ortodoxmezmur | Неотсортированное

Telegram-канал ortodoxmezmur - ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

134932

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . ዝማሬ ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Подписаться на канал

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​ነሐሴ 13/12/2016 ዓ.ም
ደብረ ታቦር
✝ በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ።

ዲያቆን፦ ዕብ 11÷23-30
ንፍቅ ዲያቆን፦ 2 ጴጥ 1÷15-ፍ.ም
ንፍቅ ካህን፦ ግብረ ሐዋርያት፦ 7÷44-51

ምስባክ ፦ መዝ 88፥12-14
ታቦር ወአርሞንዔም በስመ ዚአከ ይትፌስሁ ወይሴብሑ ለስምከ
መዝራዕትከ ምስለ ኀይል

ትርጉም
ታቦር እና አርሞንዔም በስምህ ደስ ይላቸዋል
ስምህንም ይመሰግናሉ
ክንድክ ከኃይልክ ጋር ነው

ወንጌል ፦ ሉቃ 9÷28-38
ቅዳሴ ፦ ዘእግዝእትነ

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

#አማን_በአማን

አማን በአማን /2/ ተሰብሐ
አማን በአማን /2/ ተሰብሐ
በደብረ ታቦር /2/

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

#አምላካችን_ናና

አምላካችን ናና በአምደ ደመና
አማኑኤል ናና ብርሀን ነህ እና

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

#ሆያ_ሆዬ
ሆያ ሆዬ በሉ ክርስቲያኖች በሙሉ

እንኳን ለደብረታቦር በዓል በሰላም
አደረሳችሁ አደረሰን

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

#ቡሄ_በሉ

ቡሄ በሉ (2) ልጆች ሁሉ የኛማ ጌታ
የዓለም ፈጣሪ የሰላም አምላክ
ትሁት መሀሪ በደብረ ታቦር የተገለጠው
ፊቱ እንደ ፀሐይ በርቶ የታየው
ልብሱ እንደብርሃን ያንፀባረቀው

ድምጽህን ሰማና በብህሩ ደመና(2)
የቡሄው ብርሃን ለኛ መጣልን(2)

ያዕቆብ ዮሐንስ እንዲሁም ጴጥሮስ
አምላክን አዩት ሙሴ ኤልያስ
አባቱም አለ ልጄን ስሙት
ቃሌ ነውና የወለድኩት

ታቦር አርሞንኤም ብርሃን ታየባቸው
ከቅዱስ ተራራ ስምህ ደስ አላቸው
ሰላም ሰላም የታቦር ተራራ
ብርሀነ መለኮት ባንቺ ላይ አበራ

በተዋህዶ ወልድ የከበረው
የእግዚአብሔር አብ ልጅ
ወልደማርያም ነው
ቡሄ በሉ/2/ የአዳም ልጆች
ብርሃንን ተቀበሉ

አባቴ ቤት አለኝ ለከት
እናቴ ቤት አለኝ ለከት
አጎቴም ቤት አለኝ ለከት
ተከምሯል እንደ ኩበት

የዓመት ልምዳችን ከጥንት የመጣው
ከተከመረው ከመሶቡ ይውጣ
ከደብረ ታቦር ጌታ ሰለመጣ
የተጋገረው ሙልሙሉ ይምጣ

ኢትዮጵያውያን ታሪክ ያላችሁ
ባህላችሁን ያዙ አጥብቃችሁ
ችቦውን አብሩት እንዳባቶቻችሁ
ምስጢር ስላለው ደስ ይበላችሁ

አባቶቻችን ያወረሱን
የቡሄን ትርጉም ያሳወቁን
እንድንጠብቀው ለእኛ የሰጡን
ይህን ነውና ያስረከቡን

ለድንግል ማርያም አሥራት የሆንሽ
ቅዱሳን ጻድቃን የሞሉብሽ
በረከታቸው ያደረብሽ
ሁሌም እንግዶች የሚያርፉብሽ
ሀገረ እግዚአብሔር ኢትዮጵያ ነሽ

ለሐዋርያት የላከ መንፈስ
ዛሬም ለኢትዮጵያ ጸጋውን ያፍስስ
በበጎ ምግባር እንድንታነጽ
በቅን ልቦና በጥሩ መንፈስ
በረከተ ቡሄ ለሁላችን ይድረስ

ዓመት ዓውዳመት ድገም እና ዓመት ድገም እና
በጋሽዬ ቤ ድገም እና ዓመት ድገም እና
ያውርድ በረከት ድገም እና ዓመት ድገም እና
ወርቅ ይፍሰስበት ድገም እና ዓመት ድገም እና

በእማምዬ ቤት ድገም እና ዓመት ድገም እና
ይግባ በረከት ድገም እና ዓመት ድገም እና
ማርና ወተት ድገም እና ዓመት ድገም እና
ይትረፍረፍ በእውነት ድገም እና ዓመት ድገም እና


እንዲሁ እንዳላችሁ በፍቅር አይለያችሁ
ላመቱ በሰላም በፍቅር ያድርሳችሁ
ክርስቶስ በቀኙ በፍቅር ያቁማችሁ
የመንግስቱ ወራሽ በፍቅር ያድርጋችሁ
እንዲሁ እንዳለን በፍቅር አይለየን
ለዓመቱ በሰላም በፍቅር ያድርሰን
አማኑኤል በቀኙ በፍቅር ያቁመን
የመንግስቱ ወራሽ በፍቅር ያድርገን


የቅዱሳን መላክት የፃድቃን ሰማዕታት
ረድኤት በረከት ይግባ በሁሉም ቤት
በሁሉም ቤት(2) ይግባ በረከት(2)

እንቁም በሃይማኖት ፀንተን በትጋት
የአስራት አገር የአበው ቀደምት
የቅዱሳን አባቶች ትውፊት
ይገባልና ልንጠብቅ በእውነት
ባህላችንን የአባቶች ትውፊት (3)

