል ወይም በቴሌግራም አካውንት ቴክስት በመላክ ቀድመው ቀጠሮ ማስያዝ ይችላሉ።

📍ቢሮአችን አዲስ አበባ ፒያሳ Downtown ሕንጻ(ፒያሳ የገበያ ማዕከል) ላይ

☎️ 0912085085 ዲያቆን ዳግማዊ ሰለሞን (Certified psychiatrist from yale,Sydney and Harvard University)

Telegram account- @Orthodoxtewahed0

ይደውሉ ይመዝገቡ የምክክር አገልግሎቱን ያግኙ።

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

በጾም

በጾም ትትፌውስ ቁስለ ነፍስ
ወበጸሎት ትትሐሠይ መንፈስ /2/

መአልትና ሌሊት በጾም ጸሎት ተግቶ
አሳይቷል ጌታ ስርዓትን ሰርቶ
አይቀርም ፈተናው ትጋት ከሌለበት
ስጋ ካልደከመች በጾምና ጸሎት
አዝ
ሙሴ የተባለው ያ የእግዚአብሔር ሰው
ፊቱን የበራለት አርባ ቀን ጾሞ ነው
በሲና ተራራ ተቀብሎ ህግን
እርሙን እንድንተው አሳየን መንገድን
አዝ
የጸሎት እናቷ ስለሆነች ጾም
ትህትናን ይዘን ደግሞም አንድ ሆነን
ብንተጋ በጸሎት ከንስሐ ጋራ
ጾም ታደርሰናለች ከጽዮን ተራራ
አዝ
አንድበትም ይጹም ዓይንም ይረጋጋ
ጆሮም ክፉ ሰምቶ ነፍሱን እንዳይወጋ
ድሀን ከመበደል ልብም ተመልሶ
መጾምስ እንዲህ ነው የበደለን ክሶ

ዘማሪ መምህር አቤል ተስፋዬ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

 ✞ ዘወረደ
"በእርሱ ፍቃድ"

በእርሱ ፍቃድ በአባቱ ፍቃድ
በመንፈስ ቅዱስ ፍቃድ
ከሰማያት ወረደ
ከድንግል ማርያም ተወለደ

ዓለሙን እንዲሁ ወደደና
ከሰማያት በላይ ወረደና
በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት
ተወሰነ አምላከ አማልክት
ከሰማያት የወረደው
ፍቅር ስቦት የመጣዉ
ወልደ አብ ወልደ ማርያም
ኢየሱስ ፈራጅ ነዉ
አዝ
ቅድመ ዓለም ተወልዶ ያለ እናት
ድህረ ዓለምም ያለ አባት
የእግዚአብሔር ልጅ በእርግጥም ሰው ሆነ
ሁሉ በእርሱ ይኸው ተከናወነ
ከሰማያት የወረደው
ፍቅር ስቦት የመጣዉ
ወልደ አብ ወልደ ማርያም
ክርስቶስ አምላክ ነዉ
አዝ
የማይታይ ታየ በምድር
ረቂቁ ገዘፈ ስለፍቅር
ሥጋን ተዋህዶ ሆነልን ፈውስ
አማኑኤል የነገስታት ንጉሥ
ከሰማያት የወረደው
ፍቅር ስቦት የመጣዉ
ወልደ አብ ወልደ ማርያም
እግዚአብሔር እርሱ ነዉ
   
ዲ/ን ቀዳሜጸጋ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​​«በዐቢይ ጾም የተከለከሉ»
ክፍል 2

(ለሚጠጡ፣ ለሴቶች፣ ላገቡ፣ ለወለዱ፣ ለካህናት)

የአጽዋማትን ሱታፌ አስመልክቶ የተከለከሉ ነገሮች አሉ። የሚከተሉትን እንመልከት።

👉 “በዐቢይ ጾም ሰርግ ማድረግም አይገባም፣
👉 ሰውን ወደ መጠጥ ቤት መጥራትም አይገባም፣
👉 ሰው ሁሉ ከሚስቱ ጋር አይተኛ” በማለትም መጠጥ እና የባልና ሚስት ሩካቤም ተከልክሏል። (ፍት.ነገ አን 15፥592 – 593)

በተጨማሪም “በዓቢይ ጾም አያጊጡ፣ ሴቶች ጌጣቸውን ይተው፣ ሁሉም ለእያንዳንዱ በጾመ ዐርብዓ እና በሰሙነ ሕማማት መጠበቅ ይቀባዋል፣ በምንጣፍ የሚገናኙ ሰዎች ከጋብቻ ህግ የወጣ ነው፣ ክብርት በምትሆን በሰሙነ ሕማማት ይህቺን ኃጢአት የሚሠራት ወዮለት!” ብሎ ጌጥን ከልክሎ ሩካቤን በሰሙነ ሕማማት ይበልጥ መከልከሉት «ወዮለት» በሚል ቃል ጠበቅ ያደርገዋል። (ፍት.ነገ አን 15፥597)

እንደገናም “በሰሙነ ሕማማት ክርስትና ማንሳት፣ ክህነት መስጠት፣ ለሞቱ ሰዎች መጸለይ አይገባም፣ በእነዚህ ቀናት ለሚሞቱ ሰዎች ግንዘትና ፍታት በሆሣዕና በዓል ቀን ይነበብ እንጂ” (ፍት.ነገ አን 15፥600) ካለ በኋላ ቁጥር 601 ላይ “በዓርባው ቀናትም ደስታ ማድረግ መጋባት ክህነት መሾም ክርስትና ማንሳት አይገባም፤ ይሞታል ተብሎ ለሚያስፈራው ግን ጥምቀተ ክርስትና ይደረግለታል” በማለት ልዩ ምክንያትን (Exception) ብቻ ክርስትና ለማንሳት በመፍቀድ አዝዘዋል።

“በዐቢይ ጾም የሰማእታት በዓል ልናከብር አይገባም፣ የሰማእታት መታሰቢያ በእሑድ በቅዳሜ ይሁን እንጂ” (ፍት.ነገ አን 15፥591) በማለት የንግሥ ክብረ በዓላት በተለይ ከሰንበት ውጪ ባሉት ዕለታት ተከልክለዋል።

ጾም ላይ ብቻ ሳይሆን ትንሳኤንም ጨምሮ “በዕለተ እሑድ የትንሳኤ ዕለት ግንዘት ማድረግ በፋሲካ ቀንም ማልቀስ አይገባም” (ፍት.ነገ አን 15፥601) በማለት ይከለክላል።

👉 “ዓቢይ ጾምንና እሮብንና አርብን የማይጾም ሰው ካህን ከሆነ ይሻር ምእመን /ሕዝብ/ ቢሆን ይለይ” የሚልም ለውግዘት የሚያበቃም ህግ አለ። (ፍት.ነገ.አን 15፥589)

በተቃራኒው ከካህናት ወገን የማይገባ ጾም የጾመም የተከለከለ መሆኑን “ከስዑር ቅዳሜ ዉጪ ሰንበታን የጾመና በሰሙነ ሕማማት ቀንና ሌሊቱን ሳያስተካክል የቀኑን ሥርዓት አስቀድሞ ቢያውል ከክህነቱ ይሻር” ተብሏል። (ፍት.ነገ.አን 15፥590) ለምመን ደግሞ ቀኖና የሚያስፈልገው መሆኑ ነው።

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​«ጾም እስከ ስንት ሰዓት ነው?»
ክፍል 1


እንኳን በሰላም አደረሳችሁ! ?
የቅድስቲቱ ቤተክርስቲያን ሥርዓቱ በልኬት እና በምክንያት የታጀበ ነው። ጾምን ስንመለከት አብዛኞቻችን በተለምዶ ሰዓት ሳንጠብቅ (እስከ 3፣ 6፣ 7፣ 9፣ 11 ሰዓታት እያልን) እንጾማለን እንጂ የአዋጅ አጽዋማት የተወሰነ የተገደበ ሰዓት አላቸው።

ፍትሐ ነገሥታችን “ሕማማት እስከ 12 ሰዓት ይጹሟቸው፥ ሌሎቹን አጽዋማት በዓለ ልደት እና ጥምቀት ረቡዕ እና ዐርብ የሚውሉባቸው ካልሆኑ በቀር እስከ 9 ሰዓት ይጹሙ” (ፍት.ነገ አን 15፥565-566) ብሏል።

የአጽዋማትን ዝርዝር ካስቀመጠ በኋላም በዚሁ አንቀጽ ቁጥር 572 ላይ ደግሞ “በእነዚህ በታዘዙት ጾሞች ከቀኑ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ ይጹሙ፣ ... ከዚህ አብልጦ የጾመ ግን ዋጋው ይበዛለታል፣ ከጥሉላት ምግቦች መታቀብ ካልሆነ በቀር እሑድና ቅዳሜ ግን አይጹሙ” ብሎ ወስኗል።