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ኧረ ምን ዘመን ደረስን 😭😭😭

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​ነሐሴ 12/12/2016 ዓ.ም

✝ በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ።

ዲያቆን፦ 1 ቆሮ 9÷17-ፍ.ም
ንፍቅ ዲያቆን፦ ይሁዳ 1÷8-14
ንፍቅ ካህን፦ ግብረ ሐዋ፦ 24÷1-22

#ምስባክ ፦ መዝ 71፥1-3
እግዚኦ ኩነኔከ ሀቦ ለንጉስ
ወጽድቀከኒ ለወልደ ንጉሥ
ከመ ይኮንኖሙ ለሕዝብከ በጽድቅ

#ትርጉም ፦
አቤቱ ፍርድህን ለንጉስ ስጥ
ጽድቅክንም ለንጉስ ልጅ
ሕዝብክን በጽድቅ ችግረኛዎችክንም
በፍርድ ይዳኝ ዘንድ

#ወንጌል ፦ ማቴ 22÷1-15
#ቅዳሴ ፦ ዘእግዝእትነ

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

👉 የአርብ ውዳሴ ማርያም አንድምታ
🎙 ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​ሕልመ ሌሊት በራሱ ኃጢአት ነውን?

ወዳጆቼ ሕልመ ሌሊት በራሱ ኃጢአት አይደለም፡፡ ግን ኃጢአት የሚሆንበት ሂደት አለው፡፡ አንድ ሰው በሕልሙ ሕልመ ሌሊት ቢመታው በዚህም ከሰውነቱ አባለ ዘር ይፈሳል፡፡ የአባለ ዘር መፍሰስ ኃጢአት የሚሆነው በራስ ፍቃድ ሲሆን ነው፡፡ ለምሳሌ ወዶ እና ፈቅዶ ግለ ወሲብ ሲፈጽም፣ የወሲብ ፊልም በማየት ከሚመጣ የሰውነት ሙቀት ጋር ዘር ሲፈስ፣ ከተቃራኒ ጾና ጋር በሚደረግ አልባል ንክኪና መሳሳም ነው፡፡

ሕልመ ሌሊት እላፊ በልቶ እና ጠጥቶ ከሚመጣ የሥጋ ፈተና ከሆነ ኃጢአት ይሆንበታል፡፡ ቅድስናን የሚያጎድል በመሆኑ የኃጢአተኝነት ስሜት እንዲጫነን ያደርገናል፡፡ ግን አንድ ሰውን ሕልመ ሌሊት ቢመታው ኃጢአት የሚሆንበት ሂደት አለ፡፡ ይህም አንድን ሰው ሕልመ ሌሊት ሲመታው ማለትም አጋንንቱ በሚያውቃት ሴት ተመስሎ በተኛበት ተገናኝቶት ዘሩን ቢያስፈስሰው የዚህ ችግር ሰለባ የሆነው ሰው በተፈጠረው ነገር ለምሳሌ ሴቷን እያሰበ፣ በሕልሙ ያየውን እያሰበ የሚደሰት፣ በሕልሙ የተፈጠረውን ግንኙነት በምልሰት እያየ ደስታን ካጣጣመ ኃጢአት ነው፡፡

ምክንያቱም ይሁዳ በመልእክቱ ‹‹እያለሙ ሥጋቸውን ያስደስታሉ›› ብሏልና፡፡ /ይሁ 1÷8/ በሕልማችን የተፈጠረውን ሕልመ ሌሊት በምልሰት በማየት እና በማሰብ መደሰት ሳይሆን መጸጸት መቆጨት ካልተሰማን ኃጢአት ነው የሚሆንብን፡፡

ወዳጆቼ የአጋንንት የረከሰ ሐሳብ በሕልማችን እየተከሰተ ሕልመ ሌሊት ሲያጋጥመን የተፈጠረውን ክስተት በጸጸት አጋንንቱን ልናሳፍረው ይገባል እንጂ የሆነውን እንደ በጎ ነገር ልንቀበለው አይገባም፡፡ ይህ እሳቤያችን ከፈጣሪ መለኮታዊ እርዳታ እንድናገኝ ይረዳናል፡፡ የማንቆጭ፣የማንጸጸት ከሆነ የዝንየት አጋንንት ይለምድና የሌሊት ደንበኛው ያደርገናል፡፡

እዚህ ላይ አንድ መረሳት የሌለበት ነገር አለ፡፡ አንዳንዴ ሕልመ ሌሊት (ዝንየት) በሰይጣን ፈተና ብቻ ላይከሰት ይችላል፡፡ ምናልባት ከምንጠቀማቸው ምግብና መጠጥ እንዲሁም ከሥጋ ባህርያችን ሊከሰት ይችላል፡፡ ምክንያቱም ሰውነታችን ሲስማማው በራሱ ጊዜ ፈሳሽ ሊወጣ ይችላል፡፡

ይህ ደግሞ ተፈጥሮ ነው፤ ምንም ማድረግ አይቻልም በጸጋ መቀበል ነው፡፡ ለምሳሌ ማታ ትኩስ ነገር ሙቅ፣ ሻይ አብዝተን የምንጠጣ ከሆነ በዘር ከረጢጣችን ያለው አባለ ዘር በራሱ ጊዜ ሊፈስ ይችላል፡፡

ተወዳጆች ሆይ በተአምረ ማርያም ላይ እንደሰማችሁት በሕልመ ሌሊት የተፈተነው ወጣት መነኩሴ ሕልመ ሌሊት ሳይሆን በሥጋው ምክንያት ሞት የመጣበት ስለመሰለው ‹‹የፍትወትን ጣዕም ዛሬ ቀምሰሻልና ወዮልሽ›› በማለት አምርሮ እራሱን ጠልቶ ወደ እመቤታችን አንብቶ ቢማጸናት እመቤታችን ተገልጣ ፈተናውን አርቃለት፣ በእጆችዋም ምልክት አድርጋለት ከሕልመ ሌሊት ተላቆ በሰጠችው ሐብተ ፈውስ ብዙ ድንቆችን አድርጎ ነበር፡፡

እኛም ወለላይቱ እመ ብርሃን በሕልመ ሌሊት የሚፈትነንን አጋንንት በጸሎቷ እንድታስርልን፣ እንድታርቅልን ከተማጸናት በእውነትም ይህን ፈተና፣ይህን መናጢ ታርቅልናለች፡፡

በቀጣይ 👉 ሕልመ ሌሊት በምን ይከሰታል?

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​ነሐሴ 9/12/2016 ዓ.ም
 
✝ በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ።

ዲያቆን፦ ፊል 1÷12-24
ንፍቅ ደያቆን፦2 ዮሐ 1፥6-ፍ.ም
ንፍቅ ካህን፦ ግብረ ሐዋርያት፦ 15÷19-ፍ.ም
   
#የዕለቱ ምስባክ፦ መዝ 44 ÷ 10
ወትቀውም ንግስት በየማንከ።
በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወሁብርት።
ስምኢ ወለትየ ወርእዩ- ወአጽምኢ እዝነኪ።
                         
ወንጌል ፦ ዮሐ 10÷1-12
ቅዳሴ ፦ ዘእግዝእትነ(የእመቤታችን ቅዳሴ)

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​👉 በሱባኤ ወቅት ህልመ ሌሊት (ዝንየት) ቢመታን ምን እናደርጋለን?
👉 ሕልመ ሌሊት በራሱ ኃጢአት ነውን?
👉 ሕልመ ሌሊት በምን ይከሰታል?
👉 ከዝሙት አጋንንት እና ከዝንየት በተጨማሪ በሕልመ ሌሊት የሚፈትነን አጋንንት የትኛው ነው?
👉 የሕልመ ሌሊት መፍትሔ ምንድን ነው?


ተወዳጆች ሆይ መቼም ሱባኤ አይደል! በድካም ውስጥ ሆኜ ስለጻፍኩ የሐሳብ መደጋገም ካለ እያረማችሁ አንብቡት፡፡ በዚህ በሱባኤ የአጋንንት ውጊያ የሚበረታበት፣ ሕልመ ሌሊት ደግሞ በተደጋጋሚ የሚከሰትበት ነው፡፡ የበጎ ነገር ጠላት አጋንንት እኛን ከመንፈሳዊ አገልግሎት እና ተገልጎሎት ለማሰናከል እኛ ላይ ዓይኑን ፈጠጥ፣ ጥርሱን ገጠጥ የሚያደርግበት ጊዜ በአጽዋማት ወቅት ነው፡፡

ሕልመ ሌሊት (ዝንየት) የሚባለው አንድ ሰው ተኝቶ በሕልሙ ወንድን በሴት፣ ሴትን በወንድ አምሳል እንደ ገሐዱ በሚመስል ሩካቤ ሥጋ የሚታየንና ከሰውነታችን ፈሳሽ የሚወጣበት ሂደት ነው፡፡ ዝንየት የሚባለው ደግሞ በሕልመ ሌሊት የሚፈታተነን አጋንንት ነው፡፡ ሕልመ ሌሊት (ዝንየት) ወንድና ሴት ሳይል በማንኛውም ሰው ላይ በተለያየ ምክንያት ሊከሰት ይችላል፡፡

በሱባኤ ጊዜ ሕልመ ሌሊት ከመታን እለቱን ቤተ-ክርስትያን በተለይም ቤተ-መቅደስ መግባት፣ ቅዱስ ቁርባን መቀበል፣ ጸበል መጠመቅና መጠጣት፣ አንችልም፡፡ በማግስቱ ግን ሰውነታችንን ታጥበን፣ልብሳችንን ቀይረን ቤተ-ክርስትያን መግባት፣ ቅዱስ ቁርባን መቀበል፣ ጸበል መጠመቅና መጠጣት እንችላለ፡፡

እንደዚህ የምናደርገው አንደኛ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትእዛዝ ስለሆነ ነው፡፡ ሁለተኛ ቅድስት ለሆነችው እናት ቤተ-ክርስትያን ክብር ከመስጠት አንጻር ነው፡፡ እግዚአብሔር ሙሴንና አሮንን በዘሌዋውያን ምዕራፍ 15÷2 ላይ ‹‹ማንም ሰው ከሥጋው ፈሳሽ ነገር ቢወጣ፣ስለሚወጣው ነገር ርኩስ ነው›› ይልና እዛው ቁጥር 16 ላይ ‹‹ማንም ሰው ዘር ከእርሱ ቢወጣ፣ገላውን ሁሉ በውኃ ይታጠባል፣እስከ ማታም ድረስ ርኩስ ነው›› ይላል፡፡ /ዘሌ 15÷16/

ተወዳጆች ሆይ ልብ በሉ ‹‹ማንም ሰው›› ነው እንጂ ወንድ ሴት፣ወጣት አዛውንት አይልም፡፡ ይህ የሚያሳየው ኦርቶዶክስ የሆነ በየትኛው ጾታ እና የእድሜ ክልል ያለ ሁሉ ሕልመ ሌሊት ከመታው እለቱን ሳይሆን ማግስቱን ነው ቤተ-ክርስትያን መግባት የሚችለው፡፡ ‹‹እስከ ማታ›› የሚለው ሕልመ ሌሊት ሲመታን ለአንድ ቀን ብቻ የተከለከልን መሆናችን ያስረዳል፡፡ መቼም ሕልመ ሌሊት የሚመታን ማታ ወይም ሌሊት ነው፡፡ ስለዚህ አንድ ሰው ማታ ወይም ሌሊት ሕልመ ሌሊት ከመታው ቀኑን ውሎ እስከ ማታ ነው የሚረክሰው፡፡ ከማታ በኃላ ንፁህ ይሆናል፡፡

ወዳጆቼ አንዳንዶች ‹‹ሕልመ ሌሊት ከተመታችሁ እስከ ሦስት ቀን ቤተ-ክርስትያን መግባት አይቻልም›› ይላሉ፡፡ ይህንም ‹‹ማነው ያለው›› ስትሉ የፈረደባቸው ‹‹አባቶች›› ናቸው ይላሉ፡፡ ቅዱስ መጽሐፍም አባቶቻችንም የሚነግሩን እስከ ሦስት ቀን ድረስ ቤተ-ክርስትያን የማንገበው ሩካቤ ሥጋ ስንፈጽም ብቻ ነው፡፡