ዐቢይ ጾም ሁዳዴ፣ ጾመ ዐርብዓ ግን ይለያል። “በዐቢይ ጾም መጀመሪያ ሱባኤ ፀሐይ እስኪገባ ይጹሙ፣ ሌሎቹን ሳምንታት እስከ 11 ሰዓት ይጹሙ፥ በሰሙነ ሕማማት ግን ኮከብ እስኪወጣ ይጹሙ” ብለዋል። (ፍት.ነገ.አን 15፥595)።

ፍትሐ ነገሥት ቁጥር 578 ላይ ደግሞ “(የሰሙነ ሕማማትን) ዓርብንና ቅዳሜን ግን ሁለቱንም በአንድነት ይጹሟቸው፣ የሚችል እስከ ሌሊት ዶሮ ጩኸት ድረስ ምንም ምን አይቅመስባቸው፣ ሁለቱን በአንድነት መጾም የማይቻለው ግን ቅዳሜን ይጹም” ተብሎ ህግ ተሠርቷል።

ይቀጥላል
በቀጣይ ክፍል 👉 በዐቢይ ጾም የተከለከሉ ነገሮች ምንድን ናቸው?

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​​​ዐቢይ ጾም

ዐቢይ ለምን ተባለ ቢሉ ‹‹ዐበየ›› ማለት ከፍ አለ ማለት ሲሆን ከዚህም ግስ አቢይ የሚለው ቅጽል ይገኛል፡፡ ዐቢይ ማለት ከፍ ያለ ትልቅ ማለት ነው፡፡

ዐቢይ ጾም የተባለበት ምክንያት፡-

. ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ጾም ስለሆነ

. በቀኑ ቁጥር ከሌሎች አጽዋማት የሚበልጥ ስለሆነ

. ሦስቱ ታላላቅ የሰይጣን ፈተናዎች ማለትም 'ትዕቢት' 'ስስት' 'ፍቅረ ነዋይ' ድል የተመቱበት ስለሆነ ነው፡፡

በቤተክርስቲያን ስያሜ መሰረት በዐቢይ ጾም ውስጥ የሚውሉ ሰንበታት እያንዳንዳቸው መጠሪያ ስም ሲኖራቸው እነርሱም፡-

1. ዘወረደ
የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሰንበት ሲሆን ይህም ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን ፈጥሮ የሚኖር አልፋና ኦሜጋ ከሰማየ ሰማያት መውረዱንና ከእመቤታችን ከቅድስተ ቅዱሳን ከንጽሕተ ንጹሐን ከድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመለክት ሥያሜ ነው፡፡

2. ቅድስት
ይህ የሁለተኛው ሰንበት ስያሜ ሲሆን የተባለበትም ምክንያት ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ስለሚያወሳ ነው፡፡ እንዲሁም ይህ ዕለት ዕለተ እግዚአብሔር የተባለች የሰንበት ክርስቲያን ቅድስናን ያመለክታል ምክንያቱም የዚች ዕለት ጌታ እርሱ ቅዱስ እግዚአብሔር ነውና ስለዚህም ዕለተ ሰንበት ቅድስት ተብላለች፡፡

3. ምኩራብ
ይህ የሦስተኛው ሰንበት ስያሜ ሲሆን በዚህ ሰንበት ጌታ በመዋዕለ ትምህርቱ በምኩራብ ገብቶ ማስተማሩ ይነገራል፡፡ እንዲሁም ይህች ዕለት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ ገብቶ እንዳስተማረ የሚታሰብበት ዕለት ነው፡፡ ምኩራብ ማለት የቤተ አይሁዳውያን የጸሎት ቤት ነው፡፡

4. መጻጉዕ
ይህ የአራተኛው ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ድውያንን መፈወሱ እውራንን ማብራቱ ለምጻምን ማንጻቱ ሽባዎችን መተርተሩ የሚያነሳ መዝሙር የሚዘመርበት እንዲሁም እነዚህ ሁሉ ድንቅ ገቢራተ ታምራቶች የሚዘከሩበት ዕለት ነው፡፡

5. ደብረ ዘይት
ይህ የአምስተኛው ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሆኖ ነገረ ምጽአቱን እንዳስተማረ የሚወሳበት ሰንበት ነው፡፡ ደብረ ዘይት ማለት ወይራ የበዛበት ተራራ ማለት ነው፡፡