ሕልመ ሌሊት መታን ማለት በቤት እና በቅጽረ ቤተ-ክርስትያን ሆኖ መጸለይ አይቻልም ማለት አይደለም፡፡ በሱባኤም ሆነን ሕልመ ሌሊት ቢመታን ሰውነታችን ታጥበት ሱባኤው መቀጠል እንጂ ማፍረስ የለብንም፡፡

በቀጣይ👉 ሕልመ ሌሊት በራሱ ኃጢአት ነውን?
ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

👉 የማክሰኞ ውዳሴ ማርያም አንድምታ
🎙 ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​#ነሃሴ_7
#ቅዱስ_ጴጥሮስ_ሊቀ_ሐዋርያት

ዳግመኛ ይህች ዕለት የቅዱስ ጴጥሮስ መታሰቢያ ናት። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ስብከቱ በዚህች ቀን ደቀ መዛሙርቱን ወደ ቂሣርያ ፊልጶስ ይዟቸው ሔደ። በዚያም ጌታ ከእነሱ ራቅ ብሎ ተቀምጦ ነበርና የማይሰማቸው መስሏቸው እርስ በእርስ ይከራከሩ ገቡ።

የክርክራቸው መነሻ ደግሞ ጌታችን ነበር። የዋሃን (ገና ምሥጢርን ያልተረዱ) ነበሩና አንዱ ተነስቶ "ኤልያስ ነው": ሌላኛው "ሙሴ": ሦስተኛው "ኤርምያስ ነው" በሚል ተከራከሩ። ቅዱስ ጴጥሮስ ለብቻው ቆሞ ነበርና ጠርተው "ሃሳባችንን አስታርቅልን። ለአንተስ ማን ይመስልሃል?" አሉት።

አረጋዊው ሐዋርያም ተቆጣቸው። "እናንተ እንደምታስቡት እርሱ ከነቢያት አንዱ ሳይሆን "እግዚአ ነቢያት-የነቢያት ፈጣሪ ነው" አላቸው። ወዲያውም ጌታ ጠርቷቸው ወደ እርሱ ቀረቡ።

ቸር አምላክ "ለምን ተጠራጠራችሁኝ" ብሎ መገሰጽ ሲችል እንዳይደነግጡ ጥያቄውን በፈሊጥ አደረገ። "የሰውን ልጅ ሰዎች ማን ይሉታል?" አላቸው። እነርሱም በልባቸው ያለውን የሌላ አስመስለው ተናገሩ።

ጌታችን "እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ?" ቢላቸው ጸጥ አሉ። ገና ሃይማኖታቸው አልጸናም ነበርና። በዚያን ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስ ተነስቶ "አንተ ውእቱ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው-አንተ የሕያው እግዚአብሔር የባሕርይ ልጁ ክርስቶስ ነህ" አለው። (ማቴ. 16:16)

ይህች ቃል የክርስትና ሃይማኖት መሠረት ናትና ጌታችን "አንተ ዓለት (መሠረት) ነህ" ብሎ የቤተ ክርስቲያንን በዚህ እምነት ላይ መመስረት ተናገረ። ለቅዱስ ጴጥሮስም "መራሑተ መንግስት-የመንግስተ ሰማያት መክፈቻ ቁልፍ (ሥልጣን)" ተሰጠው።

ሊቀ ሐዋርያትነትንም ደረበ። ዛሬ ለበርካቶቹ የጸነነባቸው ይሔው እምነት ነው። ኢየሱስ ክርስቶስን "አምላክ ወልደ አምላክ: ወልደ ማርያም: አካላዊ ቃል: ሥግው ቃል: ገባሬ ኩሉ: የሁሉ ፈጣሪ" ብለው ካላመኑ እንኳን ጽድቅ ክርስትናም የለም።

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​ነሃሴ_7
እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የጽንሰት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ቁጽረታ (ጽንሰታ)ለማርያም

ይህችን ዕለት አበው ሊቃውንት "ጥንተ መድኃኒት፤ የድኅነት መነሻ ቀን" ሲሉ ይጠሯታል።

ስለ
ምን ነው_ቢሉ :- ለዓለም ድኅነት ምክንያት የሆነች የአምላክ እናቱ የተጸነሰችበት ዕለት በመሆኑ ነው። አንድም ከአዳም ስሕተት በኋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተጸነሰች የመጀመሪያ ሰው እርሷ ናትና እንዲህ ይላሉ።

"ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ እማኅጸን ቅዱስ።" - "ድንግል ሆይ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው: የተወለድሽበት ማኅጸንም ቅዱስ ነው።"
(መጽሐፈ ሰዓታት, ኢሳ. 1:9, መኃ. 4)

ይሕች ዕለት ለኢያቄምና ለሐና ብቻ ሳይሆን ለፍጥረት ሁሉ የተስፋ ድኅነት ቀን ናትና ሐሴትን ልናደርግ ይገባል።

የእመቤታችን መጸነስስ እንደ ምን ነው ቢሉ :- ከነገደ ይሁዳ የሚወለድ ቅዱስ ኢያቄም የሚባል ደግ ሰው ከነገደ ሌዊ(አሮን) የተወለደች ሐና የምትባል ደግ ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ ነበር። ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች "ልጅ የላችሁም" በሚል ይናቁ ነበር።

ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን "ኅጡአ በረከት-ከጸጋ እግዚአብሔር የራቀ" ነው ብለው ያምኑ ነበር። ኢያቄምና ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ አረጁ። እነሱ ግን የሚያመልኩት የአብርሃምና ሣራን አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም።

የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን አደረገላቸው። አንድ ቀን ርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲጫወቱ የተመለከተች ቅድስት ሐና ፈጽማ አለቀሰች። "እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?" ብላ አዘነች።

ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ ያዘ። ለአርባ ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ። በአርባኛው ቀን ሁለቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- ነጭ ርግብ ሰማያትን ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጆሮ ገብታ: በማኅጸኗ ስትደርስ አየ።

እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች። ቅዱስ ኢያቄም ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው "ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን" አሉ:: ለሰባት ቀናትም በጋራ እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ።

በሰባተኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7) መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ እነርሱ ወረደ:: "ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ" ብሏቸው ተሠወራቸው። እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ።

እንደ ሥርዓቱም በዚህች ቀን አብረው አድረው እመ ብርሃን ተጸነሰች።
"ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ" - "ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ አይደለም" እንዳለ ሊቁ። (ቅዳሴ ማርያም)

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

👉 ለሱባዔ እንቅፋት ንስሐ አለመግባት!
👉 እውን እመቤታችን በራዕይ ትታያለች?
👉 ሱባኤ እና ሕልም ምን ይመስላሉ?
🎤 በቀሲስ ሔኖክ ወ/ማርያም
#የመጨረሻው_ክፍል

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​​​#ቡሄ

ቡሄ ማለት ብራ፣ ብርሃን፣ ደማቅ ማለት ነው፡፡ ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት በዓል የሚዘከርበት እና ለበዓሉም ችቦ ስለሚበራ የብርሃን በዓል በማለት የቡሄ በዓል እንላለን፡፡ ወቅቱ የክረምት ፤ጨለማ አልፎ የብርሃን የሚወጣበት፤ ሰማይ ከጭጋጋማነት ወደ ብሩህነት የሚለወጥበት የመሸጋገሪያ ወቅት ነው፡፡ “ቡሄ ከዋለ የለም ክረምት፤ ዶሮ ከጮኸ የለም ሌሊት” እንዲሉ፡፡ በሌላ በኩልም “ቡኮ/ሊጥ” ተቦክቶ ዳቦ የሚጋገርበት “#ሙልሙል” የሚታደልበት በዓል በመሆኑ ቡሄ ተብሏል፡፡

#ጅራፍ

በደብረ ታቦር በዓል በትውፊታዊ መልኩ የሚታየው ምስጢር፤ በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው የጌታችን ምስጢራዊ ሞቱ ነው፡፡ ጅራፍ መገመድ(መጥለፍ) እና ጅራፍ ማጮኽ ሁለት ዓይነት ምስጢር የያዘ ትውፊታዊ ተግባር ነው፡፡

የመጀመሪያው ግርፋቱንና ሞቱን እናስብበታለን፡፡ ሁለተኛው ደግሞ ፤ድምፁን ስንሰማ የባሕርይ አባቱን የአብን ምስክርነት ቃል፤ እንደ ነጎድጓድ ድምፅ ያስታውሰናል፡፡

የጅራፍ ትውፊታዊነት /ውርስ/፣ መጽሐፋዊ ትምህርትና ምስጢር ጠብቆ ለትውልድ እንዲተላለፍ ለማድረግ ጨዋታውን በተራራማ አካባቢ፣ ከመኖሪያ ቤት ርቆና፣ በሜዳ ማድረጉ ጠቃሚ ነው፡፡ ጅራፍን #በርችት መቀየር የሚያመጣውን የምስጢር ተፋልሶ ብቻ መመልከት ከማኅበራዊ ጎጂ ገጽታው በላይ እንድናስወግደው ያስገድደናል፡፡

#ችቦ

ችቦ የጌታችንን ብርሃነ መለኮት መገለጥ የሚያመለክት ነው፡፡ በመሆኑም ችቦ ለኩሰን በዓሉን እናከብራለን፡፡ የዚህ ትውፊታዊ አመጣጥ በብርሃኑ ድምቀት የቀኑን መምሸት ያልተረዱ እረኞች በሜዳ ቀርተዋልና ወላጆች ከመንደር ችቦ ለኩሰው ልጆቻቸውን ፍለጋ ሔደዋልና ታሪኩን እያዘከርን በዓሉት እናከብራለን፡፡

የችቦው መንደድም ሌላ ትርጉም አለው፡፡ አንድ ምእመን ለሌላው ምእመን መካሪ አስተማሪ መሆኑን፣ መከራ እየተቀበለም አርአያ፣ ምሳሌ፣ ብርሃን መሆኑን ያሳያል፡፡ በሃይማኖትም አርአያ ምሳሌ ይሆንላቸዋል፡፡ ከዚህ ጋርም ተያይዘዞ ችቦ በ13 ምሽት ይበራል ፣ብርሃኑ የተገለጠው በዚችው ዕለት ነውና ፡፡

#ሙልሙል

በችቦ ብርሃን ልጆቻቸውን ፍለጋ የወጡ ወላጆች ዳቦ ጋግረው ይዘውላቸው ወጥተዋል፡፡ ስጦታው ቤተሰባዊነትን፣ ፍቅርንና መተሳሰብን መግለጫ ነው፡፡ ወደ ቤታችን “ ቡሄ ” እያሉ ለሚመጡ አዳጊዎችም፤ ዘምረው እንዳበቁ የሚሰጥ “ሙልሙል” ዳቦ አለ፡፡ ሕፃናቱም ሊዘምሩ ሲመጡ ዳቦ መስጠት ልማዳዊ ብቻ አይደለም፡፡

ሕፃናቱ የደቀመዛሙርት ምሳሌ ናቸው፡፡ መዝሙራቸው ደግሞ ሐዋርያት “የምሥራች” ይዘው የመምጣታቸው ምሳሌ ነው፡፡ ሐዋርያት በገቡበት አገር አስተምረው አጥምቀው የጸጋ ልጅነትን አሰጥተው በረከት አድለው እንደሚሔዱም፣ ልጆችም ዘምረው፣ አመስግነው፣ መርቀው “ውለዱ ክበዱ፣ ሀብት አግኙ፣ የመንግሥተ ሰማያት ወራሾች ያድርጋችሁ ….” ይላሉ፡፡

በአጠቃላይ በዓለ ደብረ ታቦር ከእነዚህ ምስክር ካላቸው ትምህርቶቹ፣ ምሥጢር ከሚራቀቅባቸው ትርጓሜያቱና ከትውልድ ትውልድ በቅብብል በተላለፈው ቅዱስ ትውፊት ጋር ሃይማኖታዊ ባሕል ሆኖ ሊቀጥል ይገባዋል፡፡

ይህን ማድረግ የሚቻለው ግን አዳጊዎች ሃይማኖታዊ ትውፊቱን ይዘው እንዲያድጉ ጥቆማ በመስጠት፣ ግጥም በመግጠምና ምሥጢሩን በማብራራት የመጀመሪያዎቹ ባለድርሻዎች ወላጆች ናቸው፡፡