6. ገብርኄር
ይህ የስድስተኛው ሳምንት ሰንበት ስያሜ ሲሆን ይህም ዕለት ለጌታው ታማኝና በጎ የሆነው ባርያ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ ተብሎ እንደተመሰገነ የሚነገርበት ዕለት ነው፡፡

7. ኒቆዲሞስ
ይህ የሰባተኛው ሰንበት ስያሜ ነው፡፡ ይህም ዕለት ኒቆዲሞስ የተባለው የአይሁድ መምህር በሌሊት ወደ ጌታው ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ እየመጣ ይማር እንደነበረ ይታሰብበታል በዚም ዕለት የኒቆዲሞስን ታሪክ የሚያስታውስ መዝሙር ይዘመርበታል፡፡

8. ሆሳዕና
ይህ የስምንተኛው ሳምንት ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት በነቢዩ በዘካርያስ ላይ የተጻፈው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ጌታችም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያይቷ እና በውርንጭላይቷ ላይ ተቀምጦ ሆሳዕና በአርያም ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ ተብ እየተመሰገነ ወደ ቤተ መቅደስ መግባቱ የሚተሰብበት ዕለት ነው፡፡ ሆሳዕና ማለት ‹‹እባክህ አሁን አድን አሁን ባርከን›› ማለት ነው፡፡ በሰሙነ ሕማማት ጸሎተ ፍትሃት ጸሎተ አስተስርዮ ስለማይፈጸም ጸሎተ ፍትሃትና አስተስርዮ የሚደረገው በዚሁ ዕለት ነው::

ጾሙን የበረከት ጾም ያድርግልን፡፡

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

"ጾማችን በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት የሚኖረው የተፈናቀሉት ወገኖቻችን ወደ ቀያቸው ተመልሰው ሰላማዊ ኑሮ መኖር ሲችሉ፣ የተራቡት ሲደገፉ፣ ፍትሕ ያጡት ፍትሕ ሲያገኙ ነው፡፡"
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ 2016 ዓ.ም ዐቢይ ጾምን አስመልክተው መልእክት አስተላልፈዋል።

ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት ሙሉ መልእክት እንደሚከተለው ቀርቧል።

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

በሀገር ውስጥና በዓለም ዙሪያ ሁሉ የምትገኙ ምእመናንና ምእመናት ልጆቻችን በሙሉ!

እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ስድስት ዓመተ ምሕረት የጾመ ኢየሱስ ሱባኤ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!

“ወእምዝ ኃደጎ ዲያብሎስ ወናሁ መጽኡ መላእክት ይትለአክዎ፡- ከዚህ በኋላ ዲያብሎስ ትቶት ሄደ፤ እነሆም ያገለግሉት ዘንድ መላእክት መጡ›› (ማቴ ፬፲፩)፡፡

በቀጣዮቹ ሁለት ወራት በከፍተኛ ሃይማኖታዊ ተመሥጦ የምንጾመው ጾም፣ ጾመ ኢየሱስ ተብሎ የሚታወቀው ነው፡፡ ይህ ጾም በጥንት ጊዜ ሰው በኃጢአት የወደቀበትን ምክንያት፣ እንደዚሁም ሰው ኃጢአትንና ዲያብሎስን እንዴት እንደሚያሸንፍ ጌታችን እኛን ያስተማረበት ጾም ነው፡፡

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🤗ጸሎት
የወደቁትን የምታነሣ፣ የአማንያን ተስፋ፣ የዕድሜዬ ባለቤት፣ በጠፊው ዓለም ላይ ያገኘሁህ የማትጠፋው ሀብቴ ፈጣሪ ሆይ አመሰግንሃለሁ፡፡

ያላሰብኩትን መልካም ነገር እንድጀምር፣ የጀመርኩትን እንድፈጽም የምትወተውተኝ አንተ ነህና አመሰግንሃለሁ...ሙሉውን ለማንበብ

ሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​አንተ ሰው እስኪ ንገረኝ!