አንዳንድ ጊዜ የሚሰሙ ግጥሞች ስድብ፣ ፌዝና ሥላቅ የተቀላቀለባቸው ይሆናሉ፡፡ ሕፃናቱም ዝማሬውን ሲጀምሩ “ከሰጡን እንነሣ ከነሱን እናርዳ” ብለው ይጀምሩታል፡፡ ከሰጡን እንመርቃለን ካልሰጡን እንራገማለን በማለት፡፡

አሳሳቢው ነገር ደግሞ ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን ወደ ገንዘብ ማግኛነት የቀየሩ ሁኔታዎች መታየታቸው ነው፡፡ ዳቦ /ሙልሙል/ ትምህርቱንም፣ ምስጢሩንም፣ ትውፊቱንም በአግባቡ ልንጠቀምበት ይገባል።

ከዚም ጋር ተያይዞ ሰንበት ት/ት ቤታችን ለበረካታ ዓመታት ሲወርድ የመጣውን የዝማሬ ሥርዓት ለአጥብያው ምእምን በየቤቱ በመሄድ የብሄን ዝማሬ ከነሥርዓቱ በመዘመር አገልግሎት ይሰጣል ፤የደብር ታቦርን በዓል በተመለከትም የወረቀት ጽሑፎችን ይበትናል በዝማሬ መኃል ያድላል፡፡

ቤተክርስቲያን የምሥጢር ግምጃ ቤት ናት፤ የምታከናውነውን ሁሉ ከበቂ መረጃ ጋር ነው ተግባራዊ የምታደርገው፡፡ በተለይ ወጣቱ ክፍል ይህንን አውቀን ተረድተን ለቀሪው ትውልድ ማስተላለፋ እንችል ዘንድ ከክፉ ጠላት ከሰይጣን ፈተና፣ በሽታ ከመሳሰሉት ችግሮች ለመዳን ወደ ተራራዋ ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመሸሽ ከክፉ ነገሮች ሁሉ ማምለጥ ይቻላል፡፡

በቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር የሚጠለሉ ሁሉ ዕድሜያቸው ይረዝማል፡፡ አስተዋዮችም ይሆናሉ ሁሉን ማየትና የሚጠቅማቸውን መምረጥ ይችላሉ በሥነ-ምግባር የታነፁ አገርንና ወገንን የሚጠቅሙ ወደ ቅድስት ቤተክርስቲያን በመጠጋት ከክፉ ሁሉ የሚያመልጡ ይሆናሉ ለዚህም የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ይርዳን፡፡

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

#በስመ_ዚአከ

በስመ ዚአከ ይትፌሥሑ ዮም /2/
ታቦር ወአርሞንዔም /2/

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

#ሃሌ_ሉያ

ሃሌ ሉያ አንተ ሰው ሆይ
ቡሄ መድረሱን ሰምተሀል ወይ

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

#ቡሄ_በሉ

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

👉 የቅዳሜ ውዳሴ ማርያም አንድምታ
🎙 ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​ሕልመ ሌሊት በምን ይከሰታል

2ኛ/ የዝሙት መንፈስ ካለብን

ተወዳጆች ሆይ የዝሙት አጋንንት ያው አጋንንት ቢሆንም ከሌሎቹ አጋንንት የሚለው በተልዕኮው ነው፡፡ የዝሙት አጋንንት ሰዎችን በዝሙት ማጥመድና መጣል፣ከቅድስና ሕይወት ሰዎችን ማግለል ነው፡፡ የዝሙት መንፈስ ካለብን ይበልጥ ሕልመ ሌሊት (ዝንየት) ሊፈትነን ይችላል፡፡

የዝሙት መንፈስ ማለት በልቦናችንና በአእምሮአችን ዝሙትን በማሰብና ሲከፋም ወደ መፈጸም የሚያደርሰንና ከፈጣሪ የሚያጣላን እርኩስ መንፈስ ነው፡፡ የዝሙት መንፈስ በተለይ ባላገቡ ወጣቶች ላይ ይጸናል፡፡ አሁን አሁን ግን ያገቡትም የዚህ መንፈስ ተጠቂ እየሆኑ ነው፡፡

ወዳጆቼ ወጣቱ በዝሙት መንፈስ በተለያየ መንገድ ሊጠቃ ይችላል፡፡ አንዱ ተፈጥሮአችንን በመጠቀም ነው፡፡ ይህ ማለት ወደ እሳትነት ዕድሜ ክልል በምንገባበት ጊዜ የሥጋ ባህሪያችንን በመጠቀም የዝሙት መንፈስ ሊጠናወተን ይችላል፡፡

ይህም የሚሆነው ወንዶች ዓይናችን ወደ ሴቶች፣ ሴቶችም አይናችን ወደ ወንዶች ማማተር፣ በልዩ ፈቃድ መመኘትና ልባችንም ፈቃደ ሥጋን ለመፈጸም በሚከጅልበት ሰዓት ውሻ በቀደደው አንዲሉ የዝሙት መንፈስ ወደ ውስጣችን ይገባል፡፡

በዚህ መልኩ ውስጣችን ገብቶ ለዓመታት ከተቀመጠ በኋላ በተደጋጋሚ ቤተ-ክርስትያን ለመሄድ በተዘጋጀንበት ጊዜና በሱባኤ ላይ ፈተናውን በግልፅ ይጀምራል፡፡ ሳናውቅ በድብቅ ገየባው የዝሙት መንፈስ በግልጽ ይፈትነናል፡፡

ሌላው በዓለማዊ ሕይወት በምንኖርበት ጊዜ የተለያዩ ዝሙት ተስቃሽ ፊልሞችን በምንመለከትበትና መጽሐፍቶችን በምናነብበት ጊዜ መንፈሱ ሳናውቀው ወደ ውስጣችን ይገባና፤ በኋላ ሁሉን ትተን በመንፈሳዊነት ወደ ቤተ-ክርስትያን መገስገስ ስንጀምር በሕልመ ሌሊት (በዝንየት) በመፈተን ከቤተ-ክርስትያን ያስቀረናል፣ በፈተናም ያስመርረናል፡፡

ውድ አንባቢያን ፊልም ማየትና መጽሐፍት ማንበብ ኃጢኃት ባይሆንም የምናየውን ፊልምና የምናነበውን መጽሐፍ መምረጥ ይገባል፡፡ ጸያፍ እና ሥጋና ነፍስን የሚያሳድፍ ፊልም/ቨዲዮ/ ከሆነ ድብን ያለ ኃጢአት ነው፡፡

3ኛ/ ስንታበይ
ይቀጥላል

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​​ሕልመ ሌሊት በምን ይከሰታል?