አንድን የሥጋ ቁስል ለመፈወስ ለእያንዳንዱ ሰው ከባድ ነው፤ የነፍስን ቁስል መፈወስ ግን ለኹሉም ቀላል ነው፡፡ የሥጋ ቁስል ለመፈወስ መድኃኒት ብሎም ገንዘብ ያስፈልጋል፤ ነፍስን ለመፈወስ ግን ቀላል ብሎም ወጪን የማይጠይቅ ነው፡፡ ሥጋን ከዚያ ከሚያሰቃይ ቁስሉ ለመፈወስ አድካሚ ነው፡፡ ምክንያቱም በቀዶ ጥገና ምላጭ መቀደድ አለበት፤ መራራ መድኃኒቶችም ሊጨመሩበት ይገባል፡፡

ነፍስን ለመፈወስ ግን እንዲህ ዓይነት ነገር አያስፈልግም፡፡ ፈቃደኛ መኾን ብቻ በቂ ነው፤ ፍላጎቱ ካለ ኹሉንም ነገር ለማድረግ ቀላል ነው፡፡ የእግዚአብሔር መግቦቱም እስከ አሁን ድረስ ይህ ነው፡፡ ሥጋ ቢቆስል ያን ያህል ከባድ ጉዳትን አያመጣብንም፤ ምክንያቱም ምንም ባንታመምም እንኳን ሞት መጥቶ ይህን ሥጋችን ያፈርሷል፤ ያበሰብሷልምና፡፡ ነፍሳችን ብትታመም ግን ጉዳቱ ብዙ ነው፡፡ እግዚአብሔር የነፍስን ሕመም ለመፈወስ መድኃኒቱ ቀላል፣ ምንም ወጪና ስቃይ የሌለበት ያደረገውም ስለዚሁ ነው፡፡

ታዲያ ምንም እንኳን በሕመሙ ምክንያት የሚያገኘን ጉዳት ያን ያህል ብዙ ባይኾንም የገንዘብ ወጪን የሚጠይቀው፣ ሐኪም የሚያስፈልገው፣ ብዙ ስቃይ ያለበት ሥጋችን ሲታመም እርሱን ለማከም እጅግ የምንደክም ኾነን ሳለ፥ እጅግ ብዙ ጉዳት የሚያመጣውን፣ እርሱን ለመፈወስ ወጪ የማይጠይቀውን ፣ ለማስታመም ሌሎች ሰዎች የማያስቸግረውን፣ እንደ ምላጩና እንደ መራራ መድኃኒቱ ስቃይ የሌለበትን ይልቁንም ከእነዚህ አንዱስ እንኳን ሳይፈልግ በእኛ ኃይል ባሉ ምርጫና ፈቃድ ብቻ መዳን የሚችለውን፣ ይህን ማድረግ ሳንችል ስንቀርም ከባድ ፍርድና ቅጣት ስቃይም እንደሚያገኘን በእርግጥ እያወቅን የነፍሳችንን ቁስል ችላ የምንል ከኾነ ሊደረግልን የሚችል ምሕረት እንደ ምን ያለ ምሕረት ነው? እኮ የምናገኘው ይቅርታ እንደ ምን ያለ ይቅርታ ነው?

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ - በእንተ ሐውልታት መጽሐፍ #በገብረ_እግዚአብሔር_ኪደ

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

🌺 ሰላም፡ለኵልክሙ። እነሆ የምስራች ግእዝን በዐቢይ ጾም በሚል ልዩ ዝግጅት የግእዝ ቋንቋን ኮርስ ለመስጠት ምዝገባ ጀመርን።

📜 እርስዎም ግእዝ ቋንቋን ቀለል ባለና ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅታችንን አጠናቀናል ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመመዝገብ ጥንታዊና ውዱ ቋንቋችንን እናጥና ፥ ዕንወቅ።

📖 ትምህርቱን ከ14 ዓመት ዕድሜ በላይ የሆነ ማንኛውም ሰው ፤  ስልክ፣ ላፕቶፕ ወይም ዴስክቶፕ በመጠቀም መማር ይቻላል።

✅ ምዝገባውን ለማካሄድ በዚህ ውስጥ ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር በመላክ የመማማሪያ ቦታዎችን መቀበል ነው ✅
@Geez202
@Geez202
@Geez202 👈
                

⛳️ ለበለጠ መረጃ በምዝገባው ይደርስዎታል። ጥያቄ ሲኖር ከታች በተቀመጠው በስልክ ያግኙን። ሠናይ፡ጊዜ።

🗣 ለሌሎችም ሼር በማድረግ እንድናዳርስ በአክብሮት እንጠይቃለን
🌺 መሠረተ፡ግእዝ 🌺
@MesereteGeez - 0918026533

Читать полностью…
Подписаться на канал