ተወዳጆች ሆይ ሕልመ ሌሊት ከሚከሰትብን ምክንያቶች ዋና ዋናዎችን ከዚህ በታች እናያለን፡፡

1ኛ/ በአጋንንት ይከሰታል

በጣም የሚገርመው በሕልመ ሌሊት (ዝንየት) የተፈተናችሁ እስቲ ልብ በሉ፡፡ ወደ መንፈሳዊ ሕይወት ውስጥ ሳትገቡ በዓለም ሳላችሁ ብዙም አይከሰትም፡፡ ቢከሰትም ለአቅመ-አዳምና ለአቅመ ሔዋን በደረስንበት ወቅት በሥጋ ባህሪያችን ይከሰታል፡፡ ወደ መንፈሳዊ ሕይወት ውስጥ ገብተን በተግባር መኖር ስንጀምር ሕልመ ሌሊት (ዝንየት) በተደጋጋሚ ይመታናል፡፡ በተለይ ወንዶችን ቋሚ ደንበኞች ያደርገናል፡፡

ወዳጆቼ አጋንንት ጸበል እንዳንጠመቅ፣ ቤተ ክርስትያን ገብተን ጸሎት እንዳናደርስ፣ ከመለኮታዊው ማዕድ እንዳንቋደስ /ቅዱስ ቁርባን እንዳንቀበል/ ከሱባኤ ዋሻ ለማስወጣት ከሚጠቀምበት ዋንኛ ማሰናከያ መፈተኛው ሕልመ ሌሊት (ዝንየት) ነው፡፡ አባቶቻችን ‹‹ተጻቦዖ›› ይሉታል ‹‹ተጻብዖ›› ማለት ቃሉ የግዕዝ ሲሆን መጣላትን ያመለክታል፡፡

እኛ ሀገር ሰላም ብለን በተኛንበት ሰይጣን በማናየው መልኩ በሕልመ ሌሊት ስለሚጣባንና እኛ የማንፈልገውን ፈቃደ ሥጋ በማሳየት ፈትኖን ከሰውነታችን ፈሳሽ እንዲወጣ ስለሚያደርግ ‹‹ተጻብዖ›› ብለውታል፡፡ በእውነት ከዚህ በላይ ምን ጸብ አለ? ሰው የማይገላግለን፣ሰው የማይደርስልን ፣ጮኸን የማናመልጠው ጠብ፡፡

ተወዳጆች ሆይ በሱባኤ ላይ ሆነን አጋንንት በሕልመ ሌሊት ቢፈትነን ሱባኤያችን አይፋረስም፡፡ ሕልመ ሌሊት ስለመታን ሱባኤያችን አይቋረጥም፡፡ ምናልባት በዋሻ ውስጥ ሱባኤውን የያዝን ከሆንን ለአንድ ቀን ከደጅ እንሆናለን አልያም ሰውነታችንን ታጥበን ተመልሰን ልንገባ እንችላለን፡፡ ይህን የሚወስነው የገዳሙ የአባቶች ሥርዓት ነው፡፡

ስለዚህ በሱባኤ ጊዜ በሕልመ ሌሊት በተደጋጋሚ ብንፈተን ሊደንቀን አይገባም፡፡ ይልቁንም ከአጋንንቱ ጋር በስውርና በገሃድ እየተዋጋን ስለሆነ ደስ ሊለንና በጸሎት ልንዋጋው ይገባል፡፡

ሰይጣን ሕልመ ሌሊትን (ዝንየትን) ለጸሎት ማስታጎያነት ይጠቀምበታል፡፡ ሌሊት ጸሎት ካስለመድን ከመነሳታችን በፊት ሕልመ ሌሊት ይመታናል፡፡ ከዛ በኋላ ተነስተን መጸለይ ይከብደናል፡፡ ከሰውነታችን ፈሳሽ ስለወጣ፤ ጥሩ ስሜት ስለማይሰማን ‹‹ጠዋት ታጥቤ እጸልያለሁ›› በማለት ጸሎታችንን እናስተጓጉላለን፡፡

ለዚህ መፍትሄው በፍፁም ጸሎታችንን አለመተው ነው፡፡ በዚያ በሌሊት ሙሉ ሰውነትን መታጠብ ስለሚከብድ ከቻልን ፈሳሽ የወጣበትን እርጥበት የተሰማንን ቦታ ታጥቦ መጸለይ፡፡ ሴቶችም አንቀጸ ሥጋችሁን አሊያም እጃችሁን በመታጠብ ጸሎታችሁን መቀጠል፡፡

ሰይጣን የራሳችንን ሰውነት እየተጠየፍን ጸሎት እንድንተው ነውና የሚሻው በምንም ምክንያት ጸሎት መተው የለብንም፡፡ እንኳን በሕልመ ሌሊት (ዝንየት) ተመትተን ቀርቶ በጥሩ ሰዓት ማናችውንም ንፁሆች አይደለንም፡፡ የሚገርመው የማያፍረው ሰይጣን በሕልመ ሌሊት (ዝንየት) ቤተክርስትያን ገብቶ ይፈትነናል ማለት ሳይሆን፤ እኛ ላይ ያለው አጋንንት በስውር ለዚህ ፈተና ሊዳርገን ይችላል፡፡

ቤተ ክርስትያን ለንግሥ አዳር ስንሄድ አባቶች አትተኙ የሚሉን አንድም ሕልመ ሌሊት (ዝንየት) ሊመታንና ሊፈትነን ስለሚችል ነው፡፡ ለአንድ ቀን ሌሊት ቤተ-ክርስትያን ጊዜያችንን በጸሎት ብናሳልፍ ካልሆነ ማህሌቱንና ሰዓታቱን ብንሰማ ይበልጥ ጥቅም ስላለው አለመተኛቱ ይመረጣል፡፡

2ኛ/ የዝሙት መንፈስ ካለብን
ይቀጥላል

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

ነገረ ማርያም ክፍል ፪
እነሆ🤲🤲🤲


ክፍል ፩ ያላዳመጣችሁ ካላችሁ በኮመንት አሳውቁን

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​ነሐሴ 10/12/2016 ዓ.ም

✝ በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ።

ዲያቆን፦ ዕብ 12÷22-ፍ.ም
ንፍቅ ዲያቆን፦1 ጴጥ 1፥6-13
ንፍቅ ካህን፦ ግብረ ሐዋርያት፦ 4÷31-ፍ.ም
ምስባክ ፦ መዝ 73፥2-4
ተዘከር ማኅበረከ ዘአቅድምከ ፈጢረ
ወአድኀንከ በትረ ርስትከ
ደብረ ጽዮን ዘኀደርከ ውስቴታ

ትርጉም
አስቀድመህ የፈጠርካትን ማኅበርህን
የተቤዤሃትንም የርስትህን በትር
በርስዋ ያደርህባትን የጽዮንን ተኣኣ አስብ፡፡

ወንጌል ፦ ሉቃ 16÷9-19
ቅዳሴ ፦ ዘእግዝእትነ

💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

👉 የሐሙስ ውዳሴ ማርያም አንድምታ
🎙 ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

👉 የረቡዕ ውዳሴ ማርያም አንድምታ
🎙 ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

#አፄ_ናዖድ_ጻድቅ

ሃገራችን ኢትዮጵያ ምስፍና ከክህነት: ንግሥናን ከጽድቅ ያጣመሩ ብዙ መሪዎች ነበሯ። ከእነዚህ አንዱ ደግሞ አፄ ናዖድ ናቸው። ጻድቁ ንጉሥ የነገሡት ከ1487 እስከ 1499 ዓ/ም ሲሆን ለእመቤታችን በነበራቸው ልዩ ፍቅር ይታወቃሉ ካህን እንደ ነበሩም ይነገራል።

ዛሬ ሁላችን የምንወዳትን ጸሎት (ሰላም ለኪ: እንዘ ንሰግድ ንብለኪ . . .) የደረሷት እርሳቸው ናቸው። ትልቁን መልክአ ማርያምም ደርሰዋል። ይህ መልክእ ጣዕሙ ልዩ ነው።

የጻድቁ ንጉሥ ሚስት (ማርያም ክብራ): ልጆቻቸው (አፄ ልብነ ድንግልና ቡርክት ሮማነ ወርቅ) እጅግ መልካም ክርስቲያኖች ነበሩ። ንጉሡ አፄ ናዖድ ከባለሟልነት የተነሳ ድንግል ማርያምን "እመቤቴ ስምንተኛው ሺ መቼ ይገባል? ጊዜውስ እንዴት ያለ ነው?" አሏት።

እመ ብርሃንም በአካል ተገልጻ የዘመኑንና የሰውን ክፋት ነገረቻቸው። ንጉሡም አዝነው "እመቤቴ! ከዛ ዘመን አታድርሺኝ" አሏት። በዚህ ምክንያት የስምንተኛው ሺህ ዘመን መስከረም 1 በ1500 ዓ/ም ሊገባ እርሳቸው #ነሐሴ_7 ቀን በ1499 ዓ/ም ዐርፈዋል::

ጌታችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ የድንግል እናቱን ጣዕም: ፍቅር: የቅዱስ ጴጥሮስን ሃይማኖትና የአፄ ናዖድን በረከት ያሳድርብን።

👉 ነሐሴ 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.በዓለ ጽንሰታ ለእግዝእትነ ማርያም
2.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
3.ቅዱስ ገብርኤል መበሥር
4.ቅዱስ ጴጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
5.አፄ ናዖድ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮጵያ)
6.ቅዱስ ዮሴፍ ጻድቅ (ወልደ ያዕቆብ-ልደቱ)
7.አባ ጢሞቴዎስ ሊቀ ጳጳሳት

👉 ወርኀዊ በዓላት
1.ሥሉስ ቅዱስ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ)
2.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
3.አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ)
4.አባ ዳንኤል ዘገዳመ ሲሐት
5.አባ ባውላ ገዳማዊ
6.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
7.ቅዱስ አግናጥዮስ (ለአንበሳ የተሰጠ)

"መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው። ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወዳቸዋል።
የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ! በአንቺ የተደረገው ድንቅ ነው . . . ሰው እናታችን ጽዮን ይላል::"
(መዝ. ፹፮፥፩-፮)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

​ነሐሴ 7/12/2016 ዓ.ም

✝ በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ።

ዲያቆን :- ዕብራው - 9:1-11
ንፍቅ ዲያቆን :- 1ኛጴጥሮስ - 2:6-18
ንፍቅ ካህን :- የሐዋ
ሥራ - 10:1-30

ምስባክ:- መዝ 93:12
ብፁዕ ብእሲ ዘአንተ ገሠጽኮ እግዚኦ
ወዘመሀርኮ ሕገከ
ከመ ይትገሃሥ እመዋዕለ እኩያት፡፡

ትርጉም
አቤቱ አንተ የገሠጽኸው
ሕግህንም ያስተማርኸው ሰው ምስጉን ነው
እግዚአብሔር ሕዝቡን አይጥልምና፡፡

ወንጌል:- ማቴዎስ
16:13-24
ቅዳሴ፡ ዘእግዝእትነ(ጎሥዓ)

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

👉 የሰኞ ውዳሴ ማርያም አንድምታ
🎙 ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

👉 በሱባዔ ወቅት ምን ልጸልይ?
👉 እንዴትስ ልጸልይ?
👉 ሁለት ሦስት ግዜ ሱባዔ ገብተን መልስ ብናጣ ምን እናድርግ?
🎤 በቀሲስ ሔኖክ ወ/ማርያም
#ክፍል_ሦስት

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur

Читать полностью…
Подписаться на канал